.
.
.
Default setting
___
ከሃሳብ የሚያረጅ ስልተ-ምት አለ... ከቋንቋ የሚጠልቅ ጸጥታ አለ... በጎህ መቅደድ እርጋታ፣ በምትወድቅ ቅጠል ዥውታ፣ በሚመላለስ ትንፋሽ ፋታ፣ አንድ ስም የለሽ መሆንታ (being) አለ... ተፈጥሮአዊነት!!... ከስርዓቷ ጋር መዛነቅ፣ ከቅኝቷ ጋር መስማማት፣ ከአደራረጓ ጋር ስሙር መሆን...
የሆነ ጊዜ ከዚህ ተፈጥሮአዊ ቅንብር (setting) ጋር ያለ ድካም ሕብር እንፈጥር ነበር... ሰዓታት ከመተለማቸው በፊት፣ ጫጫታ ከመንገሱ በፊት፣ የሆነ ሰው ለመሆን ከመራወጣችን በፊት... ከኑረት ጡዘት፣ ከውድድር ቅኝት፣ ከፉክክር ውጥረታችን በፊት ከተፈጥሮ ስልተ-ምት ጋር ተጣጥሞሽ ነበረን...
ዛሬ ይሄ የለም...
ራሳችንን ዕረፍት አልባ አድርገነዋል... መንፈሳችንን በታትነነዋል... ለነፍሳችን ዓለም ባዕድ ሆነናል... የፈጠርነው ስርዓት ከተፈጥሮ ዝማሜ ለይቶን ሳይበቃው ስጋችንን እያጎሳቆለ ነው... ግንኙነታችንን እያቀጨጨ ነው...
የምር... ነፍሳችን ታፍናለች...
የሆነ ዓይነት መደንዘዝ ውስጥ እንዳለን ብናውቅም ስህተት ነው ለማለት ወኔ አላገኘንም... አንዳች መርግ ቢጫነንም መጉበጣችንን መቀበል አንፈልግም... የተፈጥሮን ስልተ-ምት ንቀን የፈጠርናቸው ሁሉም ስርዓቶች መልሰው እየበሉን ነው... ሆኖም በስሪታቸው ጥመት ላይ ስላልተግባባን በፈጠሩብን መዓት ላይ የጋራ አቋም አልያዝንም...
በቤትህ፣ በሰፈርህ፣ በከተማህ፣ በሃገርህ፣ በዓለም ዙሪያና በምድሪቱ ሁሉ ምን እየሆነ እንዳለ ተመልከት... አዕምሮና ልብህ ይስማሙልሃል?... በምትሰማው ወሬ፣ በምታየው ተግባር፣ በምትኖረው ኑሮ ደስተኛ ነህ?...
በጭራሽ!... የአኗኗራችንን ሙሉ ጤነኛነት justify የሚያደርግ አንድም ምክንያት የለም...
[የሆነ ነገራችንንማ አሞናል...]
___
እዚህች ጋ አንዳንድ ጉዳዮች እናንሳና የተፈጥሮን ቅኝት ዓለሚቱ function በምታደርግበት መነጽር እንመልከት...
__
@bridgethoughts
.
.
Default setting
___
ከሃሳብ የሚያረጅ ስልተ-ምት አለ... ከቋንቋ የሚጠልቅ ጸጥታ አለ... በጎህ መቅደድ እርጋታ፣ በምትወድቅ ቅጠል ዥውታ፣ በሚመላለስ ትንፋሽ ፋታ፣ አንድ ስም የለሽ መሆንታ (being) አለ... ተፈጥሮአዊነት!!... ከስርዓቷ ጋር መዛነቅ፣ ከቅኝቷ ጋር መስማማት፣ ከአደራረጓ ጋር ስሙር መሆን...
የሆነ ጊዜ ከዚህ ተፈጥሮአዊ ቅንብር (setting) ጋር ያለ ድካም ሕብር እንፈጥር ነበር... ሰዓታት ከመተለማቸው በፊት፣ ጫጫታ ከመንገሱ በፊት፣ የሆነ ሰው ለመሆን ከመራወጣችን በፊት... ከኑረት ጡዘት፣ ከውድድር ቅኝት፣ ከፉክክር ውጥረታችን በፊት ከተፈጥሮ ስልተ-ምት ጋር ተጣጥሞሽ ነበረን...
ዛሬ ይሄ የለም...
ራሳችንን ዕረፍት አልባ አድርገነዋል... መንፈሳችንን በታትነነዋል... ለነፍሳችን ዓለም ባዕድ ሆነናል... የፈጠርነው ስርዓት ከተፈጥሮ ዝማሜ ለይቶን ሳይበቃው ስጋችንን እያጎሳቆለ ነው... ግንኙነታችንን እያቀጨጨ ነው...
የምር... ነፍሳችን ታፍናለች...
የሆነ ዓይነት መደንዘዝ ውስጥ እንዳለን ብናውቅም ስህተት ነው ለማለት ወኔ አላገኘንም... አንዳች መርግ ቢጫነንም መጉበጣችንን መቀበል አንፈልግም... የተፈጥሮን ስልተ-ምት ንቀን የፈጠርናቸው ሁሉም ስርዓቶች መልሰው እየበሉን ነው... ሆኖም በስሪታቸው ጥመት ላይ ስላልተግባባን በፈጠሩብን መዓት ላይ የጋራ አቋም አልያዝንም...
በቤትህ፣ በሰፈርህ፣ በከተማህ፣ በሃገርህ፣ በዓለም ዙሪያና በምድሪቱ ሁሉ ምን እየሆነ እንዳለ ተመልከት... አዕምሮና ልብህ ይስማሙልሃል?... በምትሰማው ወሬ፣ በምታየው ተግባር፣ በምትኖረው ኑሮ ደስተኛ ነህ?...
በጭራሽ!... የአኗኗራችንን ሙሉ ጤነኛነት justify የሚያደርግ አንድም ምክንያት የለም...
[የሆነ ነገራችንንማ አሞናል...]
___
እዚህች ጋ አንዳንድ ጉዳዮች እናንሳና የተፈጥሮን ቅኝት ዓለሚቱ function በምታደርግበት መነጽር እንመልከት...
__
@bridgethoughts
🔥4❤3👍3
.
.
.
ፍጥነትን በምትሸልም ዓለም ውስጥ ነው የምንኖረው... እናም ሁሉም ነገር ይቸኩላል... ማሽኑ ይቸኩላል፣ እግረኛው ይቸኩላል፣ ንግግራችን ይቸኩላል፣ ማዕዳችን ይቸኩላል፣ ወዳጅነታችን ይቸኩላል፣ ጥላቻችን ይቸኩላል፣ ተግባራችን ይቸኩላል... የማይጣደፍ ነገር የለም...
እንቅስቃሴን ከለውጥ ሂደት ጋር እናምታታለን... ጫጫታን ከሃቂቃ ልክ እናዛንፋለን... ስክነትን ከጡዘት ጋር እናጋባለን... በንቃት ለመተንፈስ፣ ከልቡና ሆነን ለመስማት፣ ስሜታችንን ለማድመጥ በቂ ጊዜ የለንም...
[ይህ ምን ወለደ?... ጤናህን፣ ግንኙነትህን፣ ስሜትህን - አጢንና ምላሹን ለራስህ ስጥ...]
__
የተፈጥሮን ያልተነካካ ስርዓት (default setting) በመኖር ውስጥ ተጨማሪ ነገር ግድ አይደለም... አበቦች እንዲያብቡ 'ማሽነሪ' አይፈልጉም... ምድር ዙረቷን እንድትጠብቅ 'ሶፍትዌር' አትሻም... ጨረቃና ከዋክብት ለመድመቅ 'ካላንደር' አይጠይቁም... ወንዞች እንዲፈሱ 'ቱቦ' አያስፈልጋቸውም...
[እኔና አንተ ንቁ ሆነን ለመቆየት እንኳ ስንት ነገር ነው የሚያስፈልገን?...]
"Nature is pleased with simplicity. And nature is no dummy." — Isaac Newton
__
የዓለም ስርዓት ግለኝነትን ያበረታል፤ ተፈጥሮአዊነት ግን በሕብር ብቻ ይገለጣል... በጫካ ውስጥ አንዱም ፍጡር የብቻ ዓለም የለውም... ዛፎች የሚተነፍሱትን እንስሳቱ ይስቡታል፣ የአራዊቱ ውጋጅ ምድርን ያለሰልሳል... በተፈጥሮ ውስጥ ቅርጹን የሚቀይር እንጂ የሚጠፋ ነገር የለም...
ባልተረዳነው ጊዜ እንኳ የሚሰራ፣ ልንተማመንበት የሚገባ ታላቅ አስተውሎት ተፈጥሮ ውስጥ አለ... የኛን ቁጥጥር የማይፈልግ፣ ሁሉን በሰዓቱ የሚከውን፣ በፍጽምና የሚጓዝ አስደማሚ ጥበብ ተፈጥሮ ውስጥ አለ...
የምታዋጣው ክህሎት ሳይኖር የደም ዝውውርህ ይሳለጣል፣ ልብ በማትለው ጊዜም ቢሆን ትንፋሽህ ገብቶ ይወጣል፣ የሰውነትህ ክፍሎች (ልብህ፣ ኩላሊትህ፣ ጉበትህ...) ከአንተ ቁጥጥር ውጪ ሆነው መደበኛ ተግባራቸውን ይከውናሉ...
“Look deep into nature, and then you will understand everything better.” — Albert Einstein
ተፈጥሮ ውስጥ እያከማቹ መዝለቅ የለም፣ እየተው መሄድ እንጂ... ዛፎች ቅጠላቸውን ያረግፋሉ - በስብሰው ምድርን ያለማሉ፣ ፍሬያቸውን ይጥላሉ - ሌላ ዘር ይተካሉ፣ ብስሉን ይሰጣሉ - ረሃብ ይከላሉ... ደመና ይዘንባል፣ ከዋክብት ይወድቃሉ፣ ምድር ከፈኗን ትጥላለች...
[እኔና አንተስ?... ትርፋችንንም አንጋራም!... ይሄ ምን ወለደ?...]
___
ተፈጥሮ በውድድር ስርዓት እርስ በእርስ አትባላም - ሚዛን አኑራ ትጓዛለች እንጂ... መስመር አስምራ ድንበር ገፉብኝ አትልም - ልዩነት አጥፍታ ታጣምራለች እንጂ...
ተፈጥሮአዊነት ኋላ-ቀርነት አይደለም፣ አሁንና እዚህ መገኘት ብቻ እንጂ... ስልጣኔዎቻችንን መናቅ አይደለም፣ ጌቶቻችን እንዲሆኑ አለመፍቀድ እንጂ... ኑረትን ማጣጣል አይደለም፣ አማናዊውን ማንነት አለመርሳት እንጂ...
ነገሩ እኮ መመለስ ነው... ፊትን ወደ ቤት ማዞር!!... ወደ ጥንተ ማንነታችን መጓዝ...
____
አስተውለህ ካየህ...
በስልጣኔ ስም ኑረትን አወሳስበናታል... በውድድር ስም ዓለሚቱን ሲዖል አድርገናታል... ሃብት በማካበት ስም ንፍገትን አንብረናል... ምድሪቱ የገጠሙዋትን ፈተናዎች በሙሉ ብትመረምር የሰው ልጅ የተፈጥሮን ስርዓት ትቶ 'የኔ' የሚለውን ዘዬ በመከተሉ ምክንያት የገባበት ጭንቅ ጎልቶ ይታይሃል...
ጦርነት፣ ረሃብ፣ ስደት፣ እርዛት፣ አምባገነንነት፣ ጭካኔ፣ ጥላቻ... የሁሉም ምንጭ እኛው ነን... ችግሩ ያለው የፈጠርነው የዓለም ስርዓት ላይ እንጂ የተፈጥሮ 'ኢፍትሐዊነት' ላይ አይደለም...
ወደ ቤታችን እንመለስ... የተፈጥሮን default setting እንኑር...
___
ይህ ከዓለም ክፋት የመመነን ጥሪ አይደለም... በውስጧ ሆኖ የመንቃት ደወል እንጂ... ጨለምተኝነት፣ ኢ-ዘመናዊነት፣ አልያም የለውጥን ተፈጥሮአዊነት የመካድ ጉዳይ አይደለም... የእርጋታ፣ የመጠየቅ፣ ትንፋሽ የመውሰድ፣ የተማሩትን ትቶ ከተፈጥሮ ስልተ ምት ጋር የመጣማት ፍንጭ እንጂ...
[በግዳጅ ውስጥ የመኖር ጭቆና ሳይሆን በፍቃድ የመፍሰስ ሕልውና ነው... በፍርሃት የመጓዝ ድንብርብር ሳይሆን በነፃነት ከፍ የማለት ግብር ነው...]
ይህ የምልሰት ግብዣ ነው... አዲስ ነገር የመሆን ሳይሆን ወደ ቦታ የመመለስ ጥሪ... ስር የመትከል፣ መሬት የመርገጥ፣ የመስከን ደወል...
___
@bridgethoughts
.
.
ፍጥነትን በምትሸልም ዓለም ውስጥ ነው የምንኖረው... እናም ሁሉም ነገር ይቸኩላል... ማሽኑ ይቸኩላል፣ እግረኛው ይቸኩላል፣ ንግግራችን ይቸኩላል፣ ማዕዳችን ይቸኩላል፣ ወዳጅነታችን ይቸኩላል፣ ጥላቻችን ይቸኩላል፣ ተግባራችን ይቸኩላል... የማይጣደፍ ነገር የለም...
እንቅስቃሴን ከለውጥ ሂደት ጋር እናምታታለን... ጫጫታን ከሃቂቃ ልክ እናዛንፋለን... ስክነትን ከጡዘት ጋር እናጋባለን... በንቃት ለመተንፈስ፣ ከልቡና ሆነን ለመስማት፣ ስሜታችንን ለማድመጥ በቂ ጊዜ የለንም...
[ይህ ምን ወለደ?... ጤናህን፣ ግንኙነትህን፣ ስሜትህን - አጢንና ምላሹን ለራስህ ስጥ...]
__
የተፈጥሮን ያልተነካካ ስርዓት (default setting) በመኖር ውስጥ ተጨማሪ ነገር ግድ አይደለም... አበቦች እንዲያብቡ 'ማሽነሪ' አይፈልጉም... ምድር ዙረቷን እንድትጠብቅ 'ሶፍትዌር' አትሻም... ጨረቃና ከዋክብት ለመድመቅ 'ካላንደር' አይጠይቁም... ወንዞች እንዲፈሱ 'ቱቦ' አያስፈልጋቸውም...
[እኔና አንተ ንቁ ሆነን ለመቆየት እንኳ ስንት ነገር ነው የሚያስፈልገን?...]
"Nature is pleased with simplicity. And nature is no dummy." — Isaac Newton
__
የዓለም ስርዓት ግለኝነትን ያበረታል፤ ተፈጥሮአዊነት ግን በሕብር ብቻ ይገለጣል... በጫካ ውስጥ አንዱም ፍጡር የብቻ ዓለም የለውም... ዛፎች የሚተነፍሱትን እንስሳቱ ይስቡታል፣ የአራዊቱ ውጋጅ ምድርን ያለሰልሳል... በተፈጥሮ ውስጥ ቅርጹን የሚቀይር እንጂ የሚጠፋ ነገር የለም...
ባልተረዳነው ጊዜ እንኳ የሚሰራ፣ ልንተማመንበት የሚገባ ታላቅ አስተውሎት ተፈጥሮ ውስጥ አለ... የኛን ቁጥጥር የማይፈልግ፣ ሁሉን በሰዓቱ የሚከውን፣ በፍጽምና የሚጓዝ አስደማሚ ጥበብ ተፈጥሮ ውስጥ አለ...
የምታዋጣው ክህሎት ሳይኖር የደም ዝውውርህ ይሳለጣል፣ ልብ በማትለው ጊዜም ቢሆን ትንፋሽህ ገብቶ ይወጣል፣ የሰውነትህ ክፍሎች (ልብህ፣ ኩላሊትህ፣ ጉበትህ...) ከአንተ ቁጥጥር ውጪ ሆነው መደበኛ ተግባራቸውን ይከውናሉ...
“Look deep into nature, and then you will understand everything better.” — Albert Einstein
ተፈጥሮ ውስጥ እያከማቹ መዝለቅ የለም፣ እየተው መሄድ እንጂ... ዛፎች ቅጠላቸውን ያረግፋሉ - በስብሰው ምድርን ያለማሉ፣ ፍሬያቸውን ይጥላሉ - ሌላ ዘር ይተካሉ፣ ብስሉን ይሰጣሉ - ረሃብ ይከላሉ... ደመና ይዘንባል፣ ከዋክብት ይወድቃሉ፣ ምድር ከፈኗን ትጥላለች...
[እኔና አንተስ?... ትርፋችንንም አንጋራም!... ይሄ ምን ወለደ?...]
___
ተፈጥሮ በውድድር ስርዓት እርስ በእርስ አትባላም - ሚዛን አኑራ ትጓዛለች እንጂ... መስመር አስምራ ድንበር ገፉብኝ አትልም - ልዩነት አጥፍታ ታጣምራለች እንጂ...
ተፈጥሮአዊነት ኋላ-ቀርነት አይደለም፣ አሁንና እዚህ መገኘት ብቻ እንጂ... ስልጣኔዎቻችንን መናቅ አይደለም፣ ጌቶቻችን እንዲሆኑ አለመፍቀድ እንጂ... ኑረትን ማጣጣል አይደለም፣ አማናዊውን ማንነት አለመርሳት እንጂ...
ነገሩ እኮ መመለስ ነው... ፊትን ወደ ቤት ማዞር!!... ወደ ጥንተ ማንነታችን መጓዝ...
____
አስተውለህ ካየህ...
በስልጣኔ ስም ኑረትን አወሳስበናታል... በውድድር ስም ዓለሚቱን ሲዖል አድርገናታል... ሃብት በማካበት ስም ንፍገትን አንብረናል... ምድሪቱ የገጠሙዋትን ፈተናዎች በሙሉ ብትመረምር የሰው ልጅ የተፈጥሮን ስርዓት ትቶ 'የኔ' የሚለውን ዘዬ በመከተሉ ምክንያት የገባበት ጭንቅ ጎልቶ ይታይሃል...
ጦርነት፣ ረሃብ፣ ስደት፣ እርዛት፣ አምባገነንነት፣ ጭካኔ፣ ጥላቻ... የሁሉም ምንጭ እኛው ነን... ችግሩ ያለው የፈጠርነው የዓለም ስርዓት ላይ እንጂ የተፈጥሮ 'ኢፍትሐዊነት' ላይ አይደለም...
ወደ ቤታችን እንመለስ... የተፈጥሮን default setting እንኑር...
___
ይህ ከዓለም ክፋት የመመነን ጥሪ አይደለም... በውስጧ ሆኖ የመንቃት ደወል እንጂ... ጨለምተኝነት፣ ኢ-ዘመናዊነት፣ አልያም የለውጥን ተፈጥሮአዊነት የመካድ ጉዳይ አይደለም... የእርጋታ፣ የመጠየቅ፣ ትንፋሽ የመውሰድ፣ የተማሩትን ትቶ ከተፈጥሮ ስልተ ምት ጋር የመጣማት ፍንጭ እንጂ...
[በግዳጅ ውስጥ የመኖር ጭቆና ሳይሆን በፍቃድ የመፍሰስ ሕልውና ነው... በፍርሃት የመጓዝ ድንብርብር ሳይሆን በነፃነት ከፍ የማለት ግብር ነው...]
ይህ የምልሰት ግብዣ ነው... አዲስ ነገር የመሆን ሳይሆን ወደ ቦታ የመመለስ ጥሪ... ስር የመትከል፣ መሬት የመርገጥ፣ የመስከን ደወል...
___
@bridgethoughts
❤7👍6💊4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"... Part of me was frustrated because what did i do wrong?
Because you heard the music when i wrote the song."
___
Celia
___
@bridgethoughts
Because you heard the music when i wrote the song."
___
Celia
___
@bridgethoughts
❤5🥰1👌1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
.
.
.
አንተ አለህ ከጎኔ - ዝናብ የታባቱ
ክንድህ ይከልለኝ - ጥላ ምኑ ብርቱ?
ገላዬ ቢርስም - በደመና ፍ*ራሽ
ምድጃ ነው ልቤ - በፍቅርህ ተለኳሽ።
___
@bridgethoughts
.
.
አንተ አለህ ከጎኔ - ዝናብ የታባቱ
ክንድህ ይከልለኝ - ጥላ ምኑ ብርቱ?
ገላዬ ቢርስም - በደመና ፍ*ራሽ
ምድጃ ነው ልቤ - በፍቅርህ ተለኳሽ።
___
@bridgethoughts
❤9🔥2
.
.
.
የምሰራበት ተቋም "በቀጣይ አገልግሎቶቼን የማቀርበው የፋይዳ መታወቂያ ላላቸው ሰራተኞች ብቻ ስለሆነ ከወዲሁ መታወቂያ እንድታወጡ" የሚለውን ማሳሰቢያ ሰብሰብ ብለን በተቀመጥን ባልደረቦች የእጅ ስልክ ላይ ላከ...
ስልኮቻችን ጢው፣ ጺው፣ ኳኳ፣ ቡምቡም... እያሉ 'እንደየሃገራቸው' ጮሁ...
ይህ እንደሆነ አንደኛው ባልደረባችን 'ቴክስቱን' አንብቦ ሲጨርስ ለሌላኛው "እከሌ ፋይዳ አለህ?" ሲል ጠየቀው...
Oh my day!!
ሃሳቡ እኮ ገብቶኛል... ግን ደነገጥኩ...
ወደ ራሴ ዞሬ እኔዬን ጠየቅሁት... "እውን ፋይዳ አለህ?" ብዬ...
ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት ጥያቄ ለመመለስ ሲያምጥ ያላየሁት እኔታዬ ቁዘማ ሲወርሰው ታዘብኩ...
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አላችሁ?...
በቤታችሁ፣
በሰፈራችሁ፣
በማሕበረሰብ፣
በሃገራችሁ፣
በሕይወታችሁ፣
በመኖራችሁ፣
በስራ ቦታችሁ... ፋይዳ አላችሁ?... እውነት ፋይዳችሁ ምንድነው?...
የመኖር ዘፍጥረት፣ የሕላዌ አሃዱ፣ የመውጣት መግባታችን ውበት ፋይዳ ነው... አበርክቶ... ዋጋ... ክብረት... ከተቀበሉት በላይ መስጠት፣ ማኖር፣ መብራት፣ መምራት፣ ወዝ መቀላቀል፣ መፍጋት፣ ምርኩዝ መሆን...
እንጂማ መኖር ምን ትርጉም አለው? - እየፈየዱ ትርጉም ካልሰጡት...
___
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አለሽሽ?...
___
ሁለቱ የምድራችን ታላላቅ ነፍሶች ስለ ፋይዳ ይህን ብለው ነበር...
"Only a life lived for others is a life worthwhile." ~ Albert Eisenstein
"The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others." ~ Mahatma Gandhi
___
@bridgethoughts
.
.
የምሰራበት ተቋም "በቀጣይ አገልግሎቶቼን የማቀርበው የፋይዳ መታወቂያ ላላቸው ሰራተኞች ብቻ ስለሆነ ከወዲሁ መታወቂያ እንድታወጡ" የሚለውን ማሳሰቢያ ሰብሰብ ብለን በተቀመጥን ባልደረቦች የእጅ ስልክ ላይ ላከ...
ስልኮቻችን ጢው፣ ጺው፣ ኳኳ፣ ቡምቡም... እያሉ 'እንደየሃገራቸው' ጮሁ...
ይህ እንደሆነ አንደኛው ባልደረባችን 'ቴክስቱን' አንብቦ ሲጨርስ ለሌላኛው "እከሌ ፋይዳ አለህ?" ሲል ጠየቀው...
Oh my day!!
ሃሳቡ እኮ ገብቶኛል... ግን ደነገጥኩ...
ወደ ራሴ ዞሬ እኔዬን ጠየቅሁት... "እውን ፋይዳ አለህ?" ብዬ...
ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት ጥያቄ ለመመለስ ሲያምጥ ያላየሁት እኔታዬ ቁዘማ ሲወርሰው ታዘብኩ...
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አላችሁ?...
በቤታችሁ፣
በሰፈራችሁ፣
በማሕበረሰብ፣
በሃገራችሁ፣
በሕይወታችሁ፣
በመኖራችሁ፣
በስራ ቦታችሁ... ፋይዳ አላችሁ?... እውነት ፋይዳችሁ ምንድነው?...
የመኖር ዘፍጥረት፣ የሕላዌ አሃዱ፣ የመውጣት መግባታችን ውበት ፋይዳ ነው... አበርክቶ... ዋጋ... ክብረት... ከተቀበሉት በላይ መስጠት፣ ማኖር፣ መብራት፣ መምራት፣ ወዝ መቀላቀል፣ መፍጋት፣ ምርኩዝ መሆን...
እንጂማ መኖር ምን ትርጉም አለው? - እየፈየዱ ትርጉም ካልሰጡት...
___
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አለሽሽ?...
___
ሁለቱ የምድራችን ታላላቅ ነፍሶች ስለ ፋይዳ ይህን ብለው ነበር...
"Only a life lived for others is a life worthwhile." ~ Albert Eisenstein
"The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others." ~ Mahatma Gandhi
___
@bridgethoughts
❤15🥰2
.
.
.
ድሃ ቤት ስታድግ 'ሃብታም' የማያውቃቸውን ብዙ ወጎች ትለምዳለህ...
ለምሳሌ...
እናትህ እራትህ ላይ ጨው በዛ አድርጋ የሰጠችህ ዕለት... ምግቡን ቀመስ ታደርግና...
'እማዬ፣ ጨው እኮ በዝቷል...' ስትላት፤
'አውቄያለሁ ዝም ብለህ ብላ... ውሃ እንዲያስጠጣህ ብዬ ነው' ትልሃለች...
___
የሆነ ቀን ደግሞ መባያው ያንስባታል... እንዲርብህ ግን በጭራሽ አትፈልግም ድስቱን ጠራርጋም ቢሆን ታቀርብልህና...
'በል እያጠቀስክ ብላ፣ መበያና ወንድም ማስፈራሪያ ነው' ትልሃለች...
___
ያው ሁሌ አይሳካም አይደል?... ሌላ ጊዜ ደግሞ ቤቱ ብጣሽ እንጀራ ብርቅ ይሆንበታል... ይሄኔ እናትህ...
'ይህችን ቀምሰህ ውሃ ጠጣበት፣ ሆድ እንዳሳዩት ነው' ብላ ለእራት ሽምብራ ቆሎ ትሰጥሃለች...
___
በዓል ደርሶ፣ ጎረቤት የተሰራው ሥጋ ወጥ ሲያስጎመዥህና ምራቅህን እያስዋጠ ሲያስቸግርህ...
'እማዬ፣ እዚህ ቤት ግን ሥጋ ወጥ የሚበላው መች ነው?' ስትላት...
'ያለለት... አለች የያለለት እናት፤ ያለለት ነዋ ልጄ!' ትልሃለች...
ምናልባት በጥያቄህ ገፍተህ ከተጫንካት ደግሞ፣ 'ሰው እንደ ቤቱ እንጂ እንደ ጎረቤቱ አይኖርም' ብላ ኮስተር ትልብሃለች...
___
እናት ግን ሳታበላህ የማትበላ፣ 'አፈር ልብላ' ሳትልህ የማትውል፣ የሆዷን ጥያቄ በመቀነት ጨቁና የአንተን ሆድ ብቻ ለመሙላት የምትታትር... መሆኗን ልብ በል!!
___
ደግሞ ወዲህ...
ጥሬ ሽሮ ተበጥብጦ፣ ብትን ጨው በውሃ ሟሙቶ፣ ሚጥሚጣ ተጠቅሶ፣ በርበሬ ድልህ ሆኖ፣ ተልባ በውሃ ርሶ፣ ቃሪያ በጨው ተሰንጎ፣ ጎመን ተለብልቦ (ዘይት የጠፋ'ለት)፣ ሽንኩርት በጨው ተጠቅሶ... ወዘተ
በመበያነት የሚታወቁት ድሃ ቤት ብቻ ነው...
___
ሌላም አለ...
"አይቶ አጣ ቤት ጎመን የተቀቀለ ዕለት ሲጨበጨብ ያድራል"
"ሆድን በጎመን ቢደልሉት፣ ጉልበት በዳገት ይለግማል"
"ለአኩራፊ ምሳው እራቱ ነው"
"ምን ያመጣ ድሃ፣ ምን ያገሳ ውሃ"
"በሚያዝያ ጎመን የዘራ፣ ክረምቱን ሁሉ በላ"
"አህያ እንደምትታለብ፣ ከላሞች ፊት ትቅለበለብ"
"የችግር ክፉ እህል ማጣት፣ የኃጢዓት ክፉ ነፍስ ማጥፋት"
"ያፌን እስክውጥ ዕድሜ ይስጠኝ፣ ይላል እርኩም"
.
.
.
ዓይነቶቹን ተረት የምትሰማው ከድሃ ብቻ ነው...
___
Damn!!...
ዛሬም እዚያው ነን...
___
አንድ እውነት ግን አለ...
የድሃ ድህነት የሞራል አይደለም!!... ለማግኘት ብሎ ክብሩን አይጥልም!!!... ሆዱን ሊሞላ ሃገር አይሰርቅም!!!... ረሃብ ሊከላ ቃሉን አይበላም!!!...
___
@bridgethoughts
.
.
ድሃ ቤት ስታድግ 'ሃብታም' የማያውቃቸውን ብዙ ወጎች ትለምዳለህ...
ለምሳሌ...
እናትህ እራትህ ላይ ጨው በዛ አድርጋ የሰጠችህ ዕለት... ምግቡን ቀመስ ታደርግና...
'እማዬ፣ ጨው እኮ በዝቷል...' ስትላት፤
'አውቄያለሁ ዝም ብለህ ብላ... ውሃ እንዲያስጠጣህ ብዬ ነው' ትልሃለች...
___
የሆነ ቀን ደግሞ መባያው ያንስባታል... እንዲርብህ ግን በጭራሽ አትፈልግም ድስቱን ጠራርጋም ቢሆን ታቀርብልህና...
'በል እያጠቀስክ ብላ፣ መበያና ወንድም ማስፈራሪያ ነው' ትልሃለች...
___
ያው ሁሌ አይሳካም አይደል?... ሌላ ጊዜ ደግሞ ቤቱ ብጣሽ እንጀራ ብርቅ ይሆንበታል... ይሄኔ እናትህ...
'ይህችን ቀምሰህ ውሃ ጠጣበት፣ ሆድ እንዳሳዩት ነው' ብላ ለእራት ሽምብራ ቆሎ ትሰጥሃለች...
___
በዓል ደርሶ፣ ጎረቤት የተሰራው ሥጋ ወጥ ሲያስጎመዥህና ምራቅህን እያስዋጠ ሲያስቸግርህ...
'እማዬ፣ እዚህ ቤት ግን ሥጋ ወጥ የሚበላው መች ነው?' ስትላት...
'ያለለት... አለች የያለለት እናት፤ ያለለት ነዋ ልጄ!' ትልሃለች...
ምናልባት በጥያቄህ ገፍተህ ከተጫንካት ደግሞ፣ 'ሰው እንደ ቤቱ እንጂ እንደ ጎረቤቱ አይኖርም' ብላ ኮስተር ትልብሃለች...
___
እናት ግን ሳታበላህ የማትበላ፣ 'አፈር ልብላ' ሳትልህ የማትውል፣ የሆዷን ጥያቄ በመቀነት ጨቁና የአንተን ሆድ ብቻ ለመሙላት የምትታትር... መሆኗን ልብ በል!!
___
ደግሞ ወዲህ...
ጥሬ ሽሮ ተበጥብጦ፣ ብትን ጨው በውሃ ሟሙቶ፣ ሚጥሚጣ ተጠቅሶ፣ በርበሬ ድልህ ሆኖ፣ ተልባ በውሃ ርሶ፣ ቃሪያ በጨው ተሰንጎ፣ ጎመን ተለብልቦ (ዘይት የጠፋ'ለት)፣ ሽንኩርት በጨው ተጠቅሶ... ወዘተ
በመበያነት የሚታወቁት ድሃ ቤት ብቻ ነው...
___
ሌላም አለ...
"አይቶ አጣ ቤት ጎመን የተቀቀለ ዕለት ሲጨበጨብ ያድራል"
"ሆድን በጎመን ቢደልሉት፣ ጉልበት በዳገት ይለግማል"
"ለአኩራፊ ምሳው እራቱ ነው"
"ምን ያመጣ ድሃ፣ ምን ያገሳ ውሃ"
"በሚያዝያ ጎመን የዘራ፣ ክረምቱን ሁሉ በላ"
"አህያ እንደምትታለብ፣ ከላሞች ፊት ትቅለበለብ"
"የችግር ክፉ እህል ማጣት፣ የኃጢዓት ክፉ ነፍስ ማጥፋት"
"ያፌን እስክውጥ ዕድሜ ይስጠኝ፣ ይላል እርኩም"
.
.
.
ዓይነቶቹን ተረት የምትሰማው ከድሃ ብቻ ነው...
___
Damn!!...
ዛሬም እዚያው ነን...
___
አንድ እውነት ግን አለ...
የድሃ ድህነት የሞራል አይደለም!!... ለማግኘት ብሎ ክብሩን አይጥልም!!!... ሆዱን ሊሞላ ሃገር አይሰርቅም!!!... ረሃብ ሊከላ ቃሉን አይበላም!!!...
___
@bridgethoughts
❤22👍3🥰3🙏1
.
.
.
ለራስህ እውነተኛ ስሜት ታማኝ ሆነህ ትቆያለህ ወይስ ለሌሎች ስሜት ለመመቸት ስትል ሚዛን ትስታለህ?
ዋጋ የምትሰጣቸው ነገሮች ምንነት አጠቃላይ ነገርህን ይወስኑታል... እሴትህ ወይም 'value' የምታደርጋቸው ነገሮች ስላንተ ያለውን አጠቃላይ እውነት ይናገራሉ...
ለሃቅ ዋጋ ትሰጣለህ - እውነተኛ ትሆናለህ... ሃሰት ካልጎረበጠህ በክህደት ትሰለጥናለህ... ገንዘብ ታመልካለህ - ለሃብት ስትል እስከ መግደል ትደርሳለህ... ባለህ ከተብቃቃህ መካፈል ታውቃለህ...
የሰው ልጅ 'ሰውነት' የተለየው በጥላው ቅርጽ አይደለም... በሚጠራበት ስም፣ በተሸከመው ስመ-ማሕተም፣ በሰበሰበው ሃብት እና ምድራዊ ቁሳቁስ አይደለም... በልቡ መሰዊያ ላይ በሚያቀርባት የዕጣን ሽቱ፣ ዓይን ባላየው ጊዜ በሚንበረከክላት እውነቱ፣ ሁሉ ባወገዘው ጊዜ በሚቆምላት እምነቱ እንጂ...
ብዙዎች 'ለወርቅ' ይሰግዳሉ - ጥቂቶች የጸጥታን ውበት ያመልካሉ... እልፎች እውነትን ለጭብጨባና ርካሽ አድናቆት አሳልፈው ይሰጣሉ - ጥቂቶች የሃቂቃቸውን ላምባ ከፍ አድርገው ይጓዛሉ...
እነዚያ 'እኛን ምሰል' ማለት ያዘወትራሉ - ያልመሰለን ማራቅ፣ ያልመሰለን ማድቀቅ ያውቁበታል...
እነዚህ መሆንን ይኖራሉ - መምሰል የነፍስያን ቀለም የሚያጠፋ ጥላት፣ ውስጠትን የሚበላ ሻህላ እንደሆነ ያውቃሉ...
አዎን... መንጋውን ከሚያብር ፍም ይልቅ በሚያረግድ ንፋስ ፊት የሚቆም የኩራዝ ነበልባል የበለጠ የሞራል ብርታት አለው...
እሴተኝነት እስረኝነት አይደለም - ፍሬ እንጂ... አጥልቀህ ስትቀብረው ተልቆ ብቅ ይላል... ሥጋህ እንኳ ቢያልፍ ለስምህ ዘብነት ደን ሆኖ ይበቅላል... ልጆችህ ይኮሩበታል - መንዝረው ይከብሩበታል...
ይህን ያጣህ'ለት ግን ማንም ትሆናለህ... ከቆምክበት ሞገስ አይኖርህም... ባለፍክበት ክብር አይቆይልህም...
እንጂማ...
ሰው ከእሴቱ ውጭ ምንድነው?...
___
@bridgethoughts
.
.
ለራስህ እውነተኛ ስሜት ታማኝ ሆነህ ትቆያለህ ወይስ ለሌሎች ስሜት ለመመቸት ስትል ሚዛን ትስታለህ?
ዋጋ የምትሰጣቸው ነገሮች ምንነት አጠቃላይ ነገርህን ይወስኑታል... እሴትህ ወይም 'value' የምታደርጋቸው ነገሮች ስላንተ ያለውን አጠቃላይ እውነት ይናገራሉ...
ለሃቅ ዋጋ ትሰጣለህ - እውነተኛ ትሆናለህ... ሃሰት ካልጎረበጠህ በክህደት ትሰለጥናለህ... ገንዘብ ታመልካለህ - ለሃብት ስትል እስከ መግደል ትደርሳለህ... ባለህ ከተብቃቃህ መካፈል ታውቃለህ...
የሰው ልጅ 'ሰውነት' የተለየው በጥላው ቅርጽ አይደለም... በሚጠራበት ስም፣ በተሸከመው ስመ-ማሕተም፣ በሰበሰበው ሃብት እና ምድራዊ ቁሳቁስ አይደለም... በልቡ መሰዊያ ላይ በሚያቀርባት የዕጣን ሽቱ፣ ዓይን ባላየው ጊዜ በሚንበረከክላት እውነቱ፣ ሁሉ ባወገዘው ጊዜ በሚቆምላት እምነቱ እንጂ...
ብዙዎች 'ለወርቅ' ይሰግዳሉ - ጥቂቶች የጸጥታን ውበት ያመልካሉ... እልፎች እውነትን ለጭብጨባና ርካሽ አድናቆት አሳልፈው ይሰጣሉ - ጥቂቶች የሃቂቃቸውን ላምባ ከፍ አድርገው ይጓዛሉ...
እነዚያ 'እኛን ምሰል' ማለት ያዘወትራሉ - ያልመሰለን ማራቅ፣ ያልመሰለን ማድቀቅ ያውቁበታል...
እነዚህ መሆንን ይኖራሉ - መምሰል የነፍስያን ቀለም የሚያጠፋ ጥላት፣ ውስጠትን የሚበላ ሻህላ እንደሆነ ያውቃሉ...
አዎን... መንጋውን ከሚያብር ፍም ይልቅ በሚያረግድ ንፋስ ፊት የሚቆም የኩራዝ ነበልባል የበለጠ የሞራል ብርታት አለው...
እሴተኝነት እስረኝነት አይደለም - ፍሬ እንጂ... አጥልቀህ ስትቀብረው ተልቆ ብቅ ይላል... ሥጋህ እንኳ ቢያልፍ ለስምህ ዘብነት ደን ሆኖ ይበቅላል... ልጆችህ ይኮሩበታል - መንዝረው ይከብሩበታል...
ይህን ያጣህ'ለት ግን ማንም ትሆናለህ... ከቆምክበት ሞገስ አይኖርህም... ባለፍክበት ክብር አይቆይልህም...
እንጂማ...
ሰው ከእሴቱ ውጭ ምንድነው?...
___
@bridgethoughts
🥰6❤4
.
.
.
ትናንት ስለመጣሽበት መንገድ አብዝተሽ ከተጨነቅሽ ዛሬን አልደረስሽም፤ ነገም ያንቺ አይደለም ማለት ነው...
የስብዕናሽ ጥራት የሚለካው ትናንት በፈጸምሻቸው ስህተቶች ሳይሆን ዛሬ ላትደግሚያቸው በምትይዥው አቋም ነው...
የእኔ እህት...
ከየት መምጣትሽ አይደለም ችግሩ ወደየት ለመሄድ መወሰንሽ እንጂ...
ወደኋላ የሚያዩ ዓይኖች ወደፊት የሚጓዙበትን መላ ሲቀምሩ - ተማሩ፤ ይበልጥ የሚቆዝሙበትን ትውስታ ሲጭሩ - ተቸነከሩ ይባላል...
መቸንከር ትፈልጊያለሽ?... [I know አትፈልጊም!!...]
የኔ ውድ!!...
ፊትሽን ከትናንት አዙሪ!... ሁላችንም እዚያ ነበርን... ደስ የሚል መልክ የለውም... ቢያንስ ሲሶ፣ እርቦ፣ ሩብ፣ ግማሽ፣ ምናምን ገጽታው ግርጣት አያጣውም...
የሚገርምሽ - ሊፈርዱብሽ፣ ሊያሸማቅቁሽ፣ ሊያሳንሱሽ የሚፈልጉ ሁሉ እዚያው ነበሩ... ማንም ንጹህ የለም!!...
ዛሬ ግን ውብ ነው!!... ከእጅሽ ያለ ዕንቁ - የምርጫ ጎተራ!!
ዳይ!!... ወደፊት ብቻ!!
____
@bridgethoughts
.
.
ትናንት ስለመጣሽበት መንገድ አብዝተሽ ከተጨነቅሽ ዛሬን አልደረስሽም፤ ነገም ያንቺ አይደለም ማለት ነው...
የስብዕናሽ ጥራት የሚለካው ትናንት በፈጸምሻቸው ስህተቶች ሳይሆን ዛሬ ላትደግሚያቸው በምትይዥው አቋም ነው...
የእኔ እህት...
ከየት መምጣትሽ አይደለም ችግሩ ወደየት ለመሄድ መወሰንሽ እንጂ...
ወደኋላ የሚያዩ ዓይኖች ወደፊት የሚጓዙበትን መላ ሲቀምሩ - ተማሩ፤ ይበልጥ የሚቆዝሙበትን ትውስታ ሲጭሩ - ተቸነከሩ ይባላል...
መቸንከር ትፈልጊያለሽ?... [I know አትፈልጊም!!...]
የኔ ውድ!!...
ፊትሽን ከትናንት አዙሪ!... ሁላችንም እዚያ ነበርን... ደስ የሚል መልክ የለውም... ቢያንስ ሲሶ፣ እርቦ፣ ሩብ፣ ግማሽ፣ ምናምን ገጽታው ግርጣት አያጣውም...
የሚገርምሽ - ሊፈርዱብሽ፣ ሊያሸማቅቁሽ፣ ሊያሳንሱሽ የሚፈልጉ ሁሉ እዚያው ነበሩ... ማንም ንጹህ የለም!!...
ዛሬ ግን ውብ ነው!!... ከእጅሽ ያለ ዕንቁ - የምርጫ ጎተራ!!
ዳይ!!... ወደፊት ብቻ!!
____
@bridgethoughts
🙏6❤5🥰4❤🔥1👍1
ማስተንከሪያ
___
📢 Are we evolving or are we just getting better at masking our madness?
[በጥያቄ ነቃሁ... ጠዋቴ ከማወቅ ጉጉቴ ጋር በራች... እንዲሁ ነኝ... አንዳንድ ቀኔን የሚረከቡ ሃሳቦች ማለዳዬ ላይ ይራወጣሉ... ዛሬም የሆነው እንዲሁ ነበር...]
እናም ጠየቅሁ...
'እውን ሰይጣን ይሉት 'አካል' አለ?... ቀንዳም፣ የጨለማ ገዢ፣ አስፈሪ፣ ጨካኝ entity በሕዋችን ላይ ታቅፏል?... ወይስ ላልተቀበልነው ተፈጥሮአችን፣ ለውድመት፣ ለበደል፣ ለግፊያችን - ማምለጫ፣ ማቋረጫ፣ መሿለኪያ የተቀመጠ የስርየት ፍየል ይሆን?... 🤔🤔🤔
___
ማጮለቂያ... 👀
___
ርዕዮት - ፩
የሐይማኖት መጽሐፍት የሰይጣንን ኑባሬ ይቀበላሉ... ለምሳሌ ክርስትና 'የተጣለው መልዓክ፣ መከራ አማጭ፣ ፈታኝ' ብሎ የሚጠራው ሰይጣንን 'ከመለኮት ትዕዛዝ በተቃርኖ የሚጓዝ አማጺ' አድርጎ ያስቀምጠዋል...
በእስልምና 'ኢብሊስ' ተብሎ የሚጠራው ሰይጣን 'ለአዳም ባለመገዛቱ የተባረረ፣ የኩራትና ያለመታዘዝ ምልክት ነው'...
አይሁዶች በዕብራይስጥ 'ሃ-ሴታን' ወይም ከሳሽ ሲሉ የሚጠሩት ሰይጣን 'በፈጣሪ የፍርድ ችሎት ላይ የሚቀመጥና የሰዎችን ታማኝነት የሚፈታተን ነው' ሲሉ ያስተምራሉ...
ርዕዮት - ፪
ነገሩን ምዕራባዊ መሰረት ካላቸው ሐይማኖቶች አስተምህሮ አውጥተን በአሳቢያን እና ማላዮች መነጽር ብንመለከተው ሰይጣን ከአካላዊ ግዝፈት ይልቅ ምልክታዊ ጉላት ያይልበታል...
ሰይጣን የሰው ልጅ ባሕሪያዊ ጽላሎት (Inner shadow) ትዕምርት ሲሆን ያልተፈተነ ፍርሐት፣ ስግብግብነትና ድብቅ ጭካኔያችን ነጸብራቅ ነው...
ከእውነት፣ ከፍቅር እና ከሕላዌ ነቅዕ (Being) የመለያየት ተምሳሌት፤ እንዲሁም ኃላፊነትንና ተጠያቂነትን ለማምለጥ የምንከለልበት ዓይነ-ርግብ (mask) ነው...
Carl Jung ቆንጆ አድርጎ እንዳስቀመጠው...
🔔 "The devil is the personification of the shadow side of human nature." 🔔
ማላዮችም ስለ ሰይጣን አብዝተው ከመናገር ይልቅ ስለ ንቃትና ተገንዝቦት ማውጋትን የሚመርጡት ለዚህ ነው...
ለምሳሌ ሱፊስቶች - “There is no Satan but the ego unobserved.” በማለት ከነዩንግ እሳቤ ጋር ሲዛመዱ ሌሎች ምስራቃዊ መሰረት ያላቸው አስተምህሮዎችም ከዚህ መሰረት ብዙም ያልራቀ ዕይታን ያስተጋባሉ...
___
📌 የሰይጣንን እሳቤ የወለደው ክህደት፣ ድንዛዜ እና ኃላፊነትን ያለመውሰድ ቅዋሜ ነው... ሁሌም ቢሆን አጥፊነታችንን መቀበል ሲቸግረን ሌላ ተወቃሽ እናሻትታለን... የሁኔታው ሰበብና የቅጣቱ ተቀባይ እኛው ራሳችን ብንሆንም እኛን ተገብቶ እንዲጠየቅልን የምንፈልገው የጦስ ዶሮ መፈለጋችን የተለመደ ነው...
📌 ክፋታችንን ውጫዊ ስናደርግ 'ለምንድነው ይህን ያደረግሁት? የትኛው እኔታዬ ነው ይህ እንዲሆን የፈለገው?' ብለን ከመጠየቅ ይልቅ 'እኔ አላደረግሁትም ወይም ሰይጣን አስቶኝ ነው' የማለትን ቀላል መንገድ እንመርጣለን...
___
@bridgethoughts
___
📢 Are we evolving or are we just getting better at masking our madness?
[በጥያቄ ነቃሁ... ጠዋቴ ከማወቅ ጉጉቴ ጋር በራች... እንዲሁ ነኝ... አንዳንድ ቀኔን የሚረከቡ ሃሳቦች ማለዳዬ ላይ ይራወጣሉ... ዛሬም የሆነው እንዲሁ ነበር...]
እናም ጠየቅሁ...
'እውን ሰይጣን ይሉት 'አካል' አለ?... ቀንዳም፣ የጨለማ ገዢ፣ አስፈሪ፣ ጨካኝ entity በሕዋችን ላይ ታቅፏል?... ወይስ ላልተቀበልነው ተፈጥሮአችን፣ ለውድመት፣ ለበደል፣ ለግፊያችን - ማምለጫ፣ ማቋረጫ፣ መሿለኪያ የተቀመጠ የስርየት ፍየል ይሆን?... 🤔🤔🤔
___
ማጮለቂያ... 👀
___
ርዕዮት - ፩
የሐይማኖት መጽሐፍት የሰይጣንን ኑባሬ ይቀበላሉ... ለምሳሌ ክርስትና 'የተጣለው መልዓክ፣ መከራ አማጭ፣ ፈታኝ' ብሎ የሚጠራው ሰይጣንን 'ከመለኮት ትዕዛዝ በተቃርኖ የሚጓዝ አማጺ' አድርጎ ያስቀምጠዋል...
በእስልምና 'ኢብሊስ' ተብሎ የሚጠራው ሰይጣን 'ለአዳም ባለመገዛቱ የተባረረ፣ የኩራትና ያለመታዘዝ ምልክት ነው'...
አይሁዶች በዕብራይስጥ 'ሃ-ሴታን' ወይም ከሳሽ ሲሉ የሚጠሩት ሰይጣን 'በፈጣሪ የፍርድ ችሎት ላይ የሚቀመጥና የሰዎችን ታማኝነት የሚፈታተን ነው' ሲሉ ያስተምራሉ...
ርዕዮት - ፪
ነገሩን ምዕራባዊ መሰረት ካላቸው ሐይማኖቶች አስተምህሮ አውጥተን በአሳቢያን እና ማላዮች መነጽር ብንመለከተው ሰይጣን ከአካላዊ ግዝፈት ይልቅ ምልክታዊ ጉላት ያይልበታል...
ሰይጣን የሰው ልጅ ባሕሪያዊ ጽላሎት (Inner shadow) ትዕምርት ሲሆን ያልተፈተነ ፍርሐት፣ ስግብግብነትና ድብቅ ጭካኔያችን ነጸብራቅ ነው...
ከእውነት፣ ከፍቅር እና ከሕላዌ ነቅዕ (Being) የመለያየት ተምሳሌት፤ እንዲሁም ኃላፊነትንና ተጠያቂነትን ለማምለጥ የምንከለልበት ዓይነ-ርግብ (mask) ነው...
Carl Jung ቆንጆ አድርጎ እንዳስቀመጠው...
🔔 "The devil is the personification of the shadow side of human nature." 🔔
ማላዮችም ስለ ሰይጣን አብዝተው ከመናገር ይልቅ ስለ ንቃትና ተገንዝቦት ማውጋትን የሚመርጡት ለዚህ ነው...
ለምሳሌ ሱፊስቶች - “There is no Satan but the ego unobserved.” በማለት ከነዩንግ እሳቤ ጋር ሲዛመዱ ሌሎች ምስራቃዊ መሰረት ያላቸው አስተምህሮዎችም ከዚህ መሰረት ብዙም ያልራቀ ዕይታን ያስተጋባሉ...
___
📌 የሰይጣንን እሳቤ የወለደው ክህደት፣ ድንዛዜ እና ኃላፊነትን ያለመውሰድ ቅዋሜ ነው... ሁሌም ቢሆን አጥፊነታችንን መቀበል ሲቸግረን ሌላ ተወቃሽ እናሻትታለን... የሁኔታው ሰበብና የቅጣቱ ተቀባይ እኛው ራሳችን ብንሆንም እኛን ተገብቶ እንዲጠየቅልን የምንፈልገው የጦስ ዶሮ መፈለጋችን የተለመደ ነው...
📌 ክፋታችንን ውጫዊ ስናደርግ 'ለምንድነው ይህን ያደረግሁት? የትኛው እኔታዬ ነው ይህ እንዲሆን የፈለገው?' ብለን ከመጠየቅ ይልቅ 'እኔ አላደረግሁትም ወይም ሰይጣን አስቶኝ ነው' የማለትን ቀላል መንገድ እንመርጣለን...
___
@bridgethoughts
❤4👍2🥰2👏1👌1
[የቀጠለ...]
🤔 ማብሰልሰያ - ፩
ሰይጣን አለ ብለን ብናስብና እንደተነገረን ክፋቱን ብንቀበል፣ maximum ሊያደርግብን የሚችለው ነገር ምንድነው?... ስቃይ ማብዛት?፣ መከራ መቆለል?፣ ለሞት መዳረግ? ወይስ ሌላ?... ታዲያ ሰይጣን የሚያደርገው እኛ እስካሁን ያላደረግነው ምን ነገር አለ?...
መንደሮችን አቃጥለናል... ሕፃናትን በቦምብ ደብድበናል... አፍላጋትን መርዘናል... ድንበር ፈጥረን ተቋስለናል... በረሃብ ሰው ፈጅተናል... ፍቅርን ሸቅጠናል... ሃቂቃን አፍነናል... ጨቅላ ሕፃን ደፍረናል... እርጉዝ ሴት በሳንጃ ዘንጥለናል... ሰውን በቁሙ አቃጥለናል... ስጋውን ቀርጥፈን ከርስ ሞልተናል... ከመሰዊያ ላይ አርደናል... በስልጣናችን ባልገናል... ዘርፈናል፣ ቀጥፈናል፣ ሰስነናል - ይህች ምድር በእኛ ምክንያት ያላየችው ምን ቀሪ መከራ አለ?...
[ለኢጎአችን እስከጠቀመ ድረስ ጆሮ አደንዛዡን፣ ዓይን አፍዛዡን ሁሉ አድርገናል - እስካሁን ካደረግነው የሚበልጥ ምንም ሌላ ነገር ወደፊት አናደርግም... ከኛ በላይ የሚያደርግ ሌላ 'ሰይጣንም' የለም]
🌟 "If Satan is the exile of love, then maybe redemption is not believing in God — but becoming someone who does not create hell for another."
እውነት ሰይጣን ካለ ግን በእርግጠኝነት በዚህ ሰዓት ጡረታ ወጥቷል... አልያም መዝገብ ይዞ ክፋታችንን እየከተበ ነው... ወይም ደግሞ ከከፋው ተግባራችን ልምድ እየቀሰመ ይሆናል...
ያን የ Desert father's wisdom ታስታውሱት የለ?...
በአንድ ገዳም ውስጥ፣ አንድ ወጣኒ መነኩሴ እንቁላል ይሰርቅና ተደብቆ ሲጠብስ ይገኛል...
'ምን እያደረግህ ነው?' ያገኙት አባት ይጠይቁታል...
'አይ አባ... ሰይጣን አስቶኝ...' ወጣቱ ይርበተበታል...
ጉዳዩን ከመስኮት በኩል ሆኖ ሲከታተል የነበረው 'ሰይጣን' ታዲያ እንዲህ ሲል ራሱን ነፃ አወጣ...
'አባ ውሸቱን ነው... ይህችን መላ ያለዛሬም አላየሁዋት'...
___
🌟 ጎበዝ ሰዋዊ ጉዳዮቻችን የሚመሩት በግላጭም በስውርም ነው... እኛ - አስበን፣ ወስነን የምንከውነው ብቻ አይደለንም... ከማለዳ ዕድሜያችን ጀምሮ በልቡሰ-ጥላ (subconscious mind) ሲሞላ የኖረው ፕሮግራምም በድብቅ ይመራናል፤ ይቆጣጠረናል...
እርሱ ማንነታችንን ይገነባል... እርሱ ግንኙነታችንን ይመራል...
እዚያ ቅይጥ መልካችን ይከተባል... እዚያ መሻት መጥላታችን ይቀመራል...
ደግነት ክፋታችን፣ ርህራሔ ተንኮላችን፣ ጨዋነት ወራዳነታችን፣ ንቃት ድንዛዜያችን የመንታ አንድ ሆኖ ይላቆጣል...
___
🤔 ማብሰልሰያ - ፪
ንድፈ ሃሳባዊውን መለኪያ ትተን በተግባር ብንፈተሽ 'ሰይጣን' ከሚባለው 'ትርክት' የሚለየን ምንድነው?...
ለምሳሌ - ሰይጣን 'ፈታኝ ነው' እንላለን... እኛም በአባይ ቃል፣ በአታላይ ጥቅም ሌሎችን በማማለል እንፈትናለን...
ሰይጣን 'ከፋፋይ ነው' እንላለን... እኛም 'ልዩነትን' የጥላቻ ምንጭ፣ 'ማንነትን' የጦር መስበቂያ ሰበብ አድርገን የሰውን ልጅ ስንበልት እንኖራለን...
ሰይጣን 'ሐሰተኛ ነው' እንላለን... ነግቶ እስኪመሽ ቅጥፈት፣ መሽቶ እስኪነጋ እብለት አሽሞንሙነን ወገናችንን እንወጋለን...
🦋 ሰይጣን ለመባል ቀንድ አያስፈልገንም - ከቀንድ በላይ የሚወጋ ምላስ አለን... ገሃነመ እሳት አያስፈልገንም - ከጥይት አረር እስከ ከፋው ኒውክለር ሁሉን ታጥቀናል...
___
አንድ ጥንታዊ የሱፊ ወግ ልንገራችሁ...
አንድ ቀን አንድ ደርቪሽ መምህሩን እንዲህ ሲል ጠየቀ...
"መምህር ሆይ፣ ሰይጣንን ማሸነፍ የምችለው እንዴት ነው?"
መምህሩ መለሱ...
"በቅድሚያ የእርሱን ጫማ መዋስ አቁም"
መምህሩ በጫማ ነጽሮት ውስጥ ውስጠ ቅኝታችንን ነው ያጠየቁት... አሳባቢ፣ ጥሩር ቀጥቃጭ፣ ኃላፊነት ካጂ ውስጠ ማንነታችንን...
ያመሰጠሩት ስለ ዓይነ ትልልቅ፣ ባለ ጨልጨሌ፣ ቀንዳም ሰይጣን ሳይሆን - ልናይ ስላልፈቀድነው ማንነታችን ነው...
___
Meister Eckhart እንዲህ ይላል...
“The devil is simply that which pushes you away from your own center.”
🌟 ማዕከል (center) የሰው ልጅ ለሕላዌው ጣዕም የሚፈጥርበት፣ እንዲሁም በመኖር ወጀብ ከመናወጥ የሚድንበት መልህቁ ነው... ፍቅሩ፣ አገልጋይነቱ፣ እሴቱ፣ የሕይወት ፍቺው... ሻገር ብሎ ደግሞ ከነፍስያው፣ ከምንጩ፣ ከምልዓተ ዓለሙ የሚዋደድበት እትብቱ... ከዚህ ማዕከል የሚገፋውን ነገር ነው ማላዩ ኤካርት 'devil' ሲል የጠራው...
___
መውጫ - መወጣጫ
___
🔔 [ሰይጣን ከአካላዊ ማንነት ይልቅ ከፍቅር የመፋታት ምልክት ቢሆንስ?... ምናልባትም የንቃት ስንጥቃት አልያም ከአማናዊው የማንነታችን ምንጭ የመለያያት ጥልቀት ቢሆንስ?...]
እንደ እውነቱ ከሆነ ክፉ አስፈፃሚ አይደለም ያለው - ፈፃሚው ራሱ እንጂ... በሌላ አነጋገር ወይ እኛ ሰይጣን ነን - አልያም ብቅ እልም የምትል ስይጥንና አለችብን...
___
👉 ጨለማን ሁልጊዜ ሻማ በመለኮስ አንፋታውም... አንዳንዴ ጨለማነቱን መቀበልም ይኖርብናል... በተለይ የውስጣችን ኑባሬ ሲሆን በዓይኖቻችን ልናየው መድፈርም ግድ ይሆናል... ልክ ራሳችንን በመስታወት ፊት እያየን እንደምናወራው ሁሉ - "አንተ - እኔን ነህ... ያልተፈቀርከው፣ ያልተጎበኘኸው፣ ያልተደመጥከው እኔ... አሁን አጠገብህ ነኝ፣ እያየሁህ ነው..." ልንለው ይገባል...
___
@bridgethoughts
🤔 ማብሰልሰያ - ፩
ሰይጣን አለ ብለን ብናስብና እንደተነገረን ክፋቱን ብንቀበል፣ maximum ሊያደርግብን የሚችለው ነገር ምንድነው?... ስቃይ ማብዛት?፣ መከራ መቆለል?፣ ለሞት መዳረግ? ወይስ ሌላ?... ታዲያ ሰይጣን የሚያደርገው እኛ እስካሁን ያላደረግነው ምን ነገር አለ?...
መንደሮችን አቃጥለናል... ሕፃናትን በቦምብ ደብድበናል... አፍላጋትን መርዘናል... ድንበር ፈጥረን ተቋስለናል... በረሃብ ሰው ፈጅተናል... ፍቅርን ሸቅጠናል... ሃቂቃን አፍነናል... ጨቅላ ሕፃን ደፍረናል... እርጉዝ ሴት በሳንጃ ዘንጥለናል... ሰውን በቁሙ አቃጥለናል... ስጋውን ቀርጥፈን ከርስ ሞልተናል... ከመሰዊያ ላይ አርደናል... በስልጣናችን ባልገናል... ዘርፈናል፣ ቀጥፈናል፣ ሰስነናል - ይህች ምድር በእኛ ምክንያት ያላየችው ምን ቀሪ መከራ አለ?...
[ለኢጎአችን እስከጠቀመ ድረስ ጆሮ አደንዛዡን፣ ዓይን አፍዛዡን ሁሉ አድርገናል - እስካሁን ካደረግነው የሚበልጥ ምንም ሌላ ነገር ወደፊት አናደርግም... ከኛ በላይ የሚያደርግ ሌላ 'ሰይጣንም' የለም]
🌟 "If Satan is the exile of love, then maybe redemption is not believing in God — but becoming someone who does not create hell for another."
እውነት ሰይጣን ካለ ግን በእርግጠኝነት በዚህ ሰዓት ጡረታ ወጥቷል... አልያም መዝገብ ይዞ ክፋታችንን እየከተበ ነው... ወይም ደግሞ ከከፋው ተግባራችን ልምድ እየቀሰመ ይሆናል...
ያን የ Desert father's wisdom ታስታውሱት የለ?...
በአንድ ገዳም ውስጥ፣ አንድ ወጣኒ መነኩሴ እንቁላል ይሰርቅና ተደብቆ ሲጠብስ ይገኛል...
'ምን እያደረግህ ነው?' ያገኙት አባት ይጠይቁታል...
'አይ አባ... ሰይጣን አስቶኝ...' ወጣቱ ይርበተበታል...
ጉዳዩን ከመስኮት በኩል ሆኖ ሲከታተል የነበረው 'ሰይጣን' ታዲያ እንዲህ ሲል ራሱን ነፃ አወጣ...
'አባ ውሸቱን ነው... ይህችን መላ ያለዛሬም አላየሁዋት'...
___
🌟 ጎበዝ ሰዋዊ ጉዳዮቻችን የሚመሩት በግላጭም በስውርም ነው... እኛ - አስበን፣ ወስነን የምንከውነው ብቻ አይደለንም... ከማለዳ ዕድሜያችን ጀምሮ በልቡሰ-ጥላ (subconscious mind) ሲሞላ የኖረው ፕሮግራምም በድብቅ ይመራናል፤ ይቆጣጠረናል...
እርሱ ማንነታችንን ይገነባል... እርሱ ግንኙነታችንን ይመራል...
እዚያ ቅይጥ መልካችን ይከተባል... እዚያ መሻት መጥላታችን ይቀመራል...
ደግነት ክፋታችን፣ ርህራሔ ተንኮላችን፣ ጨዋነት ወራዳነታችን፣ ንቃት ድንዛዜያችን የመንታ አንድ ሆኖ ይላቆጣል...
___
🤔 ማብሰልሰያ - ፪
ንድፈ ሃሳባዊውን መለኪያ ትተን በተግባር ብንፈተሽ 'ሰይጣን' ከሚባለው 'ትርክት' የሚለየን ምንድነው?...
ለምሳሌ - ሰይጣን 'ፈታኝ ነው' እንላለን... እኛም በአባይ ቃል፣ በአታላይ ጥቅም ሌሎችን በማማለል እንፈትናለን...
ሰይጣን 'ከፋፋይ ነው' እንላለን... እኛም 'ልዩነትን' የጥላቻ ምንጭ፣ 'ማንነትን' የጦር መስበቂያ ሰበብ አድርገን የሰውን ልጅ ስንበልት እንኖራለን...
ሰይጣን 'ሐሰተኛ ነው' እንላለን... ነግቶ እስኪመሽ ቅጥፈት፣ መሽቶ እስኪነጋ እብለት አሽሞንሙነን ወገናችንን እንወጋለን...
🦋 ሰይጣን ለመባል ቀንድ አያስፈልገንም - ከቀንድ በላይ የሚወጋ ምላስ አለን... ገሃነመ እሳት አያስፈልገንም - ከጥይት አረር እስከ ከፋው ኒውክለር ሁሉን ታጥቀናል...
___
አንድ ጥንታዊ የሱፊ ወግ ልንገራችሁ...
አንድ ቀን አንድ ደርቪሽ መምህሩን እንዲህ ሲል ጠየቀ...
"መምህር ሆይ፣ ሰይጣንን ማሸነፍ የምችለው እንዴት ነው?"
መምህሩ መለሱ...
"በቅድሚያ የእርሱን ጫማ መዋስ አቁም"
መምህሩ በጫማ ነጽሮት ውስጥ ውስጠ ቅኝታችንን ነው ያጠየቁት... አሳባቢ፣ ጥሩር ቀጥቃጭ፣ ኃላፊነት ካጂ ውስጠ ማንነታችንን...
ያመሰጠሩት ስለ ዓይነ ትልልቅ፣ ባለ ጨልጨሌ፣ ቀንዳም ሰይጣን ሳይሆን - ልናይ ስላልፈቀድነው ማንነታችን ነው...
___
Meister Eckhart እንዲህ ይላል...
“The devil is simply that which pushes you away from your own center.”
🌟 ማዕከል (center) የሰው ልጅ ለሕላዌው ጣዕም የሚፈጥርበት፣ እንዲሁም በመኖር ወጀብ ከመናወጥ የሚድንበት መልህቁ ነው... ፍቅሩ፣ አገልጋይነቱ፣ እሴቱ፣ የሕይወት ፍቺው... ሻገር ብሎ ደግሞ ከነፍስያው፣ ከምንጩ፣ ከምልዓተ ዓለሙ የሚዋደድበት እትብቱ... ከዚህ ማዕከል የሚገፋውን ነገር ነው ማላዩ ኤካርት 'devil' ሲል የጠራው...
___
መውጫ - መወጣጫ
___
🔔 [ሰይጣን ከአካላዊ ማንነት ይልቅ ከፍቅር የመፋታት ምልክት ቢሆንስ?... ምናልባትም የንቃት ስንጥቃት አልያም ከአማናዊው የማንነታችን ምንጭ የመለያያት ጥልቀት ቢሆንስ?...]
እንደ እውነቱ ከሆነ ክፉ አስፈፃሚ አይደለም ያለው - ፈፃሚው ራሱ እንጂ... በሌላ አነጋገር ወይ እኛ ሰይጣን ነን - አልያም ብቅ እልም የምትል ስይጥንና አለችብን...
___
👉 ጨለማን ሁልጊዜ ሻማ በመለኮስ አንፋታውም... አንዳንዴ ጨለማነቱን መቀበልም ይኖርብናል... በተለይ የውስጣችን ኑባሬ ሲሆን በዓይኖቻችን ልናየው መድፈርም ግድ ይሆናል... ልክ ራሳችንን በመስታወት ፊት እያየን እንደምናወራው ሁሉ - "አንተ - እኔን ነህ... ያልተፈቀርከው፣ ያልተጎበኘኸው፣ ያልተደመጥከው እኔ... አሁን አጠገብህ ነኝ፣ እያየሁህ ነው..." ልንለው ይገባል...
___
@bridgethoughts
❤14👌3🔥2👍1🙏1