.
.
.
ከፊትለፊቴ ነው፣ ፍሬን የበጠሰ መኪና ድንገት የነጠቀው... ማንም ቦታው ላይ አልነበረም... ሮጬ ሄድኩ... ሆኖም በደም የጨቀየ ሰውነቱን ልነካ አልደፈርኩም... እጆቼ ተንቀጠቀጡብኝ... ደግሞስ ምን አደርግለታለሁ?...
በሰከንዶች ውስጥ ዕልፍ ነገሮች ተለዋውጠዋል...
ልብሶቹ አጥንት፣ ስጋና ደም ተላቁጠውበታል... ፊቱ እሳት ያገኘው ፕላስቲክ መስሏል... የሰውነት ክፍሎቹ ተሰባብረው ደቀዋል...
ዓይኖቹ ሊያወሩኝ እንደሚፈልጉ ነገሩኝ... መንቀሳቀስ አይችልም... ዝቅ አልኩ፣ አፉን የሞላው ደም ቱግ እንደሚል ጀበና እያስቸገረው አጉተመተመ... የምጥ ያህል በከበደ ትግል ውስጥ ሆኖ ደጋግሞ የነገረኝን ገጣጥሜ ልሰማው ሞከርኩ...
"ለልጄ እያየሁህ ነው በለው" ነበር ያለኝ...
ትንፋሹ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀጥ አለች...
ይህን እንዲለኝ ነበር ነፍሱ የጠበቀችው?...
የማላውቀውን ሰው መልዕክት ተሸክሜ የማላውቀው ልጁን በሕሊናዬ አመላለስኩ... በአካል ኑረት አብሮት ባይዘልቅ በመንፈስ ጎዳናው እጁን ይዞት እንዳለ እንዲሰማው ፈልጓል...
በዚህች የቅጽበት ዕድሜ፣ በአስደንጋጭ ክስተት ውስጥ፣ ምንም መሆን በማይችልበት ሁኔታ፣ 'ልጄ' የማለትን አቅምና ትውስታ እንዴት አገኘ?... ነፍሱ በምን ፍጥነት የስጋ ሞቱን ነገረችው?...
ውስጤ ብዙ ጥያቄዎች ተመላለሱ... ፈዝዤ ሳለሁ አካባቢው በጩኸት ተናጠ... እንደመንቃት አልኩ... ሰዎች ከበቡን... ልራመድ ስሞክር ግን እግሮቼ ጠፉብኝ... ደንዝዘው ነበር...
"ለልጄ እያየሁህ ነው በለው"
ልረሳ በማልችለው ፊት፣ ሊረሳ በማይችል ቃል፣ ቀድሞ ዕውቂያ የሌለን ሰው በልቤ ሰሌዳ ላይ ላይጠፋ እንደተከተበ ገባኝ...
____
[Re-ለአባቶች ቀን]
___
@bridgethoughts
.
.
ከፊትለፊቴ ነው፣ ፍሬን የበጠሰ መኪና ድንገት የነጠቀው... ማንም ቦታው ላይ አልነበረም... ሮጬ ሄድኩ... ሆኖም በደም የጨቀየ ሰውነቱን ልነካ አልደፈርኩም... እጆቼ ተንቀጠቀጡብኝ... ደግሞስ ምን አደርግለታለሁ?...
በሰከንዶች ውስጥ ዕልፍ ነገሮች ተለዋውጠዋል...
ልብሶቹ አጥንት፣ ስጋና ደም ተላቁጠውበታል... ፊቱ እሳት ያገኘው ፕላስቲክ መስሏል... የሰውነት ክፍሎቹ ተሰባብረው ደቀዋል...
ዓይኖቹ ሊያወሩኝ እንደሚፈልጉ ነገሩኝ... መንቀሳቀስ አይችልም... ዝቅ አልኩ፣ አፉን የሞላው ደም ቱግ እንደሚል ጀበና እያስቸገረው አጉተመተመ... የምጥ ያህል በከበደ ትግል ውስጥ ሆኖ ደጋግሞ የነገረኝን ገጣጥሜ ልሰማው ሞከርኩ...
"ለልጄ እያየሁህ ነው በለው" ነበር ያለኝ...
ትንፋሹ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀጥ አለች...
ይህን እንዲለኝ ነበር ነፍሱ የጠበቀችው?...
የማላውቀውን ሰው መልዕክት ተሸክሜ የማላውቀው ልጁን በሕሊናዬ አመላለስኩ... በአካል ኑረት አብሮት ባይዘልቅ በመንፈስ ጎዳናው እጁን ይዞት እንዳለ እንዲሰማው ፈልጓል...
በዚህች የቅጽበት ዕድሜ፣ በአስደንጋጭ ክስተት ውስጥ፣ ምንም መሆን በማይችልበት ሁኔታ፣ 'ልጄ' የማለትን አቅምና ትውስታ እንዴት አገኘ?... ነፍሱ በምን ፍጥነት የስጋ ሞቱን ነገረችው?...
ውስጤ ብዙ ጥያቄዎች ተመላለሱ... ፈዝዤ ሳለሁ አካባቢው በጩኸት ተናጠ... እንደመንቃት አልኩ... ሰዎች ከበቡን... ልራመድ ስሞክር ግን እግሮቼ ጠፉብኝ... ደንዝዘው ነበር...
"ለልጄ እያየሁህ ነው በለው"
ልረሳ በማልችለው ፊት፣ ሊረሳ በማይችል ቃል፣ ቀድሞ ዕውቂያ የሌለን ሰው በልቤ ሰሌዳ ላይ ላይጠፋ እንደተከተበ ገባኝ...
____
[Re-ለአባቶች ቀን]
___
@bridgethoughts
❤🔥8👍3🙏2❤1
.
.
.
የተናገራት ነገር ከንክኗታል... ደጋግማ ሰውነቷን ትመለከታለች... የሰውየው አስተያየት ምቾት አልሰጣትም...
ከጓደኛዬ ጋር ካፌ ውስጥ ተቀምጠን ነበር...
ከውጭ የተቀመጠ አንድ ደንበኛ ልጅቱን የሆነ ነገር ተናግሯት ስትረበሽ አየን... ቃል በቃል ከእርሱ አፍ ባንሰማም ከሰሞኑ በገጠማት ሚጢጢ ህመም ምክንያት ለአመል ያህል 'የቀነሰ' ሰውነቷ ላይ መዘባበቱ ግን ገብቶናል ...
ነገሩ ተፈጥሮአዊ ቢሆንም ሰውየው እንዲህ ሊረዳው የፈለገ አይመስልም... ጭራሽ በወጣች በገባች ቁጥር ሊያሳቅቃት ይሞክር ነበር...
[ህመሙ ከፈጠረባት ድካም በላይ የሰውየው ንግግር ሸክም ሲሆንባት ተሰማን...]
ልጅቱ እኮ በጣም ቆንጆ ናት!!
እርሱ ግን ይሄ አልታየውም... ወይም ደግሞ በእርሱ ቤት ጨዋታ ማሳመሩ ነው...
ልጅቱ እኮ እጅግ ትሁት ናት!!
እርሱ ግን ይሄ አልታየውም... ወይም ደግሞ ያዘነላት መስሎ አንጀት መብላቱ ነው...
ልጅቱ እኮ ዛሬም እንዳማረባት ነው!!
ሰውየው ግን ይህ ግድ አልሰጠውም... ወይም ደግሞ ለሰው ስሜት ፍጹም ደንታ ቢስ ነው...
እናም ማሳቀቅ ብቻ ነው የቻለበት...
___
Unfortunately ለሴት ልጅ የውበትና የማማር ጉዳይ 'አሳሳቢ' ርዕስ ነው... እንደ ወንድ ልጅ Careless ልትሆን የማትፈቅድበት ጉዳይዋ እንደሆነም ይታወቃል...
እናም...
'ዛሬ እንዴት እንዳማረብሽ!' ተብሎ ጨዋታ ይጀመራል... 'ትህትናሽ እኮ የትም አይገኝም' ተብሎ በውዳሴ ይለኮሳል... 'ልብሱን እኮ አሳመርሽው' ማለትም የአባት ነው...
ስለምን...
['ቁንጅና ታጥቦ ባይጠጣም' - ሰውን ስለ ገጹ ውበት አውስቶ ማጉላት ስለ ክሳቱ አውርቶ ከማድማት ይሻላልና]
[አልባስ ከከፈንነት ባይዘልም - ሰውን በልብሱ አመካኝቶ ማድነቅ ገላህ ሳሳ ብሎ ከማድቀቅ ይሻላልና]
ግና እርሱ...
"ከስተሻል" ነው ያላት... [በትክክል ያላትን እዚህ መድገም ነውር ሆኖብኝ ነው]
እናም እርሷ...
በጣም ደበራት!!...
[ሕመሟን ተኝቶ ማዳመጥ ትታ ነው ስራ የገባችው... ከአልጋ ሰው መርጣ ነው በዚህ የተገኘችው... ግና ያልጠበቀችው ሆነና ከፋት...]
___
ነገሩ ተራ አጋጣሚ ሊመስል ይችላል... ስለተለመደም ትኩረት ባይስብ አይገርምም... [በዚህ እግረ መንገድ ግን ልምምዳችን መነቀፍ ይኖርበታል...]
ምን መሰለህ?...
ስንገናኝ ቀልባችን የሚወሰደው በተራ ነገሮቻችን የመሆኑ ጉዳይ የሚያስቆዝም ነው... በአላፊ ጠፊው ላይ እናተኩራለን... በከንቱ ጉዳዮቻችን ላይ እንመሰጣለን... ያልበላንን እናካለን... የሰውን ቅስም እንሰብራለን...
ግልጽ እኮ ነው... "ስጋ ባዳ ነው"... ይመጣል ይሄዳል... ስለወፈሩ ሙላት፣ ስለከሱም ጉድለት የለም...
ሰው ያደረጉን ቁምነገሮቻችን ያሉት እኮ በማይታየው ነገራችን ውስጥ ነው... ደግነታችን፣ ቅንነታችን፣ ታማኝነታችን፣ ፍቅራችን ውስጥ... እኒህን ማየት አንችልም - መረዳት እንጂ...
___
[አየህ የልጅቱ ህመም ጊዜያዊ ነው... በድካም ስለተፈጠረ የሁለትና ሦስት ቀን ዕረፍት ከነመፈጠሩ ያጠፋዋል...]
የምላስ ወለምታ ግን እረፍት አይረታውም...
ስናሳጥረው...
ሰዎች ጉድለቴ የሚሉትን ነገር ማስታወስ ልክ አይደለም... 'በሰው ቁስል እንጨት የመስደድ' ቅሽምና ከሌለብህ በቀር...
ልትረዳው አልያም ልትቀይርለት በማትችለው ሁኔታ ውስጥ ያለን ሰው ብሶት ማባባስ በጎ አይደለም... በጥላቻ ካልታወርክ በቀር...
በቆዳህ ጥራት፣ በስጋህ ክብደት፣ በሃብትህ ብዛትም ሆነ በወንበርህ ክብደት መመካት ስህተት ነው... 'ሰከንዶች የሸሸጉትን አውቃለሁ' የማለት ድፍረት ካልሆነ በቀር...
___
ሁላችንም ሁሉን ነገር በተመሳሳይ መንገድ አንረዳም... የሸክም ልምዳችን ልዩ ልዩ ነው... አንዳንዶቻችን ስንጥር ያጎብጠናል፣ ሌሎቻችን ግንድ ይሰግድልናል...
እናም ይህን አስታውስ...
የቃል ክብሩ - ሳይቀል መነገሩ!!...
___
@bridgethoughts
.
.
የተናገራት ነገር ከንክኗታል... ደጋግማ ሰውነቷን ትመለከታለች... የሰውየው አስተያየት ምቾት አልሰጣትም...
ከጓደኛዬ ጋር ካፌ ውስጥ ተቀምጠን ነበር...
ከውጭ የተቀመጠ አንድ ደንበኛ ልጅቱን የሆነ ነገር ተናግሯት ስትረበሽ አየን... ቃል በቃል ከእርሱ አፍ ባንሰማም ከሰሞኑ በገጠማት ሚጢጢ ህመም ምክንያት ለአመል ያህል 'የቀነሰ' ሰውነቷ ላይ መዘባበቱ ግን ገብቶናል ...
ነገሩ ተፈጥሮአዊ ቢሆንም ሰውየው እንዲህ ሊረዳው የፈለገ አይመስልም... ጭራሽ በወጣች በገባች ቁጥር ሊያሳቅቃት ይሞክር ነበር...
[ህመሙ ከፈጠረባት ድካም በላይ የሰውየው ንግግር ሸክም ሲሆንባት ተሰማን...]
ልጅቱ እኮ በጣም ቆንጆ ናት!!
እርሱ ግን ይሄ አልታየውም... ወይም ደግሞ በእርሱ ቤት ጨዋታ ማሳመሩ ነው...
ልጅቱ እኮ እጅግ ትሁት ናት!!
እርሱ ግን ይሄ አልታየውም... ወይም ደግሞ ያዘነላት መስሎ አንጀት መብላቱ ነው...
ልጅቱ እኮ ዛሬም እንዳማረባት ነው!!
ሰውየው ግን ይህ ግድ አልሰጠውም... ወይም ደግሞ ለሰው ስሜት ፍጹም ደንታ ቢስ ነው...
እናም ማሳቀቅ ብቻ ነው የቻለበት...
___
Unfortunately ለሴት ልጅ የውበትና የማማር ጉዳይ 'አሳሳቢ' ርዕስ ነው... እንደ ወንድ ልጅ Careless ልትሆን የማትፈቅድበት ጉዳይዋ እንደሆነም ይታወቃል...
እናም...
'ዛሬ እንዴት እንዳማረብሽ!' ተብሎ ጨዋታ ይጀመራል... 'ትህትናሽ እኮ የትም አይገኝም' ተብሎ በውዳሴ ይለኮሳል... 'ልብሱን እኮ አሳመርሽው' ማለትም የአባት ነው...
ስለምን...
['ቁንጅና ታጥቦ ባይጠጣም' - ሰውን ስለ ገጹ ውበት አውስቶ ማጉላት ስለ ክሳቱ አውርቶ ከማድማት ይሻላልና]
[አልባስ ከከፈንነት ባይዘልም - ሰውን በልብሱ አመካኝቶ ማድነቅ ገላህ ሳሳ ብሎ ከማድቀቅ ይሻላልና]
ግና እርሱ...
"ከስተሻል" ነው ያላት... [በትክክል ያላትን እዚህ መድገም ነውር ሆኖብኝ ነው]
እናም እርሷ...
በጣም ደበራት!!...
[ሕመሟን ተኝቶ ማዳመጥ ትታ ነው ስራ የገባችው... ከአልጋ ሰው መርጣ ነው በዚህ የተገኘችው... ግና ያልጠበቀችው ሆነና ከፋት...]
___
ነገሩ ተራ አጋጣሚ ሊመስል ይችላል... ስለተለመደም ትኩረት ባይስብ አይገርምም... [በዚህ እግረ መንገድ ግን ልምምዳችን መነቀፍ ይኖርበታል...]
ምን መሰለህ?...
ስንገናኝ ቀልባችን የሚወሰደው በተራ ነገሮቻችን የመሆኑ ጉዳይ የሚያስቆዝም ነው... በአላፊ ጠፊው ላይ እናተኩራለን... በከንቱ ጉዳዮቻችን ላይ እንመሰጣለን... ያልበላንን እናካለን... የሰውን ቅስም እንሰብራለን...
ግልጽ እኮ ነው... "ስጋ ባዳ ነው"... ይመጣል ይሄዳል... ስለወፈሩ ሙላት፣ ስለከሱም ጉድለት የለም...
ሰው ያደረጉን ቁምነገሮቻችን ያሉት እኮ በማይታየው ነገራችን ውስጥ ነው... ደግነታችን፣ ቅንነታችን፣ ታማኝነታችን፣ ፍቅራችን ውስጥ... እኒህን ማየት አንችልም - መረዳት እንጂ...
___
[አየህ የልጅቱ ህመም ጊዜያዊ ነው... በድካም ስለተፈጠረ የሁለትና ሦስት ቀን ዕረፍት ከነመፈጠሩ ያጠፋዋል...]
የምላስ ወለምታ ግን እረፍት አይረታውም...
ስናሳጥረው...
ሰዎች ጉድለቴ የሚሉትን ነገር ማስታወስ ልክ አይደለም... 'በሰው ቁስል እንጨት የመስደድ' ቅሽምና ከሌለብህ በቀር...
ልትረዳው አልያም ልትቀይርለት በማትችለው ሁኔታ ውስጥ ያለን ሰው ብሶት ማባባስ በጎ አይደለም... በጥላቻ ካልታወርክ በቀር...
በቆዳህ ጥራት፣ በስጋህ ክብደት፣ በሃብትህ ብዛትም ሆነ በወንበርህ ክብደት መመካት ስህተት ነው... 'ሰከንዶች የሸሸጉትን አውቃለሁ' የማለት ድፍረት ካልሆነ በቀር...
___
ሁላችንም ሁሉን ነገር በተመሳሳይ መንገድ አንረዳም... የሸክም ልምዳችን ልዩ ልዩ ነው... አንዳንዶቻችን ስንጥር ያጎብጠናል፣ ሌሎቻችን ግንድ ይሰግድልናል...
እናም ይህን አስታውስ...
የቃል ክብሩ - ሳይቀል መነገሩ!!...
___
@bridgethoughts
❤10💊3👍1🔥1
“Think of Others”
__
As you prepare your breakfast — think of others.
Don’t forget to feed the pigeons.
As you conduct your wars — think of others.
Don’t forget those who want peace.
As you pay your water bill — think of others.
Think of those who have only the clouds to drink from.
As you go home, your own home — think of others — don’t forget those who live in tents.
As you sleep and count the stars, think of others — there are people who have no place to sleep.
As you liberate yourself with metaphors think of others — those who have lost their right to speak.
And as you think of distant others — think of yourself and say‘I wish I were a candle.
___
By: Mahmoud Darwish
___
[Mahmoud Darwish (1941–2008) was a Palestinian poet, essayist, and one of the most celebrated literary voices of the Arab world. He’s often called the poet of exile, the voice of Palestine, and a modern mystic of resistance and longing.]
___
@bridgethoughts
__
As you prepare your breakfast — think of others.
Don’t forget to feed the pigeons.
As you conduct your wars — think of others.
Don’t forget those who want peace.
As you pay your water bill — think of others.
Think of those who have only the clouds to drink from.
As you go home, your own home — think of others — don’t forget those who live in tents.
As you sleep and count the stars, think of others — there are people who have no place to sleep.
As you liberate yourself with metaphors think of others — those who have lost their right to speak.
And as you think of distant others — think of yourself and say‘I wish I were a candle.
___
By: Mahmoud Darwish
___
[Mahmoud Darwish (1941–2008) was a Palestinian poet, essayist, and one of the most celebrated literary voices of the Arab world. He’s often called the poet of exile, the voice of Palestine, and a modern mystic of resistance and longing.]
___
@bridgethoughts
❤2🕊1
እዚህ መንደራችን ውስጥ @HiwotWog ቻናል ላይ አጫጭር ታሪኮች ስትከትብ የምታውቋት ደራሲት ሕይወት እምሻው:
'ነገ ከስራ በኋላ አብራችሁኝ ብትሆኑ:
ቡና ፉት እያላችሁ፣
ወግ እየጠረቃችሁ
ጮርናቄ እየገመጣችሁ
፭ መፃሕፍት ሸምታችሁ ትደሰታላችሁ' ብላችኋለች...
___
ቦታ - አራት ኪሎ [ኢክላስ ሕንፃ - ዋልያ መፃሕፍት መደብር]
ሰዓት - ማምሻ 11:00
የመግቢያ ዋጋ - ምንም አይጠየቁም፣ ይልቅ ለመገኘትዎ ዋጋ ይቀበላሉ።
___
https://t.me/HiwotWog
'ነገ ከስራ በኋላ አብራችሁኝ ብትሆኑ:
ቡና ፉት እያላችሁ፣
ወግ እየጠረቃችሁ
ጮርናቄ እየገመጣችሁ
፭ መፃሕፍት ሸምታችሁ ትደሰታላችሁ' ብላችኋለች...
___
ቦታ - አራት ኪሎ [ኢክላስ ሕንፃ - ዋልያ መፃሕፍት መደብር]
ሰዓት - ማምሻ 11:00
የመግቢያ ዋጋ - ምንም አይጠየቁም፣ ይልቅ ለመገኘትዎ ዋጋ ይቀበላሉ።
___
https://t.me/HiwotWog
Telegram
የሕይወት እምሻው አጫጭር ታሪኮች/ Hiwot Emishaw
ሕይወት እምሻው የተወዳጆቹ ባርቾ፣ ፍቅፋቂ፣ ማታ ማታ፣ ለእርቃን ሩብ ጉዳይ፣ የቡና ቁርስ እና ዥዋዥዌ መጽሐፍት ደራሲ ናት። በዚህ መድረክ ወጎችን እና ልብ ወለዶችን ታቀርባለች።
🥰5🔥2❤1
.
.
.
Default setting
___
ከሃሳብ የሚያረጅ ስልተ-ምት አለ... ከቋንቋ የሚጠልቅ ጸጥታ አለ... በጎህ መቅደድ እርጋታ፣ በምትወድቅ ቅጠል ዥውታ፣ በሚመላለስ ትንፋሽ ፋታ፣ አንድ ስም የለሽ መሆንታ (being) አለ... ተፈጥሮአዊነት!!... ከስርዓቷ ጋር መዛነቅ፣ ከቅኝቷ ጋር መስማማት፣ ከአደራረጓ ጋር ስሙር መሆን...
የሆነ ጊዜ ከዚህ ተፈጥሮአዊ ቅንብር (setting) ጋር ያለ ድካም ሕብር እንፈጥር ነበር... ሰዓታት ከመተለማቸው በፊት፣ ጫጫታ ከመንገሱ በፊት፣ የሆነ ሰው ለመሆን ከመራወጣችን በፊት... ከኑረት ጡዘት፣ ከውድድር ቅኝት፣ ከፉክክር ውጥረታችን በፊት ከተፈጥሮ ስልተ-ምት ጋር ተጣጥሞሽ ነበረን...
ዛሬ ይሄ የለም...
ራሳችንን ዕረፍት አልባ አድርገነዋል... መንፈሳችንን በታትነነዋል... ለነፍሳችን ዓለም ባዕድ ሆነናል... የፈጠርነው ስርዓት ከተፈጥሮ ዝማሜ ለይቶን ሳይበቃው ስጋችንን እያጎሳቆለ ነው... ግንኙነታችንን እያቀጨጨ ነው...
የምር... ነፍሳችን ታፍናለች...
የሆነ ዓይነት መደንዘዝ ውስጥ እንዳለን ብናውቅም ስህተት ነው ለማለት ወኔ አላገኘንም... አንዳች መርግ ቢጫነንም መጉበጣችንን መቀበል አንፈልግም... የተፈጥሮን ስልተ-ምት ንቀን የፈጠርናቸው ሁሉም ስርዓቶች መልሰው እየበሉን ነው... ሆኖም በስሪታቸው ጥመት ላይ ስላልተግባባን በፈጠሩብን መዓት ላይ የጋራ አቋም አልያዝንም...
በቤትህ፣ በሰፈርህ፣ በከተማህ፣ በሃገርህ፣ በዓለም ዙሪያና በምድሪቱ ሁሉ ምን እየሆነ እንዳለ ተመልከት... አዕምሮና ልብህ ይስማሙልሃል?... በምትሰማው ወሬ፣ በምታየው ተግባር፣ በምትኖረው ኑሮ ደስተኛ ነህ?...
በጭራሽ!... የአኗኗራችንን ሙሉ ጤነኛነት justify የሚያደርግ አንድም ምክንያት የለም...
[የሆነ ነገራችንንማ አሞናል...]
___
እዚህች ጋ አንዳንድ ጉዳዮች እናንሳና የተፈጥሮን ቅኝት ዓለሚቱ function በምታደርግበት መነጽር እንመልከት...
__
@bridgethoughts
.
.
Default setting
___
ከሃሳብ የሚያረጅ ስልተ-ምት አለ... ከቋንቋ የሚጠልቅ ጸጥታ አለ... በጎህ መቅደድ እርጋታ፣ በምትወድቅ ቅጠል ዥውታ፣ በሚመላለስ ትንፋሽ ፋታ፣ አንድ ስም የለሽ መሆንታ (being) አለ... ተፈጥሮአዊነት!!... ከስርዓቷ ጋር መዛነቅ፣ ከቅኝቷ ጋር መስማማት፣ ከአደራረጓ ጋር ስሙር መሆን...
የሆነ ጊዜ ከዚህ ተፈጥሮአዊ ቅንብር (setting) ጋር ያለ ድካም ሕብር እንፈጥር ነበር... ሰዓታት ከመተለማቸው በፊት፣ ጫጫታ ከመንገሱ በፊት፣ የሆነ ሰው ለመሆን ከመራወጣችን በፊት... ከኑረት ጡዘት፣ ከውድድር ቅኝት፣ ከፉክክር ውጥረታችን በፊት ከተፈጥሮ ስልተ-ምት ጋር ተጣጥሞሽ ነበረን...
ዛሬ ይሄ የለም...
ራሳችንን ዕረፍት አልባ አድርገነዋል... መንፈሳችንን በታትነነዋል... ለነፍሳችን ዓለም ባዕድ ሆነናል... የፈጠርነው ስርዓት ከተፈጥሮ ዝማሜ ለይቶን ሳይበቃው ስጋችንን እያጎሳቆለ ነው... ግንኙነታችንን እያቀጨጨ ነው...
የምር... ነፍሳችን ታፍናለች...
የሆነ ዓይነት መደንዘዝ ውስጥ እንዳለን ብናውቅም ስህተት ነው ለማለት ወኔ አላገኘንም... አንዳች መርግ ቢጫነንም መጉበጣችንን መቀበል አንፈልግም... የተፈጥሮን ስልተ-ምት ንቀን የፈጠርናቸው ሁሉም ስርዓቶች መልሰው እየበሉን ነው... ሆኖም በስሪታቸው ጥመት ላይ ስላልተግባባን በፈጠሩብን መዓት ላይ የጋራ አቋም አልያዝንም...
በቤትህ፣ በሰፈርህ፣ በከተማህ፣ በሃገርህ፣ በዓለም ዙሪያና በምድሪቱ ሁሉ ምን እየሆነ እንዳለ ተመልከት... አዕምሮና ልብህ ይስማሙልሃል?... በምትሰማው ወሬ፣ በምታየው ተግባር፣ በምትኖረው ኑሮ ደስተኛ ነህ?...
በጭራሽ!... የአኗኗራችንን ሙሉ ጤነኛነት justify የሚያደርግ አንድም ምክንያት የለም...
[የሆነ ነገራችንንማ አሞናል...]
___
እዚህች ጋ አንዳንድ ጉዳዮች እናንሳና የተፈጥሮን ቅኝት ዓለሚቱ function በምታደርግበት መነጽር እንመልከት...
__
@bridgethoughts
🔥4❤3👍3
.
.
.
ፍጥነትን በምትሸልም ዓለም ውስጥ ነው የምንኖረው... እናም ሁሉም ነገር ይቸኩላል... ማሽኑ ይቸኩላል፣ እግረኛው ይቸኩላል፣ ንግግራችን ይቸኩላል፣ ማዕዳችን ይቸኩላል፣ ወዳጅነታችን ይቸኩላል፣ ጥላቻችን ይቸኩላል፣ ተግባራችን ይቸኩላል... የማይጣደፍ ነገር የለም...
እንቅስቃሴን ከለውጥ ሂደት ጋር እናምታታለን... ጫጫታን ከሃቂቃ ልክ እናዛንፋለን... ስክነትን ከጡዘት ጋር እናጋባለን... በንቃት ለመተንፈስ፣ ከልቡና ሆነን ለመስማት፣ ስሜታችንን ለማድመጥ በቂ ጊዜ የለንም...
[ይህ ምን ወለደ?... ጤናህን፣ ግንኙነትህን፣ ስሜትህን - አጢንና ምላሹን ለራስህ ስጥ...]
__
የተፈጥሮን ያልተነካካ ስርዓት (default setting) በመኖር ውስጥ ተጨማሪ ነገር ግድ አይደለም... አበቦች እንዲያብቡ 'ማሽነሪ' አይፈልጉም... ምድር ዙረቷን እንድትጠብቅ 'ሶፍትዌር' አትሻም... ጨረቃና ከዋክብት ለመድመቅ 'ካላንደር' አይጠይቁም... ወንዞች እንዲፈሱ 'ቱቦ' አያስፈልጋቸውም...
[እኔና አንተ ንቁ ሆነን ለመቆየት እንኳ ስንት ነገር ነው የሚያስፈልገን?...]
"Nature is pleased with simplicity. And nature is no dummy." — Isaac Newton
__
የዓለም ስርዓት ግለኝነትን ያበረታል፤ ተፈጥሮአዊነት ግን በሕብር ብቻ ይገለጣል... በጫካ ውስጥ አንዱም ፍጡር የብቻ ዓለም የለውም... ዛፎች የሚተነፍሱትን እንስሳቱ ይስቡታል፣ የአራዊቱ ውጋጅ ምድርን ያለሰልሳል... በተፈጥሮ ውስጥ ቅርጹን የሚቀይር እንጂ የሚጠፋ ነገር የለም...
ባልተረዳነው ጊዜ እንኳ የሚሰራ፣ ልንተማመንበት የሚገባ ታላቅ አስተውሎት ተፈጥሮ ውስጥ አለ... የኛን ቁጥጥር የማይፈልግ፣ ሁሉን በሰዓቱ የሚከውን፣ በፍጽምና የሚጓዝ አስደማሚ ጥበብ ተፈጥሮ ውስጥ አለ...
የምታዋጣው ክህሎት ሳይኖር የደም ዝውውርህ ይሳለጣል፣ ልብ በማትለው ጊዜም ቢሆን ትንፋሽህ ገብቶ ይወጣል፣ የሰውነትህ ክፍሎች (ልብህ፣ ኩላሊትህ፣ ጉበትህ...) ከአንተ ቁጥጥር ውጪ ሆነው መደበኛ ተግባራቸውን ይከውናሉ...
“Look deep into nature, and then you will understand everything better.” — Albert Einstein
ተፈጥሮ ውስጥ እያከማቹ መዝለቅ የለም፣ እየተው መሄድ እንጂ... ዛፎች ቅጠላቸውን ያረግፋሉ - በስብሰው ምድርን ያለማሉ፣ ፍሬያቸውን ይጥላሉ - ሌላ ዘር ይተካሉ፣ ብስሉን ይሰጣሉ - ረሃብ ይከላሉ... ደመና ይዘንባል፣ ከዋክብት ይወድቃሉ፣ ምድር ከፈኗን ትጥላለች...
[እኔና አንተስ?... ትርፋችንንም አንጋራም!... ይሄ ምን ወለደ?...]
___
ተፈጥሮ በውድድር ስርዓት እርስ በእርስ አትባላም - ሚዛን አኑራ ትጓዛለች እንጂ... መስመር አስምራ ድንበር ገፉብኝ አትልም - ልዩነት አጥፍታ ታጣምራለች እንጂ...
ተፈጥሮአዊነት ኋላ-ቀርነት አይደለም፣ አሁንና እዚህ መገኘት ብቻ እንጂ... ስልጣኔዎቻችንን መናቅ አይደለም፣ ጌቶቻችን እንዲሆኑ አለመፍቀድ እንጂ... ኑረትን ማጣጣል አይደለም፣ አማናዊውን ማንነት አለመርሳት እንጂ...
ነገሩ እኮ መመለስ ነው... ፊትን ወደ ቤት ማዞር!!... ወደ ጥንተ ማንነታችን መጓዝ...
____
አስተውለህ ካየህ...
በስልጣኔ ስም ኑረትን አወሳስበናታል... በውድድር ስም ዓለሚቱን ሲዖል አድርገናታል... ሃብት በማካበት ስም ንፍገትን አንብረናል... ምድሪቱ የገጠሙዋትን ፈተናዎች በሙሉ ብትመረምር የሰው ልጅ የተፈጥሮን ስርዓት ትቶ 'የኔ' የሚለውን ዘዬ በመከተሉ ምክንያት የገባበት ጭንቅ ጎልቶ ይታይሃል...
ጦርነት፣ ረሃብ፣ ስደት፣ እርዛት፣ አምባገነንነት፣ ጭካኔ፣ ጥላቻ... የሁሉም ምንጭ እኛው ነን... ችግሩ ያለው የፈጠርነው የዓለም ስርዓት ላይ እንጂ የተፈጥሮ 'ኢፍትሐዊነት' ላይ አይደለም...
ወደ ቤታችን እንመለስ... የተፈጥሮን default setting እንኑር...
___
ይህ ከዓለም ክፋት የመመነን ጥሪ አይደለም... በውስጧ ሆኖ የመንቃት ደወል እንጂ... ጨለምተኝነት፣ ኢ-ዘመናዊነት፣ አልያም የለውጥን ተፈጥሮአዊነት የመካድ ጉዳይ አይደለም... የእርጋታ፣ የመጠየቅ፣ ትንፋሽ የመውሰድ፣ የተማሩትን ትቶ ከተፈጥሮ ስልተ ምት ጋር የመጣማት ፍንጭ እንጂ...
[በግዳጅ ውስጥ የመኖር ጭቆና ሳይሆን በፍቃድ የመፍሰስ ሕልውና ነው... በፍርሃት የመጓዝ ድንብርብር ሳይሆን በነፃነት ከፍ የማለት ግብር ነው...]
ይህ የምልሰት ግብዣ ነው... አዲስ ነገር የመሆን ሳይሆን ወደ ቦታ የመመለስ ጥሪ... ስር የመትከል፣ መሬት የመርገጥ፣ የመስከን ደወል...
___
@bridgethoughts
.
.
ፍጥነትን በምትሸልም ዓለም ውስጥ ነው የምንኖረው... እናም ሁሉም ነገር ይቸኩላል... ማሽኑ ይቸኩላል፣ እግረኛው ይቸኩላል፣ ንግግራችን ይቸኩላል፣ ማዕዳችን ይቸኩላል፣ ወዳጅነታችን ይቸኩላል፣ ጥላቻችን ይቸኩላል፣ ተግባራችን ይቸኩላል... የማይጣደፍ ነገር የለም...
እንቅስቃሴን ከለውጥ ሂደት ጋር እናምታታለን... ጫጫታን ከሃቂቃ ልክ እናዛንፋለን... ስክነትን ከጡዘት ጋር እናጋባለን... በንቃት ለመተንፈስ፣ ከልቡና ሆነን ለመስማት፣ ስሜታችንን ለማድመጥ በቂ ጊዜ የለንም...
[ይህ ምን ወለደ?... ጤናህን፣ ግንኙነትህን፣ ስሜትህን - አጢንና ምላሹን ለራስህ ስጥ...]
__
የተፈጥሮን ያልተነካካ ስርዓት (default setting) በመኖር ውስጥ ተጨማሪ ነገር ግድ አይደለም... አበቦች እንዲያብቡ 'ማሽነሪ' አይፈልጉም... ምድር ዙረቷን እንድትጠብቅ 'ሶፍትዌር' አትሻም... ጨረቃና ከዋክብት ለመድመቅ 'ካላንደር' አይጠይቁም... ወንዞች እንዲፈሱ 'ቱቦ' አያስፈልጋቸውም...
[እኔና አንተ ንቁ ሆነን ለመቆየት እንኳ ስንት ነገር ነው የሚያስፈልገን?...]
"Nature is pleased with simplicity. And nature is no dummy." — Isaac Newton
__
የዓለም ስርዓት ግለኝነትን ያበረታል፤ ተፈጥሮአዊነት ግን በሕብር ብቻ ይገለጣል... በጫካ ውስጥ አንዱም ፍጡር የብቻ ዓለም የለውም... ዛፎች የሚተነፍሱትን እንስሳቱ ይስቡታል፣ የአራዊቱ ውጋጅ ምድርን ያለሰልሳል... በተፈጥሮ ውስጥ ቅርጹን የሚቀይር እንጂ የሚጠፋ ነገር የለም...
ባልተረዳነው ጊዜ እንኳ የሚሰራ፣ ልንተማመንበት የሚገባ ታላቅ አስተውሎት ተፈጥሮ ውስጥ አለ... የኛን ቁጥጥር የማይፈልግ፣ ሁሉን በሰዓቱ የሚከውን፣ በፍጽምና የሚጓዝ አስደማሚ ጥበብ ተፈጥሮ ውስጥ አለ...
የምታዋጣው ክህሎት ሳይኖር የደም ዝውውርህ ይሳለጣል፣ ልብ በማትለው ጊዜም ቢሆን ትንፋሽህ ገብቶ ይወጣል፣ የሰውነትህ ክፍሎች (ልብህ፣ ኩላሊትህ፣ ጉበትህ...) ከአንተ ቁጥጥር ውጪ ሆነው መደበኛ ተግባራቸውን ይከውናሉ...
“Look deep into nature, and then you will understand everything better.” — Albert Einstein
ተፈጥሮ ውስጥ እያከማቹ መዝለቅ የለም፣ እየተው መሄድ እንጂ... ዛፎች ቅጠላቸውን ያረግፋሉ - በስብሰው ምድርን ያለማሉ፣ ፍሬያቸውን ይጥላሉ - ሌላ ዘር ይተካሉ፣ ብስሉን ይሰጣሉ - ረሃብ ይከላሉ... ደመና ይዘንባል፣ ከዋክብት ይወድቃሉ፣ ምድር ከፈኗን ትጥላለች...
[እኔና አንተስ?... ትርፋችንንም አንጋራም!... ይሄ ምን ወለደ?...]
___
ተፈጥሮ በውድድር ስርዓት እርስ በእርስ አትባላም - ሚዛን አኑራ ትጓዛለች እንጂ... መስመር አስምራ ድንበር ገፉብኝ አትልም - ልዩነት አጥፍታ ታጣምራለች እንጂ...
ተፈጥሮአዊነት ኋላ-ቀርነት አይደለም፣ አሁንና እዚህ መገኘት ብቻ እንጂ... ስልጣኔዎቻችንን መናቅ አይደለም፣ ጌቶቻችን እንዲሆኑ አለመፍቀድ እንጂ... ኑረትን ማጣጣል አይደለም፣ አማናዊውን ማንነት አለመርሳት እንጂ...
ነገሩ እኮ መመለስ ነው... ፊትን ወደ ቤት ማዞር!!... ወደ ጥንተ ማንነታችን መጓዝ...
____
አስተውለህ ካየህ...
በስልጣኔ ስም ኑረትን አወሳስበናታል... በውድድር ስም ዓለሚቱን ሲዖል አድርገናታል... ሃብት በማካበት ስም ንፍገትን አንብረናል... ምድሪቱ የገጠሙዋትን ፈተናዎች በሙሉ ብትመረምር የሰው ልጅ የተፈጥሮን ስርዓት ትቶ 'የኔ' የሚለውን ዘዬ በመከተሉ ምክንያት የገባበት ጭንቅ ጎልቶ ይታይሃል...
ጦርነት፣ ረሃብ፣ ስደት፣ እርዛት፣ አምባገነንነት፣ ጭካኔ፣ ጥላቻ... የሁሉም ምንጭ እኛው ነን... ችግሩ ያለው የፈጠርነው የዓለም ስርዓት ላይ እንጂ የተፈጥሮ 'ኢፍትሐዊነት' ላይ አይደለም...
ወደ ቤታችን እንመለስ... የተፈጥሮን default setting እንኑር...
___
ይህ ከዓለም ክፋት የመመነን ጥሪ አይደለም... በውስጧ ሆኖ የመንቃት ደወል እንጂ... ጨለምተኝነት፣ ኢ-ዘመናዊነት፣ አልያም የለውጥን ተፈጥሮአዊነት የመካድ ጉዳይ አይደለም... የእርጋታ፣ የመጠየቅ፣ ትንፋሽ የመውሰድ፣ የተማሩትን ትቶ ከተፈጥሮ ስልተ ምት ጋር የመጣማት ፍንጭ እንጂ...
[በግዳጅ ውስጥ የመኖር ጭቆና ሳይሆን በፍቃድ የመፍሰስ ሕልውና ነው... በፍርሃት የመጓዝ ድንብርብር ሳይሆን በነፃነት ከፍ የማለት ግብር ነው...]
ይህ የምልሰት ግብዣ ነው... አዲስ ነገር የመሆን ሳይሆን ወደ ቦታ የመመለስ ጥሪ... ስር የመትከል፣ መሬት የመርገጥ፣ የመስከን ደወል...
___
@bridgethoughts
❤7👍6💊4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"... Part of me was frustrated because what did i do wrong?
Because you heard the music when i wrote the song."
___
Celia
___
@bridgethoughts
Because you heard the music when i wrote the song."
___
Celia
___
@bridgethoughts
❤5🥰1👌1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
.
.
.
አንተ አለህ ከጎኔ - ዝናብ የታባቱ
ክንድህ ይከልለኝ - ጥላ ምኑ ብርቱ?
ገላዬ ቢርስም - በደመና ፍ*ራሽ
ምድጃ ነው ልቤ - በፍቅርህ ተለኳሽ።
___
@bridgethoughts
.
.
አንተ አለህ ከጎኔ - ዝናብ የታባቱ
ክንድህ ይከልለኝ - ጥላ ምኑ ብርቱ?
ገላዬ ቢርስም - በደመና ፍ*ራሽ
ምድጃ ነው ልቤ - በፍቅርህ ተለኳሽ።
___
@bridgethoughts
❤9🔥2
.
.
.
የምሰራበት ተቋም "በቀጣይ አገልግሎቶቼን የማቀርበው የፋይዳ መታወቂያ ላላቸው ሰራተኞች ብቻ ስለሆነ ከወዲሁ መታወቂያ እንድታወጡ" የሚለውን ማሳሰቢያ ሰብሰብ ብለን በተቀመጥን ባልደረቦች የእጅ ስልክ ላይ ላከ...
ስልኮቻችን ጢው፣ ጺው፣ ኳኳ፣ ቡምቡም... እያሉ 'እንደየሃገራቸው' ጮሁ...
ይህ እንደሆነ አንደኛው ባልደረባችን 'ቴክስቱን' አንብቦ ሲጨርስ ለሌላኛው "እከሌ ፋይዳ አለህ?" ሲል ጠየቀው...
Oh my day!!
ሃሳቡ እኮ ገብቶኛል... ግን ደነገጥኩ...
ወደ ራሴ ዞሬ እኔዬን ጠየቅሁት... "እውን ፋይዳ አለህ?" ብዬ...
ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት ጥያቄ ለመመለስ ሲያምጥ ያላየሁት እኔታዬ ቁዘማ ሲወርሰው ታዘብኩ...
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አላችሁ?...
በቤታችሁ፣
በሰፈራችሁ፣
በማሕበረሰብ፣
በሃገራችሁ፣
በሕይወታችሁ፣
በመኖራችሁ፣
በስራ ቦታችሁ... ፋይዳ አላችሁ?... እውነት ፋይዳችሁ ምንድነው?...
የመኖር ዘፍጥረት፣ የሕላዌ አሃዱ፣ የመውጣት መግባታችን ውበት ፋይዳ ነው... አበርክቶ... ዋጋ... ክብረት... ከተቀበሉት በላይ መስጠት፣ ማኖር፣ መብራት፣ መምራት፣ ወዝ መቀላቀል፣ መፍጋት፣ ምርኩዝ መሆን...
እንጂማ መኖር ምን ትርጉም አለው? - እየፈየዱ ትርጉም ካልሰጡት...
___
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አለሽሽ?...
___
ሁለቱ የምድራችን ታላላቅ ነፍሶች ስለ ፋይዳ ይህን ብለው ነበር...
"Only a life lived for others is a life worthwhile." ~ Albert Eisenstein
"The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others." ~ Mahatma Gandhi
___
@bridgethoughts
.
.
የምሰራበት ተቋም "በቀጣይ አገልግሎቶቼን የማቀርበው የፋይዳ መታወቂያ ላላቸው ሰራተኞች ብቻ ስለሆነ ከወዲሁ መታወቂያ እንድታወጡ" የሚለውን ማሳሰቢያ ሰብሰብ ብለን በተቀመጥን ባልደረቦች የእጅ ስልክ ላይ ላከ...
ስልኮቻችን ጢው፣ ጺው፣ ኳኳ፣ ቡምቡም... እያሉ 'እንደየሃገራቸው' ጮሁ...
ይህ እንደሆነ አንደኛው ባልደረባችን 'ቴክስቱን' አንብቦ ሲጨርስ ለሌላኛው "እከሌ ፋይዳ አለህ?" ሲል ጠየቀው...
Oh my day!!
ሃሳቡ እኮ ገብቶኛል... ግን ደነገጥኩ...
ወደ ራሴ ዞሬ እኔዬን ጠየቅሁት... "እውን ፋይዳ አለህ?" ብዬ...
ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት ጥያቄ ለመመለስ ሲያምጥ ያላየሁት እኔታዬ ቁዘማ ሲወርሰው ታዘብኩ...
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አላችሁ?...
በቤታችሁ፣
በሰፈራችሁ፣
በማሕበረሰብ፣
በሃገራችሁ፣
በሕይወታችሁ፣
በመኖራችሁ፣
በስራ ቦታችሁ... ፋይዳ አላችሁ?... እውነት ፋይዳችሁ ምንድነው?...
የመኖር ዘፍጥረት፣ የሕላዌ አሃዱ፣ የመውጣት መግባታችን ውበት ፋይዳ ነው... አበርክቶ... ዋጋ... ክብረት... ከተቀበሉት በላይ መስጠት፣ ማኖር፣ መብራት፣ መምራት፣ ወዝ መቀላቀል፣ መፍጋት፣ ምርኩዝ መሆን...
እንጂማ መኖር ምን ትርጉም አለው? - እየፈየዱ ትርጉም ካልሰጡት...
___
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አለሽሽ?...
___
ሁለቱ የምድራችን ታላላቅ ነፍሶች ስለ ፋይዳ ይህን ብለው ነበር...
"Only a life lived for others is a life worthwhile." ~ Albert Eisenstein
"The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others." ~ Mahatma Gandhi
___
@bridgethoughts
❤15🥰2
.
.
.
ድሃ ቤት ስታድግ 'ሃብታም' የማያውቃቸውን ብዙ ወጎች ትለምዳለህ...
ለምሳሌ...
እናትህ እራትህ ላይ ጨው በዛ አድርጋ የሰጠችህ ዕለት... ምግቡን ቀመስ ታደርግና...
'እማዬ፣ ጨው እኮ በዝቷል...' ስትላት፤
'አውቄያለሁ ዝም ብለህ ብላ... ውሃ እንዲያስጠጣህ ብዬ ነው' ትልሃለች...
___
የሆነ ቀን ደግሞ መባያው ያንስባታል... እንዲርብህ ግን በጭራሽ አትፈልግም ድስቱን ጠራርጋም ቢሆን ታቀርብልህና...
'በል እያጠቀስክ ብላ፣ መበያና ወንድም ማስፈራሪያ ነው' ትልሃለች...
___
ያው ሁሌ አይሳካም አይደል?... ሌላ ጊዜ ደግሞ ቤቱ ብጣሽ እንጀራ ብርቅ ይሆንበታል... ይሄኔ እናትህ...
'ይህችን ቀምሰህ ውሃ ጠጣበት፣ ሆድ እንዳሳዩት ነው' ብላ ለእራት ሽምብራ ቆሎ ትሰጥሃለች...
___
በዓል ደርሶ፣ ጎረቤት የተሰራው ሥጋ ወጥ ሲያስጎመዥህና ምራቅህን እያስዋጠ ሲያስቸግርህ...
'እማዬ፣ እዚህ ቤት ግን ሥጋ ወጥ የሚበላው መች ነው?' ስትላት...
'ያለለት... አለች የያለለት እናት፤ ያለለት ነዋ ልጄ!' ትልሃለች...
ምናልባት በጥያቄህ ገፍተህ ከተጫንካት ደግሞ፣ 'ሰው እንደ ቤቱ እንጂ እንደ ጎረቤቱ አይኖርም' ብላ ኮስተር ትልብሃለች...
___
እናት ግን ሳታበላህ የማትበላ፣ 'አፈር ልብላ' ሳትልህ የማትውል፣ የሆዷን ጥያቄ በመቀነት ጨቁና የአንተን ሆድ ብቻ ለመሙላት የምትታትር... መሆኗን ልብ በል!!
___
ደግሞ ወዲህ...
ጥሬ ሽሮ ተበጥብጦ፣ ብትን ጨው በውሃ ሟሙቶ፣ ሚጥሚጣ ተጠቅሶ፣ በርበሬ ድልህ ሆኖ፣ ተልባ በውሃ ርሶ፣ ቃሪያ በጨው ተሰንጎ፣ ጎመን ተለብልቦ (ዘይት የጠፋ'ለት)፣ ሽንኩርት በጨው ተጠቅሶ... ወዘተ
በመበያነት የሚታወቁት ድሃ ቤት ብቻ ነው...
___
ሌላም አለ...
"አይቶ አጣ ቤት ጎመን የተቀቀለ ዕለት ሲጨበጨብ ያድራል"
"ሆድን በጎመን ቢደልሉት፣ ጉልበት በዳገት ይለግማል"
"ለአኩራፊ ምሳው እራቱ ነው"
"ምን ያመጣ ድሃ፣ ምን ያገሳ ውሃ"
"በሚያዝያ ጎመን የዘራ፣ ክረምቱን ሁሉ በላ"
"አህያ እንደምትታለብ፣ ከላሞች ፊት ትቅለበለብ"
"የችግር ክፉ እህል ማጣት፣ የኃጢዓት ክፉ ነፍስ ማጥፋት"
"ያፌን እስክውጥ ዕድሜ ይስጠኝ፣ ይላል እርኩም"
.
.
.
ዓይነቶቹን ተረት የምትሰማው ከድሃ ብቻ ነው...
___
Damn!!...
ዛሬም እዚያው ነን...
___
አንድ እውነት ግን አለ...
የድሃ ድህነት የሞራል አይደለም!!... ለማግኘት ብሎ ክብሩን አይጥልም!!!... ሆዱን ሊሞላ ሃገር አይሰርቅም!!!... ረሃብ ሊከላ ቃሉን አይበላም!!!...
___
@bridgethoughts
.
.
ድሃ ቤት ስታድግ 'ሃብታም' የማያውቃቸውን ብዙ ወጎች ትለምዳለህ...
ለምሳሌ...
እናትህ እራትህ ላይ ጨው በዛ አድርጋ የሰጠችህ ዕለት... ምግቡን ቀመስ ታደርግና...
'እማዬ፣ ጨው እኮ በዝቷል...' ስትላት፤
'አውቄያለሁ ዝም ብለህ ብላ... ውሃ እንዲያስጠጣህ ብዬ ነው' ትልሃለች...
___
የሆነ ቀን ደግሞ መባያው ያንስባታል... እንዲርብህ ግን በጭራሽ አትፈልግም ድስቱን ጠራርጋም ቢሆን ታቀርብልህና...
'በል እያጠቀስክ ብላ፣ መበያና ወንድም ማስፈራሪያ ነው' ትልሃለች...
___
ያው ሁሌ አይሳካም አይደል?... ሌላ ጊዜ ደግሞ ቤቱ ብጣሽ እንጀራ ብርቅ ይሆንበታል... ይሄኔ እናትህ...
'ይህችን ቀምሰህ ውሃ ጠጣበት፣ ሆድ እንዳሳዩት ነው' ብላ ለእራት ሽምብራ ቆሎ ትሰጥሃለች...
___
በዓል ደርሶ፣ ጎረቤት የተሰራው ሥጋ ወጥ ሲያስጎመዥህና ምራቅህን እያስዋጠ ሲያስቸግርህ...
'እማዬ፣ እዚህ ቤት ግን ሥጋ ወጥ የሚበላው መች ነው?' ስትላት...
'ያለለት... አለች የያለለት እናት፤ ያለለት ነዋ ልጄ!' ትልሃለች...
ምናልባት በጥያቄህ ገፍተህ ከተጫንካት ደግሞ፣ 'ሰው እንደ ቤቱ እንጂ እንደ ጎረቤቱ አይኖርም' ብላ ኮስተር ትልብሃለች...
___
እናት ግን ሳታበላህ የማትበላ፣ 'አፈር ልብላ' ሳትልህ የማትውል፣ የሆዷን ጥያቄ በመቀነት ጨቁና የአንተን ሆድ ብቻ ለመሙላት የምትታትር... መሆኗን ልብ በል!!
___
ደግሞ ወዲህ...
ጥሬ ሽሮ ተበጥብጦ፣ ብትን ጨው በውሃ ሟሙቶ፣ ሚጥሚጣ ተጠቅሶ፣ በርበሬ ድልህ ሆኖ፣ ተልባ በውሃ ርሶ፣ ቃሪያ በጨው ተሰንጎ፣ ጎመን ተለብልቦ (ዘይት የጠፋ'ለት)፣ ሽንኩርት በጨው ተጠቅሶ... ወዘተ
በመበያነት የሚታወቁት ድሃ ቤት ብቻ ነው...
___
ሌላም አለ...
"አይቶ አጣ ቤት ጎመን የተቀቀለ ዕለት ሲጨበጨብ ያድራል"
"ሆድን በጎመን ቢደልሉት፣ ጉልበት በዳገት ይለግማል"
"ለአኩራፊ ምሳው እራቱ ነው"
"ምን ያመጣ ድሃ፣ ምን ያገሳ ውሃ"
"በሚያዝያ ጎመን የዘራ፣ ክረምቱን ሁሉ በላ"
"አህያ እንደምትታለብ፣ ከላሞች ፊት ትቅለበለብ"
"የችግር ክፉ እህል ማጣት፣ የኃጢዓት ክፉ ነፍስ ማጥፋት"
"ያፌን እስክውጥ ዕድሜ ይስጠኝ፣ ይላል እርኩም"
.
.
.
ዓይነቶቹን ተረት የምትሰማው ከድሃ ብቻ ነው...
___
Damn!!...
ዛሬም እዚያው ነን...
___
አንድ እውነት ግን አለ...
የድሃ ድህነት የሞራል አይደለም!!... ለማግኘት ብሎ ክብሩን አይጥልም!!!... ሆዱን ሊሞላ ሃገር አይሰርቅም!!!... ረሃብ ሊከላ ቃሉን አይበላም!!!...
___
@bridgethoughts
❤22👍3🥰3🙏1
.
.
.
ለራስህ እውነተኛ ስሜት ታማኝ ሆነህ ትቆያለህ ወይስ ለሌሎች ስሜት ለመመቸት ስትል ሚዛን ትስታለህ?
ዋጋ የምትሰጣቸው ነገሮች ምንነት አጠቃላይ ነገርህን ይወስኑታል... እሴትህ ወይም 'value' የምታደርጋቸው ነገሮች ስላንተ ያለውን አጠቃላይ እውነት ይናገራሉ...
ለሃቅ ዋጋ ትሰጣለህ - እውነተኛ ትሆናለህ... ሃሰት ካልጎረበጠህ በክህደት ትሰለጥናለህ... ገንዘብ ታመልካለህ - ለሃብት ስትል እስከ መግደል ትደርሳለህ... ባለህ ከተብቃቃህ መካፈል ታውቃለህ...
የሰው ልጅ 'ሰውነት' የተለየው በጥላው ቅርጽ አይደለም... በሚጠራበት ስም፣ በተሸከመው ስመ-ማሕተም፣ በሰበሰበው ሃብት እና ምድራዊ ቁሳቁስ አይደለም... በልቡ መሰዊያ ላይ በሚያቀርባት የዕጣን ሽቱ፣ ዓይን ባላየው ጊዜ በሚንበረከክላት እውነቱ፣ ሁሉ ባወገዘው ጊዜ በሚቆምላት እምነቱ እንጂ...
ብዙዎች 'ለወርቅ' ይሰግዳሉ - ጥቂቶች የጸጥታን ውበት ያመልካሉ... እልፎች እውነትን ለጭብጨባና ርካሽ አድናቆት አሳልፈው ይሰጣሉ - ጥቂቶች የሃቂቃቸውን ላምባ ከፍ አድርገው ይጓዛሉ...
እነዚያ 'እኛን ምሰል' ማለት ያዘወትራሉ - ያልመሰለን ማራቅ፣ ያልመሰለን ማድቀቅ ያውቁበታል...
እነዚህ መሆንን ይኖራሉ - መምሰል የነፍስያን ቀለም የሚያጠፋ ጥላት፣ ውስጠትን የሚበላ ሻህላ እንደሆነ ያውቃሉ...
አዎን... መንጋውን ከሚያብር ፍም ይልቅ በሚያረግድ ንፋስ ፊት የሚቆም የኩራዝ ነበልባል የበለጠ የሞራል ብርታት አለው...
እሴተኝነት እስረኝነት አይደለም - ፍሬ እንጂ... አጥልቀህ ስትቀብረው ተልቆ ብቅ ይላል... ሥጋህ እንኳ ቢያልፍ ለስምህ ዘብነት ደን ሆኖ ይበቅላል... ልጆችህ ይኮሩበታል - መንዝረው ይከብሩበታል...
ይህን ያጣህ'ለት ግን ማንም ትሆናለህ... ከቆምክበት ሞገስ አይኖርህም... ባለፍክበት ክብር አይቆይልህም...
እንጂማ...
ሰው ከእሴቱ ውጭ ምንድነው?...
___
@bridgethoughts
.
.
ለራስህ እውነተኛ ስሜት ታማኝ ሆነህ ትቆያለህ ወይስ ለሌሎች ስሜት ለመመቸት ስትል ሚዛን ትስታለህ?
ዋጋ የምትሰጣቸው ነገሮች ምንነት አጠቃላይ ነገርህን ይወስኑታል... እሴትህ ወይም 'value' የምታደርጋቸው ነገሮች ስላንተ ያለውን አጠቃላይ እውነት ይናገራሉ...
ለሃቅ ዋጋ ትሰጣለህ - እውነተኛ ትሆናለህ... ሃሰት ካልጎረበጠህ በክህደት ትሰለጥናለህ... ገንዘብ ታመልካለህ - ለሃብት ስትል እስከ መግደል ትደርሳለህ... ባለህ ከተብቃቃህ መካፈል ታውቃለህ...
የሰው ልጅ 'ሰውነት' የተለየው በጥላው ቅርጽ አይደለም... በሚጠራበት ስም፣ በተሸከመው ስመ-ማሕተም፣ በሰበሰበው ሃብት እና ምድራዊ ቁሳቁስ አይደለም... በልቡ መሰዊያ ላይ በሚያቀርባት የዕጣን ሽቱ፣ ዓይን ባላየው ጊዜ በሚንበረከክላት እውነቱ፣ ሁሉ ባወገዘው ጊዜ በሚቆምላት እምነቱ እንጂ...
ብዙዎች 'ለወርቅ' ይሰግዳሉ - ጥቂቶች የጸጥታን ውበት ያመልካሉ... እልፎች እውነትን ለጭብጨባና ርካሽ አድናቆት አሳልፈው ይሰጣሉ - ጥቂቶች የሃቂቃቸውን ላምባ ከፍ አድርገው ይጓዛሉ...
እነዚያ 'እኛን ምሰል' ማለት ያዘወትራሉ - ያልመሰለን ማራቅ፣ ያልመሰለን ማድቀቅ ያውቁበታል...
እነዚህ መሆንን ይኖራሉ - መምሰል የነፍስያን ቀለም የሚያጠፋ ጥላት፣ ውስጠትን የሚበላ ሻህላ እንደሆነ ያውቃሉ...
አዎን... መንጋውን ከሚያብር ፍም ይልቅ በሚያረግድ ንፋስ ፊት የሚቆም የኩራዝ ነበልባል የበለጠ የሞራል ብርታት አለው...
እሴተኝነት እስረኝነት አይደለም - ፍሬ እንጂ... አጥልቀህ ስትቀብረው ተልቆ ብቅ ይላል... ሥጋህ እንኳ ቢያልፍ ለስምህ ዘብነት ደን ሆኖ ይበቅላል... ልጆችህ ይኮሩበታል - መንዝረው ይከብሩበታል...
ይህን ያጣህ'ለት ግን ማንም ትሆናለህ... ከቆምክበት ሞገስ አይኖርህም... ባለፍክበት ክብር አይቆይልህም...
እንጂማ...
ሰው ከእሴቱ ውጭ ምንድነው?...
___
@bridgethoughts
🥰6❤4