በአማራ ክልል በጦርነቱ ጉዳት በደረሰባቸው አራት ዞኖች የሚገኙ ከ60 ሺህ በላይ ህጻናትን መንከባከብ የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ!
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ወሎ፣ ሰሜን ሸዋና ዋግ ኽምራ ብሄረሰብ ዞኖች የሚገኙና በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ከ60 ሺህ በላይ ህጻናትን መንከባከብ የሚያስችል ፕሮጀክት በደሴ ከተማ ይፋ ተደርጓል።ፕሮጀክቱ የአንድ ዓመት መርሃ ግብር ሲሆን፤ በአራቱ ዞኖች ውስጥ በሚገኙ ስድስት ወረዳዎች ላይ ይተገበራል ተብሏል።
ፓዝ ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጦርነት በተካሄደባቸው አካባቢዎች ባደረገው የዳሰሳ ጥናት በአማራ ክልል ነፍሰ ጡርና የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ህጻናት በጦርነቱ ሳቢያ ክፉኛ መጎዳታቸውን ማረጋገጡን የፓዝ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር ትርሲት ግርሻው ተናግረዋል። በአካባቢዎቹ የተደረገው ጦርነት በበርካታ ህጻናትና እናቶች ላይ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ማድረሱን የጠቆሙት ዳይሬክተሯ፤ መርሃ ግብሩ ከሰሜን ወሎ ዞን ግዳንና ራያ ቆቦ ወረዳዎች፣ ከደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ፣ ከዋግ ኽምራ ብሄረሰብ ዞን ሰቆጣ ዙሪያና ዳህና ወረዳዎች እንዲሁም ከሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ የሚተገበር መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም 60 ሺህ የሚደርሱ ህጻናትና ከ15 ሺህ በላይ የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶች በቀጥታ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። ከ446 ሺህ በላይ ህዝብ ደግሞ በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።ይህ የቅድመ ልጅነት ዘመን እንክብካቤ መርሃ ግብር 500 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በጀት የተያዘለት ሲሆን፤ የገንዘብ ድጋፉን ያደረገው ቢግ ዊን ፊላንትሮፊ የተባለ ግብረ ሠናይ ድርጅት ነው።
በመሆኑም በአማራ ክልል የከፋ ጉዳት የደረሰባቸው በአራት ዞኖችና ስድስት ወረዳዎች የሚገኙ ህፃናትና እናቶች በዚሁ የክብካቤ በመርሐ ግብር መካተታቸውን ተናግረዋል።የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ጽ/ቤት ቤት ኃላፊ ፍቃዱ ያደታ፤ በኢትዮጵያ 59 በመቶ የሚሆኑ ህፃናት በዕድሜያቸው ልክ መድረስ ከሚገባቸው አካላዊና አዕምሯዊ ዕድገት ያልደረሱ ስለመሆናቸው ገልጸዋል።
ፓዝ ኢትዮጵያ የጀመረው የቅድመ ልጅነት ዘመን፣ የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶች ክብካቤ መርሃ ግብር ውጤታማ እንዲሆን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ መጠቆማቸውን ከደቡብ ወሎ ኮሚዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።በፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ወሎ ዞን ም/ አስተዳዳሪ ተስፋ ዳኛው በበኩላቸው፤ ፓዝ ኢትዮጵያ የቅድመ ልጅነት ዘመን እንክብካቤው ህፃናት በአካላቸው የጠነከሩ በአዕምሯቸው የጎለበቱ ሆነው እንዲያድጉ የሚያስችል በመሆኑ፤ በሚመለከታቸው የመንግስት መዋቅሮች ተገቢው ድጋፍና ክትትል ይደረጋለታል ብለዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ወሎ፣ ሰሜን ሸዋና ዋግ ኽምራ ብሄረሰብ ዞኖች የሚገኙና በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ከ60 ሺህ በላይ ህጻናትን መንከባከብ የሚያስችል ፕሮጀክት በደሴ ከተማ ይፋ ተደርጓል።ፕሮጀክቱ የአንድ ዓመት መርሃ ግብር ሲሆን፤ በአራቱ ዞኖች ውስጥ በሚገኙ ስድስት ወረዳዎች ላይ ይተገበራል ተብሏል።
ፓዝ ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጦርነት በተካሄደባቸው አካባቢዎች ባደረገው የዳሰሳ ጥናት በአማራ ክልል ነፍሰ ጡርና የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ህጻናት በጦርነቱ ሳቢያ ክፉኛ መጎዳታቸውን ማረጋገጡን የፓዝ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር ትርሲት ግርሻው ተናግረዋል። በአካባቢዎቹ የተደረገው ጦርነት በበርካታ ህጻናትና እናቶች ላይ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ማድረሱን የጠቆሙት ዳይሬክተሯ፤ መርሃ ግብሩ ከሰሜን ወሎ ዞን ግዳንና ራያ ቆቦ ወረዳዎች፣ ከደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ፣ ከዋግ ኽምራ ብሄረሰብ ዞን ሰቆጣ ዙሪያና ዳህና ወረዳዎች እንዲሁም ከሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ የሚተገበር መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም 60 ሺህ የሚደርሱ ህጻናትና ከ15 ሺህ በላይ የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶች በቀጥታ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። ከ446 ሺህ በላይ ህዝብ ደግሞ በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።ይህ የቅድመ ልጅነት ዘመን እንክብካቤ መርሃ ግብር 500 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በጀት የተያዘለት ሲሆን፤ የገንዘብ ድጋፉን ያደረገው ቢግ ዊን ፊላንትሮፊ የተባለ ግብረ ሠናይ ድርጅት ነው።
በመሆኑም በአማራ ክልል የከፋ ጉዳት የደረሰባቸው በአራት ዞኖችና ስድስት ወረዳዎች የሚገኙ ህፃናትና እናቶች በዚሁ የክብካቤ በመርሐ ግብር መካተታቸውን ተናግረዋል።የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ጽ/ቤት ቤት ኃላፊ ፍቃዱ ያደታ፤ በኢትዮጵያ 59 በመቶ የሚሆኑ ህፃናት በዕድሜያቸው ልክ መድረስ ከሚገባቸው አካላዊና አዕምሯዊ ዕድገት ያልደረሱ ስለመሆናቸው ገልጸዋል።
ፓዝ ኢትዮጵያ የጀመረው የቅድመ ልጅነት ዘመን፣ የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶች ክብካቤ መርሃ ግብር ውጤታማ እንዲሆን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ መጠቆማቸውን ከደቡብ ወሎ ኮሚዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።በፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ወሎ ዞን ም/ አስተዳዳሪ ተስፋ ዳኛው በበኩላቸው፤ ፓዝ ኢትዮጵያ የቅድመ ልጅነት ዘመን እንክብካቤው ህፃናት በአካላቸው የጠነከሩ በአዕምሯቸው የጎለበቱ ሆነው እንዲያድጉ የሚያስችል በመሆኑ፤ በሚመለከታቸው የመንግስት መዋቅሮች ተገቢው ድጋፍና ክትትል ይደረጋለታል ብለዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
👍1
#AmharaRegion
በጦርነት ምክንያት በአማራ ክልል ፤ ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ባለው እጅግ የከፋ ችግር በርካታ ህፃት እና እናቶች ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል፤ ይሄ በተደጋጋሚ ተገልጿል።
በችግር ላይ ላሉት ወገኖች ድጋፍ እየተደረገ ቢሆንም ካለው የከፋ ሁኔታ አንፃር ምንም ነው።
የአማራ ክልል ሴቶች፣ ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ለሴቶች እና ሕጻናት 3 ሚሊዮን ብር የሚገመት የአይነት እና ለ300 እናቶች ደግሞ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አሚኮ ዘግቧል።
እንዲሁም በክልሉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እስካሁን 200 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ቢያደርጉም ከተከሰተው ችግር ስፋት ጋር የሚጣጣም ሆኖ አልተገኘም።
ችግሩንም መፍታት አልተቻለም።
መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ፣ ባለሃብቶች በችግር ላይ ለወደቁ ወገኖች አሁንም ድጋፋቸው አጠናክሮ እንዲቀጥሉ እና ሕጻናትን እና እናቶችን መታደግ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
ፎቶ ፦ አሚኮ
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
በጦርነት ምክንያት በአማራ ክልል ፤ ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ባለው እጅግ የከፋ ችግር በርካታ ህፃት እና እናቶች ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል፤ ይሄ በተደጋጋሚ ተገልጿል።
በችግር ላይ ላሉት ወገኖች ድጋፍ እየተደረገ ቢሆንም ካለው የከፋ ሁኔታ አንፃር ምንም ነው።
የአማራ ክልል ሴቶች፣ ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ለሴቶች እና ሕጻናት 3 ሚሊዮን ብር የሚገመት የአይነት እና ለ300 እናቶች ደግሞ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አሚኮ ዘግቧል።
እንዲሁም በክልሉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እስካሁን 200 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ቢያደርጉም ከተከሰተው ችግር ስፋት ጋር የሚጣጣም ሆኖ አልተገኘም።
ችግሩንም መፍታት አልተቻለም።
መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ፣ ባለሃብቶች በችግር ላይ ለወደቁ ወገኖች አሁንም ድጋፋቸው አጠናክሮ እንዲቀጥሉ እና ሕጻናትን እና እናቶችን መታደግ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
ፎቶ ፦ አሚኮ
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
👍2
"ከኦነግ ጋር በጥምረት ሆነን ወደ ምርጫ ልንገባ ስንል የውላችንን ወረቀት ቀደው እስር ቤት ወረወሩን፣ብልፅግና ኡሁንም እንደ ህወሃት ሊከፋፍለን እየሞከረ ነው፣ይህ ለህወሃትም አላዋጣትም"
ጀዋር መሀመድ በኦፌኮ ጠ/ጉባኤ ላይ ከተናገረው የተወሰደ
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
ጀዋር መሀመድ በኦፌኮ ጠ/ጉባኤ ላይ ከተናገረው የተወሰደ
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
ከፍተኛ ስርቆት በመዲናችን አዲስ አበባ ተፈጽሟል!
🔰ስርቆቱ የተፈጸመው የፌደራል ፖሊስ በለበሱ ሰዎች ነው ተብሏል
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ጎሮ ሰፈራ ልዩ ቦታው ፖስታ ቤት መቲ ጋራዥ አካባቢ በቀን 11፣ 2014 ዓ.ም የቻይና ነጋዴዎች ተከራይተው ይሰሩበት የነበረው መጋዘን ላይ ከፍተኛ ስርቆት የተፈጸመው፡፡
በዚህ ስርቆት 418 ያህል ቴሌቪዥኖች የተሰረቁ ሲሆን ቁጥራቸው የማይታወቅ ላፕቶፕ ኮምፒተሮች የመኪና ባትሪዎች እንደዚሁም 63ሺህ ጥሬ ገንዘብ አብሮ መሰረቁን ነው ኢትዮ ኤፍ ኤም ያገኝው መረጃ የሚጠቁመው፡፡
እነዚህ ነጋዴዎች መጋዘኑን የተከራዩት ከአንድ ወር በፊት የነበረ ሲሆን ከቻይና በርካታ እቃዎችን እያስመጡ ለነጋዴዎች ያከፋፍሉበታል የነበረ መጋዘን ነው፡፡
አቶ መኮንን ድርጊቱን ያቀነባበሩት የጥበቃ ሰራተኞች ሳይሆኑ እንዳልቀሩ ያላቸውን ግምት ያስቀመጡ ሲሆን አሁን ላይ እነዚህ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል በለዋል፡፡
ቃላቸውን ለፖሊስ የሰጡት የጥበቃ ሰራተኞች በበኩላቸው ስርቆቱ የተፈጸመው የፌደራል ፖሊስ በለበሱ ሰዎች ነው ያሉት አቶ መኮነን ፣ከድርጊቱ መፈጸም በላይ የጸጥታ አካላት የሰጡት ምላሽ እንዳሳዘናቸው ነግረውናል፡፡
የቤት አከራዩ አቶ መኮንን ስርቆቱ በተፈጸመበት እለት መብራት ጠፍቶ እንደነበረ እና የአይሱዚ መኪና መጋዘን ውስጥ ገብቶ መጫኑን በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ጥቆማቸውን እንዳደረሱዋቸው ነግረውናል፡፡
via ፦ Ethio fm
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
🔰ስርቆቱ የተፈጸመው የፌደራል ፖሊስ በለበሱ ሰዎች ነው ተብሏል
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ጎሮ ሰፈራ ልዩ ቦታው ፖስታ ቤት መቲ ጋራዥ አካባቢ በቀን 11፣ 2014 ዓ.ም የቻይና ነጋዴዎች ተከራይተው ይሰሩበት የነበረው መጋዘን ላይ ከፍተኛ ስርቆት የተፈጸመው፡፡
በዚህ ስርቆት 418 ያህል ቴሌቪዥኖች የተሰረቁ ሲሆን ቁጥራቸው የማይታወቅ ላፕቶፕ ኮምፒተሮች የመኪና ባትሪዎች እንደዚሁም 63ሺህ ጥሬ ገንዘብ አብሮ መሰረቁን ነው ኢትዮ ኤፍ ኤም ያገኝው መረጃ የሚጠቁመው፡፡
እነዚህ ነጋዴዎች መጋዘኑን የተከራዩት ከአንድ ወር በፊት የነበረ ሲሆን ከቻይና በርካታ እቃዎችን እያስመጡ ለነጋዴዎች ያከፋፍሉበታል የነበረ መጋዘን ነው፡፡
አቶ መኮንን ድርጊቱን ያቀነባበሩት የጥበቃ ሰራተኞች ሳይሆኑ እንዳልቀሩ ያላቸውን ግምት ያስቀመጡ ሲሆን አሁን ላይ እነዚህ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል በለዋል፡፡
ቃላቸውን ለፖሊስ የሰጡት የጥበቃ ሰራተኞች በበኩላቸው ስርቆቱ የተፈጸመው የፌደራል ፖሊስ በለበሱ ሰዎች ነው ያሉት አቶ መኮነን ፣ከድርጊቱ መፈጸም በላይ የጸጥታ አካላት የሰጡት ምላሽ እንዳሳዘናቸው ነግረውናል፡፡
የቤት አከራዩ አቶ መኮንን ስርቆቱ በተፈጸመበት እለት መብራት ጠፍቶ እንደነበረ እና የአይሱዚ መኪና መጋዘን ውስጥ ገብቶ መጫኑን በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ጥቆማቸውን እንዳደረሱዋቸው ነግረውናል፡፡
via ፦ Ethio fm
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
በሳምንቱ መጨረሻ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተገለጸ!!
በአዲስ አበባ በሁለት ቀናት ውስጥ በተከሰቱ የእሳት አደጋዎች በንበረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ እሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግሯል፡፡
አንደኛው የእሳት አደጋ የደረሰው በኦሮምያ ልዪ ዞን አሸዋ ሜዳ በንግድ ሱቆች ላይ የደረሰው ነው ተብሏል፡፡
የእሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግኑኝነት አቶ ንጋቱ ማሞ እንደነገሩን ሌላኛው የእሳት አደጋ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት አወልያ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር በአንድ መኖርያ ቤት ላይ የተከሰተው የእሳት አደጋ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሶስተኛው የእሳት አደጋ የተከሰተው ደግሞ በትላንትናው እለት በኦሮሚያ ልዩ ዞን አሸዋ ሜዳ በተመሳሳይ በንግድ ሱቆች ላይ የደረሰው የእሳት አደጋ ሲሆን በነዚህ አደጋዎች ምክንያትም ከ2ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ሙሉ በሙሉ ወድሟል ብለውናል፡፡
አደጋዎቹን ለመቆጣጠር 40ሺህ ሊትር ውሀ አገልግሎት ላይ መዋሉንም አቶ ንጋቱ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
በአዲስ አበባ በሁለት ቀናት ውስጥ በተከሰቱ የእሳት አደጋዎች በንበረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ እሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግሯል፡፡
አንደኛው የእሳት አደጋ የደረሰው በኦሮምያ ልዪ ዞን አሸዋ ሜዳ በንግድ ሱቆች ላይ የደረሰው ነው ተብሏል፡፡
የእሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግኑኝነት አቶ ንጋቱ ማሞ እንደነገሩን ሌላኛው የእሳት አደጋ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት አወልያ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር በአንድ መኖርያ ቤት ላይ የተከሰተው የእሳት አደጋ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሶስተኛው የእሳት አደጋ የተከሰተው ደግሞ በትላንትናው እለት በኦሮሚያ ልዩ ዞን አሸዋ ሜዳ በተመሳሳይ በንግድ ሱቆች ላይ የደረሰው የእሳት አደጋ ሲሆን በነዚህ አደጋዎች ምክንያትም ከ2ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ሙሉ በሙሉ ወድሟል ብለውናል፡፡
አደጋዎቹን ለመቆጣጠር 40ሺህ ሊትር ውሀ አገልግሎት ላይ መዋሉንም አቶ ንጋቱ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
ፕሬዚዳንት ኤርዶኻን እና ቭላድሚር ፑቲን ቀጣዩን የሩሲያ-ዩክሬን ድርድር በቱርክ ለማካሄድ ተስማሙ!!
የቱርክ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ ሁለቱ መሪዎች እሁድ እለት የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን እና ስለ ሩሲያ – ዩክሬን ግጭት ወቅታዊ ሁኔታ እና የድርድር ሂደት መወያየታቸውን አስታውቋል፡፡
በውይይታቸውም ቀጣዩ የሩሲያ እና የዩክሬን የድርድር ሂደት በቱርክ ኢስታምቡል እንዲካሄድ ስምምነት ላይ መድረሳቸውም ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም ፕሬዚዳንት ኤርዶኻን ለሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን፥ ቱርክ በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል የተኩስ አቁም እና የሰላም ስምምነት እንዲደረግ እና በአካባቢው ያለው የሰብአዊ ሁኔታ መሻሻል እንዳለበት ገልጸውላቸዋል።
የዩክሬን ተደራዳሪ ልዑካን ቡድን አባል የሆኑት ዴቪድ አራካሚያ ቀጣዩ ዙር የዩክሬን እና የሩሲያ የሰላም ድርድር በሚቀጥለው ሳምንት በቱርክ እንደሚካሄድ ግለጻቸውን ሺንዋ በዘገባው አስነብቧል፡፡
የሩሲያ ተደራራደሪ ቡድን መሪ ቭላድሚር ሜዲንስኪ በበኩላቸው የፊት ለፊት ድርድሩ በቀጣይ ሳምንት እንደሚደረግ መናገራቸው ተሰምቷል፡፡
የዩክሬን እና የሩሲያ ልዑካን ከየካቲት 28 ጀምሮ በቤላሩስ ሶስት ዙር የሰላም ድርድር ያደረጉ ሲሆን አራተኛውን የሰላም ድርድር ደግሞ በቪዲዮ ኮንፈረንስ አካሄደዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
የቱርክ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ ሁለቱ መሪዎች እሁድ እለት የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን እና ስለ ሩሲያ – ዩክሬን ግጭት ወቅታዊ ሁኔታ እና የድርድር ሂደት መወያየታቸውን አስታውቋል፡፡
በውይይታቸውም ቀጣዩ የሩሲያ እና የዩክሬን የድርድር ሂደት በቱርክ ኢስታምቡል እንዲካሄድ ስምምነት ላይ መድረሳቸውም ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም ፕሬዚዳንት ኤርዶኻን ለሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን፥ ቱርክ በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል የተኩስ አቁም እና የሰላም ስምምነት እንዲደረግ እና በአካባቢው ያለው የሰብአዊ ሁኔታ መሻሻል እንዳለበት ገልጸውላቸዋል።
የዩክሬን ተደራዳሪ ልዑካን ቡድን አባል የሆኑት ዴቪድ አራካሚያ ቀጣዩ ዙር የዩክሬን እና የሩሲያ የሰላም ድርድር በሚቀጥለው ሳምንት በቱርክ እንደሚካሄድ ግለጻቸውን ሺንዋ በዘገባው አስነብቧል፡፡
የሩሲያ ተደራራደሪ ቡድን መሪ ቭላድሚር ሜዲንስኪ በበኩላቸው የፊት ለፊት ድርድሩ በቀጣይ ሳምንት እንደሚደረግ መናገራቸው ተሰምቷል፡፡
የዩክሬን እና የሩሲያ ልዑካን ከየካቲት 28 ጀምሮ በቤላሩስ ሶስት ዙር የሰላም ድርድር ያደረጉ ሲሆን አራተኛውን የሰላም ድርድር ደግሞ በቪዲዮ ኮንፈረንስ አካሄደዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
በኤሌክትሪክ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት በጭስ አባይና አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋረጠ!
ከባህር ዳር ወደ ጭስ አባይ በሚሄደው 15 kV የኤሌክትሪክ አስተላለፊ መስመር በተለምዶ ቆሸ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 3 የእንጨት ምሰሶዎች በመጋዝ ቆርጦ በመጣል 720 ሜትር ባለ 95 ሚ.ሜ አልሙኒየም ሽቦ በሌቦች መሰረቁን የባህር ዳር ዲስትሪክት ኦፐሬሽን ስራአስኪጅ አቶ ውባለ አብጤ ገልፀዋል፡፡
በተፈፀመው ስርቆት ምክንያት በጭስ አባይ፣ሰባት አሚት ፣አንዳሳ እና በአካባቢው ባሉ ከተሞች ከ 18/7/2014 ዓ.ም ሌሊት 7፡40 ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል፡፡
ይህ መጋቢ መስመር ከላይ ከተገለፁት ከተሞች በተጨማሪ ለጥበበ ጊዮን ሪፈራል ሆስፒታል እና ለባህርዳር ማረሚያ ቤት ኤሌክትሪክ የሚሰጥ ሲሆን ሆስፒታሉና ማረሚያ ቤቱ ዛሬ በ19/7/2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡30 ጀምሮ ጊዜያዊ መፍትሄ በመስጠት ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡
የባህር ዳር ዲስትሪክት ሰራተኞች አገልግሎቱን ወደ ነበረበት ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ መሆናቸውንና ፤ ጉዳዩን የባህር ዳር ከተማ 9ኛ ፖሊስ ጣቢያ እየተከታተለውና አጥፊዎቹን ለመያዝ ጥረት እያደረገ መሆኑን የባህርዳር ዲስትሪክት ኦፐሬሽን ስራአስኪጅ አቶ ውባለ አብጤ ገልፀዋል፡፡
የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባበሰ ጥቷል።
በመሆኑም ህብረተሰቡ እና በየደረጃው የሚገኝ የፀጥታ አካል ጉዳዩን በትኩረት በመመልከት በአካባቢው ለተዘረጉ የኤሌክትሪክ አውታሮች ጥበቃ እንዲያደርግና አጠራጣሪ ጉዳዮችንም ሲመለከት ለሚመለከታቸው የፀጥታ አካላትና ለተቋማችን ጥቆማ እንዲሰጥ እንጠይቃለን፡፡
የአማራ ኤሌክትሪክ ኃይል
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
ከባህር ዳር ወደ ጭስ አባይ በሚሄደው 15 kV የኤሌክትሪክ አስተላለፊ መስመር በተለምዶ ቆሸ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 3 የእንጨት ምሰሶዎች በመጋዝ ቆርጦ በመጣል 720 ሜትር ባለ 95 ሚ.ሜ አልሙኒየም ሽቦ በሌቦች መሰረቁን የባህር ዳር ዲስትሪክት ኦፐሬሽን ስራአስኪጅ አቶ ውባለ አብጤ ገልፀዋል፡፡
በተፈፀመው ስርቆት ምክንያት በጭስ አባይ፣ሰባት አሚት ፣አንዳሳ እና በአካባቢው ባሉ ከተሞች ከ 18/7/2014 ዓ.ም ሌሊት 7፡40 ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል፡፡
ይህ መጋቢ መስመር ከላይ ከተገለፁት ከተሞች በተጨማሪ ለጥበበ ጊዮን ሪፈራል ሆስፒታል እና ለባህርዳር ማረሚያ ቤት ኤሌክትሪክ የሚሰጥ ሲሆን ሆስፒታሉና ማረሚያ ቤቱ ዛሬ በ19/7/2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡30 ጀምሮ ጊዜያዊ መፍትሄ በመስጠት ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡
የባህር ዳር ዲስትሪክት ሰራተኞች አገልግሎቱን ወደ ነበረበት ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ መሆናቸውንና ፤ ጉዳዩን የባህር ዳር ከተማ 9ኛ ፖሊስ ጣቢያ እየተከታተለውና አጥፊዎቹን ለመያዝ ጥረት እያደረገ መሆኑን የባህርዳር ዲስትሪክት ኦፐሬሽን ስራአስኪጅ አቶ ውባለ አብጤ ገልፀዋል፡፡
የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባበሰ ጥቷል።
በመሆኑም ህብረተሰቡ እና በየደረጃው የሚገኝ የፀጥታ አካል ጉዳዩን በትኩረት በመመልከት በአካባቢው ለተዘረጉ የኤሌክትሪክ አውታሮች ጥበቃ እንዲያደርግና አጠራጣሪ ጉዳዮችንም ሲመለከት ለሚመለከታቸው የፀጥታ አካላትና ለተቋማችን ጥቆማ እንዲሰጥ እንጠይቃለን፡፡
የአማራ ኤሌክትሪክ ኃይል
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
👍1
ኢትዮ ሱዳን ድንበር ጦርነት❗❗
ዛሬ ሰባተኛ ቀኑን የያዘው የኢትዮ ሱዳን ድንበር ጦርነት በኢትዮጵያ ጦር በኩል ጥሩ ድሎች እየተገኘ ሲሆን ዛሬ አለው በሚባል አካባቢ ከሶስት በላይ የህወሓት ታጣቂዎች የሰሩት የኮንክሪት ምሽግ በከባድ መሳሪያ ከጥቅም ውጪ ሆኗል ተብሏል። የኢትዮጵያ ሰራዊት በረከትን ለመቆጣጠር በቅርብ ርቀት እንደሚገኝ ታውቋል፣ከ11 በላይ የህወሓት ታጣቂዎችም እጅ ሰጥተዋል። በርካታ መካናይዝድ ጦራቸውም ከጥቅም ውጪ ሆኗል፣በቅርቡ ሙሉ ለሙሉ ለመደምሰስ መንግሥት ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
ዛሬ ሰባተኛ ቀኑን የያዘው የኢትዮ ሱዳን ድንበር ጦርነት በኢትዮጵያ ጦር በኩል ጥሩ ድሎች እየተገኘ ሲሆን ዛሬ አለው በሚባል አካባቢ ከሶስት በላይ የህወሓት ታጣቂዎች የሰሩት የኮንክሪት ምሽግ በከባድ መሳሪያ ከጥቅም ውጪ ሆኗል ተብሏል። የኢትዮጵያ ሰራዊት በረከትን ለመቆጣጠር በቅርብ ርቀት እንደሚገኝ ታውቋል፣ከ11 በላይ የህወሓት ታጣቂዎችም እጅ ሰጥተዋል። በርካታ መካናይዝድ ጦራቸውም ከጥቅም ውጪ ሆኗል፣በቅርቡ ሙሉ ለሙሉ ለመደምሰስ መንግሥት ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
#University_of_Malaya_Scholarships
▪️Host Country - Study in Malaysia
▪️Host University - University of Malaya
▪️Offered By - University Funded
▪️Scholarships Coverage - Fully Funded
▪️Find More Details Here
👇👇👇👇👇
ሌሎች ዛሬ የወጡ ስራዎችን በዚህ ይመለከቱ
👉 New Jobs here https://t.me/ethiosmartjobs
▪️Host Country - Study in Malaysia
▪️Host University - University of Malaya
▪️Offered By - University Funded
▪️Scholarships Coverage - Fully Funded
▪️Find More Details Here
👇👇👇👇👇
ሌሎች ዛሬ የወጡ ስራዎችን በዚህ ይመለከቱ
👉 New Jobs here https://t.me/ethiosmartjobs
👍1
“መንግስት ከታጠቁ ሃይሎች ጋር ድርድር መጀመር አለበት ”የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ)
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ) 2 መደበኛ ጉባዔ ከመጋቢት 17-18 ማካሄዱን ተከትሎ በሀገሪቱና በህዝቡ ያጋጠሙ ፈተናዎች ላይ በመወያየት የፓርቲውን ቀጣይ የትግል መዕራፍ እና እስትራቲጂ አቅጣጫውን አስቀምጧል።
ከ 4 ዓመታተ በፊት የመጣው ለውጥ ሀገራችን ወደአዲስ የሰላም እና ዲሞክራሲ ያሸጋገራል የሚል ተስፋ ቢኖርም የለውጡ ሂደት ተቀልብሶ ወደ ዲሞክራሲ የነበርው ሽግግር እድል ባክኖ የእርስ በርስ ጦርነትና የሀገር መፍረስ አደጋ ተጋርጦብናል ሲል የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ) የመደበኛው ግባዔ መጠናቀቁን ተከትሎ ባውጣው መግለጫ አስታውቋል ።
በቅርቡም የፌደራሉ እና የትግራይ ክልላዊ መንግስት ጦርነትን ለማቆም ያሳለፉት ውሳኔ በፍጥነት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲለውጥ ጥሪውን አስተላልፏል ኦፌኮ።
መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋርም የገባበትን ጦርነት በሰላማዊ መንግድ ለመፍታት ቁርጠኝነቱን ሊያሳይ እንደሚገባም ፓርቲው አሳስቧል።
በሁሉም የአገሪት አካባቢዎች ግጭት እንዲቆም ፤ መንግስት ከታጠቁ ሃይሎች ጋር ድርድር እንዲጀምር እና ብሔራዊ ምክክሩ ላይ እንዲሳትፉ ፤ ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች በተለይም የኦፌኮ እና ኦነግ አባለት ከእስር እንዲፈቱ የሚሉት ጉዳዮዎች ኦፌኮ በአቋም መግልጫው አጽኖት የሰጠባቸው ጉዳዮች ናቸው።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ) 2 መደበኛ ጉባዔ ከመጋቢት 17-18 ማካሄዱን ተከትሎ በሀገሪቱና በህዝቡ ያጋጠሙ ፈተናዎች ላይ በመወያየት የፓርቲውን ቀጣይ የትግል መዕራፍ እና እስትራቲጂ አቅጣጫውን አስቀምጧል።
ከ 4 ዓመታተ በፊት የመጣው ለውጥ ሀገራችን ወደአዲስ የሰላም እና ዲሞክራሲ ያሸጋገራል የሚል ተስፋ ቢኖርም የለውጡ ሂደት ተቀልብሶ ወደ ዲሞክራሲ የነበርው ሽግግር እድል ባክኖ የእርስ በርስ ጦርነትና የሀገር መፍረስ አደጋ ተጋርጦብናል ሲል የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ) የመደበኛው ግባዔ መጠናቀቁን ተከትሎ ባውጣው መግለጫ አስታውቋል ።
በቅርቡም የፌደራሉ እና የትግራይ ክልላዊ መንግስት ጦርነትን ለማቆም ያሳለፉት ውሳኔ በፍጥነት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲለውጥ ጥሪውን አስተላልፏል ኦፌኮ።
መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋርም የገባበትን ጦርነት በሰላማዊ መንግድ ለመፍታት ቁርጠኝነቱን ሊያሳይ እንደሚገባም ፓርቲው አሳስቧል።
በሁሉም የአገሪት አካባቢዎች ግጭት እንዲቆም ፤ መንግስት ከታጠቁ ሃይሎች ጋር ድርድር እንዲጀምር እና ብሔራዊ ምክክሩ ላይ እንዲሳትፉ ፤ ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች በተለይም የኦፌኮ እና ኦነግ አባለት ከእስር እንዲፈቱ የሚሉት ጉዳዮዎች ኦፌኮ በአቋም መግልጫው አጽኖት የሰጠባቸው ጉዳዮች ናቸው።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
👍1
አዲስ አበባ ኑሮ ውድ ከሆነባቸው 15 የአፍሪካ ከተሞች አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች
አዲስ አበባ ከተማ በኑሮ ዉድ ከሆነባቸው 15 የአፍሪካ ሀገራት ከተሞች ዉስጥ ቀዳሚ መሆኗን ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ ዘግቧል።
በጀርመን ሀገር ተቀማጭ የሆነውን ‘ስታቲስታ’ የመረጃ ማዕከል ዋቢ ያደረገው ዘገባ እንደ ምግብ፣ ልብስ፣ ህክምና እና መዝናኛን የመሳሰሉ በከተማዎች የመሰረታዊ ፍላጎቶች አማካይ ዋጋን መሰረት በማድረግ በተዘጋጀ ልኬት አዲስ አበባ በከፍተኛ ደረጃ ኑሮ ውድ የሆነባት ከተማ ሆናለች።
ልኬቱ የኪራይ እና የመያዣ ዋጋዎችን አያጠቃልልም የተባለ ሲሆን እስከ 15ተኛ ባለው ደረጃ ውስጥ ከደቡብ አፍሪካ እና ከሞሮኮ ከእያንዳንዳቸው አራት አራት ከተሞች ተካተዋል።
በደረጃው ሁለት የምዕራብ አፍሪካ ሀገር ከተሞች ብቻ መኖራቸው እና የናይጄሪያ ግዙፏ ከተማ ሌጎስ አለመካተት አስገራሚ ነው ሲል ቢዝነስ ኢንሳይደር አስነብቧል።
በአዲስ አበባ የሸቀጦች ዋጋ ከሌሎች የአህጉሩ ከተሞች አንፃር ውድ ሲሆን የኮት ዲቮሯ አቢጃን፣ ከዚምባብዌ ሀረሬ እንዲሁም የደቡብ አፍሪካዎቹ ጆሀንስበርግ እና ፕሪቶርያ በደረጃዉ ከአንድ እስከ አምስት ተቀምጠዋል። ካሳብላንካ፣ ናይሮቢ እና ራባት ደግሞ ከ15ቱ ከተማዎች የመጨረሻዎቹ ሶስቱ ከተማዎች ሆነዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
አዲስ አበባ ከተማ በኑሮ ዉድ ከሆነባቸው 15 የአፍሪካ ሀገራት ከተሞች ዉስጥ ቀዳሚ መሆኗን ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ ዘግቧል።
በጀርመን ሀገር ተቀማጭ የሆነውን ‘ስታቲስታ’ የመረጃ ማዕከል ዋቢ ያደረገው ዘገባ እንደ ምግብ፣ ልብስ፣ ህክምና እና መዝናኛን የመሳሰሉ በከተማዎች የመሰረታዊ ፍላጎቶች አማካይ ዋጋን መሰረት በማድረግ በተዘጋጀ ልኬት አዲስ አበባ በከፍተኛ ደረጃ ኑሮ ውድ የሆነባት ከተማ ሆናለች።
ልኬቱ የኪራይ እና የመያዣ ዋጋዎችን አያጠቃልልም የተባለ ሲሆን እስከ 15ተኛ ባለው ደረጃ ውስጥ ከደቡብ አፍሪካ እና ከሞሮኮ ከእያንዳንዳቸው አራት አራት ከተሞች ተካተዋል።
በደረጃው ሁለት የምዕራብ አፍሪካ ሀገር ከተሞች ብቻ መኖራቸው እና የናይጄሪያ ግዙፏ ከተማ ሌጎስ አለመካተት አስገራሚ ነው ሲል ቢዝነስ ኢንሳይደር አስነብቧል።
በአዲስ አበባ የሸቀጦች ዋጋ ከሌሎች የአህጉሩ ከተሞች አንፃር ውድ ሲሆን የኮት ዲቮሯ አቢጃን፣ ከዚምባብዌ ሀረሬ እንዲሁም የደቡብ አፍሪካዎቹ ጆሀንስበርግ እና ፕሪቶርያ በደረጃዉ ከአንድ እስከ አምስት ተቀምጠዋል። ካሳብላንካ፣ ናይሮቢ እና ራባት ደግሞ ከ15ቱ ከተማዎች የመጨረሻዎቹ ሶስቱ ከተማዎች ሆነዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
👍3
በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ በክልል ፖሊስ እና ፌደራል ፖሊስ አባላት መካከል በተነሳ ግጭት የአንድ ሰዉ ህይወት አለፈ
በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ ትናንት ምሽት በክልል ፖሊስ እና ፌደራል ፖሊስ አባላት መካከል በተነሳ ግጭት የአንድ ሰዉ ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰዉ ላይ የመቁሰል አደጋ እንደደረሰበት የክልሉ ፕረስ ሰክረታሪያት ጽ/ቤት አስታውቋል።
በግጭቱ ተሳታፊ የነበሩ አካላት ላይ ማጣራት እየተደረገ መሆኑንም ክልሉ አስታውቋል።
ሪፖርተር ተጨማሪ ማጣራት በማድረግ ላይ ሲገኝ ሙሉ መረጃዉ ሲደርስ የምናቀርበዉ ይሆናል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ ትናንት ምሽት በክልል ፖሊስ እና ፌደራል ፖሊስ አባላት መካከል በተነሳ ግጭት የአንድ ሰዉ ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰዉ ላይ የመቁሰል አደጋ እንደደረሰበት የክልሉ ፕረስ ሰክረታሪያት ጽ/ቤት አስታውቋል።
በግጭቱ ተሳታፊ የነበሩ አካላት ላይ ማጣራት እየተደረገ መሆኑንም ክልሉ አስታውቋል።
ሪፖርተር ተጨማሪ ማጣራት በማድረግ ላይ ሲገኝ ሙሉ መረጃዉ ሲደርስ የምናቀርበዉ ይሆናል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
698 የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለዋል
የአዲስ አበባ ፖሊስ በልደታ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማዎች ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ 698 የሞባይል ስልኮችን መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3፣ ወረዳ 4 እና ወረዳ 7 አካባቢ አንዳንድ ሱቆች በስርቆት የሚመጡ የተለያዩ እቃዎችን እንደሚቀበሉ ተደርሶባቸዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
የአዲስ አበባ ፖሊስ በልደታ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማዎች ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ 698 የሞባይል ስልኮችን መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3፣ ወረዳ 4 እና ወረዳ 7 አካባቢ አንዳንድ ሱቆች በስርቆት የሚመጡ የተለያዩ እቃዎችን እንደሚቀበሉ ተደርሶባቸዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
የኢትዮጵያ ኮምንኬሽን ባለሥልጣን ሁለተኛውን የቴሌኮም አገልግሎት ፍቃድ ጨረታ በመጭው መስከረም እንደገና እንደሚጀምር ካፒታል ጋዜጣ ከባለሥልጣኑ መስማቱን ጠቅሶ ዘግቧል። ባለሥልጣኑ ጨረታውን ለማውጣት የሚያስችለውን ቅድመ ጥናት እንዳጠናቀቀ ዘገባው ገልጧል። ባለሥልጣኑ ለሁለተኛው የቴሌኮም አገልግሎት ፍቃድ በተያዘው ዓመት መግቢያ ላይ ጀምሮት የነበረውን የጨረታ ሂደት ባለፈው ታኅሳስ ላልተወሰነ ጊዜ አቋርጫለሁ ማለቱ ይታወሳል።የሁለተኛው ቴሌኮም አገልግሎት ፍቃድ ጨረታ ሂደት የተቋረጠው፣ በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ኩባንያዎች ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት እንደሆነ በወቅቱ ተገልጧል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
👍2
በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎች ከነገ በስቲያ ጀምሮ ወደ አገር ቤት ይመለሳሉ!
በሳዑዲ አረቢያ በእስር ቤት እና በማዕከላት ውሰጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ዜጎችን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ ብሄራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።16 የመንግስት ተቋማትን በአባልነት የያዘው ኮሚቴው ዜጎችን መመለስ ለመጀመር የተደረጉ የመጨረሻ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ዛሬ የገመገመ ሲሆን ከመጪው ረቡዕ ጀምሮ ዜጎችን መመለሱ እንደሚጀምር ይፋ ሆኗል።
በውይይቱ እንደተገለፀው የበረራ፣ የማቆያ ማዕከላት ዝግጅት፣ የመገልገያ ቁሳቁስ፣ የምግብ እና መጠጥ አቅርቦት፣ የአልባሳት፣ የትራንስፖርት እንዲሁም የህክምና አገልግሎትን ለተመላሾች በበቂ ሁኔታ ለማቅረብ በመቻል ረገድ የተደረጉ ዝግጅቶች በግብረ ሃይሉ አባላት ውይይት ተደርጎባቸዋል።የኮሚቴው ሰብሳቢ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እንዳሉት የመመለሱ ተግባር ተመላሽ ዜጎችን ካሉበት አምጥቶ እስከ መኖሪያ ቀያቸው የማድረስ ስራን የሚሸፍን ነው።
ይህንኑ ከመነሻው እስከ መድረሻው በተሳለጠ ቅብብሎሽ ለመፈፀም ተቋማት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አምባሳደር ብርቱካን አሳስበዋል።ተመላሾች አዲስ አበባ ከደረሱ በኋላ ክልሎች ከየማዕከላቱ ቶሎ በማንሳት ወደ መኖሪያቸው መውሰድ ያለባቸው በመሆኑ ያደረጉት ዝግጅትም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
ክልሎቹ ያልተጠናቀቁ የዝግጅት ስራዎችን በቀሪ ቀናት እንዲያጠናቅቁ አሳስበዋል።በየጊዜው የቅበላ አቅምን በማሳደግ ዜጎችን ካሉበት አስቸጋሪ ሁኔታ ለማውጣት መንግሥት የተቻለውን ጥረት ማድረጉን እንደሚቀጥልም አምባሳደሯ ማረጋገጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
https://t.me/ethiopian_reporter
በሳዑዲ አረቢያ በእስር ቤት እና በማዕከላት ውሰጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ዜጎችን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ ብሄራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።16 የመንግስት ተቋማትን በአባልነት የያዘው ኮሚቴው ዜጎችን መመለስ ለመጀመር የተደረጉ የመጨረሻ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ዛሬ የገመገመ ሲሆን ከመጪው ረቡዕ ጀምሮ ዜጎችን መመለሱ እንደሚጀምር ይፋ ሆኗል።
በውይይቱ እንደተገለፀው የበረራ፣ የማቆያ ማዕከላት ዝግጅት፣ የመገልገያ ቁሳቁስ፣ የምግብ እና መጠጥ አቅርቦት፣ የአልባሳት፣ የትራንስፖርት እንዲሁም የህክምና አገልግሎትን ለተመላሾች በበቂ ሁኔታ ለማቅረብ በመቻል ረገድ የተደረጉ ዝግጅቶች በግብረ ሃይሉ አባላት ውይይት ተደርጎባቸዋል።የኮሚቴው ሰብሳቢ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እንዳሉት የመመለሱ ተግባር ተመላሽ ዜጎችን ካሉበት አምጥቶ እስከ መኖሪያ ቀያቸው የማድረስ ስራን የሚሸፍን ነው።
ይህንኑ ከመነሻው እስከ መድረሻው በተሳለጠ ቅብብሎሽ ለመፈፀም ተቋማት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አምባሳደር ብርቱካን አሳስበዋል።ተመላሾች አዲስ አበባ ከደረሱ በኋላ ክልሎች ከየማዕከላቱ ቶሎ በማንሳት ወደ መኖሪያቸው መውሰድ ያለባቸው በመሆኑ ያደረጉት ዝግጅትም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
ክልሎቹ ያልተጠናቀቁ የዝግጅት ስራዎችን በቀሪ ቀናት እንዲያጠናቅቁ አሳስበዋል።በየጊዜው የቅበላ አቅምን በማሳደግ ዜጎችን ካሉበት አስቸጋሪ ሁኔታ ለማውጣት መንግሥት የተቻለውን ጥረት ማድረጉን እንደሚቀጥልም አምባሳደሯ ማረጋገጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
https://t.me/ethiopian_reporter
👍2❤1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
" ወያኔም አልቻለም፤ ብልፅግናም አልቻለም " - አቶ ጃዋር መሀመድ
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ከወራት በፊት ከእስር ከተፈቱ በኃላ በአደባባይ ንግግር ሲየደርጉ/ ሃሳባቸውን ሲገልፁ/ለሚዲያ ቃላቸውን ሲሰጡ አልተስተዋለም።
ባለፉት ቀናት በነበረው የፓርቲያቸው ጉባኤ ላይ ግን ንግግር አድርገዋል።
አቶ ጃዋር በንግግራቸው ሊበታትኗቸው የፈለጉ ኃይሎች ሁሉ ሊሳካላቸው እንዳልቻለ ገልፀዋል።
አቶ ጃዋር መሀመድ " ' ይሄን ካላደረጋችሁ እናፈርሳችኋለን " ይሄን ወያኔም አልቻለም፣ ብልፅግናም አልቻለም። ሊበታትኑን በፍፁም አይችሉም። ኦሮሞን በፍጹም ማስፈራራት አይቻልም በፍጹም " ብለዋል።
"እኔ በራሴ ከኦፌኮ ከወጣክ ይሄን እናደርግልሃለን ፣ ይሄንን ካላደረክ እንደዚህ አናደርግም ብለውኛል " ያሉት አቶ ጃዋር " ሞተን እንገኛለን እንጂ ካመንበት ነገር ወደኋላ አንመለስም " ሲሉ ተደምጠዋል።
አክለው፥ " ብልፅግና ከግማሽ በላይ ኦነግን ወስዶት እንኳን ኦነግን ማፍረስ አልቻለም። ኦነግ ፈርሷል? አልፈረሰም " ሲሉ ገልፀዋል።
አቶ ጃዋር፥ " ከቦረና፣ ከጉጂ የሚነሳውን ቅሬታ እንሰማለን፣ እንመካከራለን፣ እናስተካክላለን " ያሉ ሲሆን " እኔ ያልኩትን ካልወሰዳችሁ አርሲን ከዚህ አወጣለሁ፣ ሸዋን አወጣለሁ፣ ወለጋን ከዚህ አወጣለሁ ካልክ አንተ ነህ የምትወጣው እንጂ ጉጂም አርሲም አይወጡም " ሲሉ ተናግረዋል።
"እኔ OMN በነበርኩበት ሰዓት እንደዚህ አይነት ሙከራዎች ነበሩ " ያሉት አቶ ጃዋር " አንደዚህ ካላደረክ ከሀረርጌ የሚመጣውን ገንዘብ አንቆርጥብሃለን ከወለጋ የሚመጣውን ገንዘብ እንቆርጥብሃለን...ከቆረጣችሁ ትቆርጣላችሁ እንጂ የኦሮሞ አንድነት አይቆረጥም። ከተበታተንን እንበታተናለን እንጂ ወደኋላ አንመለስም" ብለዋል።
@ethiopian_reporter
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ከወራት በፊት ከእስር ከተፈቱ በኃላ በአደባባይ ንግግር ሲየደርጉ/ ሃሳባቸውን ሲገልፁ/ለሚዲያ ቃላቸውን ሲሰጡ አልተስተዋለም።
ባለፉት ቀናት በነበረው የፓርቲያቸው ጉባኤ ላይ ግን ንግግር አድርገዋል።
አቶ ጃዋር በንግግራቸው ሊበታትኗቸው የፈለጉ ኃይሎች ሁሉ ሊሳካላቸው እንዳልቻለ ገልፀዋል።
አቶ ጃዋር መሀመድ " ' ይሄን ካላደረጋችሁ እናፈርሳችኋለን " ይሄን ወያኔም አልቻለም፣ ብልፅግናም አልቻለም። ሊበታትኑን በፍፁም አይችሉም። ኦሮሞን በፍጹም ማስፈራራት አይቻልም በፍጹም " ብለዋል።
"እኔ በራሴ ከኦፌኮ ከወጣክ ይሄን እናደርግልሃለን ፣ ይሄንን ካላደረክ እንደዚህ አናደርግም ብለውኛል " ያሉት አቶ ጃዋር " ሞተን እንገኛለን እንጂ ካመንበት ነገር ወደኋላ አንመለስም " ሲሉ ተደምጠዋል።
አክለው፥ " ብልፅግና ከግማሽ በላይ ኦነግን ወስዶት እንኳን ኦነግን ማፍረስ አልቻለም። ኦነግ ፈርሷል? አልፈረሰም " ሲሉ ገልፀዋል።
አቶ ጃዋር፥ " ከቦረና፣ ከጉጂ የሚነሳውን ቅሬታ እንሰማለን፣ እንመካከራለን፣ እናስተካክላለን " ያሉ ሲሆን " እኔ ያልኩትን ካልወሰዳችሁ አርሲን ከዚህ አወጣለሁ፣ ሸዋን አወጣለሁ፣ ወለጋን ከዚህ አወጣለሁ ካልክ አንተ ነህ የምትወጣው እንጂ ጉጂም አርሲም አይወጡም " ሲሉ ተናግረዋል።
"እኔ OMN በነበርኩበት ሰዓት እንደዚህ አይነት ሙከራዎች ነበሩ " ያሉት አቶ ጃዋር " አንደዚህ ካላደረክ ከሀረርጌ የሚመጣውን ገንዘብ አንቆርጥብሃለን ከወለጋ የሚመጣውን ገንዘብ እንቆርጥብሃለን...ከቆረጣችሁ ትቆርጣላችሁ እንጂ የኦሮሞ አንድነት አይቆረጥም። ከተበታተንን እንበታተናለን እንጂ ወደኋላ አንመለስም" ብለዋል።
@ethiopian_reporter
👍4👎4
የእለተ ሰኞ አጫጭር መረጃዎች በሩሲያ-ዩክሬን ቀዉስ ዙሪያ
🇭🇺በሃንጋሪ የሚኖሩ ዜጎች በቡዳፔስት የዳኑቤ ወንዝ ዳርቻ ላይ 300 ጥንድ ያረጁ ጫማዎችን በማስቀመጠጥ በማሪፑል ቲያትር ላይ በደረሰ የቦምብ ጥቃት ህይወታቸዉ ያለፉ ሰዎችን ዘክረዋል፡፡
🇺🇦በዩክሬን ያለው ጦርነት ከ63 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የመሰረተ ልማት ዉድመት ማድረሱን የኪየቭ ኢኮኖሚክስ ትምህርት ቤት ባወጣው አዲስ መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡ቢያንስ 4,431 የመኖሪያ ሕንፃዎች ፣ 92 ፋብሪካዎች እና መጋዘኖች እና 378 ትምህርት ቤቶች ጋር ዉድመት እንደደረሰባቸዉ ተገልጿል፡፡በተጨማሪም 12 አየር ማረፊያዎች እና ሰባት የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች ዉድመት ከደረሰባቸዉ መካከል ናቸዉ፡፡
🇺🇦የዩክሬን ፕሬዝዳንት ዝለንስኪ በወታደራዊ ጄኔራል ሰራተኞች ካልተገለጸ ወይም ካልተፈቀደ በቀር በወታደሮች እና በወታደራዊ መሳሪያዎች እንቅስቃሴ ላይ ዘገባ መስራት የሚገድብ ህግን ፈርመዋል ።
🇷🇺🇺🇦የሩስያ ወታደሮች ከቼርኖቤል የኒውክሌር ጣቢያ ወጣ ብሎ ከምትገኘዉ ከተማ ለቀው መውጣታቸው ተሰምቷል።ሮይተርስ እንደዘገበው ከንቲባ ዩሪ ፎሚቼቭ ወታደሮቹ “ሊሰሩት ያሰቡትን” ስራ አጠናቀው የስላቭች ከተማን ለቀው መውጣታቸውን ተናግረዋል።የሩሲያ ጦር ቅዳሜ ዕለት የስላቫትቺን ከተማ በመቆጣጠር ከንቲባውን ለአጭር ጊዜ አግተዉ ነበር።
🇺🇦በሰሜን ምዕራብ ዩክሬን በምትገኘው የቮልይን ግዛት በሆነችዉ በሉትስክ ከተማ የነዳጅ ማከማቻ ቦታ ላይ የሚሳኤል ጥቃት መፈጸሙ ተሰማ፡፡የቮልይን ግዛት ገዢ ዩሪ ፖሁሊያይኮ እንደተናገሩት ሚሳኤሉ የተተኮሰው ከቤላሩስ ግዛት እንደሆነ ገልጸዋል።
🇺🇸በኦስካር ከታጩት የዜማ ደራሲ ዳያን ዋረን፣ የባለፈው አመት የኦስካር ምርጥ ረዳት ተዋናይት ዩን ዩህ-ጁንግ እና የ"ሃሎዊን" ኮከብ ጄሚ ሊ ከርቲስ፣ ቤኔዲክት ኩምበርባች እና ጄሰን ሞሞአ ለዩክሬን ያላቸዉን አጋርነት በአካዳሚ አዋርድ ስነስርዓት ላይ አሳይተዋል፡፡
🇺🇸🇷🇺የሩሲያ ፕሬዝዳንት ከስልጣን እንዲለቁ ጥሪ አላደረኩም ሲሉ ባይደን አስተባበሉ፡፡የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ባሳለፍነዉ ቅዳሜ በፖላንድ ዋና ከተማ ዋርሶ ባደረጉት ንግግር ፑቲን "በስልጣን መቆየት አይችሉም" ሲሉ የተናገሩ ሲሆን ሞስኮ በበኩሏ የሩሲያን መሪ የሚመርጡት የሩሲያ ዜጎች ናቸዉ በማለት ክሬምሊን የዋይትሀዉስ አለቃ የአእምሮ ጤና እንዲፈተሸ ጠይቃለች፡፡
🇩🇪ጀርመን የሩስያ ጥቃትን ለመከላከል የጸረ ሚሳኤል መሳሪያ ለመግዛት እያሰበች ነው ሲሉ ቻንስለር ኦላፍ ሾልስ ተናግረዋል ።በርሊን ምን ዓይነት የሚሳኤል መከላከያ መሳሪያ ለመግዛት እንዳሰበች ግን ከመናገር ተቆጥበዋል፡፡
🇺🇦🇷🇺የዩክሬን ወታደራዊ መረጃ አገልግሎት እንዳስታወቀዉ ሩሲያ ዩክሬንን ልክ እንደ ሰሜን እና ደቡብ ኮሪያ ለሁለት ለመከፋፈል እየሞከረች መሆኑን አስጠነቀቀቸ፡፡የሩስያው ፕሬዝዳንት ፑቲን ምስራቃዊ እና ደቡባዊ የዩክሬንን ግዛቶች ከሌላው የሀገሪቱ ክፍል ለመለየት እየሞከሩ ነው ሲሉ የዩክሬን የስለላ ሃላፊ ኪሪሎ ቡዳኖቭ ተናግረዋል፡፡
🇬🇧ሩሲያ ዩክሬንን ከአለም አቀፍ የባህር ላይ ንግድ እየገለለች ነዉ ስትል ብሪታኒያ ተናግራለች፡፡ ዩክሬንን ከጥቁር ባህር ዳርቻ አግዳለች ሲል የብሪታኒያ የመከላከያ ጽህፈት ቤት ባወጣዉ መረጃ አስታዉቋል፡፡
🇹🇷የሩሲያ እና የዩክሬን ተደራዳሪ ቡድኖች በቱርክ ኢስታንቡል ከተማ ለውይይት እንደሚገናኙ የቱርክ እና የሩሲያ ፕሬዝዳንቶች ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ስብሰባው በተያዘዉ ሳምንት የሚካሄድ እንደሆነ ቢነገርም ቀኑ ግን አልተገለጸም፡፡
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
🇭🇺በሃንጋሪ የሚኖሩ ዜጎች በቡዳፔስት የዳኑቤ ወንዝ ዳርቻ ላይ 300 ጥንድ ያረጁ ጫማዎችን በማስቀመጠጥ በማሪፑል ቲያትር ላይ በደረሰ የቦምብ ጥቃት ህይወታቸዉ ያለፉ ሰዎችን ዘክረዋል፡፡
🇺🇦በዩክሬን ያለው ጦርነት ከ63 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የመሰረተ ልማት ዉድመት ማድረሱን የኪየቭ ኢኮኖሚክስ ትምህርት ቤት ባወጣው አዲስ መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡ቢያንስ 4,431 የመኖሪያ ሕንፃዎች ፣ 92 ፋብሪካዎች እና መጋዘኖች እና 378 ትምህርት ቤቶች ጋር ዉድመት እንደደረሰባቸዉ ተገልጿል፡፡በተጨማሪም 12 አየር ማረፊያዎች እና ሰባት የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች ዉድመት ከደረሰባቸዉ መካከል ናቸዉ፡፡
🇺🇦የዩክሬን ፕሬዝዳንት ዝለንስኪ በወታደራዊ ጄኔራል ሰራተኞች ካልተገለጸ ወይም ካልተፈቀደ በቀር በወታደሮች እና በወታደራዊ መሳሪያዎች እንቅስቃሴ ላይ ዘገባ መስራት የሚገድብ ህግን ፈርመዋል ።
🇷🇺🇺🇦የሩስያ ወታደሮች ከቼርኖቤል የኒውክሌር ጣቢያ ወጣ ብሎ ከምትገኘዉ ከተማ ለቀው መውጣታቸው ተሰምቷል።ሮይተርስ እንደዘገበው ከንቲባ ዩሪ ፎሚቼቭ ወታደሮቹ “ሊሰሩት ያሰቡትን” ስራ አጠናቀው የስላቭች ከተማን ለቀው መውጣታቸውን ተናግረዋል።የሩሲያ ጦር ቅዳሜ ዕለት የስላቫትቺን ከተማ በመቆጣጠር ከንቲባውን ለአጭር ጊዜ አግተዉ ነበር።
🇺🇦በሰሜን ምዕራብ ዩክሬን በምትገኘው የቮልይን ግዛት በሆነችዉ በሉትስክ ከተማ የነዳጅ ማከማቻ ቦታ ላይ የሚሳኤል ጥቃት መፈጸሙ ተሰማ፡፡የቮልይን ግዛት ገዢ ዩሪ ፖሁሊያይኮ እንደተናገሩት ሚሳኤሉ የተተኮሰው ከቤላሩስ ግዛት እንደሆነ ገልጸዋል።
🇺🇸በኦስካር ከታጩት የዜማ ደራሲ ዳያን ዋረን፣ የባለፈው አመት የኦስካር ምርጥ ረዳት ተዋናይት ዩን ዩህ-ጁንግ እና የ"ሃሎዊን" ኮከብ ጄሚ ሊ ከርቲስ፣ ቤኔዲክት ኩምበርባች እና ጄሰን ሞሞአ ለዩክሬን ያላቸዉን አጋርነት በአካዳሚ አዋርድ ስነስርዓት ላይ አሳይተዋል፡፡
🇺🇸🇷🇺የሩሲያ ፕሬዝዳንት ከስልጣን እንዲለቁ ጥሪ አላደረኩም ሲሉ ባይደን አስተባበሉ፡፡የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ባሳለፍነዉ ቅዳሜ በፖላንድ ዋና ከተማ ዋርሶ ባደረጉት ንግግር ፑቲን "በስልጣን መቆየት አይችሉም" ሲሉ የተናገሩ ሲሆን ሞስኮ በበኩሏ የሩሲያን መሪ የሚመርጡት የሩሲያ ዜጎች ናቸዉ በማለት ክሬምሊን የዋይትሀዉስ አለቃ የአእምሮ ጤና እንዲፈተሸ ጠይቃለች፡፡
🇩🇪ጀርመን የሩስያ ጥቃትን ለመከላከል የጸረ ሚሳኤል መሳሪያ ለመግዛት እያሰበች ነው ሲሉ ቻንስለር ኦላፍ ሾልስ ተናግረዋል ።በርሊን ምን ዓይነት የሚሳኤል መከላከያ መሳሪያ ለመግዛት እንዳሰበች ግን ከመናገር ተቆጥበዋል፡፡
🇺🇦🇷🇺የዩክሬን ወታደራዊ መረጃ አገልግሎት እንዳስታወቀዉ ሩሲያ ዩክሬንን ልክ እንደ ሰሜን እና ደቡብ ኮሪያ ለሁለት ለመከፋፈል እየሞከረች መሆኑን አስጠነቀቀቸ፡፡የሩስያው ፕሬዝዳንት ፑቲን ምስራቃዊ እና ደቡባዊ የዩክሬንን ግዛቶች ከሌላው የሀገሪቱ ክፍል ለመለየት እየሞከሩ ነው ሲሉ የዩክሬን የስለላ ሃላፊ ኪሪሎ ቡዳኖቭ ተናግረዋል፡፡
🇬🇧ሩሲያ ዩክሬንን ከአለም አቀፍ የባህር ላይ ንግድ እየገለለች ነዉ ስትል ብሪታኒያ ተናግራለች፡፡ ዩክሬንን ከጥቁር ባህር ዳርቻ አግዳለች ሲል የብሪታኒያ የመከላከያ ጽህፈት ቤት ባወጣዉ መረጃ አስታዉቋል፡፡
🇹🇷የሩሲያ እና የዩክሬን ተደራዳሪ ቡድኖች በቱርክ ኢስታንቡል ከተማ ለውይይት እንደሚገናኙ የቱርክ እና የሩሲያ ፕሬዝዳንቶች ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ስብሰባው በተያዘዉ ሳምንት የሚካሄድ እንደሆነ ቢነገርም ቀኑ ግን አልተገለጸም፡፡
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
👍5🔥1😁1
#መረጃ #ትኩረት
ለሽመልስ አብዲሳ ቢሮ ማስፋፊያ ቤታቸው እንዲፈርስ የተደረጉ ሁለት ሰዎች ሞተዋል።
# ለ2 ሰዎች ሞት ምክንያት ሆኗል የሚባለው የሽመልስ አብዲሳ ቢሮ ጉዳይ የነዋሪዎችን ብሶት አባብሷል!
# በከፍተኛ ጥንቃቄ የተቀረፀ ቪዲዮ ይለቀቃል!
/
የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘደንት የሆኑት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ቢሮ ሳቢያ ሁለት ሰዎች መሞታቸውን የአካባቢው ነዋሪ በምሬት ገለፀ፡፡ የባልደራስ አመራር አባላት በአካባቢው ሰሞኑን ባደረገው የመስክ ጉብኝት፣ በርካታ ሰዎች ተሰባስበው ያለውን ሁኔታ አስረድተዋል፡፡
በአካባቢው ቀረፃ ስለማይቻል ሰወር ባለ ቦታ ላይ የተገናኙት የአመራር አባላቱና የአካባቢው ነዋሪዎች ያደረጉት ቆይታ በከፍተኛ ጥንቃቄ በቪዲዮ ተቀርጾ በጥንቃቄ ከአካባቢው እንዲወጣ ተደርጓል፡፡
በሶስት ቀን ውስጥ ቤታቸውን እንዲለቁ የታዘዙት ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት፣ “በድንገት እየመጡ ውጡ ሲሉን ከመካከላችን ሁለት ሰዎች ሞተዋል ” ብለዋል፡፡ ከመካከላቸውም የሐዘን ልብስ የለበሰች እንስት ያለውን ሁኔታ ተናግራ በቪዲዮ ተቀርፃለች፡፡
በነዋሪዎቹ አስተያየት፣ አሁን ለቢሮ ማስፋፊያ የተፈለገው ቦታ በጣም ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ ለተባላለት ዓላማ ብቻ የተፈለገ ነው ለማለት እንደሚቸገሩ ተናግርዋል፡፡ “ ይህ ሁሉ መሬት ለአንድ ቢሮ ብቻ ያስፈልጋል ለማለት ያስቸግራል፡፡ ለምን እንደሆነ ባናውቅም፣ ይዞታቸውን ነው ማስፋፋት የፈለጉት፡፡ በዚህ ሂደት እኛ ደሀዎቹ እየተጨፈለቅን ነው ” ብለዋል፡፡
ስንታየሁ ቸኮል
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
ለሽመልስ አብዲሳ ቢሮ ማስፋፊያ ቤታቸው እንዲፈርስ የተደረጉ ሁለት ሰዎች ሞተዋል።
# ለ2 ሰዎች ሞት ምክንያት ሆኗል የሚባለው የሽመልስ አብዲሳ ቢሮ ጉዳይ የነዋሪዎችን ብሶት አባብሷል!
# በከፍተኛ ጥንቃቄ የተቀረፀ ቪዲዮ ይለቀቃል!
/
የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘደንት የሆኑት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ቢሮ ሳቢያ ሁለት ሰዎች መሞታቸውን የአካባቢው ነዋሪ በምሬት ገለፀ፡፡ የባልደራስ አመራር አባላት በአካባቢው ሰሞኑን ባደረገው የመስክ ጉብኝት፣ በርካታ ሰዎች ተሰባስበው ያለውን ሁኔታ አስረድተዋል፡፡
በአካባቢው ቀረፃ ስለማይቻል ሰወር ባለ ቦታ ላይ የተገናኙት የአመራር አባላቱና የአካባቢው ነዋሪዎች ያደረጉት ቆይታ በከፍተኛ ጥንቃቄ በቪዲዮ ተቀርጾ በጥንቃቄ ከአካባቢው እንዲወጣ ተደርጓል፡፡
በሶስት ቀን ውስጥ ቤታቸውን እንዲለቁ የታዘዙት ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት፣ “በድንገት እየመጡ ውጡ ሲሉን ከመካከላችን ሁለት ሰዎች ሞተዋል ” ብለዋል፡፡ ከመካከላቸውም የሐዘን ልብስ የለበሰች እንስት ያለውን ሁኔታ ተናግራ በቪዲዮ ተቀርፃለች፡፡
በነዋሪዎቹ አስተያየት፣ አሁን ለቢሮ ማስፋፊያ የተፈለገው ቦታ በጣም ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ ለተባላለት ዓላማ ብቻ የተፈለገ ነው ለማለት እንደሚቸገሩ ተናግርዋል፡፡ “ ይህ ሁሉ መሬት ለአንድ ቢሮ ብቻ ያስፈልጋል ለማለት ያስቸግራል፡፡ ለምን እንደሆነ ባናውቅም፣ ይዞታቸውን ነው ማስፋፋት የፈለጉት፡፡ በዚህ ሂደት እኛ ደሀዎቹ እየተጨፈለቅን ነው ” ብለዋል፡፡
ስንታየሁ ቸኮል
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
👍10🤯5
#Update
የኢትዮጵያ መንግስት እርዳታ ወደ' ትግራይ ክልል' እንዲገባ የህወሓት ታጣቂዎች የያዟቸውን የአፋር ክልል አካባቢዎች ለቀው ሊወጡ ይገባል ሲል አስገነዘበ።
መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል መንግስት ግጭት የማቆም ውሳኔ ማሳለፉ ከትግራይ ክልል በኩልም በጎ ምላሽ መሰጠቱ ይታወሳል።
ነገር ግን ውሳኔ ከተላላለፈበት ቀን አንስቶ እስከ ዛሬ ምንም አይነት ሰብዓዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል ሊገባ እንዳልቻለ የክልሉ ባለስልጣናት አሳውቀዋል።
ክልሉን ወክለው ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡት ፕ/ር ክንደያ ገ/ህይወት ፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ወደግጭት ማቆም እንዲደረስ ብዙ ጥረት አድርጓል፤ የባለፈው ሳምንት ስምምነት ዝም ብሎ የመጣ ስምምነት አይደለም ብዙ ጊዜ የተሰራበት ስምምነት ነው ብለዋል።
የሰብዓዊ እርዳታ ወደ ክልሉ ለምን እንዳልገባ የተጠየቁት ፕ/ር ክንደያ ፤ ኃይላቸው በሚቆጣጠራቸው አካባቢዎች የእርዳታ መኪናዎች ስላልደረሱ ማወቅ እንዳልቻሉ ፤ ለምን እንዳልተላኩ መላክና ማሳለፍ የሚገባቸው አካላት ማብራሪ ሊሰጡ ይገባል ብለዋል።
ከባለፈው ሃምሌ ወር በየዕለቱ 100 የሰብዓዊ ድጋፍ የያዙ ተሽከርካሪዎች ወደ ክልሉ መግባት እንደነበረባቸው የሰብአዊ ድጋፍ ሰጪ ተቋማት ይገልፃሉ አሁን ያለው ችግር ሲታይ ፍላጎቱ ጨምሯል ሲሉ አስረድተዋል።
አሁን ያለው ግጭት ለማቆም እና ሰብዓዊ እርዳታ እንዲገባ የሚለው ውሳኔ ካልተሳካ ለረጅም ጊዜ ተዘጋግቶ መጠበቅ ስለማይቻል ሌላ አማራጭ እናያለን ሲሉም ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጠው ቃል ፤ እርዳታ ወደክልሉ እንዲገባ የህወሓት ኃይሎች ከያዟቸው የአፋር ክልል አካባቢዎች ለቀው ሊወጡ ይገባል ብሏል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ፤
" ... እነሱ ግጭት እናቆማለን ብለው አልነበር እንዴ ? ቀደም ብሎ መንግስት የትኛውም አይነት ትንኮሳ እንደማይፈፅም እና የትኛውም አይነት ግጭት ውስጥ እንደማይገባ አስቀምጧል።
በአንፃሩ እነሱ እርዳታው በቀላሉ ወደ ህብረተሰቡ እንዲደርስ በጉልበት ከያዟቸው የአፋር ክልል ወረዳዎች መውጣት አለባቸው ብሎ አስቀምጧል። እስከዛሬ ድረስ ከ5 ወይም 6 ወረዳዎች አልወጡም።
እንደውም ትላንትና 'ኮኖባ' በሚባል ቦታ ከአፋር ሚሊሻ ጋር ጦርነት ነበር።
ለህዝቡ ካሰቡ ከያዙት ቦታ መውጣት እና መንገዱን ክፍት ማድረግ አለባቸው። ይሄን ሳያደርጉ መንግስት ሆን ብሎ ነው የሚለው ትክክል አይደለም "
👉 መጋሌ ፣
👉 ኤሬብቲ ፣
👉 በርሃሌ፣
👉 አብዓላ የተባሉ የአፋር ቦታዎችን የ " ህወሓት ኃይሎች " ተቆጣጥረው እንደሚገኙ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
" ... ይሄ በዋናነት እርዳታው የሚሄድበት የአስፓልት መንገድ ላይ ነው ያለው። ይሄንን መልቀቅ አለባቸው ይሄንን ሳይለቁ ' መንግስት እርዳታ አላቀረበም ' ብለው ቅሬታ ማቅረብ ሚችሉበት ምንም አይነት ሁኔታ የለም። ስለዚህ እርዳታው ወደ ህብረተሰቡ እንዲደርስ ለህብረተሰቡ የሚያስቡ ከሆነ በጉልበት ከያዟቸው አካባቢዎች መልቀቅ ነው ያለባቸው፤ አካባቢውን ከግጭት ነፃ ነው ማድረግ ያለባቸው ። " ሲሉ ዶ/ር ለገሰ ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ ዶ/ር ለገሰ ፤ እርዳታ ለማድረስ ያለውን ዝግጅቱነት በመተመለከተ 3 የነዳጅ እና 20 የእርዳታ እህል የጫኑ 23 መኪናዎች ቆመዋል (ከዚህ በፊት ሄደው በፀጥታ ችግር የተመለሱ) ፤ በተጨማሪ ሰመራ ላይ ከመጋዘን ለመጫን የሚጠባበቁ ትልልቅ ተሽከርካሪዎችም አሉ በአጠቃላይ 43 ተሽከርካሪዎች ናቸው መንገዱ ካልተከፈተ እና ግጭት ካልቆመ እርዳታ ሊሄድ አይችልም ብለዋል።
መንግስት የወሰነው ለሰብዓዊነት ግጭት የማቆም ውሳኔ እስከመቼ እንደሚቆየ የተጠየቁት ሚኒስትሩ ፤ " በመንግስት በኩል የተቀመጠ የጊዜ ገደብ የለም። ህብረተሰቡ ወደ ተለመደው ሰላማዊ ሁኔታ እንዲመጣ ነው መንግስት የሚፈልገው ፤ አካባቢውም ተረጋግቶ መጪውም ክረምት ስለሆነ እርሻውን እንዲያርስ መንግስት የሚፈልገው ከዛ ውጭ የሚደረግ ነገር ካለ እሱን በሂደት ይታያል። " ብለዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
የኢትዮጵያ መንግስት እርዳታ ወደ' ትግራይ ክልል' እንዲገባ የህወሓት ታጣቂዎች የያዟቸውን የአፋር ክልል አካባቢዎች ለቀው ሊወጡ ይገባል ሲል አስገነዘበ።
መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል መንግስት ግጭት የማቆም ውሳኔ ማሳለፉ ከትግራይ ክልል በኩልም በጎ ምላሽ መሰጠቱ ይታወሳል።
ነገር ግን ውሳኔ ከተላላለፈበት ቀን አንስቶ እስከ ዛሬ ምንም አይነት ሰብዓዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል ሊገባ እንዳልቻለ የክልሉ ባለስልጣናት አሳውቀዋል።
ክልሉን ወክለው ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡት ፕ/ር ክንደያ ገ/ህይወት ፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ወደግጭት ማቆም እንዲደረስ ብዙ ጥረት አድርጓል፤ የባለፈው ሳምንት ስምምነት ዝም ብሎ የመጣ ስምምነት አይደለም ብዙ ጊዜ የተሰራበት ስምምነት ነው ብለዋል።
የሰብዓዊ እርዳታ ወደ ክልሉ ለምን እንዳልገባ የተጠየቁት ፕ/ር ክንደያ ፤ ኃይላቸው በሚቆጣጠራቸው አካባቢዎች የእርዳታ መኪናዎች ስላልደረሱ ማወቅ እንዳልቻሉ ፤ ለምን እንዳልተላኩ መላክና ማሳለፍ የሚገባቸው አካላት ማብራሪ ሊሰጡ ይገባል ብለዋል።
ከባለፈው ሃምሌ ወር በየዕለቱ 100 የሰብዓዊ ድጋፍ የያዙ ተሽከርካሪዎች ወደ ክልሉ መግባት እንደነበረባቸው የሰብአዊ ድጋፍ ሰጪ ተቋማት ይገልፃሉ አሁን ያለው ችግር ሲታይ ፍላጎቱ ጨምሯል ሲሉ አስረድተዋል።
አሁን ያለው ግጭት ለማቆም እና ሰብዓዊ እርዳታ እንዲገባ የሚለው ውሳኔ ካልተሳካ ለረጅም ጊዜ ተዘጋግቶ መጠበቅ ስለማይቻል ሌላ አማራጭ እናያለን ሲሉም ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጠው ቃል ፤ እርዳታ ወደክልሉ እንዲገባ የህወሓት ኃይሎች ከያዟቸው የአፋር ክልል አካባቢዎች ለቀው ሊወጡ ይገባል ብሏል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ፤
" ... እነሱ ግጭት እናቆማለን ብለው አልነበር እንዴ ? ቀደም ብሎ መንግስት የትኛውም አይነት ትንኮሳ እንደማይፈፅም እና የትኛውም አይነት ግጭት ውስጥ እንደማይገባ አስቀምጧል።
በአንፃሩ እነሱ እርዳታው በቀላሉ ወደ ህብረተሰቡ እንዲደርስ በጉልበት ከያዟቸው የአፋር ክልል ወረዳዎች መውጣት አለባቸው ብሎ አስቀምጧል። እስከዛሬ ድረስ ከ5 ወይም 6 ወረዳዎች አልወጡም።
እንደውም ትላንትና 'ኮኖባ' በሚባል ቦታ ከአፋር ሚሊሻ ጋር ጦርነት ነበር።
ለህዝቡ ካሰቡ ከያዙት ቦታ መውጣት እና መንገዱን ክፍት ማድረግ አለባቸው። ይሄን ሳያደርጉ መንግስት ሆን ብሎ ነው የሚለው ትክክል አይደለም "
👉 መጋሌ ፣
👉 ኤሬብቲ ፣
👉 በርሃሌ፣
👉 አብዓላ የተባሉ የአፋር ቦታዎችን የ " ህወሓት ኃይሎች " ተቆጣጥረው እንደሚገኙ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
" ... ይሄ በዋናነት እርዳታው የሚሄድበት የአስፓልት መንገድ ላይ ነው ያለው። ይሄንን መልቀቅ አለባቸው ይሄንን ሳይለቁ ' መንግስት እርዳታ አላቀረበም ' ብለው ቅሬታ ማቅረብ ሚችሉበት ምንም አይነት ሁኔታ የለም። ስለዚህ እርዳታው ወደ ህብረተሰቡ እንዲደርስ ለህብረተሰቡ የሚያስቡ ከሆነ በጉልበት ከያዟቸው አካባቢዎች መልቀቅ ነው ያለባቸው፤ አካባቢውን ከግጭት ነፃ ነው ማድረግ ያለባቸው ። " ሲሉ ዶ/ር ለገሰ ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ ዶ/ር ለገሰ ፤ እርዳታ ለማድረስ ያለውን ዝግጅቱነት በመተመለከተ 3 የነዳጅ እና 20 የእርዳታ እህል የጫኑ 23 መኪናዎች ቆመዋል (ከዚህ በፊት ሄደው በፀጥታ ችግር የተመለሱ) ፤ በተጨማሪ ሰመራ ላይ ከመጋዘን ለመጫን የሚጠባበቁ ትልልቅ ተሽከርካሪዎችም አሉ በአጠቃላይ 43 ተሽከርካሪዎች ናቸው መንገዱ ካልተከፈተ እና ግጭት ካልቆመ እርዳታ ሊሄድ አይችልም ብለዋል።
መንግስት የወሰነው ለሰብዓዊነት ግጭት የማቆም ውሳኔ እስከመቼ እንደሚቆየ የተጠየቁት ሚኒስትሩ ፤ " በመንግስት በኩል የተቀመጠ የጊዜ ገደብ የለም። ህብረተሰቡ ወደ ተለመደው ሰላማዊ ሁኔታ እንዲመጣ ነው መንግስት የሚፈልገው ፤ አካባቢውም ተረጋግቶ መጪውም ክረምት ስለሆነ እርሻውን እንዲያርስ መንግስት የሚፈልገው ከዛ ውጭ የሚደረግ ነገር ካለ እሱን በሂደት ይታያል። " ብለዋል።
https://t.me/ethiopian_reporter
https://t.me/ethiopian_reporter
👍9