Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
🔴 አዲስ ዝማሬ "የዋኅ መልአክ" ዘማሪ ዳዊት ክብሩ || | Yewah Melak l Z Dawit Kibru
የዋኅ መልአክ
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል
ታዳጊያችን ነህ ምክሩ ለልዑል
የአምላክ ኀይሉ መገለጫው ነህ
የእልፍ አእላፍ መላእክት መስፍናቸው ነህ
ለሠራዊተ ሰማይ መላእክት አለቃቸው
ለፍጥረቱ ለባሕር ለየብሱ አጽንዖታቸው
የዋኅ ርኅሩኅ መልአክ ኀዳጌ በቀል
በልመናው በጸሎቱ ያስምረናል ቅዱስ ሚካኤል ።
የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ቅዱስ ሚካኤል
ለሰው ልጆች የምታዝን ምታማልድ ከልዑል
እነሆ ሕይወታችንን…
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል
ታዳጊያችን ነህ ምክሩ ለልዑል
የአምላክ ኀይሉ መገለጫው ነህ
የእልፍ አእላፍ መላእክት መስፍናቸው ነህ
ለሠራዊተ ሰማይ መላእክት አለቃቸው
ለፍጥረቱ ለባሕር ለየብሱ አጽንዖታቸው
የዋኅ ርኅሩኅ መልአክ ኀዳጌ በቀል
በልመናው በጸሎቱ ያስምረናል ቅዱስ ሚካኤል ።
የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ቅዱስ ሚካኤል
ለሰው ልጆች የምታዝን ምታማልድ ከልዑል
እነሆ ሕይወታችንን…
ግጥምጥሞሽ ወይስ #እግዚአብሔር_መንፈስ_ቅዱስ?
የአንድ ሰካራም መዝሙር
" #የሰዎች ነገር #አይተኛም "
_____
ቀኑ ብሩሃማ ነው ሰሞነ ሕማማት ከገባ ሦስተኛ ቀን ሆኖታል የቀለም ቆጠራ አለ ስለተባለ እንደ ሳምንቱ ወሳኝ ኩነቶቼ ሁሉ ወደ ቀለም ትምህርት ቤት እየገሰገስኩ ነው። አንድ እብድ መሳይ የኔ ቢጤ የፕሮቲስታንት ሰባኪ በሚመስል ሁናቴ ቀኝ እጁን ወደ ላይ ከፍ አድርጎ አንድ በስፋት የሚታወቅ የይልማ ኃይሉን መዝሙር እየቀለጸ በእኔ ተቃራኒ አቅጣጫ ሲመጣ አየሁት ። መዝሙሩና የመዝሙሩ ዜማ :- "የሚጠብቀኝ አይተኛም አያንቀላፋም" የሚል መሆኑን እርግጠኛ ነኝ ግን ሰውየው የመጀመሪያውን የስንኝ አንጓ በራሱ ሆድ ብሶት ቀይሮ እየዘመረው ነበር። እንዲህ በማለት "የሰዎች ነገር አይተኛም (2)× አያንቀላፋም " ........
........ወዲያውኑ መገረም ያዘኝ ። እውነቱን እኮ ነው ጎበዝ ".......የሰዎች ነገር አይተኛም !" የሚጠብቀን ራሱ የማይተኛው የሰዎች ነገር ስለማይተኛ ይመስለኛል። ምናልባት ትክክለኛው ዘማሪ የዚህን የኔ ቢጤ አዘማመር ቢሰማ ኖሮ የሰዎች ነገር አይተኛም በሚለው ቀይሮ በዘመረው ነበር።
ዓለም ብቻ ሳትሆን የሰዎች ነገርም ብዙዎችን ወግታ ጥላለች። ለነገሩ ዓለም የሚለው በዋናነት የሰው ልጆችን አይደለምን? ነው እንጂ። #ምሳ 7÷26
ግን ግን ይህን ሰካራም እንዲህ ብሎ እስኪዘምር ድረስ የወጋው እና #ጽኑ_ሕማማም የሆነበት የሰው ነገር ምን ይሆን ? በእርግጥስ ያሰከረው ጌሾና ብቅል ነውን ወይስ ነገረ ሰብ ???
ስትወፍር ዘረጦ ፣ ስትከሳ ሜንጦ ፣ ብትረዝም ብቅል አውራጅ ፣ ብታጥርም ጉቶ ፣ ስታገኝ ሰላቢ ፣ ስታጣም ችጋራም ፣ ብታነብ ደብተራ ፤ ብትጽፍ መተታም ስትተወው ደንቆሮ ፣ ስትናገር ተናጋሪ ፣ ዝም ብትል ዝጋታም እያሉ የሚወጉ የሕማማት ሁሉ ምንጭ አንደበተ ሕማማት መጨረሻቸው ምን ይሆን ።
ንጹሐ ባህሪ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳ በመዋለ ስብከቱ ሳለ ይህ የሰዎች የነገር ውጋት አግኝታዋለች ፤ እርሱ ግን "ማይመረ ኩሉ " ሁሉን የሚያውቅ እውነተኛ አምላክ ነውና " ዮሐንስ ሳይበላና ሳይጠጣ መጣ፥ እናንተ ግን፦ ጋኔን አለበት አላችሁት። እነሆ የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጣ፥ እናንተም፦ በላተኛና የወይን ጠጅ ጠጭ፥ የቀራጮችና የኃጢአተኞች ወዳጅ አላችሁት። " ብሎ አምርሮ ወቅሷቸል። #ማቴ 11÷18-19 ክርስቶስ እንኳ በሰው አፍ ያለ በደሉ ሲነቀፍ አስተዋልክን ? ብትበላም ባትበላም ትወቀሳለህ ብታውቅም ባታውቅም ትወረፋለህ ቅንም ቅንቅንም ብትሆን ትተቻለህ
እና ወዳጄ ምን አሰብክ ? የሰውን የነገር አፍ ፈርተህ መቆምን መረጥክን? ከቆንጆ ሕልምህስ መንቃት ፈለክን?? አትሞኝ ሕልምን ብታቆምም መንገድህንም ብትገታ ከሰው አፍ አትወጣም ምክንያቱም " #የሰዎች ነገር #አይተኛም አያንቀላፋምም " ሊሰራ ተነስቶ ነበር አቅቶት ተወው ሕልመኛ መስሎን ነበር ለካ እየቃዠ ነበር ይሉሃል። #ሉቃ 14÷30
እንደ ጋሪ ፈረስ ለጥቃቅን የጎንዮሽ ዕይታ ትኩረት ነፍገህ ወደፊት ወዳለችሁ የጽድቅ መንገድ በፈጣሪህ ሕግና ትዕዛዝ መሠረት ያለ መታከት ገስግስ። ውሾች ይጩሁ ግመሎችም ይሂዱ !
ለዚያም ሰካር ዘማሪ #እግዚአብሔር_አምላክ ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን ከሰው የአፍ ፍላጻም በጽኑ ይፈውስልን አሜን!
......" የ ሰዎች ነገር አይተኛም (2) × አያንቀላፋም ".........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሚያ03/2015 ዓ.ም
የአንድ ሰካራም መዝሙር
" #የሰዎች ነገር #አይተኛም "
_____
ቀኑ ብሩሃማ ነው ሰሞነ ሕማማት ከገባ ሦስተኛ ቀን ሆኖታል የቀለም ቆጠራ አለ ስለተባለ እንደ ሳምንቱ ወሳኝ ኩነቶቼ ሁሉ ወደ ቀለም ትምህርት ቤት እየገሰገስኩ ነው። አንድ እብድ መሳይ የኔ ቢጤ የፕሮቲስታንት ሰባኪ በሚመስል ሁናቴ ቀኝ እጁን ወደ ላይ ከፍ አድርጎ አንድ በስፋት የሚታወቅ የይልማ ኃይሉን መዝሙር እየቀለጸ በእኔ ተቃራኒ አቅጣጫ ሲመጣ አየሁት ። መዝሙሩና የመዝሙሩ ዜማ :- "የሚጠብቀኝ አይተኛም አያንቀላፋም" የሚል መሆኑን እርግጠኛ ነኝ ግን ሰውየው የመጀመሪያውን የስንኝ አንጓ በራሱ ሆድ ብሶት ቀይሮ እየዘመረው ነበር። እንዲህ በማለት "የሰዎች ነገር አይተኛም (2)× አያንቀላፋም " ........
........ወዲያውኑ መገረም ያዘኝ ። እውነቱን እኮ ነው ጎበዝ ".......የሰዎች ነገር አይተኛም !" የሚጠብቀን ራሱ የማይተኛው የሰዎች ነገር ስለማይተኛ ይመስለኛል። ምናልባት ትክክለኛው ዘማሪ የዚህን የኔ ቢጤ አዘማመር ቢሰማ ኖሮ የሰዎች ነገር አይተኛም በሚለው ቀይሮ በዘመረው ነበር።
ዓለም ብቻ ሳትሆን የሰዎች ነገርም ብዙዎችን ወግታ ጥላለች። ለነገሩ ዓለም የሚለው በዋናነት የሰው ልጆችን አይደለምን? ነው እንጂ። #ምሳ 7÷26
ግን ግን ይህን ሰካራም እንዲህ ብሎ እስኪዘምር ድረስ የወጋው እና #ጽኑ_ሕማማም የሆነበት የሰው ነገር ምን ይሆን ? በእርግጥስ ያሰከረው ጌሾና ብቅል ነውን ወይስ ነገረ ሰብ ???
ስትወፍር ዘረጦ ፣ ስትከሳ ሜንጦ ፣ ብትረዝም ብቅል አውራጅ ፣ ብታጥርም ጉቶ ፣ ስታገኝ ሰላቢ ፣ ስታጣም ችጋራም ፣ ብታነብ ደብተራ ፤ ብትጽፍ መተታም ስትተወው ደንቆሮ ፣ ስትናገር ተናጋሪ ፣ ዝም ብትል ዝጋታም እያሉ የሚወጉ የሕማማት ሁሉ ምንጭ አንደበተ ሕማማት መጨረሻቸው ምን ይሆን ።
ንጹሐ ባህሪ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳ በመዋለ ስብከቱ ሳለ ይህ የሰዎች የነገር ውጋት አግኝታዋለች ፤ እርሱ ግን "ማይመረ ኩሉ " ሁሉን የሚያውቅ እውነተኛ አምላክ ነውና " ዮሐንስ ሳይበላና ሳይጠጣ መጣ፥ እናንተ ግን፦ ጋኔን አለበት አላችሁት። እነሆ የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጣ፥ እናንተም፦ በላተኛና የወይን ጠጅ ጠጭ፥ የቀራጮችና የኃጢአተኞች ወዳጅ አላችሁት። " ብሎ አምርሮ ወቅሷቸል። #ማቴ 11÷18-19 ክርስቶስ እንኳ በሰው አፍ ያለ በደሉ ሲነቀፍ አስተዋልክን ? ብትበላም ባትበላም ትወቀሳለህ ብታውቅም ባታውቅም ትወረፋለህ ቅንም ቅንቅንም ብትሆን ትተቻለህ
እና ወዳጄ ምን አሰብክ ? የሰውን የነገር አፍ ፈርተህ መቆምን መረጥክን? ከቆንጆ ሕልምህስ መንቃት ፈለክን?? አትሞኝ ሕልምን ብታቆምም መንገድህንም ብትገታ ከሰው አፍ አትወጣም ምክንያቱም " #የሰዎች ነገር #አይተኛም አያንቀላፋምም " ሊሰራ ተነስቶ ነበር አቅቶት ተወው ሕልመኛ መስሎን ነበር ለካ እየቃዠ ነበር ይሉሃል። #ሉቃ 14÷30
እንደ ጋሪ ፈረስ ለጥቃቅን የጎንዮሽ ዕይታ ትኩረት ነፍገህ ወደፊት ወዳለችሁ የጽድቅ መንገድ በፈጣሪህ ሕግና ትዕዛዝ መሠረት ያለ መታከት ገስግስ። ውሾች ይጩሁ ግመሎችም ይሂዱ !
ለዚያም ሰካር ዘማሪ #እግዚአብሔር_አምላክ ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን ከሰው የአፍ ፍላጻም በጽኑ ይፈውስልን አሜን!
......" የ ሰዎች ነገር አይተኛም (2) × አያንቀላፋም ".........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሚያ03/2015 ዓ.ም
የ13 ወራትና የ13 ሙሉ ጨረቃዎች ጸጋ ባለቤቶች
☄️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ቀመር 13 መቼም አስገራሚ ናት፤ ብዙዎች ስለዚኽ ቊጥር ሲሰሙ ይሸበራሉ፡፡ በተለይ በምዕራቡ ዓለም ቊጥር 13 በእጅጉ ይፈራል፡፡ triskaidekaphobia (ትሪስ ካይ ዴካ ፎቢያ) ይባላል፡፡ ከተመዘገቡት የፍርሃት ዓይነቶች አንዱ ይኽ ነው፡፡
☄️ በግሪክ ቋንቋ τρεισκαίδεκα “ትሪስ” ማለት “3” “ካይ” ማለት “እና” “ዴካ” (ዐሥር) “ፎቢያ” (ፍርሃት) በአጠቃላይ የ13 ቊጥር ፍርሃት ማለት ነው፡፡
በተለይ ዐርብ እና 13 ሲገጥሙ ፍርሃቱ የሚጨምር ሲኾን የፍርሃቱ መጠሪያውም paraskevidekatriaphobia ይባላል፡፡
☄️ በምዕራቡ ዓለማት ያሉት ሀገራት እጅግ ብዙዎቹ 13ኛ ፎቅ የላቸውም፡፡ በሊፍት ሲወጣ 13ኛ ቊጥርን በመዝለል 14 ቊጥር ሲል ማየት የተለመደ ነው፡፡
☄️ ሪልስቴቶች 13ኛ ፎቅ ገዢ ስለሌላቸው 12 ኤ፤ 12 ኤም … እያሉ መሸጥ የተለመደ ነው፡፡
💥 ታላላቆች አየር መንገዶች ለምሳሌ እንደ ዩናይትድ፣ አላስካ፣ ራያኔር፣ ሉፍታንዛ፣ ፓሲፊክ፣ ሲንጋፓር ያሉ 13ኛ መቀመጫ በመዝለል 12 ብለው 14 እንደሚሉ በነዚኽ አየር መንገዶች የሚበሩ መንገደኞች ኹሉ ያውቁታል፡፡
💥 13 ቊጥር ግን ማያውያንን ጨምሮ በጥንት ሥልጡን ሕዝቦች ግን ተወዳጅ ቀመር ናት፡፡ ለምሳሌ በእስራኤል ቀመረ ፊደለ ዕብራይስጥ ፍቅር ማለት “አሀባህ” (אהבה) ሲባል በ22ቱ አሌፋት ሲቀመር (1 + 5 + 2 + 5 = 13) ይሰጣል፡፡ ☄️ በእኛም በግእዝ አልፍ ቤት ቀመረ ግእዝ “ጥበብ፣ ኤል” ይኽንኑ ቀመር ይሰጣሉ፡፡
🌓 ሴቶች በዓመት ውስጥ የሚያዩት የወርኅ አበባ የጨረቃን ዑደት ማእከል ያደረገ በመኾኑ 13 ነው - 28 ቀናት (365/28 = 13) ነው።
☄️ በግእዝ ወር የሚለው ቃል “ወርኅ” (ጨረቃ) ከሚለው ቃል የመጣ ነው፡፡ በእንግሊዝኛም menstruation መባሉ በላቲኒ ሜኔ - ሙን “ጨረቃ” ማለት ነውና ይኽነን ዑደት ማእከል ያደረገ ነው፡፡
☄️ በአፍሮ አይገባ መስቀል ላይ እንደምናየው ከጐን 6 ከጐን 6 ከላይ 1 በድምሩ 13 በማሳየት 12ቱ ሐዋርያትን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በመወከል፤ 13ቱን ሕማማተ መስቀል በማሳየት አስደናቂ ምሳሌን ያስነብባል፡፡
☄️ የ2017 ዓ.ም. ደግሞ በእጅጉ ልዩ የሚያደርገው ከታላቅነቷ የተነሣ ብዙ ፈተና የተነሣባት 13ኛዋ ወር ጳጒሜን 13ኛው ሙሉ ጨረቃ በዚኽች በ13ኛ ወር ላይ ማረፉ ነው፡፡
🌓 ይኸውም የ2017 ዓ.ም. የተከሰቱ 13ቱ ሙሉ ጨረቃዎች እነሆ፡-
1ኛ) መስከረም 8 🌞
2ኛ) ጥቅምት 7 🌚
3ኛ) ኅዳር 7 🌞
4ኛ) ታኅሣሥ 6 🌚
5ኛ) ጥር 5 🌞
6ኛ) የካቲት 5 🌚
7ኛ) መጋቢት 5 🌞
8ኛ ሚያዝያ 5 🌑
9ኛ) ግንቦት 4 🌞
10ኛ) ሠኔ 4 🌑
11ኛ) ሐምሌ 3 🌞
12ኛ) ነሐሴ 3 🌑
13ኛ) ጳጉሜን 2 🌓☄️☄️☄️☄️
☄️ በመፈጸም የጨረቃ መጨለም (ግርዶሽ) በምልአተ ወርኅ (በሙሉ ጨረቃ) ጊዜ ብቻ ነውና የሚኾነው ጳጕሜን 2 ተጠባቂዋ የሙሉ ጨለማ ግርዶሽን ቢሊየኖች ያዩታል፡፡ ከምሽቱ 2፡30 ጀምሮ (82 ደቂቃዎች (1 ሰዓት ከ22 ደቂቃዎች) ሙሉ ግርዶሽ የደም ጨረቃ በርኅወተ ሰማይ ምሽት እንደነቅባታለን፡፡
☄️ በነገው የጳጉሜን 2 ምሽት ሰብሰብ ብላችኊ ይኽነን የተፈጥሮ ክስተት በማድነቅ ፎቶዎች እያነሣችኊ ለዐዲሱ ዓመት በጎ እየተመኛችኊ እንድትደሰቱበት መልእክቴን በመግለጽ የተባረከ ምሽት ለኹላችኹም እመኛለኍ፡፡
☄️ 13 ወር የፀሓይ ጸጋ ተብላ ብትደነቀው ውቧ ሀገራችንም በዚኽ ዓመት 13ኛ ሙሉ ጨረቃ በ13ኛዋ የጳጒሜን ወር ላይ በመግጠም 13 ወር የጨረቃ ጸጋ እንድንላት አስችሎናል፡፡
ጳጒሜን 2 የዓመቷን ሙሉ ጨረቃ ከግርሽዋ ጋር ካየን በኋላ የ2018 ዓ.ም. የዐዲሱ ዓመት ሙሉ የመስከረም ሙሉ ጨረቃ ማግሰኞ መስከረም 27 ደምቃ በምሥራቅ አድማስ ትወጣለችና ለዐዲሱ ዓመት የመስከረም 27 ሙሉ ጨረቃ በሰላም ደምቀን ያገናኘን፡፡
🌓 የነገው ሰዓት ለማወቅ
🌓 ከምሽቱ 12:21 ላይ 13ኛዋ ሙሉ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ ደምቃ ትወጣለች
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትጀምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ጀምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
☄️ ኹሉ ተጠናቆ 5:55 ላይ ጨረቃ ወደ ድምቀቷ ትመለሳለች።
https://youtu.be/RZlhgpKNeqM?si=Y2IlMGQjnQZFTQCd
💥 አልፋ እግዚአብሔር ሆይ ቀጣዩ ዘመናችን ኹሉ አንተን በመውደድ፤ ሰውን ኹሉ በእውነት በመውደድ፤ ከአንተ የሚገኘው ሰላም በረከት ጸጋ ኹሉ በቅናት ሳይኾን በቅንነት ነውና ሥጋዊ ቅናትን ከልባችን አስወግደኽ፤ በጠብ ሳይኾን በአንተ ጥበብ፤ በምስጋና በምድራዊ ሰማያዊ በረከቶችኽ እየተደሰትን እንድንጓዝ ፈቃድኽ ይኹንልን። መልካም የጳጉሜን ወር።
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
☄️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ቀመር 13 መቼም አስገራሚ ናት፤ ብዙዎች ስለዚኽ ቊጥር ሲሰሙ ይሸበራሉ፡፡ በተለይ በምዕራቡ ዓለም ቊጥር 13 በእጅጉ ይፈራል፡፡ triskaidekaphobia (ትሪስ ካይ ዴካ ፎቢያ) ይባላል፡፡ ከተመዘገቡት የፍርሃት ዓይነቶች አንዱ ይኽ ነው፡፡
☄️ በግሪክ ቋንቋ τρεισκαίδεκα “ትሪስ” ማለት “3” “ካይ” ማለት “እና” “ዴካ” (ዐሥር) “ፎቢያ” (ፍርሃት) በአጠቃላይ የ13 ቊጥር ፍርሃት ማለት ነው፡፡
በተለይ ዐርብ እና 13 ሲገጥሙ ፍርሃቱ የሚጨምር ሲኾን የፍርሃቱ መጠሪያውም paraskevidekatriaphobia ይባላል፡፡
☄️ በምዕራቡ ዓለማት ያሉት ሀገራት እጅግ ብዙዎቹ 13ኛ ፎቅ የላቸውም፡፡ በሊፍት ሲወጣ 13ኛ ቊጥርን በመዝለል 14 ቊጥር ሲል ማየት የተለመደ ነው፡፡
☄️ ሪልስቴቶች 13ኛ ፎቅ ገዢ ስለሌላቸው 12 ኤ፤ 12 ኤም … እያሉ መሸጥ የተለመደ ነው፡፡
💥 ታላላቆች አየር መንገዶች ለምሳሌ እንደ ዩናይትድ፣ አላስካ፣ ራያኔር፣ ሉፍታንዛ፣ ፓሲፊክ፣ ሲንጋፓር ያሉ 13ኛ መቀመጫ በመዝለል 12 ብለው 14 እንደሚሉ በነዚኽ አየር መንገዶች የሚበሩ መንገደኞች ኹሉ ያውቁታል፡፡
💥 13 ቊጥር ግን ማያውያንን ጨምሮ በጥንት ሥልጡን ሕዝቦች ግን ተወዳጅ ቀመር ናት፡፡ ለምሳሌ በእስራኤል ቀመረ ፊደለ ዕብራይስጥ ፍቅር ማለት “አሀባህ” (אהבה) ሲባል በ22ቱ አሌፋት ሲቀመር (1 + 5 + 2 + 5 = 13) ይሰጣል፡፡ ☄️ በእኛም በግእዝ አልፍ ቤት ቀመረ ግእዝ “ጥበብ፣ ኤል” ይኽንኑ ቀመር ይሰጣሉ፡፡
🌓 ሴቶች በዓመት ውስጥ የሚያዩት የወርኅ አበባ የጨረቃን ዑደት ማእከል ያደረገ በመኾኑ 13 ነው - 28 ቀናት (365/28 = 13) ነው።
☄️ በግእዝ ወር የሚለው ቃል “ወርኅ” (ጨረቃ) ከሚለው ቃል የመጣ ነው፡፡ በእንግሊዝኛም menstruation መባሉ በላቲኒ ሜኔ - ሙን “ጨረቃ” ማለት ነውና ይኽነን ዑደት ማእከል ያደረገ ነው፡፡
☄️ በአፍሮ አይገባ መስቀል ላይ እንደምናየው ከጐን 6 ከጐን 6 ከላይ 1 በድምሩ 13 በማሳየት 12ቱ ሐዋርያትን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በመወከል፤ 13ቱን ሕማማተ መስቀል በማሳየት አስደናቂ ምሳሌን ያስነብባል፡፡
☄️ የ2017 ዓ.ም. ደግሞ በእጅጉ ልዩ የሚያደርገው ከታላቅነቷ የተነሣ ብዙ ፈተና የተነሣባት 13ኛዋ ወር ጳጒሜን 13ኛው ሙሉ ጨረቃ በዚኽች በ13ኛ ወር ላይ ማረፉ ነው፡፡
🌓 ይኸውም የ2017 ዓ.ም. የተከሰቱ 13ቱ ሙሉ ጨረቃዎች እነሆ፡-
1ኛ) መስከረም 8 🌞
2ኛ) ጥቅምት 7 🌚
3ኛ) ኅዳር 7 🌞
4ኛ) ታኅሣሥ 6 🌚
5ኛ) ጥር 5 🌞
6ኛ) የካቲት 5 🌚
7ኛ) መጋቢት 5 🌞
8ኛ ሚያዝያ 5 🌑
9ኛ) ግንቦት 4 🌞
10ኛ) ሠኔ 4 🌑
11ኛ) ሐምሌ 3 🌞
12ኛ) ነሐሴ 3 🌑
13ኛ) ጳጉሜን 2 🌓☄️☄️☄️☄️
☄️ በመፈጸም የጨረቃ መጨለም (ግርዶሽ) በምልአተ ወርኅ (በሙሉ ጨረቃ) ጊዜ ብቻ ነውና የሚኾነው ጳጕሜን 2 ተጠባቂዋ የሙሉ ጨለማ ግርዶሽን ቢሊየኖች ያዩታል፡፡ ከምሽቱ 2፡30 ጀምሮ (82 ደቂቃዎች (1 ሰዓት ከ22 ደቂቃዎች) ሙሉ ግርዶሽ የደም ጨረቃ በርኅወተ ሰማይ ምሽት እንደነቅባታለን፡፡
☄️ በነገው የጳጉሜን 2 ምሽት ሰብሰብ ብላችኊ ይኽነን የተፈጥሮ ክስተት በማድነቅ ፎቶዎች እያነሣችኊ ለዐዲሱ ዓመት በጎ እየተመኛችኊ እንድትደሰቱበት መልእክቴን በመግለጽ የተባረከ ምሽት ለኹላችኹም እመኛለኍ፡፡
☄️ 13 ወር የፀሓይ ጸጋ ተብላ ብትደነቀው ውቧ ሀገራችንም በዚኽ ዓመት 13ኛ ሙሉ ጨረቃ በ13ኛዋ የጳጒሜን ወር ላይ በመግጠም 13 ወር የጨረቃ ጸጋ እንድንላት አስችሎናል፡፡
ጳጒሜን 2 የዓመቷን ሙሉ ጨረቃ ከግርሽዋ ጋር ካየን በኋላ የ2018 ዓ.ም. የዐዲሱ ዓመት ሙሉ የመስከረም ሙሉ ጨረቃ ማግሰኞ መስከረም 27 ደምቃ በምሥራቅ አድማስ ትወጣለችና ለዐዲሱ ዓመት የመስከረም 27 ሙሉ ጨረቃ በሰላም ደምቀን ያገናኘን፡፡
🌓 የነገው ሰዓት ለማወቅ
🌓 ከምሽቱ 12:21 ላይ 13ኛዋ ሙሉ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ ደምቃ ትወጣለች
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትጀምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ጀምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
☄️ ኹሉ ተጠናቆ 5:55 ላይ ጨረቃ ወደ ድምቀቷ ትመለሳለች።
https://youtu.be/RZlhgpKNeqM?si=Y2IlMGQjnQZFTQCd
💥 አልፋ እግዚአብሔር ሆይ ቀጣዩ ዘመናችን ኹሉ አንተን በመውደድ፤ ሰውን ኹሉ በእውነት በመውደድ፤ ከአንተ የሚገኘው ሰላም በረከት ጸጋ ኹሉ በቅናት ሳይኾን በቅንነት ነውና ሥጋዊ ቅናትን ከልባችን አስወግደኽ፤ በጠብ ሳይኾን በአንተ ጥበብ፤ በምስጋና በምድራዊ ሰማያዊ በረከቶችኽ እየተደሰትን እንድንጓዝ ፈቃድኽ ይኹንልን። መልካም የጳጉሜን ወር።
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
YouTube
የደም ጨረቃ ምልክት ከዐባይ ወንዝ ጋር ክስተት ወይስ እውነት?
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
https://www.tiktok.com/@glamorous100x/video/7565944114953424142?_r=1&u_code=ebc91271aa1a21&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=eg83l996af4j1c&share_item_id=7565944114953424142&source=h5_m&utm_source=more&utm_campaign=client_share&share_link_id=ad5a3b35-ce82-4914-ba9a-a188c98c6da1&share_app_id=1340&ugbiz_name=Main&lang=en&user_id=7309378473382282245&sec_user_id=MS4wLjABAAAAwqLoBxIhfoMEw-X87nj9FvlWZGPmuMjcR2JfECaN14XKEwCdFXvsZ1_XCy8K30Kl This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
🔴 አዲስ ዝማሬ "የሮማን አበባ" ዘማሪ ተዋቸው ዘሪሁን Zemari Tewachew Zerihun 🔴New orthodox Mezmur @ተልሚድ ቲዩብ
የሮማን አበባ
መዓዛዋ ጣፋጭ የሮማን አበባ
ሽልማታችን ነች የመስቀል ሥር መባ
እንደ ቅ.ኤፍሬም በእጅሽ እንድባረክ
ሰአሊ ለነ ብዬ ከፊትሽ ልንበርከክ
የዓለም መመኪያ የክርስቲያን አክሊል
የሰላም ከተማ የአሮን ጸናጽል
አንቺ የወርቅ ጽዋ የተሞላሽ ምስጢር
የሕይወት ምንጭ ነሽ የሌለብሽ ነውር
ከቶ ወዴት ነበር የአዳም ተስፋው
…
መዓዛዋ ጣፋጭ የሮማን አበባ
ሽልማታችን ነች የመስቀል ሥር መባ
እንደ ቅ.ኤፍሬም በእጅሽ እንድባረክ
ሰአሊ ለነ ብዬ ከፊትሽ ልንበርከክ
የዓለም መመኪያ የክርስቲያን አክሊል
የሰላም ከተማ የአሮን ጸናጽል
አንቺ የወርቅ ጽዋ የተሞላሽ ምስጢር
የሕይወት ምንጭ ነሽ የሌለብሽ ነውር
ከቶ ወዴት ነበር የአዳም ተስፋው
…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
#ሁለተኛውን_ልደቱን_አስደናቂ_አደረገው!
📍እግዚአብሔር እልፍ ድንቅ ነገሮችን ትላንት አድርጓል፣ ዛሬም እያደረገ ነው ለወደፊትም ያደርጋል። ከድንቆች በላይ ግን ድንቅ ምንድነው ከተባለ ይህ ነው።
አምላክ ሰው የሆነበት፣ ሰውም አምላክን የሆነበት፣ ረቂቁ
ግዙፍ የሆነበት፣ ልዑሉ ትሑት የሆነበት ይህ ሁለተኛው ልደቱ
እጅግ ይደንቃል።
ታላቅነቱን በታናሽነት፣ ኃያልነቱን በደካማ ሥጋ ሰውሮ
መምጣቱ በጣሙን ይገርማል።
ሰማይና ምድር የማይችሉት አምላክ በማኅፀነ ማርያም መወሰኑ
እጅግ ያስደንቃል።
ሰማይ ዙፋኑ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆነችለት አምላክ የዕለት
ጽንስ ሆኖ በማኅፀነ ማርያም ማደሩ በጣሙን ያስደንቃል።
የአስራ አምስት ዓመት ብላቴና እንድትሸከመው መፍቀዱ እጅግ ያስደንቃል።
የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ተብሎ መጠራቱ እጅግ
ያስደንቃል።
እኛን ወደሰማይ ሊያወጣ እርሱ ወደመሬት መውረዱ በጣም
ያስደንቃል።
እኛን ከክብር ዙፋን ላይ ሊያስቀምጥ እርሱ በውርደት በረት
መጣሉ እጅጉን ያስደንቃል።
እኛ ከመላእክት ጋራ እንድንዘምር እርሱ ከእንስሳት ጋራ በበረት
ማደሩ ያስደንቃል።
ባለዙፋን ባለበረት ሲሆን ማየት እጅግ ያስደንቃል።
ኃያል አምላክ ሕጻን ሆኖ መወለዱ ያስደንቃል። (ኢሳይያስ ሕጻን ተወለደልን አለ ማቴዎስ ደግሞ የተወለደው ንጉሥ ነው ይለናል። ሰብአ ሰገል ለዚህ ዘውዳቸውን አንሥተው ለሕጻኑ ሰግደዋል። በሚታይ ዕድሜ ቢሆን ኖሮ አይታሰብም አይሞከርም ነበር።)
#በሚታይ ሕጻንነቱ ግን ዘለዓለማዊ አባትነት አለው፣
#በሚታይ ሕጻንነት ዘለዓለማዊ ንግሥና አለው፣
#በሚታይ ሕጻንነት ዘለዓለማዊ አምላክነት ስላለው ዘውዳቸውን አንሥተው ለሕጻኑ ሰገዱለት።
ኃያል አምላክ ሕጻን ሆኖ መወለዱ እጅግ ያስደንቃል።
የዘለዓለም አባት "አንድ" ተብሎ ዘመን ሲቆጠርለት አረ
በጣሙን ያስደንቃል።
ከአንዲት ታናሽ ብላቴና ምግብ ሲለምን ማየት በጣም
ያስደንቃል።
ከአንዲት ታናሽ ብላቴና ምግብን ፈልጎ ማልቀሱ እጅግ
ያስደንቃል። እግዚአብሔርም አለቀሰ ሲባል እጅግ ያስደንቃል።
የእርሱ ማልቀስ የእርሷ እሹሩሩ ብሎ ማባበል እጅግ በጣም
ያስደንቃል።
የእርሱ መወለድ የእርሷ መውለድ በጣም ያስደንቃል።
የእርሱ ትሕትና የእርሷ ልዕልና እጅግ ያስደንቃል።
የተናቀ ማንነታችንን ያከበረበት፣ ጎስቋላ ብህርያችን ገንዘብ ያደረገበት
ሁለተኛው ልደቱ እጅግ ያስደንቃል።
የተናቁ ነገሮችን የመረጠበት ይህ ሁለተኛው ልደቱ እጅግ
ያስደንቃል።
(ከአገር የተናቀች ቤተልሄምን፣ ከፆታ ሴትን! (በሥርዐታቸው ሴት
በዘር ቆጠራ እንኳ እንደማትካተት ልብ ይሏል) ፣ከቦታ
የተናቀውን በረትን፣ከሥራ የተናቀ እረኝነትን) የመረጠበት
ያከበረበት ይህ ሁለተኛው ልደቱ እጅጉን ያስደንቃል።
.
.
.
.
አባ ጊዮርጊስ "የመጀመሪያውን ልደቱን (ከአብ ያለ እናት) ረቂቅ አደረገው። ሁለተኛውን ልደቱን (ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት) አስደናቂ አደረገው።" ብሎ እንደተናገረ በእውነት ይህ ሁለተኛ ልደቱ እጅጉን ድንቅ ነው!!
ምድር እስከ ተዘረጋችበት ውኃም እስከፈሰሰበት ድረስ ያላችሁ በክርስቶስ ክርስቶሳውያን ሁሉ እንኳን ለልደቱ ለእግዚእነ አደረሳችሁ።
መልካም በዓል!!🤲🤲
©️ስምዐ_ጽድቅ_አርአያ
📍እግዚአብሔር እልፍ ድንቅ ነገሮችን ትላንት አድርጓል፣ ዛሬም እያደረገ ነው ለወደፊትም ያደርጋል። ከድንቆች በላይ ግን ድንቅ ምንድነው ከተባለ ይህ ነው።
አምላክ ሰው የሆነበት፣ ሰውም አምላክን የሆነበት፣ ረቂቁ
ግዙፍ የሆነበት፣ ልዑሉ ትሑት የሆነበት ይህ ሁለተኛው ልደቱ
እጅግ ይደንቃል።
ታላቅነቱን በታናሽነት፣ ኃያልነቱን በደካማ ሥጋ ሰውሮ
መምጣቱ በጣሙን ይገርማል።
ሰማይና ምድር የማይችሉት አምላክ በማኅፀነ ማርያም መወሰኑ
እጅግ ያስደንቃል።
ሰማይ ዙፋኑ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆነችለት አምላክ የዕለት
ጽንስ ሆኖ በማኅፀነ ማርያም ማደሩ በጣሙን ያስደንቃል።
የአስራ አምስት ዓመት ብላቴና እንድትሸከመው መፍቀዱ እጅግ ያስደንቃል።
የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ተብሎ መጠራቱ እጅግ
ያስደንቃል።
እኛን ወደሰማይ ሊያወጣ እርሱ ወደመሬት መውረዱ በጣም
ያስደንቃል።
እኛን ከክብር ዙፋን ላይ ሊያስቀምጥ እርሱ በውርደት በረት
መጣሉ እጅጉን ያስደንቃል።
እኛ ከመላእክት ጋራ እንድንዘምር እርሱ ከእንስሳት ጋራ በበረት
ማደሩ ያስደንቃል።
ባለዙፋን ባለበረት ሲሆን ማየት እጅግ ያስደንቃል።
ኃያል አምላክ ሕጻን ሆኖ መወለዱ ያስደንቃል። (ኢሳይያስ ሕጻን ተወለደልን አለ ማቴዎስ ደግሞ የተወለደው ንጉሥ ነው ይለናል። ሰብአ ሰገል ለዚህ ዘውዳቸውን አንሥተው ለሕጻኑ ሰግደዋል። በሚታይ ዕድሜ ቢሆን ኖሮ አይታሰብም አይሞከርም ነበር።)
#በሚታይ ሕጻንነቱ ግን ዘለዓለማዊ አባትነት አለው፣
#በሚታይ ሕጻንነት ዘለዓለማዊ ንግሥና አለው፣
#በሚታይ ሕጻንነት ዘለዓለማዊ አምላክነት ስላለው ዘውዳቸውን አንሥተው ለሕጻኑ ሰገዱለት።
ኃያል አምላክ ሕጻን ሆኖ መወለዱ እጅግ ያስደንቃል።
የዘለዓለም አባት "አንድ" ተብሎ ዘመን ሲቆጠርለት አረ
በጣሙን ያስደንቃል።
ከአንዲት ታናሽ ብላቴና ምግብ ሲለምን ማየት በጣም
ያስደንቃል።
ከአንዲት ታናሽ ብላቴና ምግብን ፈልጎ ማልቀሱ እጅግ
ያስደንቃል። እግዚአብሔርም አለቀሰ ሲባል እጅግ ያስደንቃል።
የእርሱ ማልቀስ የእርሷ እሹሩሩ ብሎ ማባበል እጅግ በጣም
ያስደንቃል።
የእርሱ መወለድ የእርሷ መውለድ በጣም ያስደንቃል።
የእርሱ ትሕትና የእርሷ ልዕልና እጅግ ያስደንቃል።
የተናቀ ማንነታችንን ያከበረበት፣ ጎስቋላ ብህርያችን ገንዘብ ያደረገበት
ሁለተኛው ልደቱ እጅግ ያስደንቃል።
የተናቁ ነገሮችን የመረጠበት ይህ ሁለተኛው ልደቱ እጅግ
ያስደንቃል።
(ከአገር የተናቀች ቤተልሄምን፣ ከፆታ ሴትን! (በሥርዐታቸው ሴት
በዘር ቆጠራ እንኳ እንደማትካተት ልብ ይሏል) ፣ከቦታ
የተናቀውን በረትን፣ከሥራ የተናቀ እረኝነትን) የመረጠበት
ያከበረበት ይህ ሁለተኛው ልደቱ እጅጉን ያስደንቃል።
.
.
.
.
አባ ጊዮርጊስ "የመጀመሪያውን ልደቱን (ከአብ ያለ እናት) ረቂቅ አደረገው። ሁለተኛውን ልደቱን (ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት) አስደናቂ አደረገው።" ብሎ እንደተናገረ በእውነት ይህ ሁለተኛ ልደቱ እጅጉን ድንቅ ነው!!
ምድር እስከ ተዘረጋችበት ውኃም እስከፈሰሰበት ድረስ ያላችሁ በክርስቶስ ክርስቶሳውያን ሁሉ እንኳን ለልደቱ ለእግዚእነ አደረሳችሁ።
መልካም በዓል!!🤲🤲
©️ስምዐ_ጽድቅ_አርአያ
#አንዳንድ ልጆች ከወላጆቻቸው የሚበልጡበት ጊዜ አለ አንዳንድ ወላጆች ደግሞ በነገሮች ዕይታ ከልጆቻቸው የሚያንሱበትም ጊዜ አለ ። እናታችን ቅድስት ኢየሉጣ ይህን በመገንዘቧ ነበር ልጇን ሕፃኑ ቂርቆስን ስለ መልካም ምክሩ ልጇ ሆኖ ሳለ አባቴ ብላ ለመጥራት የተገደደችሁ ።
በእርግጥም የሥጋ ሞት እጅግ መራራና አስፈሪ ነው ። መድኅን ዓለም ክርስቶስ እንኳን ወዶ ፣ፈቅዶ የሞታችንን ጽዋ ሊጠጣልን ለካሳ፣ ለቤዛ መጥቶ ሳለ ጊዜው ደርሶ በአሙስ ምሽት የአይሁድ ወታደሮች ሊይዙት ሲመጡ ግን በአትክልት ቦታ በጌቴ ሰማኔ ሆኖ "አባት ሆይ ብትወድስ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ " ሲል ጸሎትን አድርጓል። #ማቴ 26÷39
#ይህም የሚያሳየን በመከራችን ጊዜ ወደ ሰማይ አባታችን መጸለይ እንደሚገባን ብቻ ሳይሆን የሥጋ ሞት ምነኛ አሰቃቂ ና አስፈሪ እንደሆነ ጭምር የሚያሳይ ነው ። ስለሆነም የቅድስት እየሉጣ ፍርሃት አያስደንቅም የሚያስደንቀውስ የልጇ እሳት መድፈር ነው ። “ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።” #ሉቃስ 10፥21
በቤተክርስቲያናችን ታሪክ ገና በአፍላ ዕድሜያቸው በበሳልነታቸውና በአስተሳሰብ አድማሳቸው የተነሳ አረጋዊ ወይም ሽማግሌ ተብለው የተጠሩ ቅዱሳን አሉ ለምሳሌ ወደ ሀገራችን ከመጡ ከዘጠኑ ቅዱሳን መካከል ሮማዊው ኮከብ ዘሚካኤል(አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ማንሳት ይቻላል:: ዘሚካኤል አረጋዊ የሚል ስያሜን ያገኙት ገና አስራ አምስት ዓመት እንኳን ሳይሞላቸው ነበር።
#ቅዱስ_ወንጌል ከአንዱ ከተማ ቢያሳድዷችሁ ወደ ሌላይቱ ከተማ ሽሹ እንዳለ ከሮም መኮንን ሸሽታ ወደ ሌላ ሀገር ልጇን ይዛ ብትሄድ ያን የሸሸችሁ ክፉ መኮንን በዚህም ሀገር አገኛት የምታመልከውን አምላክ ክዳ የእርሱን ጣዖት እድታመልክም ጠየቃት ቅድስት ኢየሉጣ ግን ከእግዚአብሔር በቀር ሌሎች አማልክትን ማምለክ የሚገባ ወይም የማይገባ መሆኑን ይህን የሦስት ዓመት ልጄን ጠይቀው እርሱ ይንገርህ አለችሁ
መኮንኑም ቅዱስ ቂርቆስን በተመለከተው ጊዜ ፊቱ ብሩህና ደስተኛ ሕፃን እንደሆነ አስተዋለ ቀርቦም አንተ ደስተኛ ሕፃን እንዴት ነህ ሲል የማግባባት ሰላምታን አቀረበለት ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን አዎን የኔ ደስታ ተጠብቆልኛል አንተ ግን ከዚህ እኩይ ሥራህ ካልተመለስ ልቅሶና ጥርስ ማፏጨት ጥልቅ ሐዘንም ይቆይሃል መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላና ደስታ የላቸውም ይላልና አለው።“ለክፉዎች ሰላም የላቸውም ይላል አምላኬ።” #ኢሳ 57፥21
#መኳንንቱንና ጣዖታቱንም ሁሉ እረገማቸው ከኃይሉም ጽናት የተነሳ ሁሉ አደነቁ እግዚአብሔር ንግግርንና ኃይልን ሰጥቶታልና "ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ተብሎ እንደተጻፈ #ማቴ 10÷18-20
መኮንኑም የሕፃኑን ንግግር በሰማ ጊዜ አፈረ ታላቅ የውኃ ጋን አዘጋጅታችሁ ውኃው እስከሚፍለቀለቅ በእሳት ላይ ጣዱት ውኃውም ሲፈላ ሕፃኑንና እናቱን በዚያ ጨምሯቸው ብሎ አዘዘ ።
#ጭፍሮችም እንደተባሉት አደረጉ የውኃው ፍላትም ድምጹ እንደ ክረምት ጊዜ ነጎድጓድ የሚያስፈራና የሚያስገመግም ሆነ ይህ ጊዜ የሕፃኑ እናት ቅድስት ኢየሉጣ ፈራች ሃይማኖቷም ከልቧ ተሸረሸረ ልጄ ሆይ ይህ ነገር ይቅርብን ንጉሥ ያለንን እንፈጽም አለችው።
ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ወደ ሰማይ አንጋጦ መላእክትን በጽረ አርያም ፣ ሐዋርያትን በስብከተ ዓለም ፣ ጻድቃንን በገዳም፣ ሰማዕታትን በደም ያጸናህ እናቴንም በሃይማኖት አጽናት ሲል ስለ እናቱ የእምነት መጉደል ወደ ፈጣሪው ጸለየ።
#እግዚአብሔርም የእናቱን ዐይነ ልቡና ገልጦ ለቅዱሳን ሰማዕታቱ ያዘጋጀውን የጽድቅ አክሊልን አሳያት ያን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ በመንፈስ ተጽናናች ፣ በሃይማኖት ጸናች ንጉሡንና ጣዖታቱን ናቀች ልጇ ቂርቆስንም " #ልጄ_ስትሆን_አባት_ሆንክኝ " አለችሁ ተያይዘውም በእሳት ወደ ተፍለቀለቀው የውኃ ጋን ውስጥ ገቡ
#ከእግዚአብሔር_የተላከ_የመላእክት_አለቃ_ቅዱስ ገብርኤልም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ #በጌታችን_በመድኃኒታችን_በኢየሱስ_ክርስቶስ_መስቀል ያን ፍል ውኃ እንደ ክረምት ጊዜ ውርጭ አቀዘቀዘው። ሕፃኑና እናቱም ያለ ምንም ጉዳት ከጋኑ ወጡ። " #የእግዚአብሔር_መላእክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል " እንዲል #መዝ 33÷7
.......... #ይቆየን............
#የእግዚአብሔር ቸርነት የመላእኩ ጠባቂየት የቅዱሳኑ የእናትና ልጅ በረከታቸው አይለየን !
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፲ ፰/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
በእርግጥም የሥጋ ሞት እጅግ መራራና አስፈሪ ነው ። መድኅን ዓለም ክርስቶስ እንኳን ወዶ ፣ፈቅዶ የሞታችንን ጽዋ ሊጠጣልን ለካሳ፣ ለቤዛ መጥቶ ሳለ ጊዜው ደርሶ በአሙስ ምሽት የአይሁድ ወታደሮች ሊይዙት ሲመጡ ግን በአትክልት ቦታ በጌቴ ሰማኔ ሆኖ "አባት ሆይ ብትወድስ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ " ሲል ጸሎትን አድርጓል። #ማቴ 26÷39
#ይህም የሚያሳየን በመከራችን ጊዜ ወደ ሰማይ አባታችን መጸለይ እንደሚገባን ብቻ ሳይሆን የሥጋ ሞት ምነኛ አሰቃቂ ና አስፈሪ እንደሆነ ጭምር የሚያሳይ ነው ። ስለሆነም የቅድስት እየሉጣ ፍርሃት አያስደንቅም የሚያስደንቀውስ የልጇ እሳት መድፈር ነው ። “ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።” #ሉቃስ 10፥21
በቤተክርስቲያናችን ታሪክ ገና በአፍላ ዕድሜያቸው በበሳልነታቸውና በአስተሳሰብ አድማሳቸው የተነሳ አረጋዊ ወይም ሽማግሌ ተብለው የተጠሩ ቅዱሳን አሉ ለምሳሌ ወደ ሀገራችን ከመጡ ከዘጠኑ ቅዱሳን መካከል ሮማዊው ኮከብ ዘሚካኤል(አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ማንሳት ይቻላል:: ዘሚካኤል አረጋዊ የሚል ስያሜን ያገኙት ገና አስራ አምስት ዓመት እንኳን ሳይሞላቸው ነበር።
#ቅዱስ_ወንጌል ከአንዱ ከተማ ቢያሳድዷችሁ ወደ ሌላይቱ ከተማ ሽሹ እንዳለ ከሮም መኮንን ሸሽታ ወደ ሌላ ሀገር ልጇን ይዛ ብትሄድ ያን የሸሸችሁ ክፉ መኮንን በዚህም ሀገር አገኛት የምታመልከውን አምላክ ክዳ የእርሱን ጣዖት እድታመልክም ጠየቃት ቅድስት ኢየሉጣ ግን ከእግዚአብሔር በቀር ሌሎች አማልክትን ማምለክ የሚገባ ወይም የማይገባ መሆኑን ይህን የሦስት ዓመት ልጄን ጠይቀው እርሱ ይንገርህ አለችሁ
መኮንኑም ቅዱስ ቂርቆስን በተመለከተው ጊዜ ፊቱ ብሩህና ደስተኛ ሕፃን እንደሆነ አስተዋለ ቀርቦም አንተ ደስተኛ ሕፃን እንዴት ነህ ሲል የማግባባት ሰላምታን አቀረበለት ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን አዎን የኔ ደስታ ተጠብቆልኛል አንተ ግን ከዚህ እኩይ ሥራህ ካልተመለስ ልቅሶና ጥርስ ማፏጨት ጥልቅ ሐዘንም ይቆይሃል መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላና ደስታ የላቸውም ይላልና አለው።“ለክፉዎች ሰላም የላቸውም ይላል አምላኬ።” #ኢሳ 57፥21
#መኳንንቱንና ጣዖታቱንም ሁሉ እረገማቸው ከኃይሉም ጽናት የተነሳ ሁሉ አደነቁ እግዚአብሔር ንግግርንና ኃይልን ሰጥቶታልና "ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ተብሎ እንደተጻፈ #ማቴ 10÷18-20
መኮንኑም የሕፃኑን ንግግር በሰማ ጊዜ አፈረ ታላቅ የውኃ ጋን አዘጋጅታችሁ ውኃው እስከሚፍለቀለቅ በእሳት ላይ ጣዱት ውኃውም ሲፈላ ሕፃኑንና እናቱን በዚያ ጨምሯቸው ብሎ አዘዘ ።
#ጭፍሮችም እንደተባሉት አደረጉ የውኃው ፍላትም ድምጹ እንደ ክረምት ጊዜ ነጎድጓድ የሚያስፈራና የሚያስገመግም ሆነ ይህ ጊዜ የሕፃኑ እናት ቅድስት ኢየሉጣ ፈራች ሃይማኖቷም ከልቧ ተሸረሸረ ልጄ ሆይ ይህ ነገር ይቅርብን ንጉሥ ያለንን እንፈጽም አለችው።
ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ወደ ሰማይ አንጋጦ መላእክትን በጽረ አርያም ፣ ሐዋርያትን በስብከተ ዓለም ፣ ጻድቃንን በገዳም፣ ሰማዕታትን በደም ያጸናህ እናቴንም በሃይማኖት አጽናት ሲል ስለ እናቱ የእምነት መጉደል ወደ ፈጣሪው ጸለየ።
#እግዚአብሔርም የእናቱን ዐይነ ልቡና ገልጦ ለቅዱሳን ሰማዕታቱ ያዘጋጀውን የጽድቅ አክሊልን አሳያት ያን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ በመንፈስ ተጽናናች ፣ በሃይማኖት ጸናች ንጉሡንና ጣዖታቱን ናቀች ልጇ ቂርቆስንም " #ልጄ_ስትሆን_አባት_ሆንክኝ " አለችሁ ተያይዘውም በእሳት ወደ ተፍለቀለቀው የውኃ ጋን ውስጥ ገቡ
#ከእግዚአብሔር_የተላከ_የመላእክት_አለቃ_ቅዱስ ገብርኤልም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ #በጌታችን_በመድኃኒታችን_በኢየሱስ_ክርስቶስ_መስቀል ያን ፍል ውኃ እንደ ክረምት ጊዜ ውርጭ አቀዘቀዘው። ሕፃኑና እናቱም ያለ ምንም ጉዳት ከጋኑ ወጡ። " #የእግዚአብሔር_መላእክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል " እንዲል #መዝ 33÷7
.......... #ይቆየን............
#የእግዚአብሔር ቸርነት የመላእኩ ጠባቂየት የቅዱሳኑ የእናትና ልጅ በረከታቸው አይለየን !
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፲ ፰/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም