አዲስ ሪፖርተር - NEWS
36.2K subscribers
17K photos
416 videos
21 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
የታሪኩ ጋንጋሲ አነጋጋሪ መልእክት

ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ

እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ (ታሪኩ ጋንጋሲ)

በአዲስ አበባ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ታፕ ፋይት ቻምፒዮና (ETFC 002፤ Adwa Fight Night) ዋና ፍልሚያ ጆኒ ጁጁትሱ ሰዶን ማሸነፉን ተከተሎ፣ ታዋቂው ድምፃዊ ታሪቁ ጋንክሲ በማህበራዊ ሚዲያው ያስተላለፈው የትችት መልእክት ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ተመልካቾችን በሳበው በዚህ ውድድር ዙሪያ ድምፃዊው «ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ፣ እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ» የሚል ግጥማዊ ቅሬታ ያቀረበ ሲሆን፣ ይኸውም በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ውስጥ እየተስፋፋ ያለውን የፍትህ ማጣት፣ የጦርነት ስቃይ፣ ተቋማዊ የሌብነትና የዘረፋ ወንጀል እንዲሁም የከፋ የኢኮኖሚ ውደቀት ችላ በማለት ህዝቡ ጥልቅ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ውስጥ እያለ በእንደዚህ አይነት የትግል ትዕይንቶች ላይ ትኩረት ማድረጉን ለመኮነን እንደሆነ ተገልጿል።

ድምፃዊው ይህን ማህበራዊ ተቃርኖ በማንሳት የሰጠው አስተያየት በበርካቶች ዘንድ ድጋፍና የተለያየ ትችት በማስተናገድ በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ ሰፊ አከራካሪ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍5424😢1💯1
የሟቾች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል

በኔፓልና በቻይና ቲቤት በተከሰተ ከባድ ጎርፍ ከ390 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ሲቀጠፍ፥ ከ1ሺ 500 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ሲሉ የአካባቢው ባለሥልጣናት ገልጸዋል።

አደጋው በሂማሊያ አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ውስጥ ከፍተኛ የጭቃና የድንጋይ ናዳ በመውደቁ የተነሳ ሲሆን፣ በአካባቢው ከተሞችና ሸለቆዎች ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ አስከትሏል።

የነፍስ አድን ሰራተኞች ሰዎችን በህይወት ለማትረፍ መረባረባቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል ተብሏል።

የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ቺያንግ በቲቤት የደረሰውን አደጋ በቦታው ተገኝተው ተመልክተዋል።

የኔፓል ቱሪዝም መምሪያ ትላንት ባወጣው መረጃ፣ ከ34 አገራት የመጡ 668 ቱሪስቶች ከረቡዕ ጠዋት ጀምሮ የደረሱበት እንዳልታወቀ ገልጿል።

ከእነዚህም መካከል ቢያንስ 177 ከህንድ፣ 90 ከአሜሪካ፣ 34 ከአውስትራሊያ፣ 33 ከብሪታንያ እና 25 ከካናዳ የመጡ ናቸው ብሏል።

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም በኔፓል ከጠፉት መካከል 100 የቻይና ዜጎች እንደሚገኙበት እወቁልኝ ብሏል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢128👍2
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ – የሚፈልጓቸውን አዳዲስ ዜናዎችን በአጭሩ እና በጥልቀት ከኛ ዘንድ ያንብቡ።

🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።

🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።

አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy

@sputnik_ethiopia
2👍2
በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ‼️
በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ አስከፊ ሆኗል።
ከላይ የሚታየው ምስል ዛሬ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም የተወሰደ ሲሆን የተዘራው ሰብል ሙሉ ለሙሉ እየደረቀ ነው።
ከብቶች በመኖ እጥረት እየሞቱ ይገኛሉ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢19👍32💔1
የደረቀ ውቅያኖስ የለም‼️
“በሱማሊያ በኩል ያለው ቀይ ባህር ደረቀ” የሚለው መረጃ ውሸት ነው‼️
​በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ “በሱማሊያ በኩል ያለው ቀይ ባህር ደረቀ” በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሙሉ በሙሉ አሳሳች እና የሐሰት መረጃ (Fake News / Misleading) እንጂ እውነት አይደለም።

​በጂኦግራፊ፣ በውቅያኖስ ጥናት (Oceanography) እና በአካባቢ ጥበቃ ሳይንሳዊ መረጃዎች መሠረት በቀይ ባህርም ሆነ በአደን ባሕረ ሰላጤ አካባቢ ምንም ዓይነት የውኃ መድረቅ አልተከሰተም።

​◉ ሳይንሳዊ እና ጂኦግራፊያዊ እውነታዎች

​ሱማሊያ ከቀይ ባህር ጋር ድንበር የላትም፦ ሱማሊያ የምትገኘው በህንድ ውቅያኖስ እና በአደን ባሕረ ሰላጤ (Gulf of Aden) ዳርቻ ላይ እንጂ በቀይ ባህር (Red Sea) ወሰን ላይ አይደለም። የቀይ ባህር መውጫ (ባብ ኤል-መንደብ) የሚያበቃው በጅቡቲ እና በየመን የባህር ወሰን ላይ ነው።

​የውኃ መጠኑ አልቀነሰም፦ የቀይ ባህር እና የአደን ባሕረ ሰላጤ ውኃ ከታላቁ ህንድ ውቅያኖስ ጋር የተያያዘ በመሆኑ እንደ ተነጠሉ የቤት ውስጥ ሐይቆች (ለምሳሌ እንደ አራል ባህር) የመድረቅ ዕድል የለውም።

​◉ የተሳሳተው መረጃ ምንጭ እና ሳይንሳዊ ምክንያቶች

​የሞገድ መሸሽ (Low Tide) በጨረቃ እና በፀሐይ የስበት ኃይል ምክንያት በየቀኑ የባህር ውኃ ወደ ኋላ የመሸሽ (Low Tide) ክስተት ያጋጥማል።በዚህ ወቅት የባህሩ ዳርቻ ሰፊ ሆኖ ስለሚታይ፣ አጋጣሚውን በቪዲዮ ቀርፀው "ባህሩ ደረቀ" የሚል አሳሳች መረጃ ያሰራጫሉ።

​የባህር ወለል መስፋፋት (Seafloor Spreading)፦ የአፍሪካ እና የአረቢያ ቴክቶኒክ ፕሌቶች እየተራራቁ በመሆናቸው ቀይ ባህር እና የአደን ባሕረ ሰላጤ በየዓመቱ በጥቂት ሚሊሜትር እየሰፉና እየጠለቁ እንጂ እየደረቁ አይደሉም።

​የባህር ወለል መጨመር (Sea Level Rise)፦በአለም አቀፍ ደረጃ በሚታየው የአየር ንብረት ለውጥ እና የዋልታዎች በረዶ መቅለጥ ምክንያት የባህር ወለል መጠን (Sea level) እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ አይደለም።

​◉ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጩት ምስሎች እና ቪዲዮዎች ላይ የሚታየው እውነተኛ ቦታው የት ነው?

​ትክክለኛ ቦታው ምስሎቹ የሚያሳዩት በህንድ (India) ጉጃራት ግዛት የሚገኘውን አላንግ (Alang Ship Breaking Yard) የተባለውን የዓለማችን ትልቁን አሮጌ መርከቦች ማፍረሻ ቦታ ነው።

​በምስሉ ላይ የሚታዩት መርከቦች ​በግራ በኩል የሚታየው ትልቅ የነዳጅ መጫኛ መርከብ (Tanker) ነው።​በቀኝ በኩል የምትታየው ደግሞ "Marco Polo" የተባለች አርጅታ ለመበጣጠስ የመጣች የሽርሽር መርከብ (Cruise Ship) ናት።​ከበስተጀርባ የሚታዩት መርከቦቹን ለመቁረጥ የተዘጋጁ ክሬኖች (Cranes) እና የመበጣጠሻ መሳሪያዎች ናቸው።

◉ መርከቦቹ ደረቅ መሬት ላይ እንዴት አረፉ?

​መርከቦቹ አሸዋው ላይ ያረፉት ባህር ደርቆ ሳይሆን ሆን ተብሎ በተደረገ ቴክኒካዊ አሰራር (Beaching Process) ነው። ​ውኃው በጣም በሚሞላበት ጊዜ (High Tide) መርከቦቹን በከፍተኛ ፍጥነት ወደ አሸዋማው ዳርቻ ያስጠጉዋቸዋል። ​ውኃው ወደ ኋላ በሚሸሽበት ጊዜ (Low Tide) መርከቦቹ በደረቁ አሸዋ/ጭቃ ላይ ስለሚቀሩ ሰራተኞች በእግራቸው ሄደው ለመቁረጥ ይመችቸዋል።

​በቪዲዮው ላይ የሚታየው ክስተት በህንድ አገር አሮጌ መርከቦችን ለማፍረስ በባህር ውኃ መሸሽ ወቅት (Low tide) የተቀረፀ ተራ የመርከብ ማፍረሻ ቦታ እንጂ የቀይ ባህር መድረቅ አይደለም። መረጃው ሙሉ ለሙሉ ውሸት ነው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
9👍1
የማርሻል አርት አሰልጣኙ ማስተር ሀሰን ሞሚን ከጆኒ ጋር ለመፋለም ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ

በሀገር ውስጥ የኤምኤምኤ (MMA) ስፖርት ዘርፍ አዲስ ውጥረት የሚያነሳስ መረጃ ወጥቷል። የአፋር ክልል ተወላጅ እና የዳካይቶ ሪዩ (Dakayto Ryu) ማርሻል አርት አሰልጣኝ ማስተር ሀሰን ሞሚን፡ በቅርቡ ትልቅ ትኩረት ከሳበው ተፎካካሪ ጆኒ (Johnny) ጋር በሪንግ ውስጥ ለመጋጠም ጥሪ ማቅረባቸው ተሰምቷል።

ማስተር ሀሰን የሀገር በቀል የትግል ስፖርት እና የባህል ማርሻል አርት ጥንካሬን በኦክታጎን ውስጥ ለማሳየት ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የገለፁ ሲሆን፡ አሁን ላይ የግጥሚያው መካሄድ በETFC አዘጋጆች እና በሚመለከታቸው አካላት ውሳኔ ላይ የተመሰረተ ሆኗል።

የሁለቱ ተወዳዳሪዎች የክህሎት ልዩነትና የተለያየ የስፖርት መነሻ የብዙዎችን ትኩረትስቧል።

የስፖርት ቤተሰቡ ግምት፦

• የዳካይቶ ሪዩ አሰልጣኙ ማስተር ሀሰን ሞሚን ያሸንፋሉ?
• ወይንስ የጆኒ የኤምኤምኤ ቴክኒክ የበላይነቱን ይይዛል?
እርስዎ የትኛውን ተወዳዳሪ ይደግፋሉ?

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍3🤪32🤯1
የዉሃ መስመር በመሰበሩ በአንዳንድ አከባቢዎች ላይ የዉሃ አቅርቦት ተቋረጠ

በአዲስ አበባ ከተማ በባለ 800 ሚሊ ሜትር ዲያሜትር ስፋት ያለዉ የዉሃ ግፊት መስጫ መስመር ላይ ስብራት ማጋጠሙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ዉሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታውቋል ።

የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ሰርካለም ጌታቸዉ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸዉ ቆይታ እንደገለፁት ከገላን የጋራ መኖሪያ ቤት አከባቢ የሚገኝ እና በተለምዶ አቃቂ ክፍለ ከተማ 3ሀ ተብሎ ከሚጠራዉ የግፊት መስጫ ጣቢያ ወደ ሀና ማሪያም የግፊት መስጫ ጣቢያ የሚወስደው ባለ 800 ሚሊ ሜትር ከባድ የግፊት መስጫ መስመር ግንባታ በሚገነቡ ባለሀብቶች ምክንያት ተሰብሯል ።

በዚህም የተነሳ ሀና ሰፈራ፣ሀና ማሪያም፣ አዲስ አበባ እና ኦሮሚያ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ ሀና ፉሪ፣ ላፍቶ፣ ጀሞ አንድ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እና አካባቢው እንዲሁም ቫርኔሮ እና ለቡ ሙዚቃ ቤት አካባቢ ውሃ ማሰራጨት እንዳልተቻለ ተገልጿል ።

ባለስልጣኑ መስመሩን ለመጠገን ሙሉ የከባድ መስመር ባለሙያዎችን ማሰማራቱን ገልጿል ። መስመሩን ተጠግኖ ወደ መደበኛ ስርጭት እስኪመለስ ድረስ ደንበኞች በትእግስት እንዲጠባበቁ መልዕክቱን አስተላልፏል ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
3👍2😢1👀1
ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎችን ቅበላ በፍጥነት እንዲያከናውኑ እየተሠራ ነው።

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምልመላና ቅበላ ካከናወኑ በኋላ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም በፍጥነት ጥሪ እንዲያደርጉ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም እንዲጀምር መርሐ ግብር የተያዘ ሲሆን እሱን ለመጠበቅ እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter