Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
የኔ መፅናኛ // ዘማሪት ጽጌ ገ/ማርያም @amen_tube1621
አሜን ዬትብ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማና ስርአት የጠበቁ ዝማሬዎች በየጌዜው በአሜን ቲዩብ ይለቃል በመላው አለም የምትገኙ ኦርቶዶክስዊያን ይህንን ቻናል ስብስክራይብ በማድረግ አገልግሎቱን በመለው አለም ተደራሽ እንዲሆን ሰብስክራይፕና ሼር ያድርጉ በተጨማሪ በዚህ አገልግሎት መሳተፍ የምትፈልጉ ዘማርያን አግልጋዮች +251910103597 በመደወል የአገልግሎቱ ተሳታፊ መሆን ይቻላሉ…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
Photo
“ስለ እናንተ ሲያማልዱ፥ በእናንተ ላይ ከሚሆነው ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ይናፍቁአችኋል።” (ቅዱስ ጳውሎስ 2ኛ ቆሮ 9፥14)
--------------------------------
☞ ጻድቃን "አያማልዱም" የሚለውን ክርክር ተወውና የዘፍጥረትን መጽሐፍ ገልጠህ ፈጣሪህን ጠይቅ። ደጋጎች አይደለም ማልደው ለጥፋት በተዘጋጀች ከተማ ቢኖሩ እንኳን በከተማይቱ ስለመኖራቸው ብሎ ምሕረትን ያወርዳል።
☞ እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን በኃጢአታቸው ምክንያት በእሳትና በዲን አቃጥሎ ከመቅጣቱ አስቀድሞ ለወዳጁ ለአብርሃም "እኔ የማደርገውን ከአብርሃም እሰውራለሁን? አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፥ የምድር አሕዛብም ሁሉ በእርሱ ይባረካሉና። ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።" ካለ በኋላ "የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቶአልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና፥ እንግዲህስ ወደ እኔ እንደ መጣች እንደ ጩኸትዋ አድርገው እንደ ሆነ ወርጄ አያለሁ፤ እንዲሁም ባይሆን አውቃለሁ።" በማለት ነገረው። ይህ ነገር በእግዚአብሔር የተነገረው አብርሃም ደጋግሞ ምን ብሎ እንደጸለየ ታስተውላለህን? "አምሳ ጻድቃን በከተማይቱ ውስጥ ቢገኙ በውኑ ሁሉን ታጠፋለህን? ከተማይቱንስ በእርስዋ ስለሚገኙ አምሳ ጻድቃን አትምርምን?"….... ዳግመኛም "ከአምሳው ጻድቃን አምስት ቢጐድሉ ከተማይቱን ሁሉ በአምስቱ ምክንያት ታጠፋለህን? "… ሦስተኛም "ጌታዬ አይቆጣ እኔም እናገራለሁ፤ ምናልባት ከዚያ ሠላሳ ቢገኙሳ?… አራተኛም፦ "እኔ ደግሞ አንድ ጊዜ ብቻ ብናገር ጌታዬ አይቆጣ፤ ምናልባት ከዚያ አሥር ቢገኙሳ?" አለ።" ቅዱሱ ሰው አብርሃም በመጨረሻ የጸለየውን ጸሎት ልብ በል "በእነዚህ በሁለት ታላላቅ ከተሞች አሥር ጻድቃንን ብታገኝ አትምርምን?" የሚል ነው። እግዚአብሔር ምን ብሎ የመለሰ ይመስልሃል? "አምሳ ሳይሆን አሥርም ጻድቃን ባገኝ እምራለሁ!!!" (ዘፍ 18:17-25)
☞ እስቲ ልጠይቅህ ዛሬ ግብረ ሰዶማዊነት የት ደርሶዋል? በደጅህ አልደረሰምን? ለቀደሙት ስለገባው ቃልኪዳን ታግሦዋል እንጂ ሰዶማውያኑ በጠፉበት ግብረ ሰዶም ዓለሙ ይጠፋ እንደነበር የታወቀ ነው። ጠቢቡ ሰሎሞን “ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል።” (ምሳ 29፥2) ብሎ ለምን ተናገረ? በጻድቃን ብዛት ሀገር እንደምትድን በተረዳ ነገር ስላወቀ አይደለምን?
☞ የጻድቃን ልመና ብቻ ሳይሆን መኖር እንኳን ከጥፋት ይታደግሃል። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ።” ብሎ በምሥጢረ ምጽዓት ትምህርቱ እንዳስተማረ። (ማቴ 24፥22) እግዚአብሔር ለወዳጆቹ በሚገባው ቃልኪዳን ቁጣውን በምሕረት በትእግሥት እንደሚለውጥ መከራውን እንደሚያሳጥር ይህ የጌታ ቃል ምስክር ነው። ዓለም አልገባውም እንጂ ሐሳዊ መሲሕ የሚሠለጥንባቸው እነዚያ አስጨናቂ ወራት እንኳን የሚያጥሩት በጽኑ እምነታቸው በቀና ምግባራቸው እርሱን ላስደሰቱት ወዳጆቹ በገባው ቃልኪዳን ነው።
መድኅን ዓለም ክርስቶስ ሕያዋን ቅዱሳኑን "ሙታን" ለሚሉ ሰዱቃውያን “እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።” ብሎ የተናገረውን ቃል ልብ በልና ሙታን እንደሌሉን አውቀህ ወደ ሕይወት የተሻገሩበትን የዕረፍታቸውን ቀን እንደ ዳዊት “የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” (መዝ116፥15) እያልክ እየዘመርክ አክብር። (ማቴ 22፥31-32)
እባክዎን ቃለ እግዚአብሔርን በማጋራት ለወዳጆችዎ ያድርሱ።
ቢትወደድ ወርቁ
ሠኔ 24 ቀን 2017 ዓ ም
(ሥዕለ ተክለ ሃይማኖት በ Coptic ቤተ ክርስቲያን ሠዐሊ ዐይን)
--------------------------------
☞ ጻድቃን "አያማልዱም" የሚለውን ክርክር ተወውና የዘፍጥረትን መጽሐፍ ገልጠህ ፈጣሪህን ጠይቅ። ደጋጎች አይደለም ማልደው ለጥፋት በተዘጋጀች ከተማ ቢኖሩ እንኳን በከተማይቱ ስለመኖራቸው ብሎ ምሕረትን ያወርዳል።
☞ እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን በኃጢአታቸው ምክንያት በእሳትና በዲን አቃጥሎ ከመቅጣቱ አስቀድሞ ለወዳጁ ለአብርሃም "እኔ የማደርገውን ከአብርሃም እሰውራለሁን? አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፥ የምድር አሕዛብም ሁሉ በእርሱ ይባረካሉና። ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።" ካለ በኋላ "የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቶአልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና፥ እንግዲህስ ወደ እኔ እንደ መጣች እንደ ጩኸትዋ አድርገው እንደ ሆነ ወርጄ አያለሁ፤ እንዲሁም ባይሆን አውቃለሁ።" በማለት ነገረው። ይህ ነገር በእግዚአብሔር የተነገረው አብርሃም ደጋግሞ ምን ብሎ እንደጸለየ ታስተውላለህን? "አምሳ ጻድቃን በከተማይቱ ውስጥ ቢገኙ በውኑ ሁሉን ታጠፋለህን? ከተማይቱንስ በእርስዋ ስለሚገኙ አምሳ ጻድቃን አትምርምን?"….... ዳግመኛም "ከአምሳው ጻድቃን አምስት ቢጐድሉ ከተማይቱን ሁሉ በአምስቱ ምክንያት ታጠፋለህን? "… ሦስተኛም "ጌታዬ አይቆጣ እኔም እናገራለሁ፤ ምናልባት ከዚያ ሠላሳ ቢገኙሳ?… አራተኛም፦ "እኔ ደግሞ አንድ ጊዜ ብቻ ብናገር ጌታዬ አይቆጣ፤ ምናልባት ከዚያ አሥር ቢገኙሳ?" አለ።" ቅዱሱ ሰው አብርሃም በመጨረሻ የጸለየውን ጸሎት ልብ በል "በእነዚህ በሁለት ታላላቅ ከተሞች አሥር ጻድቃንን ብታገኝ አትምርምን?" የሚል ነው። እግዚአብሔር ምን ብሎ የመለሰ ይመስልሃል? "አምሳ ሳይሆን አሥርም ጻድቃን ባገኝ እምራለሁ!!!" (ዘፍ 18:17-25)
☞ እስቲ ልጠይቅህ ዛሬ ግብረ ሰዶማዊነት የት ደርሶዋል? በደጅህ አልደረሰምን? ለቀደሙት ስለገባው ቃልኪዳን ታግሦዋል እንጂ ሰዶማውያኑ በጠፉበት ግብረ ሰዶም ዓለሙ ይጠፋ እንደነበር የታወቀ ነው። ጠቢቡ ሰሎሞን “ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል።” (ምሳ 29፥2) ብሎ ለምን ተናገረ? በጻድቃን ብዛት ሀገር እንደምትድን በተረዳ ነገር ስላወቀ አይደለምን?
☞ የጻድቃን ልመና ብቻ ሳይሆን መኖር እንኳን ከጥፋት ይታደግሃል። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ።” ብሎ በምሥጢረ ምጽዓት ትምህርቱ እንዳስተማረ። (ማቴ 24፥22) እግዚአብሔር ለወዳጆቹ በሚገባው ቃልኪዳን ቁጣውን በምሕረት በትእግሥት እንደሚለውጥ መከራውን እንደሚያሳጥር ይህ የጌታ ቃል ምስክር ነው። ዓለም አልገባውም እንጂ ሐሳዊ መሲሕ የሚሠለጥንባቸው እነዚያ አስጨናቂ ወራት እንኳን የሚያጥሩት በጽኑ እምነታቸው በቀና ምግባራቸው እርሱን ላስደሰቱት ወዳጆቹ በገባው ቃልኪዳን ነው።
መድኅን ዓለም ክርስቶስ ሕያዋን ቅዱሳኑን "ሙታን" ለሚሉ ሰዱቃውያን “እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።” ብሎ የተናገረውን ቃል ልብ በልና ሙታን እንደሌሉን አውቀህ ወደ ሕይወት የተሻገሩበትን የዕረፍታቸውን ቀን እንደ ዳዊት “የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” (መዝ116፥15) እያልክ እየዘመርክ አክብር። (ማቴ 22፥31-32)
እባክዎን ቃለ እግዚአብሔርን በማጋራት ለወዳጆችዎ ያድርሱ።
ቢትወደድ ወርቁ
ሠኔ 24 ቀን 2017 ዓ ም
(ሥዕለ ተክለ ሃይማኖት በ Coptic ቤተ ክርስቲያን ሠዐሊ ዐይን)
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በዚህ ዕለት ሐምሌ 7 ቀን #ቅድስት_ሥላሴ በአብርሃም ቤት የገቡበት እና ሣራ ይስሐቅን እንደምትወልድ የተናገረበት ዕለት ነው፡፡
ዳግመኛም በዚህ ዕለት ልደቱ እና ዕረፍቱ በአንድ ቀን የገጠመለት የእመቤታችን ወዳጅ ፣ ኢትዮጲያዊው ቄርሎስ የተባለ የሃይማኖት ጠበቃ ፣ ቅዱስ እና ሊቅ #አባ_ጊዮርግስ_ዘጋስጫ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው።
#ቅድስት_ሥላሴ
አባታችን አብርሃም ከተመሳቀለ ጐዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ መንገደኞችን ዅሉ በእንግድነት እየተቀበለ ሲያስተናግድ ይኖር ነበር፡፡ ጥንተ ጠላታችን ሰይጣን ለተንኮል አያርፍምና ይህንን መልካም ግብሩን ለማሰናክል አሰበ፡፡ አስቦም አልቀረ፤ የተጐዳ ሰው መስሎ ከጐዳና ቆሞ አብርሃም እንግዳ መቀበል እንደ ተወ፤ እርሱ ሊበላ ሊጠጣ ከቤቱ ቢሔድ ራሱን ፈንክቶ፣ ደሙን አፍሶ፣ አጥንቱን ከስክሶ፣ ልብሱን ገፎ እንደ መለሰው ወደ አብርሃም ቤት ለሚሔዱ ሰዎች ይናገር ጀመር፡፡ በዚህ የተነሣም እንግዳ ወደ አብርሃም ቤት አልመጣ አለ፡፡ በዚህ ጊዜ አብርሃምም ማዕደ እግዚአብሔርን ያለ ምስክር (ያለ እንግዳ) አልመገብም ብሎ ሦስት ቀን ሳይመገብ ጾሙን አደረ፡፡ በሦስተኛው ቀን ይህን ደግነቱን እግዚአብሔር ተመልክቶ በሦስት ሰዎች አምሳል አንድም በሥላሴው (በሦስትነቱ) ከአብርሃም ቤት ገብቷል (ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ፣ 4 ፥32 )፡፡
በኦሪት ዘፍጥረት 18 ፥ 1 -19 ተጽፎ እንደምናገኘው በቀትር ጊዜ አብርሃም በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በሦስት ሰዎች አምሳል በመምሬ አድባር ዛፍ ተገልጦለታል፡፡ አብርሃምም ሦስት ሰዎች ቆመው ባየ ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ወደ እነርሱ ሮጠ፡፡ ወደ ምድርም ሰገደና ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ኾነ ባርያህን አትለፈኝ?›› ብሎ ተማጸነ፡፡ በመቀጠል አብርሃም ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፤ እግራችሁን ታጠቡ፤ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፡፡ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፤ ልባችሁንም ደግፉ፡፡ ከዚያም በኋላ ትሔዳላችሁ፡፡ ስለዚህ ወደ ባርያችሁ መጥታችኋልና›› ሲላቸው እነርሱም ‹‹እንዳልህ አድርግ›› ብለውታል፡፡
ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ጠርቶ ‹‹ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት?›› አለው፡፡ አብርሃምም ከድንኳኑ ውስጥ እንዳለች ነገረው፡፡ እግዚአብሔርም ‹‹የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች›› ብሎ ለአብርሃም አበሠረው፡፡ ሣራ ይህንን ቃል በሰማች ጊዜ ባለቤቷም አርጅቶ፤ እርሷም የሴቶች ግዳጅ ትቷት ነበርና ‹‹‹ሲያረጁ አምባር ይዋጁ› እንዲሉ ‹‹እስከ ዛሬ ድረስ ቆንጆ ነኝን? ጌታዬ አብርሃምስ ገና ጐረምሳ ነውን?›› ብላ በማሰቧና መውለዷን በመጠራጠሯ ሳቀች፡፡ እግዚአብሔርም ምሥጢሩን በአጽንዖት ለማስረዳትና አስረግጦ ለመንገር አብርሃምን ‹‹ሣራ ለምን ትስቃለች? በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን?›› አለው፡፡ ሣራም ስለፈራች ‹‹አልሳቅሁም›› አለች፡፡ እግዚአብሔርም መሳቋን እንዳወቀባት ከነገራት በኋላ በድጋሜ በዓመቱ ወደ አብርሃም ቤት እንደሚመጣና ሣራ ወንድ ልጅ (ይስሐቅን) እንደምትወልድ አብሥሯቸዋል፡፡
የቅድስት ሥላሴ ረድኤታቸው አይየን!
የቅዱስ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ አማላጅነቱ አትለየን ። ሀገራችንን ቅድስት ኢትዮጺያን ሊለያይ የሚሽቀዳደመውን ዲያብሎስን በመስቀሉ ይምታልን።
©️ ዮቶር ደሳለኝ
#መልካም_በዓል
#ጸልዩ_በእንተ_ቤተክርስቲያን_ቅድስት@zdk24_5_21_official
ዳግመኛም በዚህ ዕለት ልደቱ እና ዕረፍቱ በአንድ ቀን የገጠመለት የእመቤታችን ወዳጅ ፣ ኢትዮጲያዊው ቄርሎስ የተባለ የሃይማኖት ጠበቃ ፣ ቅዱስ እና ሊቅ #አባ_ጊዮርግስ_ዘጋስጫ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው።
#ቅድስት_ሥላሴ
አባታችን አብርሃም ከተመሳቀለ ጐዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ መንገደኞችን ዅሉ በእንግድነት እየተቀበለ ሲያስተናግድ ይኖር ነበር፡፡ ጥንተ ጠላታችን ሰይጣን ለተንኮል አያርፍምና ይህንን መልካም ግብሩን ለማሰናክል አሰበ፡፡ አስቦም አልቀረ፤ የተጐዳ ሰው መስሎ ከጐዳና ቆሞ አብርሃም እንግዳ መቀበል እንደ ተወ፤ እርሱ ሊበላ ሊጠጣ ከቤቱ ቢሔድ ራሱን ፈንክቶ፣ ደሙን አፍሶ፣ አጥንቱን ከስክሶ፣ ልብሱን ገፎ እንደ መለሰው ወደ አብርሃም ቤት ለሚሔዱ ሰዎች ይናገር ጀመር፡፡ በዚህ የተነሣም እንግዳ ወደ አብርሃም ቤት አልመጣ አለ፡፡ በዚህ ጊዜ አብርሃምም ማዕደ እግዚአብሔርን ያለ ምስክር (ያለ እንግዳ) አልመገብም ብሎ ሦስት ቀን ሳይመገብ ጾሙን አደረ፡፡ በሦስተኛው ቀን ይህን ደግነቱን እግዚአብሔር ተመልክቶ በሦስት ሰዎች አምሳል አንድም በሥላሴው (በሦስትነቱ) ከአብርሃም ቤት ገብቷል (ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ፣ 4 ፥32 )፡፡
በኦሪት ዘፍጥረት 18 ፥ 1 -19 ተጽፎ እንደምናገኘው በቀትር ጊዜ አብርሃም በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በሦስት ሰዎች አምሳል በመምሬ አድባር ዛፍ ተገልጦለታል፡፡ አብርሃምም ሦስት ሰዎች ቆመው ባየ ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ወደ እነርሱ ሮጠ፡፡ ወደ ምድርም ሰገደና ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ኾነ ባርያህን አትለፈኝ?›› ብሎ ተማጸነ፡፡ በመቀጠል አብርሃም ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፤ እግራችሁን ታጠቡ፤ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፡፡ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፤ ልባችሁንም ደግፉ፡፡ ከዚያም በኋላ ትሔዳላችሁ፡፡ ስለዚህ ወደ ባርያችሁ መጥታችኋልና›› ሲላቸው እነርሱም ‹‹እንዳልህ አድርግ›› ብለውታል፡፡
ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ጠርቶ ‹‹ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት?›› አለው፡፡ አብርሃምም ከድንኳኑ ውስጥ እንዳለች ነገረው፡፡ እግዚአብሔርም ‹‹የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች›› ብሎ ለአብርሃም አበሠረው፡፡ ሣራ ይህንን ቃል በሰማች ጊዜ ባለቤቷም አርጅቶ፤ እርሷም የሴቶች ግዳጅ ትቷት ነበርና ‹‹‹ሲያረጁ አምባር ይዋጁ› እንዲሉ ‹‹እስከ ዛሬ ድረስ ቆንጆ ነኝን? ጌታዬ አብርሃምስ ገና ጐረምሳ ነውን?›› ብላ በማሰቧና መውለዷን በመጠራጠሯ ሳቀች፡፡ እግዚአብሔርም ምሥጢሩን በአጽንዖት ለማስረዳትና አስረግጦ ለመንገር አብርሃምን ‹‹ሣራ ለምን ትስቃለች? በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን?›› አለው፡፡ ሣራም ስለፈራች ‹‹አልሳቅሁም›› አለች፡፡ እግዚአብሔርም መሳቋን እንዳወቀባት ከነገራት በኋላ በድጋሜ በዓመቱ ወደ አብርሃም ቤት እንደሚመጣና ሣራ ወንድ ልጅ (ይስሐቅን) እንደምትወልድ አብሥሯቸዋል፡፡
የቅድስት ሥላሴ ረድኤታቸው አይየን!
የቅዱስ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ አማላጅነቱ አትለየን ። ሀገራችንን ቅድስት ኢትዮጺያን ሊለያይ የሚሽቀዳደመውን ዲያብሎስን በመስቀሉ ይምታልን።
©️ ዮቶር ደሳለኝ
#መልካም_በዓል
#ጸልዩ_በእንተ_ቤተክርስቲያን_ቅድስት@zdk24_5_21_official
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
🔴 አዲስ ዝማሬ "የዋኅ መልአክ" ዘማሪ ዳዊት ክብሩ || | Yewah Melak l Z Dawit Kibru
የዋኅ መልአክ
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል
ታዳጊያችን ነህ ምክሩ ለልዑል
የአምላክ ኀይሉ መገለጫው ነህ
የእልፍ አእላፍ መላእክት መስፍናቸው ነህ
ለሠራዊተ ሰማይ መላእክት አለቃቸው
ለፍጥረቱ ለባሕር ለየብሱ አጽንዖታቸው
የዋኅ ርኅሩኅ መልአክ ኀዳጌ በቀል
በልመናው በጸሎቱ ያስምረናል ቅዱስ ሚካኤል ።
የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ቅዱስ ሚካኤል
ለሰው ልጆች የምታዝን ምታማልድ ከልዑል
እነሆ ሕይወታችንን…
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል
ታዳጊያችን ነህ ምክሩ ለልዑል
የአምላክ ኀይሉ መገለጫው ነህ
የእልፍ አእላፍ መላእክት መስፍናቸው ነህ
ለሠራዊተ ሰማይ መላእክት አለቃቸው
ለፍጥረቱ ለባሕር ለየብሱ አጽንዖታቸው
የዋኅ ርኅሩኅ መልአክ ኀዳጌ በቀል
በልመናው በጸሎቱ ያስምረናል ቅዱስ ሚካኤል ።
የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ቅዱስ ሚካኤል
ለሰው ልጆች የምታዝን ምታማልድ ከልዑል
እነሆ ሕይወታችንን…
ግጥምጥሞሽ ወይስ #እግዚአብሔር_መንፈስ_ቅዱስ?
የአንድ ሰካራም መዝሙር
" #የሰዎች ነገር #አይተኛም "
_____
ቀኑ ብሩሃማ ነው ሰሞነ ሕማማት ከገባ ሦስተኛ ቀን ሆኖታል የቀለም ቆጠራ አለ ስለተባለ እንደ ሳምንቱ ወሳኝ ኩነቶቼ ሁሉ ወደ ቀለም ትምህርት ቤት እየገሰገስኩ ነው። አንድ እብድ መሳይ የኔ ቢጤ የፕሮቲስታንት ሰባኪ በሚመስል ሁናቴ ቀኝ እጁን ወደ ላይ ከፍ አድርጎ አንድ በስፋት የሚታወቅ የይልማ ኃይሉን መዝሙር እየቀለጸ በእኔ ተቃራኒ አቅጣጫ ሲመጣ አየሁት ። መዝሙሩና የመዝሙሩ ዜማ :- "የሚጠብቀኝ አይተኛም አያንቀላፋም" የሚል መሆኑን እርግጠኛ ነኝ ግን ሰውየው የመጀመሪያውን የስንኝ አንጓ በራሱ ሆድ ብሶት ቀይሮ እየዘመረው ነበር። እንዲህ በማለት "የሰዎች ነገር አይተኛም (2)× አያንቀላፋም " ........
........ወዲያውኑ መገረም ያዘኝ ። እውነቱን እኮ ነው ጎበዝ ".......የሰዎች ነገር አይተኛም !" የሚጠብቀን ራሱ የማይተኛው የሰዎች ነገር ስለማይተኛ ይመስለኛል። ምናልባት ትክክለኛው ዘማሪ የዚህን የኔ ቢጤ አዘማመር ቢሰማ ኖሮ የሰዎች ነገር አይተኛም በሚለው ቀይሮ በዘመረው ነበር።
ዓለም ብቻ ሳትሆን የሰዎች ነገርም ብዙዎችን ወግታ ጥላለች። ለነገሩ ዓለም የሚለው በዋናነት የሰው ልጆችን አይደለምን? ነው እንጂ። #ምሳ 7÷26
ግን ግን ይህን ሰካራም እንዲህ ብሎ እስኪዘምር ድረስ የወጋው እና #ጽኑ_ሕማማም የሆነበት የሰው ነገር ምን ይሆን ? በእርግጥስ ያሰከረው ጌሾና ብቅል ነውን ወይስ ነገረ ሰብ ???
ስትወፍር ዘረጦ ፣ ስትከሳ ሜንጦ ፣ ብትረዝም ብቅል አውራጅ ፣ ብታጥርም ጉቶ ፣ ስታገኝ ሰላቢ ፣ ስታጣም ችጋራም ፣ ብታነብ ደብተራ ፤ ብትጽፍ መተታም ስትተወው ደንቆሮ ፣ ስትናገር ተናጋሪ ፣ ዝም ብትል ዝጋታም እያሉ የሚወጉ የሕማማት ሁሉ ምንጭ አንደበተ ሕማማት መጨረሻቸው ምን ይሆን ።
ንጹሐ ባህሪ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳ በመዋለ ስብከቱ ሳለ ይህ የሰዎች የነገር ውጋት አግኝታዋለች ፤ እርሱ ግን "ማይመረ ኩሉ " ሁሉን የሚያውቅ እውነተኛ አምላክ ነውና " ዮሐንስ ሳይበላና ሳይጠጣ መጣ፥ እናንተ ግን፦ ጋኔን አለበት አላችሁት። እነሆ የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጣ፥ እናንተም፦ በላተኛና የወይን ጠጅ ጠጭ፥ የቀራጮችና የኃጢአተኞች ወዳጅ አላችሁት። " ብሎ አምርሮ ወቅሷቸል። #ማቴ 11÷18-19 ክርስቶስ እንኳ በሰው አፍ ያለ በደሉ ሲነቀፍ አስተዋልክን ? ብትበላም ባትበላም ትወቀሳለህ ብታውቅም ባታውቅም ትወረፋለህ ቅንም ቅንቅንም ብትሆን ትተቻለህ
እና ወዳጄ ምን አሰብክ ? የሰውን የነገር አፍ ፈርተህ መቆምን መረጥክን? ከቆንጆ ሕልምህስ መንቃት ፈለክን?? አትሞኝ ሕልምን ብታቆምም መንገድህንም ብትገታ ከሰው አፍ አትወጣም ምክንያቱም " #የሰዎች ነገር #አይተኛም አያንቀላፋምም " ሊሰራ ተነስቶ ነበር አቅቶት ተወው ሕልመኛ መስሎን ነበር ለካ እየቃዠ ነበር ይሉሃል። #ሉቃ 14÷30
እንደ ጋሪ ፈረስ ለጥቃቅን የጎንዮሽ ዕይታ ትኩረት ነፍገህ ወደፊት ወዳለችሁ የጽድቅ መንገድ በፈጣሪህ ሕግና ትዕዛዝ መሠረት ያለ መታከት ገስግስ። ውሾች ይጩሁ ግመሎችም ይሂዱ !
ለዚያም ሰካር ዘማሪ #እግዚአብሔር_አምላክ ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን ከሰው የአፍ ፍላጻም በጽኑ ይፈውስልን አሜን!
......" የ ሰዎች ነገር አይተኛም (2) × አያንቀላፋም ".........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሚያ03/2015 ዓ.ም
የአንድ ሰካራም መዝሙር
" #የሰዎች ነገር #አይተኛም "
_____
ቀኑ ብሩሃማ ነው ሰሞነ ሕማማት ከገባ ሦስተኛ ቀን ሆኖታል የቀለም ቆጠራ አለ ስለተባለ እንደ ሳምንቱ ወሳኝ ኩነቶቼ ሁሉ ወደ ቀለም ትምህርት ቤት እየገሰገስኩ ነው። አንድ እብድ መሳይ የኔ ቢጤ የፕሮቲስታንት ሰባኪ በሚመስል ሁናቴ ቀኝ እጁን ወደ ላይ ከፍ አድርጎ አንድ በስፋት የሚታወቅ የይልማ ኃይሉን መዝሙር እየቀለጸ በእኔ ተቃራኒ አቅጣጫ ሲመጣ አየሁት ። መዝሙሩና የመዝሙሩ ዜማ :- "የሚጠብቀኝ አይተኛም አያንቀላፋም" የሚል መሆኑን እርግጠኛ ነኝ ግን ሰውየው የመጀመሪያውን የስንኝ አንጓ በራሱ ሆድ ብሶት ቀይሮ እየዘመረው ነበር። እንዲህ በማለት "የሰዎች ነገር አይተኛም (2)× አያንቀላፋም " ........
........ወዲያውኑ መገረም ያዘኝ ። እውነቱን እኮ ነው ጎበዝ ".......የሰዎች ነገር አይተኛም !" የሚጠብቀን ራሱ የማይተኛው የሰዎች ነገር ስለማይተኛ ይመስለኛል። ምናልባት ትክክለኛው ዘማሪ የዚህን የኔ ቢጤ አዘማመር ቢሰማ ኖሮ የሰዎች ነገር አይተኛም በሚለው ቀይሮ በዘመረው ነበር።
ዓለም ብቻ ሳትሆን የሰዎች ነገርም ብዙዎችን ወግታ ጥላለች። ለነገሩ ዓለም የሚለው በዋናነት የሰው ልጆችን አይደለምን? ነው እንጂ። #ምሳ 7÷26
ግን ግን ይህን ሰካራም እንዲህ ብሎ እስኪዘምር ድረስ የወጋው እና #ጽኑ_ሕማማም የሆነበት የሰው ነገር ምን ይሆን ? በእርግጥስ ያሰከረው ጌሾና ብቅል ነውን ወይስ ነገረ ሰብ ???
ስትወፍር ዘረጦ ፣ ስትከሳ ሜንጦ ፣ ብትረዝም ብቅል አውራጅ ፣ ብታጥርም ጉቶ ፣ ስታገኝ ሰላቢ ፣ ስታጣም ችጋራም ፣ ብታነብ ደብተራ ፤ ብትጽፍ መተታም ስትተወው ደንቆሮ ፣ ስትናገር ተናጋሪ ፣ ዝም ብትል ዝጋታም እያሉ የሚወጉ የሕማማት ሁሉ ምንጭ አንደበተ ሕማማት መጨረሻቸው ምን ይሆን ።
ንጹሐ ባህሪ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳ በመዋለ ስብከቱ ሳለ ይህ የሰዎች የነገር ውጋት አግኝታዋለች ፤ እርሱ ግን "ማይመረ ኩሉ " ሁሉን የሚያውቅ እውነተኛ አምላክ ነውና " ዮሐንስ ሳይበላና ሳይጠጣ መጣ፥ እናንተ ግን፦ ጋኔን አለበት አላችሁት። እነሆ የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጣ፥ እናንተም፦ በላተኛና የወይን ጠጅ ጠጭ፥ የቀራጮችና የኃጢአተኞች ወዳጅ አላችሁት። " ብሎ አምርሮ ወቅሷቸል። #ማቴ 11÷18-19 ክርስቶስ እንኳ በሰው አፍ ያለ በደሉ ሲነቀፍ አስተዋልክን ? ብትበላም ባትበላም ትወቀሳለህ ብታውቅም ባታውቅም ትወረፋለህ ቅንም ቅንቅንም ብትሆን ትተቻለህ
እና ወዳጄ ምን አሰብክ ? የሰውን የነገር አፍ ፈርተህ መቆምን መረጥክን? ከቆንጆ ሕልምህስ መንቃት ፈለክን?? አትሞኝ ሕልምን ብታቆምም መንገድህንም ብትገታ ከሰው አፍ አትወጣም ምክንያቱም " #የሰዎች ነገር #አይተኛም አያንቀላፋምም " ሊሰራ ተነስቶ ነበር አቅቶት ተወው ሕልመኛ መስሎን ነበር ለካ እየቃዠ ነበር ይሉሃል። #ሉቃ 14÷30
እንደ ጋሪ ፈረስ ለጥቃቅን የጎንዮሽ ዕይታ ትኩረት ነፍገህ ወደፊት ወዳለችሁ የጽድቅ መንገድ በፈጣሪህ ሕግና ትዕዛዝ መሠረት ያለ መታከት ገስግስ። ውሾች ይጩሁ ግመሎችም ይሂዱ !
ለዚያም ሰካር ዘማሪ #እግዚአብሔር_አምላክ ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን ከሰው የአፍ ፍላጻም በጽኑ ይፈውስልን አሜን!
......" የ ሰዎች ነገር አይተኛም (2) × አያንቀላፋም ".........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሚያ03/2015 ዓ.ም
የ13 ወራትና የ13 ሙሉ ጨረቃዎች ጸጋ ባለቤቶች
☄️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ቀመር 13 መቼም አስገራሚ ናት፤ ብዙዎች ስለዚኽ ቊጥር ሲሰሙ ይሸበራሉ፡፡ በተለይ በምዕራቡ ዓለም ቊጥር 13 በእጅጉ ይፈራል፡፡ triskaidekaphobia (ትሪስ ካይ ዴካ ፎቢያ) ይባላል፡፡ ከተመዘገቡት የፍርሃት ዓይነቶች አንዱ ይኽ ነው፡፡
☄️ በግሪክ ቋንቋ τρεισκαίδεκα “ትሪስ” ማለት “3” “ካይ” ማለት “እና” “ዴካ” (ዐሥር) “ፎቢያ” (ፍርሃት) በአጠቃላይ የ13 ቊጥር ፍርሃት ማለት ነው፡፡
በተለይ ዐርብ እና 13 ሲገጥሙ ፍርሃቱ የሚጨምር ሲኾን የፍርሃቱ መጠሪያውም paraskevidekatriaphobia ይባላል፡፡
☄️ በምዕራቡ ዓለማት ያሉት ሀገራት እጅግ ብዙዎቹ 13ኛ ፎቅ የላቸውም፡፡ በሊፍት ሲወጣ 13ኛ ቊጥርን በመዝለል 14 ቊጥር ሲል ማየት የተለመደ ነው፡፡
☄️ ሪልስቴቶች 13ኛ ፎቅ ገዢ ስለሌላቸው 12 ኤ፤ 12 ኤም … እያሉ መሸጥ የተለመደ ነው፡፡
💥 ታላላቆች አየር መንገዶች ለምሳሌ እንደ ዩናይትድ፣ አላስካ፣ ራያኔር፣ ሉፍታንዛ፣ ፓሲፊክ፣ ሲንጋፓር ያሉ 13ኛ መቀመጫ በመዝለል 12 ብለው 14 እንደሚሉ በነዚኽ አየር መንገዶች የሚበሩ መንገደኞች ኹሉ ያውቁታል፡፡
💥 13 ቊጥር ግን ማያውያንን ጨምሮ በጥንት ሥልጡን ሕዝቦች ግን ተወዳጅ ቀመር ናት፡፡ ለምሳሌ በእስራኤል ቀመረ ፊደለ ዕብራይስጥ ፍቅር ማለት “አሀባህ” (אהבה) ሲባል በ22ቱ አሌፋት ሲቀመር (1 + 5 + 2 + 5 = 13) ይሰጣል፡፡ ☄️ በእኛም በግእዝ አልፍ ቤት ቀመረ ግእዝ “ጥበብ፣ ኤል” ይኽንኑ ቀመር ይሰጣሉ፡፡
🌓 ሴቶች በዓመት ውስጥ የሚያዩት የወርኅ አበባ የጨረቃን ዑደት ማእከል ያደረገ በመኾኑ 13 ነው - 28 ቀናት (365/28 = 13) ነው።
☄️ በግእዝ ወር የሚለው ቃል “ወርኅ” (ጨረቃ) ከሚለው ቃል የመጣ ነው፡፡ በእንግሊዝኛም menstruation መባሉ በላቲኒ ሜኔ - ሙን “ጨረቃ” ማለት ነውና ይኽነን ዑደት ማእከል ያደረገ ነው፡፡
☄️ በአፍሮ አይገባ መስቀል ላይ እንደምናየው ከጐን 6 ከጐን 6 ከላይ 1 በድምሩ 13 በማሳየት 12ቱ ሐዋርያትን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በመወከል፤ 13ቱን ሕማማተ መስቀል በማሳየት አስደናቂ ምሳሌን ያስነብባል፡፡
☄️ የ2017 ዓ.ም. ደግሞ በእጅጉ ልዩ የሚያደርገው ከታላቅነቷ የተነሣ ብዙ ፈተና የተነሣባት 13ኛዋ ወር ጳጒሜን 13ኛው ሙሉ ጨረቃ በዚኽች በ13ኛ ወር ላይ ማረፉ ነው፡፡
🌓 ይኸውም የ2017 ዓ.ም. የተከሰቱ 13ቱ ሙሉ ጨረቃዎች እነሆ፡-
1ኛ) መስከረም 8 🌞
2ኛ) ጥቅምት 7 🌚
3ኛ) ኅዳር 7 🌞
4ኛ) ታኅሣሥ 6 🌚
5ኛ) ጥር 5 🌞
6ኛ) የካቲት 5 🌚
7ኛ) መጋቢት 5 🌞
8ኛ ሚያዝያ 5 🌑
9ኛ) ግንቦት 4 🌞
10ኛ) ሠኔ 4 🌑
11ኛ) ሐምሌ 3 🌞
12ኛ) ነሐሴ 3 🌑
13ኛ) ጳጉሜን 2 🌓☄️☄️☄️☄️
☄️ በመፈጸም የጨረቃ መጨለም (ግርዶሽ) በምልአተ ወርኅ (በሙሉ ጨረቃ) ጊዜ ብቻ ነውና የሚኾነው ጳጕሜን 2 ተጠባቂዋ የሙሉ ጨለማ ግርዶሽን ቢሊየኖች ያዩታል፡፡ ከምሽቱ 2፡30 ጀምሮ (82 ደቂቃዎች (1 ሰዓት ከ22 ደቂቃዎች) ሙሉ ግርዶሽ የደም ጨረቃ በርኅወተ ሰማይ ምሽት እንደነቅባታለን፡፡
☄️ በነገው የጳጉሜን 2 ምሽት ሰብሰብ ብላችኊ ይኽነን የተፈጥሮ ክስተት በማድነቅ ፎቶዎች እያነሣችኊ ለዐዲሱ ዓመት በጎ እየተመኛችኊ እንድትደሰቱበት መልእክቴን በመግለጽ የተባረከ ምሽት ለኹላችኹም እመኛለኍ፡፡
☄️ 13 ወር የፀሓይ ጸጋ ተብላ ብትደነቀው ውቧ ሀገራችንም በዚኽ ዓመት 13ኛ ሙሉ ጨረቃ በ13ኛዋ የጳጒሜን ወር ላይ በመግጠም 13 ወር የጨረቃ ጸጋ እንድንላት አስችሎናል፡፡
ጳጒሜን 2 የዓመቷን ሙሉ ጨረቃ ከግርሽዋ ጋር ካየን በኋላ የ2018 ዓ.ም. የዐዲሱ ዓመት ሙሉ የመስከረም ሙሉ ጨረቃ ማግሰኞ መስከረም 27 ደምቃ በምሥራቅ አድማስ ትወጣለችና ለዐዲሱ ዓመት የመስከረም 27 ሙሉ ጨረቃ በሰላም ደምቀን ያገናኘን፡፡
🌓 የነገው ሰዓት ለማወቅ
🌓 ከምሽቱ 12:21 ላይ 13ኛዋ ሙሉ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ ደምቃ ትወጣለች
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትጀምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ጀምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
☄️ ኹሉ ተጠናቆ 5:55 ላይ ጨረቃ ወደ ድምቀቷ ትመለሳለች።
https://youtu.be/RZlhgpKNeqM?si=Y2IlMGQjnQZFTQCd
💥 አልፋ እግዚአብሔር ሆይ ቀጣዩ ዘመናችን ኹሉ አንተን በመውደድ፤ ሰውን ኹሉ በእውነት በመውደድ፤ ከአንተ የሚገኘው ሰላም በረከት ጸጋ ኹሉ በቅናት ሳይኾን በቅንነት ነውና ሥጋዊ ቅናትን ከልባችን አስወግደኽ፤ በጠብ ሳይኾን በአንተ ጥበብ፤ በምስጋና በምድራዊ ሰማያዊ በረከቶችኽ እየተደሰትን እንድንጓዝ ፈቃድኽ ይኹንልን። መልካም የጳጉሜን ወር።
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
☄️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ቀመር 13 መቼም አስገራሚ ናት፤ ብዙዎች ስለዚኽ ቊጥር ሲሰሙ ይሸበራሉ፡፡ በተለይ በምዕራቡ ዓለም ቊጥር 13 በእጅጉ ይፈራል፡፡ triskaidekaphobia (ትሪስ ካይ ዴካ ፎቢያ) ይባላል፡፡ ከተመዘገቡት የፍርሃት ዓይነቶች አንዱ ይኽ ነው፡፡
☄️ በግሪክ ቋንቋ τρεισκαίδεκα “ትሪስ” ማለት “3” “ካይ” ማለት “እና” “ዴካ” (ዐሥር) “ፎቢያ” (ፍርሃት) በአጠቃላይ የ13 ቊጥር ፍርሃት ማለት ነው፡፡
በተለይ ዐርብ እና 13 ሲገጥሙ ፍርሃቱ የሚጨምር ሲኾን የፍርሃቱ መጠሪያውም paraskevidekatriaphobia ይባላል፡፡
☄️ በምዕራቡ ዓለማት ያሉት ሀገራት እጅግ ብዙዎቹ 13ኛ ፎቅ የላቸውም፡፡ በሊፍት ሲወጣ 13ኛ ቊጥርን በመዝለል 14 ቊጥር ሲል ማየት የተለመደ ነው፡፡
☄️ ሪልስቴቶች 13ኛ ፎቅ ገዢ ስለሌላቸው 12 ኤ፤ 12 ኤም … እያሉ መሸጥ የተለመደ ነው፡፡
💥 ታላላቆች አየር መንገዶች ለምሳሌ እንደ ዩናይትድ፣ አላስካ፣ ራያኔር፣ ሉፍታንዛ፣ ፓሲፊክ፣ ሲንጋፓር ያሉ 13ኛ መቀመጫ በመዝለል 12 ብለው 14 እንደሚሉ በነዚኽ አየር መንገዶች የሚበሩ መንገደኞች ኹሉ ያውቁታል፡፡
💥 13 ቊጥር ግን ማያውያንን ጨምሮ በጥንት ሥልጡን ሕዝቦች ግን ተወዳጅ ቀመር ናት፡፡ ለምሳሌ በእስራኤል ቀመረ ፊደለ ዕብራይስጥ ፍቅር ማለት “አሀባህ” (אהבה) ሲባል በ22ቱ አሌፋት ሲቀመር (1 + 5 + 2 + 5 = 13) ይሰጣል፡፡ ☄️ በእኛም በግእዝ አልፍ ቤት ቀመረ ግእዝ “ጥበብ፣ ኤል” ይኽንኑ ቀመር ይሰጣሉ፡፡
🌓 ሴቶች በዓመት ውስጥ የሚያዩት የወርኅ አበባ የጨረቃን ዑደት ማእከል ያደረገ በመኾኑ 13 ነው - 28 ቀናት (365/28 = 13) ነው።
☄️ በግእዝ ወር የሚለው ቃል “ወርኅ” (ጨረቃ) ከሚለው ቃል የመጣ ነው፡፡ በእንግሊዝኛም menstruation መባሉ በላቲኒ ሜኔ - ሙን “ጨረቃ” ማለት ነውና ይኽነን ዑደት ማእከል ያደረገ ነው፡፡
☄️ በአፍሮ አይገባ መስቀል ላይ እንደምናየው ከጐን 6 ከጐን 6 ከላይ 1 በድምሩ 13 በማሳየት 12ቱ ሐዋርያትን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በመወከል፤ 13ቱን ሕማማተ መስቀል በማሳየት አስደናቂ ምሳሌን ያስነብባል፡፡
☄️ የ2017 ዓ.ም. ደግሞ በእጅጉ ልዩ የሚያደርገው ከታላቅነቷ የተነሣ ብዙ ፈተና የተነሣባት 13ኛዋ ወር ጳጒሜን 13ኛው ሙሉ ጨረቃ በዚኽች በ13ኛ ወር ላይ ማረፉ ነው፡፡
🌓 ይኸውም የ2017 ዓ.ም. የተከሰቱ 13ቱ ሙሉ ጨረቃዎች እነሆ፡-
1ኛ) መስከረም 8 🌞
2ኛ) ጥቅምት 7 🌚
3ኛ) ኅዳር 7 🌞
4ኛ) ታኅሣሥ 6 🌚
5ኛ) ጥር 5 🌞
6ኛ) የካቲት 5 🌚
7ኛ) መጋቢት 5 🌞
8ኛ ሚያዝያ 5 🌑
9ኛ) ግንቦት 4 🌞
10ኛ) ሠኔ 4 🌑
11ኛ) ሐምሌ 3 🌞
12ኛ) ነሐሴ 3 🌑
13ኛ) ጳጉሜን 2 🌓☄️☄️☄️☄️
☄️ በመፈጸም የጨረቃ መጨለም (ግርዶሽ) በምልአተ ወርኅ (በሙሉ ጨረቃ) ጊዜ ብቻ ነውና የሚኾነው ጳጕሜን 2 ተጠባቂዋ የሙሉ ጨለማ ግርዶሽን ቢሊየኖች ያዩታል፡፡ ከምሽቱ 2፡30 ጀምሮ (82 ደቂቃዎች (1 ሰዓት ከ22 ደቂቃዎች) ሙሉ ግርዶሽ የደም ጨረቃ በርኅወተ ሰማይ ምሽት እንደነቅባታለን፡፡
☄️ በነገው የጳጉሜን 2 ምሽት ሰብሰብ ብላችኊ ይኽነን የተፈጥሮ ክስተት በማድነቅ ፎቶዎች እያነሣችኊ ለዐዲሱ ዓመት በጎ እየተመኛችኊ እንድትደሰቱበት መልእክቴን በመግለጽ የተባረከ ምሽት ለኹላችኹም እመኛለኍ፡፡
☄️ 13 ወር የፀሓይ ጸጋ ተብላ ብትደነቀው ውቧ ሀገራችንም በዚኽ ዓመት 13ኛ ሙሉ ጨረቃ በ13ኛዋ የጳጒሜን ወር ላይ በመግጠም 13 ወር የጨረቃ ጸጋ እንድንላት አስችሎናል፡፡
ጳጒሜን 2 የዓመቷን ሙሉ ጨረቃ ከግርሽዋ ጋር ካየን በኋላ የ2018 ዓ.ም. የዐዲሱ ዓመት ሙሉ የመስከረም ሙሉ ጨረቃ ማግሰኞ መስከረም 27 ደምቃ በምሥራቅ አድማስ ትወጣለችና ለዐዲሱ ዓመት የመስከረም 27 ሙሉ ጨረቃ በሰላም ደምቀን ያገናኘን፡፡
🌓 የነገው ሰዓት ለማወቅ
🌓 ከምሽቱ 12:21 ላይ 13ኛዋ ሙሉ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ ደምቃ ትወጣለች
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትጀምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ጀምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
☄️ ኹሉ ተጠናቆ 5:55 ላይ ጨረቃ ወደ ድምቀቷ ትመለሳለች።
https://youtu.be/RZlhgpKNeqM?si=Y2IlMGQjnQZFTQCd
💥 አልፋ እግዚአብሔር ሆይ ቀጣዩ ዘመናችን ኹሉ አንተን በመውደድ፤ ሰውን ኹሉ በእውነት በመውደድ፤ ከአንተ የሚገኘው ሰላም በረከት ጸጋ ኹሉ በቅናት ሳይኾን በቅንነት ነውና ሥጋዊ ቅናትን ከልባችን አስወግደኽ፤ በጠብ ሳይኾን በአንተ ጥበብ፤ በምስጋና በምድራዊ ሰማያዊ በረከቶችኽ እየተደሰትን እንድንጓዝ ፈቃድኽ ይኹንልን። መልካም የጳጉሜን ወር።
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
YouTube
የደም ጨረቃ ምልክት ከዐባይ ወንዝ ጋር ክስተት ወይስ እውነት?
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
https://www.tiktok.com/@glamorous100x/video/7565944114953424142?_r=1&u_code=ebc91271aa1a21&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=eg83l996af4j1c&share_item_id=7565944114953424142&source=h5_m&utm_source=more&utm_campaign=client_share&share_link_id=ad5a3b35-ce82-4914-ba9a-a188c98c6da1&share_app_id=1340&ugbiz_name=Main&lang=en&user_id=7309378473382282245&sec_user_id=MS4wLjABAAAAwqLoBxIhfoMEw-X87nj9FvlWZGPmuMjcR2JfECaN14XKEwCdFXvsZ1_XCy8K30Kl This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite