4-3-3 ስፖርት በ ኢትዮጵያ
481K subscribers
89.6K photos
263 videos
3 files
3.06K links
ከእሁድ እስከ እሁድ ፈጣን የመረጃ ምንጭ!

➮የሃገር ቤት ትኩስ ትኩስ መረጃዎች
➮የአፍሪካ መረጃዎችን በሙሉ
➮የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ሙሉ መረጃ
➮ቁጥራዊ መረጃዎች እና ዳሰሳዎች
➮ጨዋታዎችን በቀጥታ ከየስታዲየሙ

➮በስልክ ጥሪ ምንም አይንት የማስታወቂያ ስራ አንቀበልም!

ለማስታወቂያ ስራ @Promotion_4_3_3_Bot

Cʀᴇᴀᴛᴏʀ @Simera10

⓸-⓷-⓷ስፖርት በኢትዮጵያ| 2016
Download Telegram
የ11ኛ ሳምንት የMLS የክለቦች ደረጃ...

1. ኢንተር ሚያሚ

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ እና ሉክ ሻው በዚህ ሳምንት ወደ ልምምድ ተመልሰዋል!

ምናልባት አሁንም በቅርብ ጊዜያት ውስጥ መጫወት አይችሉም ነገር ግን በግንቦት 8 ከማንቸስተር ሲቲ ጋር ለሚደረገው የኤፍኤ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ ተብሎ ተገምቷል።

[Sky Sport & MEN]

@Bisrat_sport_433et @Bisrat_sport_433et
በታሪክ ብዙ የሻምፒዮንሺፕ ዋንጫ ያነሱ ክለቦች፡-

ሌስተር ሲቲ (8)
ማንቸስተር ሲቲ (7)
ኖርዊች ሲቲ (5)
ሰንደርላንድ (5)
ሼፊልድ ዌንስደይ (5)

@Bisrat_sport_433et @Bisrat_sport_433et
ለባየር ሙኒክ በቻምፒዮንስ ሊጉ 150ኛውን ጨዋታ አድርገሃል። ይህ ማለት በቻምፒዮንስ ሊግ ታሪክ ሶስተኛው ነህ ማለት ነው።

🗣️ ቶማስ ሙለር፡ "መጥፎ አይደለም። እዚህ ላይ ለመድረስ በደንብ መብላት አለብህ በደንብም መተኛት አለብሕ" ፈገግ እያለ።

ቶማስ እራስህን እንዳረጀ ሰው ትቆጥራለህ?

🗣️ "አይ አይ አልቆጥርም። አሁን ጥሩ ይሰማኛል። ነገር ግን 😁ችዋሜኒ ለቀጣይ ጨዋታ ታክቲክ ብሎ እየሰማኝ ነው😂😂 እናም ጥሩ ይሰማኛል ሆኖም በውጤቱ አልረካሁም። ያው ሪያል ማድሪድ ነው። ታውቀዋለህ፣ ከሲቲ ጋር የነበረውን ሁለት ጨዋታ ታየዋለህ፣ ባለፉ ግጥሚያዎቹም ያለውን ትመለከታለህ ጥንቃቄ በያንዳንዱ ደቂቃ ማድረግ ይገባል።"

"እዩት ቶኒ ክሩስ እየሳቀ ነው። ሁልጊዜም እንዲህ እንደሆነ ያውቃል ለዛ ነው"😁

ሲናገሩ ለዛ ካላቸው ተጫዋቾች መሃል አንዱ የሆነው ቶማስ ሙለር ስለትላንትናው ምሽት ከሰጠው አስተያየት የተወሰደ

@Bisrat_sport_433et @Bisrat_sport_433et
ዲሚታር ቤርባቶቭ፡🗣

"በእኛ ጊዜ ማንቸስተር ዩናይትድ ሩኒ፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ጊግስ፣ ስኮልስ፣ ቪዲች፣ ኔቪል፣ ቫን ደርሳር፣ ኤቭራ፣ ፈርዲናንድ እና አሌክስ ፈርጉሰን ነበሩት። ብዙ ተፎካካሪዎች ወደ ሜዳ ከመግባታችን በፊት ተሸንፈው ነበር ጨዋታ የሚጀምሩት።"

@Bisrat_sport_433et @Bisrat_sport_433et
📅 ከ5 አመት በፊት በዚች ቀን ሊዮኔል ሜሲ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ በካምፕ ኑ ሊቨርፑል ላይ ይቺን ድንቅ የቅጣት ምት ጎል አስቆጥሯል 🤯

Unforgettable 💨

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
ፔፕ ጋርዲዮላ ኢልካይ ጉንዶጋንን ናፍቋል !

ማንቸስተር ሲቲ ይህንን ተጫዋች ለቆ ወደ ባርሴሎና እንዲሄድ በመፍቀዱ ተፀፅቷል እናም አሁን ላይ ተጫዋቹ ወደ ማንቸስተር መመለስ ከፈለገ ጋርዲዮላ በክብር ይቀበለዋል።

[Mundo Deportivo]

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
ሊዊስ ካስትሮ በዛሬው የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ከህመም አገግመሞ ቡድኑን ወደ መምራት ይመለሳል!

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
በ አንድ ወቅት በ አልያንዝ አሬና ግድግዳ ላይ በትልቁ ሰፍሮ የሚገኝ ፅሁፍ ነበር እሱም እንዲ የሚል ነበር !

"
ፈጣሪ ሁሉንም ሰው ይምራል ከ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በስተቀር "

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
4-3-3 ስፖርት በ ኢትዮጵያ
ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ ወደ ልምምድ ተመልሷል! አንዲሁም በተመሳሳይ ማርከስ ራሽፎርድም ወደ ልምምድ ተመልሷል። @Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
ስካይ ስፖርቶች በትናንትናው እለት ማርቲኔዝ ወደ ልምምድ ተመልሷል ብሎ የለቀቁትን ቪዲዮ አጥፍተውታል

ምክንያትም ቪዲዮ የቆየ በመሆኑ ነው ይህን የሚያክል ትልክ ካምፓኒ እንዴት እንደዚህ አይነት ትልቅ ስህተት ይሳሳታል

በዛ ላይ ደግሞ የተጎዳው ማክቶሚናይ ጓንት ለብሶ ልምምድ ሲሰራ የቪዲዮ ላይ ይታያል 😂

እኛ እራሱ እንዴት ተሸወድን 😁

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
💳 UPDATE

ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ እና ሉክ ሻው የግል ልምምድ ብቻቸውን በካሪንግተን የጀመሩ ሲሆን በሚቀጥሉት ሳምንታት ወደ ቡድን ልምምድ እንደሚመለሱ ይጠበቃል ሲሉ የካሪንግተን ምንጮች ተናግረዋል !

ስለ ስካይ ስፖርት ያወጣው ቪዲዮ የቆየ ቢሆን የተጫዋቾቹ መመለሻ ግዜ ግን የቀረበ ነው

ከስካይ ስፖርት እንዲህ አይነት ቀሽም ስህተት ተሰምቶ ስለ ማያውቅ ሁላችንም ቪዲዮን ብናየውም ከስካይ እውነተኛነት አንፃር ምንም ጥርጣሬ አልነበረንም ቪዲዮውን ትናንት አመሻሽ ላይ እስኪያጠፋት ድረስ !

ለማንኛውም ተሳስተን ሰላሳሳትናቹ ይቅርታ

😍 4-3-3 ስፖርት በኢትዮጵያ ☑️

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ኤቨርተኖች ሊቨርፑልን 2 ለ 0 በረቱበት ጨዋታ ላይ ጉዳት አሰተናግዶ የነበረው ቪታሊ ማይኮሌንኮ

በጨዋታው ላይ ባጋጠመው የቁርጭምጭሚት ጅማት መበጠስ ምክንያት ተጫዋቹ ከቀሪው የውድድር ዓመት ውጪ መሆኑን ተገልጿል።

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
ዲሳሲ እና ቲያጎ ሲልቫ በቼልሲ ጉዳት ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ከቶተንሃም ጋር ለሚያደርጉት ጨዋታ አይገኙም።

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
የጀርመኑ ክለብ ዶርትሙንድ ከ ፈረንሳዩ ቱጃር ክለብ ፒኤስጂ ጋር በሻምፒየንስ ሊጉ ግማሽ ፍፃሜ ይፋጠጣሉ…ይህ አጓጊ ጨዋታ በማን አሸናፊነት ይጠናቀቅ ይሆን?

እስቲ ጨዋታውን ከሄኒከን ጋር አብረን የሚሆነውን እናያለን
የትግራይ ክልል ክለቦች ከጦርነቱ በፊት ወደነበሩበት ሊግ ከ2017 ጀምሮ ተመልሰው እንዲወዳደሩ ውሳኔ ተላለፈ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ የትግራይ ክልል ክለቦች ሙሉ ለሙሉ ከጦርነቱ በፊት ሲወዳደሩበት ወደነበረው ሊግ ከ2017 ጀምሮ ተመልሰው እንዲወዳደሩ ውሳኔ አሳልፏል።

የኢፌዴሪ ባሕል እና ስፖርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የክልሉ ክለቦች በፕሪምየር ሊግ፣ ከፍተኛ ሊግ እና አንደኛ ሊግ ሲያደርጓቸው የነበሩ ውድድሮችን ማቋረጣቸውን በመጥቀስ መንግሥት እና የትግራይ ክልል አመራሮች በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶርያ የሰላም ስምምነት በመፈረም ሁሉም ነገር ወደነበረበት እንዲመለስ መግባባት ላይ በተደረሰው መሠረት ሁሉም የትግራይ ክልል ክለቦች ከጦርነቱ በፊት ሲወዳደሩበት ወደነበረው ሊግ ከ2017 ጀምሮ ተመልሰው እንዲወዳደሩ በላከው ደብዳቤ ጠይቋል።

ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ የትግራይ ክልል ክለቦች ከሁለት ዓመት በላይ በውድድር ላይ ያልተሳተፉ በመሆኑ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መተዳደርያ ደንብ መሠረት ሙሉ ለሙሉ ከውድድር ከመሰረዝ ይልቅ አንድ ደረጃ ዝቅ ብለው ውድድር እንዲጀምሩ ከዚህ ቀደም አስተላልፎት የነበረውን ውሳኔ ሙሉ ለሙሉ በመሻር የትግራይ ክልል ክለቦች ከጦርነቱ በፊት ሲወዳደሩበት ወደነበረው ሊግ ከ2017 ጀምሮ ተመልሰው እንዲወዳደሩ ከመንግሥት የቀረበውን አቅጣጫ በመቀበል ውሳኔ አሳልፏል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ለሚመለከታቸው አካላት በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን ለኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አ/ማ በተላከው ደብዳቤም ሊጉ በ2017 የወድድር ዘመን በ19 ቡድኖች መካከል ተደርጎ 5 ቡድኖች ወደ ከፍተኛ ሊግ እንዲወርዱ በማድረግ በ2018 ከዚህ ቀደም ወደነበነረበት 16 ክለቦች እንዲመለስ አቅጣጫ ተቀምጧል። የከፍተኛ ሊግ እና አንደኛ ሊግ ውድድሮች በተመሳሳይ ተግባራዊ እንዲደረጉ አቅጣጫ ተሰጥቷል።[EFF]

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
የጁድ ቤሊንግሃም ያለፉት 4 የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ሬቲንግ!

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
ቪኒ ጁኒየር በአሊያንዝ አሬና ሌላ ሪከርድ ተጋርቷል።

በአሊያንዝ አሬና ሪያል ማድሪድን ደጋግሞ ያስተናገደው ባየር ሙኒክ ለሎስ ማሪንጌዎቹ ደጋግሞ እጁን ሲሰጥ ተመልክተናል።

ሙኒክ ማድሪድን ባስተናገደባቸው የሜዳው ጨዋታዎች በክርስቲያኖ ሮናልዶ ሁለት ጊዜ ሁለት ሁለት ጎሎችን ያስተናገደ ሲሆን፡ ሰርጂዮ ራሞስም ሁለት ጎሎችን አስቆጥሮ መውጣቱን ታሪክ ይናገራል።

በትላንትናውም የአሊያንዝ ግጥሚያ ቪኒሲየስ ጁኒየር ሁለት ጎል በማስቆጠር ከቀደምት ሌጀንዶቹ ተርታ መቀመጥ ችሏል

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et
በዚ ሲዝን ፡-

ሃሪ ኬን - 43 ጎል አስቆጥሯል

ሶን ፣ ሪቻርሊሰን፣ ኩሉሴቭስኪ፣ ጆንሰን እና ማዲሰን ተደምሮ - 42 ጎል አስቆጥሯል

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et