አዲስ ሪፖርተር - NEWS
36.2K subscribers
17.1K photos
418 videos
21 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
የምሽቱ ትልቁን ፍልሚያ ጆኒ አሸነፈ

በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ሲካሄድ የሰነበተው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ኮከቦች ምሽት በጉጉት በተጠበቀውና በዋናው የዋንጫ ፍልሚያ (Main Event) በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል!

በሚድል ዌይት (Middleweight MMA Bout) ዘርፍ በጆኒ እና በሴዶ መካከል የተደረገው ይህ አስደናቂና አቃጣጣኝ ፍልሚያ የመላው ተመልካች ቀልብ የሳበ ነበር።

በከፍተኛ የኤምኤምኤ (MMA) ቴክኒክ፣ የላቀ ብቃትና ፍጹም የድል ወኔ ተጋጣሚውን ሴዶን ያሸነፈው ጆኒ፡ የምሽቱን ትልቅ ድል በመቀዳጀት አዲሱ የ ETFC 2 ቻምፒዮን (Champion) በመሆን ዘውዱን ደፍቷል!

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍199🤣7🤪2🎉1🥱1😡1
የገቢዎች ሚኒስቴር የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች የ2018 በጀት ዓመት የሂሳብ ሪፖርት ሲያቀርቡ፣ ለእያንዳንዱ የንግድ ስራ መስክ በተናጠል እና ሁሉንም የንግድ መስኮች ያካተተ የተጠቃለለ ሪፖርት ማቅረብ እንዳለባቸው አውቀው ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳሰበ።

የገቢዎች ሚኒስቴር፣ ከአንድ በላይ የንግድ መስክ ላይ ለተሰማሩ የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች ለእያንዳንዱ የንግድ ዘርፍ የተለየ የሂሳብ መዝገብ መያዝ እንዳለባቸው አውቀው ዝግጅት እንዲያደርጉ ጠይቋል።

ይህ አሰራር ተግባራዊ የሚደረገው በገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 አንቀጽ 86 እና በሠንጠረዥ "ሐ" በተቀመጠው ድንጋጌ መሠረት ነው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍21
የሳይነስ ህመም (Sinusitis) ሲያጋጥም መደረግ እና መደረግ የሌለባቸው ወሳኝ የህክምና ጥንቃቄዎች ይፋ ሆኑ

በአፍንጫ አካባቢ የሚገኙ የአየር ክፍሎች በባክቴሪያ፣ በቫይረስ ወይም በአለርጂ ምክንያት ሲያብጡ እና በፈሳሽ ሲታፈኑ የሚከሰተው አጣዳፊ የሳይነስ ኢንፌክሽን፣ በብዙዎች ዘንድ ከፍተኛ የፊት ምታት እና የእስትንፋስ መዘጋት እንደሚያስከትል የህክምና ባለሙያዎች ይገልጻሉ።

የህመሙን ጽኑነት ለመቀነስ እና ፈጣን መፍትሄ ለማግኘት ህመምተኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ አበይት መመሪያዎች ተዘርዝረዋል።

የሳይነስ ህመምን በፍጥነት ለማስታገስ ውሃ፣ ሞቅ ያሉ የዕፅዋት ሻዮች እና ንጹህ ሾርባዎችን አብዝቶ መጠጣት በአፍንጫ እና በሳይነስ ውስጥ የተከማቸውን ወፍራም ፈሳሽ በማቅጠል አየር መንገዱ እንዲከፈት ያደርጋል።

ከዚህ በተጨማሪ የሞቀ ውሃ እንፋሎት መታጠን ታፍኖ የቆየውን የሳይነስ መስመር በማላላት የፊት እብጠት እና ምታትን በፍጥነት ያቀልላል።

በጨው ውሃ የተዘጋጁ የአፍንጫ ማጽጃዎችን መጠቀም በአፍንጫ ውስጥ የተከማቹ ባክቴሪያዎችን እና አለርጂዎችን አጥቦ ለማስወገድ የሚረዳ ሲሆን፣ ሰውነት በሽታን የመከላከል አቅሙን አጠናክሮ ህመሙን እንዲያሸንፍ በቂ እረፍት እና እንቅልፍ ማግኘት ወሳኝ ነው ተብሏል።

በሌላ በኩል አፍንጫን በኃይል ተጭኖ መያዝ ፈሳሹን እና ባክቴሪያውን ወደ ጥልቅ የሳይነስ ክፍሎች ወይም ወደ ጆሮ አየር መንገድ በመግፋት ተጨማሪ ኢንፌክሽን ስለሚያመጣ ሊወገድ ይገባል ነው የተባለው።

እንደ Otrivin ያሉ የአፍንጫ ማታገሻ ስፕሬዮችን ከ3 እስከ 5 ቀናት በላይ መጠቀም መድኃኒቱ ሲቆም ህመሙ በባሰ ሁኔታ ተመልሶ እንዲመጣ ያደርጋል።

በተጨማሪም ቡና፣ ሻይ እና አልኮል የሰውነትን ፈሳሽ በማዳከም የአፍንጫ ፈሳሽ ይበልጥ እንዲወፍር ስለሚያደርጉ መተው አስፈላጊ መሆኑ ተመላክቷል።

አብዛኞቹ የሳይነስ ህመሞች በቫይረስ ወይም በአለርጂ ምክንያት የሚመጡ በመሆናቸው ያለ ሐኪም ትዕዛዝ አንቲባዮቲክስ መውሰድ ምንም አይነት ውጤት አይኖረውም።

ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ የሚያስፈልገው መቼ ነው?ህመሙ ከ10 ቀናት በላይ ካልተሻለ፣ ከፍተኛ ትኩሳት ከተጨመረበት፣ ወይም በአይን አካባቢ እብጠት እና የእይታ መደብዘዝ ካጋጠመ በአፋጣኝ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
14👍7
ህወሃት ጦርነቱን የሚመራና ውሳኔ የሚሰጥ አስራ አንድ አባላት ያሉት ሴንትራል ኮማንድ ማቋቋሙ ተነገረ።

ይህ ሴንትራል ኮማንድ አቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ከሲቪል አስተዳደር አምስት ከወታደራዊ አመራሮች ደግሞ ስድስት አባላት እንዳሉት የተነገረ ሲሆን የሚመጣውን ጦርነት አመራር ሰጪ ነው ተብሏል።

በተያያዘ የአማራ ሀይሎችም ለቀጣዩ ጦርነት የአደረጃጀት ለውጥ ማድረጋቸው የተዘገበ ሲሆን ይሄም በሌላ የጦርነት ግንባር ቢሆንም ከጥምር ጦሩ ጋር እንደአንድ ሰራዊት ሆነው በጋራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት አደረጃጀት ነው ተብሏል።

ከህወሓት
1) ዶ/ር ደብረፅየን ገ/ሚካኤል
2) ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ሄር (ሞንጀሪኖ)
3) አቶ አማኑኤል አሰፋ
4) ዶ/ር አብርሃም ተኸስተ
5) አቶ ጌታቸው አሰፋ ሲሆኑ

ከወታደራዊ አዛዦች ደግሞ

1) ሌፍተናል ጀነራል ፍስሃ ኪዳኑ(ፍስሃ ማንጁስ)
2) ብርጋዴር ጀነራል ሃ/ስላሴ ግርማይ (ወዲ እምበይተይ)
3) ሜጀር ጀነራል የውሃንስ ወ/ጅወርግስ (ጆን መዲድ)
4) ብርጋዴር ጀነራል ምግበይ ሃይለ(መርዘን) ራሴ ያወጣሁለት ቅፅል ስም ወይም ሳጓ ነው)
5) ሜጀር ጀነራል ብርሃነ ነጋሽ ( ወዲ መድህን)
6) ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ናቸው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍1411😢3🕊1🥱1🤪1😡1
ትናንት ማታ ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም በራያ አላማጣ ከተማ ላይ የህወሓት ታጣቂዎች ከፍተኛ አፈሳ መፈፀማቸው ታውቋል።
ብዛት ያላቸው የወያኔ ወታደሮች አላማጣ ከተማ ከገቡ በኋላ ጭምብል በመልበስ አፈሳ ጀምረዋል ፊታቸውን ጭምብል አጥልቀው በርካታ ወጣቶችን ወስደዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍144😢2
የታሪኩ ጋንጋሲ አነጋጋሪ መልእክት

ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ

እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ (ታሪኩ ጋንጋሲ)

በአዲስ አበባ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ታፕ ፋይት ቻምፒዮና (ETFC 002፤ Adwa Fight Night) ዋና ፍልሚያ ጆኒ ጁጁትሱ ሰዶን ማሸነፉን ተከተሎ፣ ታዋቂው ድምፃዊ ታሪቁ ጋንክሲ በማህበራዊ ሚዲያው ያስተላለፈው የትችት መልእክት ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ተመልካቾችን በሳበው በዚህ ውድድር ዙሪያ ድምፃዊው «ማደሪያ የሌለው ህዝብ - ሲገፋ የኖረ፣ እርግጫ ለማየት - ጎዳና አደረ» የሚል ግጥማዊ ቅሬታ ያቀረበ ሲሆን፣ ይኸውም በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ውስጥ እየተስፋፋ ያለውን የፍትህ ማጣት፣ የጦርነት ስቃይ፣ ተቋማዊ የሌብነትና የዘረፋ ወንጀል እንዲሁም የከፋ የኢኮኖሚ ውደቀት ችላ በማለት ህዝቡ ጥልቅ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ውስጥ እያለ በእንደዚህ አይነት የትግል ትዕይንቶች ላይ ትኩረት ማድረጉን ለመኮነን እንደሆነ ተገልጿል።

ድምፃዊው ይህን ማህበራዊ ተቃርኖ በማንሳት የሰጠው አስተያየት በበርካቶች ዘንድ ድጋፍና የተለያየ ትችት በማስተናገድ በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ ሰፊ አከራካሪ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍5928💯3😢1
የሟቾች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል

በኔፓልና በቻይና ቲቤት በተከሰተ ከባድ ጎርፍ ከ390 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ሲቀጠፍ፥ ከ1ሺ 500 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ሲሉ የአካባቢው ባለሥልጣናት ገልጸዋል።

አደጋው በሂማሊያ አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ውስጥ ከፍተኛ የጭቃና የድንጋይ ናዳ በመውደቁ የተነሳ ሲሆን፣ በአካባቢው ከተሞችና ሸለቆዎች ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ አስከትሏል።

የነፍስ አድን ሰራተኞች ሰዎችን በህይወት ለማትረፍ መረባረባቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል ተብሏል።

የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ቺያንግ በቲቤት የደረሰውን አደጋ በቦታው ተገኝተው ተመልክተዋል።

የኔፓል ቱሪዝም መምሪያ ትላንት ባወጣው መረጃ፣ ከ34 አገራት የመጡ 668 ቱሪስቶች ከረቡዕ ጠዋት ጀምሮ የደረሱበት እንዳልታወቀ ገልጿል።

ከእነዚህም መካከል ቢያንስ 177 ከህንድ፣ 90 ከአሜሪካ፣ 34 ከአውስትራሊያ፣ 33 ከብሪታንያ እና 25 ከካናዳ የመጡ ናቸው ብሏል።

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም በኔፓል ከጠፉት መካከል 100 የቻይና ዜጎች እንደሚገኙበት እወቁልኝ ብሏል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢149👍2
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ – የሚፈልጓቸውን አዳዲስ ዜናዎችን በአጭሩ እና በጥልቀት ከኛ ዘንድ ያንብቡ።

🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።

🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።

አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy

@sputnik_ethiopia
3👍2
በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ‼️
በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ አስከፊ ሆኗል።
ከላይ የሚታየው ምስል ዛሬ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም የተወሰደ ሲሆን የተዘራው ሰብል ሙሉ ለሙሉ እየደረቀ ነው።
ከብቶች በመኖ እጥረት እየሞቱ ይገኛሉ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢28👍32💔2🤯1
የደረቀ ውቅያኖስ የለም‼️
“በሱማሊያ በኩል ያለው ቀይ ባህር ደረቀ” የሚለው መረጃ ውሸት ነው‼️
​በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ “በሱማሊያ በኩል ያለው ቀይ ባህር ደረቀ” በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሙሉ በሙሉ አሳሳች እና የሐሰት መረጃ (Fake News / Misleading) እንጂ እውነት አይደለም።

​በጂኦግራፊ፣ በውቅያኖስ ጥናት (Oceanography) እና በአካባቢ ጥበቃ ሳይንሳዊ መረጃዎች መሠረት በቀይ ባህርም ሆነ በአደን ባሕረ ሰላጤ አካባቢ ምንም ዓይነት የውኃ መድረቅ አልተከሰተም።

​◉ ሳይንሳዊ እና ጂኦግራፊያዊ እውነታዎች

​ሱማሊያ ከቀይ ባህር ጋር ድንበር የላትም፦ ሱማሊያ የምትገኘው በህንድ ውቅያኖስ እና በአደን ባሕረ ሰላጤ (Gulf of Aden) ዳርቻ ላይ እንጂ በቀይ ባህር (Red Sea) ወሰን ላይ አይደለም። የቀይ ባህር መውጫ (ባብ ኤል-መንደብ) የሚያበቃው በጅቡቲ እና በየመን የባህር ወሰን ላይ ነው።

​የውኃ መጠኑ አልቀነሰም፦ የቀይ ባህር እና የአደን ባሕረ ሰላጤ ውኃ ከታላቁ ህንድ ውቅያኖስ ጋር የተያያዘ በመሆኑ እንደ ተነጠሉ የቤት ውስጥ ሐይቆች (ለምሳሌ እንደ አራል ባህር) የመድረቅ ዕድል የለውም።

​◉ የተሳሳተው መረጃ ምንጭ እና ሳይንሳዊ ምክንያቶች

​የሞገድ መሸሽ (Low Tide) በጨረቃ እና በፀሐይ የስበት ኃይል ምክንያት በየቀኑ የባህር ውኃ ወደ ኋላ የመሸሽ (Low Tide) ክስተት ያጋጥማል።በዚህ ወቅት የባህሩ ዳርቻ ሰፊ ሆኖ ስለሚታይ፣ አጋጣሚውን በቪዲዮ ቀርፀው "ባህሩ ደረቀ" የሚል አሳሳች መረጃ ያሰራጫሉ።

​የባህር ወለል መስፋፋት (Seafloor Spreading)፦ የአፍሪካ እና የአረቢያ ቴክቶኒክ ፕሌቶች እየተራራቁ በመሆናቸው ቀይ ባህር እና የአደን ባሕረ ሰላጤ በየዓመቱ በጥቂት ሚሊሜትር እየሰፉና እየጠለቁ እንጂ እየደረቁ አይደሉም።

​የባህር ወለል መጨመር (Sea Level Rise)፦በአለም አቀፍ ደረጃ በሚታየው የአየር ንብረት ለውጥ እና የዋልታዎች በረዶ መቅለጥ ምክንያት የባህር ወለል መጠን (Sea level) እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ አይደለም።

​◉ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጩት ምስሎች እና ቪዲዮዎች ላይ የሚታየው እውነተኛ ቦታው የት ነው?

​ትክክለኛ ቦታው ምስሎቹ የሚያሳዩት በህንድ (India) ጉጃራት ግዛት የሚገኘውን አላንግ (Alang Ship Breaking Yard) የተባለውን የዓለማችን ትልቁን አሮጌ መርከቦች ማፍረሻ ቦታ ነው።

​በምስሉ ላይ የሚታዩት መርከቦች ​በግራ በኩል የሚታየው ትልቅ የነዳጅ መጫኛ መርከብ (Tanker) ነው።​በቀኝ በኩል የምትታየው ደግሞ "Marco Polo" የተባለች አርጅታ ለመበጣጠስ የመጣች የሽርሽር መርከብ (Cruise Ship) ናት።​ከበስተጀርባ የሚታዩት መርከቦቹን ለመቁረጥ የተዘጋጁ ክሬኖች (Cranes) እና የመበጣጠሻ መሳሪያዎች ናቸው።

◉ መርከቦቹ ደረቅ መሬት ላይ እንዴት አረፉ?

​መርከቦቹ አሸዋው ላይ ያረፉት ባህር ደርቆ ሳይሆን ሆን ተብሎ በተደረገ ቴክኒካዊ አሰራር (Beaching Process) ነው። ​ውኃው በጣም በሚሞላበት ጊዜ (High Tide) መርከቦቹን በከፍተኛ ፍጥነት ወደ አሸዋማው ዳርቻ ያስጠጉዋቸዋል። ​ውኃው ወደ ኋላ በሚሸሽበት ጊዜ (Low Tide) መርከቦቹ በደረቁ አሸዋ/ጭቃ ላይ ስለሚቀሩ ሰራተኞች በእግራቸው ሄደው ለመቁረጥ ይመችቸዋል።

​በቪዲዮው ላይ የሚታየው ክስተት በህንድ አገር አሮጌ መርከቦችን ለማፍረስ በባህር ውኃ መሸሽ ወቅት (Low tide) የተቀረፀ ተራ የመርከብ ማፍረሻ ቦታ እንጂ የቀይ ባህር መድረቅ አይደለም። መረጃው ሙሉ ለሙሉ ውሸት ነው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
20👍21
የማርሻል አርት አሰልጣኙ ማስተር ሀሰን ሞሚን ከጆኒ ጋር ለመፋለም ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ

በሀገር ውስጥ የኤምኤምኤ (MMA) ስፖርት ዘርፍ አዲስ ውጥረት የሚያነሳስ መረጃ ወጥቷል። የአፋር ክልል ተወላጅ እና የዳካይቶ ሪዩ (Dakayto Ryu) ማርሻል አርት አሰልጣኝ ማስተር ሀሰን ሞሚን፡ በቅርቡ ትልቅ ትኩረት ከሳበው ተፎካካሪ ጆኒ (Johnny) ጋር በሪንግ ውስጥ ለመጋጠም ጥሪ ማቅረባቸው ተሰምቷል።

ማስተር ሀሰን የሀገር በቀል የትግል ስፖርት እና የባህል ማርሻል አርት ጥንካሬን በኦክታጎን ውስጥ ለማሳየት ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የገለፁ ሲሆን፡ አሁን ላይ የግጥሚያው መካሄድ በETFC አዘጋጆች እና በሚመለከታቸው አካላት ውሳኔ ላይ የተመሰረተ ሆኗል።

የሁለቱ ተወዳዳሪዎች የክህሎት ልዩነትና የተለያየ የስፖርት መነሻ የብዙዎችን ትኩረትስቧል።

የስፖርት ቤተሰቡ ግምት፦

• የዳካይቶ ሪዩ አሰልጣኙ ማስተር ሀሰን ሞሚን ያሸንፋሉ?
• ወይንስ የጆኒ የኤምኤምኤ ቴክኒክ የበላይነቱን ይይዛል?
እርስዎ የትኛውን ተወዳዳሪ ይደግፋሉ?

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪14👍93🤯1
የዉሃ መስመር በመሰበሩ በአንዳንድ አከባቢዎች ላይ የዉሃ አቅርቦት ተቋረጠ

በአዲስ አበባ ከተማ በባለ 800 ሚሊ ሜትር ዲያሜትር ስፋት ያለዉ የዉሃ ግፊት መስጫ መስመር ላይ ስብራት ማጋጠሙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ዉሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታውቋል ።

የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ሰርካለም ጌታቸዉ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸዉ ቆይታ እንደገለፁት ከገላን የጋራ መኖሪያ ቤት አከባቢ የሚገኝ እና በተለምዶ አቃቂ ክፍለ ከተማ 3ሀ ተብሎ ከሚጠራዉ የግፊት መስጫ ጣቢያ ወደ ሀና ማሪያም የግፊት መስጫ ጣቢያ የሚወስደው ባለ 800 ሚሊ ሜትር ከባድ የግፊት መስጫ መስመር ግንባታ በሚገነቡ ባለሀብቶች ምክንያት ተሰብሯል ።

በዚህም የተነሳ ሀና ሰፈራ፣ሀና ማሪያም፣ አዲስ አበባ እና ኦሮሚያ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ ሀና ፉሪ፣ ላፍቶ፣ ጀሞ አንድ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እና አካባቢው እንዲሁም ቫርኔሮ እና ለቡ ሙዚቃ ቤት አካባቢ ውሃ ማሰራጨት እንዳልተቻለ ተገልጿል ።

ባለስልጣኑ መስመሩን ለመጠገን ሙሉ የከባድ መስመር ባለሙያዎችን ማሰማራቱን ገልጿል ። መስመሩን ተጠግኖ ወደ መደበኛ ስርጭት እስኪመለስ ድረስ ደንበኞች በትእግስት እንዲጠባበቁ መልዕክቱን አስተላልፏል ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
9👍2😢2🤣1👀1
ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎችን ቅበላ በፍጥነት እንዲያከናውኑ እየተሠራ ነው።

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምልመላና ቅበላ ካከናወኑ በኋላ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም በፍጥነት ጥሪ እንዲያደርጉ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም እንዲጀምር መርሐ ግብር የተያዘ ሲሆን እሱን ለመጠበቅ እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
4👍4
የደም ግፊት መጠን መጨመር (Hypertension) ሲያጋጥም መደረግ እና መደረግ የሌለባቸው ወሳኝ የህክምና ጥንቃቄዎች ይፋ ሆኑ
 
ደም በደም መላሾች ውስጥ በከፍተኛ ኃይል ሲፈስ የሚከሰተው እና ብዙ ጊዜ ምንም አይነት ግልጽ ምልክት ሳይያሳይ የልብ እና የኩላሊት ህመሞችን የሚያስከትለው የደም ግፊት መጨመር፣ በብዙዎች ዘንድ "ጸጥተኛው ገዳይ" በመባል እንደሚታወቅ የህክምና ባለሙያዎች ይገልጻሉ።
 
የህመሙን ስጋት ለመቀነስ እና የደም ግፊትን በጤናማ ደረጃ ውስጥ ለማቆየት ህመምተኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ አበይት መመሪያዎች ተዘርዝረዋል።
 
የደም ግፊትን በዘላቂነት ለመቆጣጠር በፖታሺየም የበለፀጉ ምግቦችን፣ አትክልትና ፍራፍሬዎችን አብዝቶ መመገብ እና በየቀኑ ቢያንስ ለ30 ደቂቃ ያህል ቀልጣፋ የእግር ጉዞ ወይም ቀላል እንቅስቃሴዎችን ማድረግ የደም መላሾችን በማስፋት ግፊቱን ይቀንሳል።
 
ከዚህ በተጨማሪ በቂ እንቅልፍ ማግኘት፣ ጭንቀትን የሚቀንሱ የአእምሮ እረፍቶችን መውሰድ እና የደም ግፊት መጠንን በቤት ውስጥ በየጊዜው በመለካት መመዝገብ የህክምና ክትትሉን ውጤታማ ያደርገዋል ተብሏል።
 
በሌላ በኩል ጨው እና ከፍተኛ የሶዲየም መጠን ያላቸውን የታሸጉ ምግቦች አብዝቶ መመገብ የሰውነት ፈሳሽ እንዲከማች በማድረግ ግፊቱን በከፍተኛ ሁኔታ ስለሚጨምር ሊወገድ ይገባል ነው የተባለው።
 
ያለ ሐኪም ትዕዛዝ የሚወሰዱ የህመም ማስታገሻዎች (እንደ Ibuprofen እና Diclofenac ያሉ) የደም ግፊትን ይበልጥ ስለሚቀሰቅሱና የኩላሊት ስራን ስለሚጎዱ ያለ አግባብ መጠቀም አይገባም።
 
በተጨማሪም ሲጋራ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣት እና ከመጠን በላይ ቡና ማብዛት የደም መላሾችን በማጥበብ ግፊቱ እንዲያቅበዘብዝ ስለሚያደርጉ መተው አስፈላጊ መሆኑ ተመላክቷል።
 
ከታዘዘ የደም ግፊት መድኃኒት ውጭ የባህላዊ ህክምናዎችን ብቻ አምኖ የመድኃኒት መጠን መቀነስ ወይም ማቋረጥ ለድንገተኛ የልብ ድካም እና የአእምሮ ደም መፈሰስ (Stroke) ያጋልጣል።
 
ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ የሚያስፈልገው መቼ ነው? የደም ግፊት መጠኑ ድንገት ከፍ ብሎ ከጽኑ የራስ ምታት፣ የደረት ህመም፣ የእይታ መደብዘዝ ወይም የመተንፈስ ችግር ጋር ከተያያዘ በአፋጣኝ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል። 

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
10👍9
በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማራቹ  ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተጠንቀቁ ።

በ3 የሻይ ሲኒ  ደረሰኝ  ምክንያት 300 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል።

በአዲሱ የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ደረሰኝ አለመስጠት ንብረትዎን ሊያሳጣዎት ይችላል!

አንድ ሰራተኛዎ ቸልተኛ ሆና 100 ብር ለሚያወጣ 'ሻይ' ደረሰኝ ባትቆርጥ... ቅጣቱ 100 ብር ሳይሆን 100 ሺህ ብር ነው ተብሏል።

ይባስ ብሎ ደግሞ... ሰራተኛዋ ለ3 ደንበኞች ደረሰኝ ካልሰጠች፣ ለድርጅቱ ባለቤት የ300 ሺህ ብር መብረቅ የመሰለ ቅጣት ይወርድበታል።

ይህ ቅጣት ደግሞ በአዋጁ አንቀጽ 125 ንኡስ ቁጥር 2 መሰረት በባለስልጣኑ ሊነሳ ወይም 'ይቅር' ሊባል አይችልም!

መፍትሄው መክፈል ብቻ ነው! ነጋዴዎች ተጠንቀቁ፣ ሰራተኞቻችሁን አስተምሩ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
14👍12😡6😢2🥱2🙉2🤣1👀1