አዲስ ሪፖርተር - NEWS
36.2K subscribers
17.1K photos
418 videos
21 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት በአሳሳቢ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ‹‹ዎል ስትሪት ጆርናል›› የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘገበ።

በመካከለኛው ምስራቅ ከኢራን ጋር ያለው ግጭት በአውሮፓ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት ክፉኛ እየጎዳው መሆኑ ተገልጿል።

በተለይም የ‹ፓክ-3 ፓትሪዮት› ሚሳኤል መከላከያዎች እና የረዥም ርቀት ሚሳኤሎች ክምችት ከወትሮው በበለጠ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተመላክቷል።

በዚህም ግጭት እስካሁን፦ 1 ሺህ 7 መቶ የፓትሪዮት ሚሳኤል መከላከያዎች፣ 2 መቶ የታድ መከላከያዎች፣ እና 150 የባህር ኃይል ስታንዳርድ ሚሳኤሎች አገልግሎት ላይ ውለዋል።

ይህንኑ እጥረት ለማቃለል ሲባልም፤ በርካታ የታድ ስርዓቶች እና ድሮን ተከላካይ መሣሪያዎች ከአውሮፓ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ተዛውረዋል።

ይህ የመሣሪያዎች እጥረት አሁን በጦርነት እቅድ ዝግጅት ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ፣ የአሜሪካ አውሮፓ እዝ የተግባር እቅዶቹን ማስተካከሉ ተሰምቷል።

ነጩ ቤተ መንግስት እና ፔንታጎን ግን “እጥረት አለ” የሚለውን ዘገባ በመቃወም፣ ያለው ክምችት ለስትራቴጂካዊ አላማዎች በቂ እንደሆነ አስምረው ተናግረዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
5👍5🤯2
አጋቾችንና ዘራፊዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ‼️
በደብረ ብርሃን ከተማ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ የፀጥታ መዋቅር ህገወጥ ተግባራትን በመከታተል አጋቾችንና ዘራፊዎችን ከነ ማስረጃዎቻቸው በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተገለጸ።

ተጠርጣሪዎቹ ከዚህ በፊት አንድ ልጅ በማገት 5 ሚሊዮን ብር የጠየቁ ሲሆን፣ ከልጅ ቤተሰብ ጋር በመደራደር 3 ሚሊዮን ብር መቀበላቸው ታውቋል።

የክፍለ ከተማው የፀጥታ መዋቅር በወቅቱ የተገኘውን መረጃ ተከትሎ ለተወሰነ ጊዜ መረጃ በማሰባሰብና ክትትል በማድረግ ቆይቶ፣ ተጠርጣሪዎቹን ከነ ማስረጃዎቻቸው በቁጥጥር ስር አውሏል።

በእርምጃውም በርካታ የጦር መሳሪያዎች፣ የሞባይል ስልኮች፣የተለያዩ የባንክ አካውንት ደብተሮችና የተለያዩ መጠን ያላቸው ጥሬ ገንዘቦች መያዛቸውን ከከተማው ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
18👍3😢1
#ትኩረት ያሸዋል ተባለ

"አዲስ አበባ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ታወር ፊት ለፊት፣ ከቡናና ሻይ አጠገብ ባለው ዋና መንገድ ላይ የሚገኝ ይህ 'ፖል' የብዙዎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥሏል ነው የተባለው ። 😱

በተለይ በምሽት እይታው ስለሚቀንስ፣ አሽከርካሪዎችም ሆኑ እግረኞች ለማይፈለግ አደጋ እየተጋለጡ ይገኛሉ።

ይህ ፖል ከመንገዱ ተነስቶ ሌላ ምቹ ቦታ ላይ ካልተተከለ የከፋ አደጋ ሊያደርስ ይችላል።

የሚመለከተው አካል አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ እና የአካባቢው ነዋሪዎችም ሆኑ አሽከርካሪዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እናሳስባለን።
⚠️⚠️
ይህ መረጃ ለሚመለከተው አካል እስኪደርስ ሼር በማድረግ ተባበሩ!"

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
19👍6🙏1
የ 46 አመቱ የአንበሳ ባንክ ጥበቃ የ 12 ክፍል ፈተናን 320.25 ዉጤት አመጡ

👉🏼ባንኩ በዉጤቱ ተደስቶ የተለያዩ ስጦታዎችንም አበርክቶላቸዋል


የአንበሳ ባንክ የጥበቃ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ሰይፈ ተስፋዬ ካሕሳይ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማለፊያ ነጥብ ማግኘታቸዉን ዳጉ ጆርናል ከባንኩ ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል።

በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን ሰለዋ ወረዳ ደላ ከተማ በሚገኘው የአንበሳ ባንክ ቅርንጫፍ ላለፉት ሰባት አመታት በጥበቃ ስራ እየሰሩ የሚገኙ አቶ ሰይፈ በ46 አመታቸው የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቅያ ፈተና ተፈትነው 320.25 ነጥብ በማምጣት ወደ ዩንቨርስቲ ማለፋቸውን ባንኩ ማሳወቁን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል።

በዚህም የባንኩ የዳይሬክቶሮች ቦርድ አባላት ፣ ማኔጅመንት እና ሰራተኞች በሙሉ የተሰማቸዉን ደስታ ገልጸዋል።

በዚሁ መሰረት ለአቶ ሰይፈ ተስፋዬ ባንኩ ማበረታቻዎች ለመስጠት ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን አቶ ሰይፈ ተስፋይ ካሕሳይ ወደ ዩንቨርስቲ ለመግባት እና ለመማር የሚያስፈልጋቸው ማንኛውም ወጪ የዩንቨርስቲ ቆይታቸው እስከሚያጠናቅቁ ድረስ ሙሉ ወጪያቸውን ባንኩ እሸፍንላቸዋለሁ ብሏል።

በተጨማሪም አቶ ሰይፈ ወደ ዩንቨርስቲ ከገቡበት ወር ጀምሮ አሁን የሚከፈላቸ ወርሃዊ ደመወዝ ሙሉ በሙሉ በየወሩ ለቤተሰቦቻቸው እንዲከፈል እንደሚደረግም ዳጉ ጆርናል ሰምቷል።

በሌላ በኩል አቶ ሰይፈ ተስፋይ ካሕሳይ የዩንቨርስቲ ትምህርታቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባንኩ በተገቢው የስራ ዘርፍ በመመደብ በቋሚነት ቀጥሮ የሚያሰራቸው ይሆናል ተብሏል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
87👍35🥰5
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የድሮን አሰሳ እና ጥቃት‼️
በራያ አካባቢ በህወሓት ወታደራዊ ቦታዎች ላይ የሚፈፀመው የድሮን ጥቃት እና አሰሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በዛሬው ዕለት በአካባቢው ከፍተኛ የተባለ የድሮን አሰሳ ሲደረግ መዋሉን የአካባቢው ምንጮች ከምስል ጋር ገልፀውልናል። ህወሃት የትራንስ ኢትዮጵያ ተሽከርካሪዎችን በድርቅ ሰበብ ለወታደራዊ አገልግሎት እያዋላቸው መሆኑን፣የአዲግራት እና የአክሱም ዩኒቨርስቲ ሆስፒታሎችን ወታደራዊ የህክምና መስጫ ለማድረግ እንቅስቃሴ ጀምሯል።

Via : አዩዘሀበሻ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
10👍5🕊5
የኢሕአፓ አመራርና አባል ተጨማሪ ምስክር እንዲያቀርቡ ለቀጣይ ሳምንት ሐሙስ ቀጠሮ ተሰጣቸው

ተጠርጣሪዎቹ ተጨማሪ ምስክር እንዲያቀርቡ በማለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለነሐሴ  28 ቀጠሮ መስጠቱን ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ተናገሩ።

በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩት፤ የኢሕአፓ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው  ይስሐቅ ወልዳይ፣ የፓርቲው አባል አበበ አካሉ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ በዛሬው ዕለት  በከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው እንደነበር ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

የከፍተኛ  ፍርድ ቤት ዛሬ ባስቻለው ችሎት ተከሳሾቹ  የፌደራል ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን ማጠናቀቁን እና የቴክኒክና የፎረንሲክ መረጃዎች በቂ ስለሆኑ የፌደራል ፖሊስም መረጃዎችን ወደ ማጠናቀቁ  እንደደረሠ አሰረድቷል።

ነገር ግን ተከሳሾቹ ያቀረቧቸው ምስክሮች በቁጥር ሁለት ብቻ  በመሆናቸው ፍርድ ቤቱ ለመጨረሻ ጊዜ በሚል ለቀጣይ ሳምንት ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ እንደተሠጣቸው ጠበቃ ሰለሞን አስረድተዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
10🤔4👍2
የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ጌታቸው ረዳ፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት በምዕራብ ኢትዮጵያ የድንበር አካባቢዎችንና መንደሮችን በከባድ መሳሪያ በመደብደብ ጉዳት እያደረሠ ይገኛል በማለት ለአልጀዚራ በሠጡት ቃል ከሰሱ።

ጌታቸው፣ የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች ይረዳል በማለት ጭምር መወንጀላቸውን ዜና አውታሩ ማምሻውን ዘግቧል።

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ከኢትዮጵያ ግዛት እየተነሳ በሱዳን ጦር ሠራዊት ላይ ጥቃት ይፈጽማል የሚለውን የሱዳን ባለሥልጣናት ውንጀላ ያስተባበሉት ጌታቸው፣ ኢትዮጵያ የሱዳንን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት እንደምታከብር ተናግረዋል ተብሏል።

ሱዳን ጦሯን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጋር ወደሚዋሠነው ብሉናይል ግዛት ደማዚን ከተማ አካባቢ በብዛት እያንቀሳቀሰች መኾኗንም ዘገባው የሱዳን ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
18🤣8👍2
የውጭ ሀገር መንጃ ፈቃድ ወደ ሀገር ውስጥ ለመቀየር የሚያሥፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች ምንድን ናቸው?
ሙሉ መረጃው ከላይ ተያይዟል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
3👍2
ተሸንፎም ድርጅቶች ለማስታወቂያ በሩን በሰልፍ እያንኳኩለት ያለው ሴዶ ማርሻል::

በቅርቡ በተደረገው የኤምኤምኤ (MMA) ፍልሚያ በመጀመሪያው ዙር በጆኒ የተሸነፈው ሴዶ ማርሻል፣ ከተሸነፈ በኋላ ያየው ነገር ግን ከድል በላይ የሆነ ድንቅ እድል ሆኖለታል!

ብዙ ጊዜ በተዋጊዎች ዓለም ውድድር መሸነፍ ከስፖንሰሮችና ማስታወቂያዎች መራቅን እያመጣ፣

በሴዶ ላይ ግን የሆነው ተአምር ነው! ሴዶ በተሸነፈ ማግስት ብቻ ከ4 በላይ ትልልቅ ማስታወቂያዎችን የሰራ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ድርጅቶች ማስታወቂያቸውን በእሱ ለማስራት በረጅም ተራ እየጠበቁ እንደሚገኙ ተሰምቷል!

"መሸነፍ የውድቀት መጨረሻ ሳይሆን ለአዲስ መንገድ በር ከፋች ነው" የሚሉትን ወገኖች እውነት የሚያስመስለው የሴዶ ማርሻል ነገር፣ አሁን ላይ በማህበራዊ ሚዲያ እና በንግዱ ዓለም ትልቅ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኗል!

እውነትም ኢትዮጵያ ውስጥ ተሸንፎ እንደ ሴዶ ማተርፍ የትም የለም!

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍1511🙉6👀1😡1
ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ያሳየችው የንግድ እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ስምምነቱን በቀዳሚነት ከፈረሙና ካጸደቁ ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን፤ እ.ኤ.አ ጥቅምት 9 ቀን 2025 በይፋ ንግድ መጀመሯ ይታወሳል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር  በማህበራዊ ትስስር ገጹ እንዳጋራው መረጃ ንግዱ በይፋ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስከ ማዝያ ወር 2018 ዓ.ም ድረስ ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ ብቻ ኢትዮጵያ ከሌሎች አባል ሀገራት ጋር ባደረገችው የንግድ ልውውጥ፦ከ14 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ ምርቶችን ወደ ውጭ የላከች ሲሆን፤
ከ8 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚገመቱ ምርቶችን ደግሞ ወደ አገር ውስጥ አስገብታለች።

በወጪ ንግድ የቅባት እህሎች፣ በቆሎና የኬሚካል ምርቶች ተጠቃሽ ናቸው።

የኢትዮጵያ የወጪ ንግድመዳረሻዎችም ከነበሩበት አራት ወደ ሰባት የአፍሪካ ሀገራት (ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ጋና እና አልጄሪያ) ከፍ ማለታቸው ተገልጿል።

በአሁኑ ወቅትም 37 የግል ድርጅቶች በወጪ እና 76 ድርጅቶች በገቢ ንግድ ላይ በንቃት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ ብሏል።

ይህ አህጉራዊ ስኬት ኢትዮጵያ ወደ ዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት ለምታደርገው ጉዞ ትልቅ ተቋማዊና ፖሊሲያዊ ግብዓት የሚፈጥር መሆኑም ተመላክቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪98👍2