አዲስ ሪፖርተር - NEWS
36.2K subscribers
17K photos
416 videos
21 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
ቻይንኛ ቋንቋን ከመስከረም ጀምሮ በ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለመስጠት ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኝ ተገለጸ

ከቻይና መንግስት ጋር ባለው ግንኙነት መሰረት መስከረም ላይ በሚጀምረው የ2019 ትምህርት ዘመን በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የቻይንኛ ቋንቋ እንዲሰጥ ለማድረግ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

በእነዚህ ትምህርትቤቶች ውስጥ ቻይንኛን የሚያስተምሩ መምህራንን ለማስመጣትም ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል።

በትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ አስራአስፈፃሚ ዶ/ር ዮሀንስ ወጋሶ የአዳሪ ትምህርትቤት ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ያላቸውና በመለያ ፈተና አልፈው የሚገቡ መሆናቸውን አንስተዋል።

እነዚህ ተማሪዎች በአለምአቀፍ ደረጃ ውጤታማና ስኬታማ እንዲሆኑ ለማድረግም የተለያዩ የውጪ ሀገር ቋንቋዎችን እንዲማሩ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

በተለይም ደግሞ ተማሪዎች የከፍተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በውጪ ሀገር የመከታተል እድል ያላቸው በመሆኑ ለዛ እንዲጠቅማቸው የቋንቋ ትምህርቱ እንደሚሰጥ አመላክተዋል።

እንዲማሩ ከሚደረጉት ቋንቋዎች መካከል ደግሞ በቀጣዩ የ2019 የትምህርት ዘመን የቻይንኛ ቋንቋን እንዲማሩ ለማስቻል የዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከቻይንኛ በተጨማሪም ሌሎች አለምአቀፍ ቋንቋዎችን በማጠናከር የማስተማር ስራው እንደሚቀጥል ዶ/ር ዮሀንስ አስታውቀዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍65🥱5👀2🙊2🤔1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"የአንድ መንደር ነዎሪዎች ተጠርገው ሄደዋል!" - ከአደጋው የተረፈ‼️
* በኔፓል የደረሰው የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 160 የደረሰ ሲሆን የበርካታ የውጭ ሀገር ጎብኚዎች ደህንነት አሁንም አሳሳቢ ሆኗል።
በሰሜናዊ ኔፓል ራሱዋ በተባለው የተራራማ አካባቢ እ ኤ አ ኦገስት 26 ቀን 2026 በድንገት በተከሰተ የበረዶ እና የዓለት መደርመስ ምክንያት የተነሳው የጎርፍ አደጋ ከፍተኛ የሰው ሕይወት እና የንብረት ጉዳት አድርሷል።

የኔፓል ፖሊስ እና የቻይና ቲቤት ባለስልጣናት እስካሁን የ160 ሰዎችን አስከሬን ማግኘታቸውን ያረጋገጡ ሲሆን በርካታ አስከሬኖች በጭቃ እና በፍርስራሾች ውስጥ ተቀብረው በመገኘታቸው የሟቾች ቁጥር የበለጠ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጧል።

የኔፓል ቱሪዝም ቦርድ እንደተናገረው በአደጋው ቀጠና 105 የህንድ፣ 54 የአሜሪካ፣ 34 የአውስትራሊያ፣ 33 የእንግሊዝ፣ 24 የካናዳ፣ 19 የማሌዢያ እንዲሁም የሌሎች ሀገራት ዜጎችን ጨምሮ በድምሩ 384 ጎብኚዎች የት እንደገቡ ማወቅ አልተቻለም።

አደጋው በማለዳ ወቅት የተከሰተ በመሆኑ እና የቱሪስት ማረፊያዎች እንዲሁም የኮሚዩኒኬሽን መስመሮች ሙሉ በሙሉ በመውደማቸው ከተጓዦቹ ጋር ግንኙነት ማድረግ አልተቻለም።

ይህንን ተከትሎ የተለያዩ ሀገራት መንግስታት ከፍተኛ ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።

የኔፓል መንግስት አካባቢውን የአደጋ ጊዜ ቀውስ ቀጠና ብሎ ያወጀ ሲሆን የህንድ፣ የአሜሪካ እና የእንግሊዝ መንግስታት ከኔፓል የነፍስ አድን ቡድኖች ጋር በመተባበር የጠፉ ዜጎቻቸውን ለመፈለግ እየሰሩ ነው።
ከእንደዚህ አይነት ድንገተኛ አደጋ ይሰውረን።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢1614👍2
አሜሪካ በትግራይ ጉዳይ ላይ ስምምነት እንዲደረግ ጠየቀች፤ ህወሓት ከአፍሪካ ህብረት ውይይት በፊት ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀመጠ

​በአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ የመቀሌ ጉብኝት ማብቂያ ላይ አሜሪካ በኢትዮጵያ መንግስት እና በትግራይ አመራሮች መካከል እርቅ እንዲወርድ እና ስምምነት ላይ እንዲደረስ ጥሪ አቀረበች።

​በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ እና የአፍሪካ ህብረት የዩኤስ ሚሲዮን ጉዳይ ፈጻሚ ዎልተር ፓርስ በጋራ ባወጡት መግለጫ፣ የኦባሳንጆ ጥረት እንዳበረታታቸው ገልጸው  ውይይቱን እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

አሜሪካ ቀዳሚ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት እና ተፈናቃዮችን ወደ ቀደመ ቀያቸው በሰላም የመመለሱ ሂደት እንደሆነ አስታውቃለች።

​በሌላ በኩል ህወሓት በሰጠው ምላሽ በቅርቡ ከመቀሌው ውይይት ከአዲስ አበባ በኩል የመጣ "አዲስ ሃሳብ ወይም የእድገት ማሳያ የለም" ሲል ገልጿል።

ድርጅቱ ከመደበኛ ድርድር በፊት መፈታት ያለባቸውን በርካታ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጧል።

​ህወሓት ካቀረቧቸው ቅድመ ሁኔታዎች መካከል፡

👉​ወታደራዊ ከበባ እንዲያበቃ እና የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲነሳ፣

👉አከራካሪ ቦታዎች  ነፃ ወጥተው ተፈናቃዮች እንዲመለሱ፣

👉​የህወሓት ህጋዊ እና ፖለቲካዊ ህልውና ሙሉ በሙሉ እንዲመለስ የሚሉ ይገኙበታል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
8👍8
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር ቅጣት ሊጥል ነዉ

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5 ሺ ብር ቅጣት ሊጥል ነዉ የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ከጣቢያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት እየተስተዋለ ያለውን ያልተገባ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪና የመስመር ማሳጠር ችግሮችን ለመቅረፍ የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን አስታውቋል።

ቢሮው የህዝብ ትራንስፖርት ታሪፍን በማጥናትና በማስወሰን ረገድ ትልቅ ሃላፊነት እንዳለበት የገለጹት የቢሮው የስራ ሃላፊ፣ የታሪፍ ተግባራዊነቱንም በቅርበት እየተቆጣጠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍1512🤔1
በሳዑዲ ነሐሴ ላይ ብቻ ቢያንስ 60 ኢትዮጵያውያን ከዕፅ ጋር በተያያዙ ጥፋቶች መያዛቸውን ዘገባዎች አመለከቱ!

ከዕፅ ጋር በተያያዙ ጥፋቶች የሚፈረደቸባው ሰዎችን በሞት እየቀጣች ባለችው ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ፣ በነሐሴ ወር ብቻ ጫትን ጨምሮ የተለያዩ ዕፆችን በማጓጓዝ የተጠረጠሩ ቢያንስ 60 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዘገባዎች አመለከቱ።ትናንት ረቡዕ ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም. ተጨማሪ 15 ኢትዮጵያውያን ከ290 ኪሎ ግራም ጫት ጋር መያዛቸው ተዘግቧል።

የሳዑዲ የድንበር ጥበቃ ጠቅላይ ዳይሬክቶሬት፣ 12ቱ ኢትዮጵያውን በቁጥጥር ስር የዋሉት ጃዛን እና አስሪ በተባሉት ግዛቶች ውስጥ በተካሄዱ ሦስት ዘመቻዎች እንደሆነ 'ሳውዲ ጋዜት' የተባለው አገሪቱ ጋዜጣ ዘግቧል።ሪያድ ግዛት ውስጥ ደግሞ የተከለከለ መድኃኒት ሲያስታዋውቁ ነበሩ የተባሉ ሌሎች ሦስት ኢትዮጵያውን መያዛቸውን የ'አልሪያድ' ዘገባ ያሳያል።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ ሳዑዲ አረቢያ ከዕፅ ጋር በተያያዙ ክሶች ምክንያት በተፈረደባቸው ኢትዮያውያን ላይ ተከታታይ የሞት ቅጣት እየፈጸመች ባለበት ወቅት ነው።ባለፉት ሐምሌ እና ሰኔ ወራት በቀናት ልዩነት ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣቶች ተፈጻሚ ሆነዋል። ከጥር ወዲህ ቢያንስ 17 ኢትዮጵያውያን በሞት መቀጣታቸውን ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች 'ሂውማን ራይትስ ዎች' ሐምሌ ላይ አስታውቋል።

በአሁኑ ሰዓትም 200 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ተፈርዶባቸው እስር ላይ እንደሚገኙ በስፍራው የሚገኙ ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል።ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የሳዑዲ ባለሥልጣናት ከዕፅ ጋር በተያያዙ ወንጀሎች የጠረጠሯቸው ኢትዮጵያውያንን በቁጥጥር ሥር ማዋል ቀጥለዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
5👍5😢2
በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በቴሌ ብር መተግበሪያ የ4 ነጥብ 19 ትሪሊየን ብር የዲጅታል ግብይት መፈጸሙን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ።

ኢንቨስትመንት ሆልዲንግሱ ይሄንን ያለው በስሩ የሚገኙ ተቋማት አመታዊ አፈጻጸም ግምገማ ለ3ኛ ቀን መቀጠሉን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ላይ ነው።

የቴሌ ብር ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ60 ሚሊዮን በላይ መድረሱን ያነሳው ተቋሙ ቴሌ ብር በ2018 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 83 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱንም ገልጿል።

በተጨማሪም በበጀት አመቱ የኢትዮ ቴሌኮም ገቢ በ33 ነጥብ 2 በመቶ ማደጉም ነው የተጠቀሰው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
3👍2
በኢሮብ ወረዳ 35 ሺህ ህዝብ ለከባድ ድርቅ ተጋልጧል።

በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የሚገኘው ኢሮብ ወረዳ ከባድ ድርቅ እየተጋፈጠ ሲሆን በአካባቢው የሚኖሩ 35 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ለድርቅ አደጋ መጋለጣቸው ተገልጿል።

በወረዳው የክረምት ዝናብ በበቂ ሁኔታ ባለመዝነቡ የውሃ ጉድጓዶች መድረቃቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በውሃ እጥረቱም የቤት እንስሳት መሞት መጀመራቸውን አስረድተዋል።

በወረዳው የሚገኙ ስምንት ቀበሌዎች በከፍተኛ ተራራና ተዳፋት አካባቢዎች መሆናቸው የተጀመረውን የእርዳታ ማዳረስ ስራ ፈታኝ እንዳደረገው ተጠቁሟል።

የአካባቢው አርሶ አደሮች እንደሚሉት፣ ከዚህ በፊት እንደ ዘንድሮ ያለ ከባድ ድርቅ አጋጥሟቸው አያውቅም።

የዝናብ እጥረቱ በማሳ ላይ የተዘራው እህል እንዲደርቅ ከማድረጉም በላይ በክረምት ዝናብ ይሞሉ የነበሩ የውሃ ጉድጓዶች እንዲደርቁ አድርጓል።

የኢሮብ አካባቢ የኢሮብ ብሄረሰብ የሚኖርበት ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወረዳዎች አንዱ ነው። አካባቢው በ2013 ዓ.ም. በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ ጥቃት የደረሰበት ሲሆን እስካሁንም አንዳንድ የቀበሌ ገበሬ ማህበራት በኤርትራ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ይገኛሉ።

የድርቁ አደጋ በሰዎችና በእንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ከማስከተሉ በፊት ለጋሽ ድርጅቶች፣ ባለሀብቶችና ግለሰቦች የእርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉ ወረዳው ቀደም ሲል ጥሪ አቅርቧል።

በዚህ ጥሪ መሰረት አንዳንድ ግለሰቦች የእርዳታ እህል ማቅረብ መጀመራቸው ተገልጿል። ሆኖም የእንስሳት መኖ፣ የሰዎችና የእንስሳት መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት አሁንም የድርቁን ተጽዕኖ ለመቀነስ የሚደረገውን ስራ ከባድ እያደረገው እንደሆነ ተጠቁሟል።

የአካባቢው ህዝብ የውሃ፣ የምግብ እና የእንስሳት መኖ አቅርቦት በአስቸኳይ እንዲጠናከር ጥሪ እያቀረበ ነው።

@Addis_Reporter
😢154👍2💔2
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሠራተኞች የደመወዝ ክፍያ እና የመንግስት አካውንቶች ወደ ስኬት ባንክ መዛወሩ ተሰማ።
ለተለያዩ የመንግሥት ተቋማት፣ ቢሮዎች እና ትምህርት ቤቶች በተላለፈው ጥብቅ ትእዛዝ ሠራተኞች በንግድ ባንክ የነበራቸውን አካውንት ዘግተው በደብዳቤ እንዲያሳውቁና በስኬት ባንክ አዲስ አካውንት በአስቸኳይ እንዲከፍቱ ተነግሯቸዋል።

Via :- መሰረት ሚዲያ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤔9👍3😢31🤪1
"ከቡርኪና ፋሶ ውጡ ካልሆ ትሞታላችሁ‼️

የቡርኪና ፋሶው መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ከሽብርተኞች ጋር ድርድር አላደርግም አሉ።

የቡርኪና ፋሶ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ አገራቸውን እያተራመሱ ካሉ ታጣቂ እና አሸባሪ ቡድኖች ጋር ምንም ዓይነት ድርድር አናደርግም ብለዋል።

ከቡድኖቹ ጋር ምንም ዓይነት ድርድር የማድረግ ፍላጎት እንደሌላቸውና የማያወላውል ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ይፋ አድርገዋል።

ካፒቴን ትራውሬ ለታጣቂ ቡድኖቹ ግልጽና ወሳኝ የሆነ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ከቡርኪና ፋሶ ውጡ ካልሆነ ትሞታላችሁ ብለዋል።

መንግስት የአገሪቱን አንድ ስንዝር መሬት እንኳ ለሽብርተኞች አሳልፎ እንደማይሰጥና ሀገሪቷ ሉአላዊነቷ እስኪረጋገጥ ድረስ ውጊያው እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የሀገሪቱ ሰላም የሚረጋገጠው በድርድር ሳይሆን በመከላከያ ሰራዊት ጥንካሬ ነው ሲሉ ጠንካራ አቋማቸውን ገልጸዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
48👍24🤣3🥰1🤔1💔1👀1
የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት፣ ከኢትዮጵያ አቅጣጫ ወደ ሱዳን ግዛት ገብቷል ያለውን ድሮን ዛሬ ጧት መትቶ መጣሉን አስታወቀ፡፡

የሱዳን ጦር ኃይል ድሮኑን መትቶ የጣለው፣ ከኢትዮጵያው ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ጋር በሚዋሠነው ብሉ ናይል ግዛት ውስጥ መኾኑን እንደገለጠ የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ኾኖም የሱዳን ጦር ኃይል መትቼ ጣልኩት ባለው ድሮን ዙሪያ ዝርዝር ማብራሪያ አንዳልሠጠ ዘገባዎቹ ጠቅሠዋል።

የአገሪቱ ጦር ኃይል ከቀናት በፊትም በዚሁ ግዛት ውስጥ ኩርሙክ ከተማ አካባቢ ከኢትዮጵያ በኩል የገባ ድሮን መትቼ ጥያለሁ ማለቱ  አይዘነጋም።

የኢትዮጵያ መንግሥት ለሱዳን ወታደራዊ መንግሥት ውንጀላዎች ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ በይፋ ምላሽ አልሠጠም።(ዋዜማ)

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
14👍3🤔1
ቀን 22/12/2018
አስቸኳይ ክፍት የስራ ማስታወቂያ
09 09 17 48 53/09 07 36  23 85
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉   የስራ መደብ:# NGO
👉የት/ደረጃ ዲፕሎማ / ድግሪ
👉የስራ ልምድ ፡- 0አመት
👉ደሞዝ:- 40.000_50.000
👉ፆታ:-   ወ/ሴ
👉የሰራ ቦታ  አአ/ክልል
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራው  መደብ =- ሀውስ ኪፒግ
👉የትምርት ደረጃ 8 +
👉የስራ ልምድ 0-3
👉ደሞዝ 7000+
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራው መደብ =- ሆስተስ
👉የትምርት ደረጃ 10 +
👉የስራ ልምድ 0 አመት
👉ደሞዝ 15000 / 20000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራው መደብ =-መስተግዶ
👉የትምርት ደረጃ 8/10/12
👉የስራ ልምድ 0/2
👉ጾታ ወንድ /ሴት
👉ደሞዝ ማራኪ
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
የስራው መደብ /ፓስታ ፋብሪካ=-የእሸጋ ሰራተኛ
👉  የስራ ልምድ ፡- 0 አመት
👉ደሞዝ:-  17000
👉ፆታ:-   ወ/ሴ
👉የሰራ ቦታ  አአ/
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ ፡ ስልክ ኦፕሬተር 
👉የት ደረጃ ፡ 10/12/ዲፕ
👉የስራ ልምድ ፡ 0 -አመት 
👉ደሞዝ ፡ 15000+
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ:- #ሹፌር ደ/1 2 ህ/1/ሞተረኛ
👉የሰራ ልምድ :- 2-10አመት
👉የት/ት ደረጃ :- 8/10/12
👉ደሞዝ:- 7000_17000
👉ፆታ :- ወንድ
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ:- #ትኬተር/ለባስ/
👉የሰራ ልምድ :- 0አመት
👉የት/ት ደረጃ :- 10/12/ዲፕሎማ
👉ደሞዝ:- 0አመት
👉ደሞወዝ   :- 9000~20,000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ፦ሽያጭ /ለፈርኒቸር
👉የት/ደረጃ፦10/12/diploma/
👉ደሞዝ:-8000_30000+
👉የስራ ልምድ: 0አመት
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ :markting
👉የት ደረጃ ፡- degree 
👉የስራ ልምድ ፡- 0~5 አመት
👉ደሞዝ :-13000+
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ ፡ Accountant
👉የት ደረጃ ፡ Degree/"Dip
👉ፆታ: ሴ
👉የስራ ልምድ ፡ 0 - 8አመት
👉ደሞዝ ፡  8,000-16,000 
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ ፡ IT
👉የት/ደረጃ ፡-  degree /dip
👉የስራ ልምድ ፡- 0 -2አመት
👉ፆታ:- ሴ/ወ
👉ደሞዝ:- 8000-15000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ፦ካሸር
👉የት/ደረጃ፦10 +
👉የሰራ ልምድ 0~3 አመት
👉ደሞዝ:- 7000-12000
👉ፆታ፦ሴ
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ፦#nurse//ላብራቶሪ/ጠቅላላ
👉 ለክሊኒክ እና ለሆስፒታል
👉የት/ደረጃ፦ዲፕልማ / ዲግሪ
👉የስራ ልምድ: 0~8አመት
👉ደሞዝ:- በስምምነት
👉ፆታ፦ሴት/ወንድ
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራው መደብ ቡቲክ ሴልስ
👉የት ደረጃ ፡ 8
👉ፆታ: ሴ
👉የስራ ልምድ ፡ 0-1
👉ደሞዝ :7000-20,000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራው መደብ =- የጥፍር እና አይላሽ
👉የትምርት ደረጃ 8+
👉የስራ ልምድ 0 -1 አመት
👉ደሞዝ 10000-25000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራው መደብ=- ፀሀፊ
👉የትምርት ደረጃ ዲፕሎም
👉የስራ ልምድ ያላት
👉ፆታ ሴት
👉ደሞዝ 8000/13000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራው አይነት =- ባርቴንደር
👉የትምርት ደረጃ 8/10/12
👉የስራ ልድ 1/3
👉ፆታ ሴት
👉ደሞዝ 10000+
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራው መደብ =- ብስኩት ፋብሪካ
👉የትምርት ደረጃ 8/10/12
👉የስራ ልምድ 0 አመት
👉ደሞዝ 16000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ፦ሼፍ ዋና / እረዳት
👉የት/ደረጃ፦ ሰርተፍኬት
👉ደሞዝ:-9000-35000
👉ፆታ፦ወንድ/ሴት
👉የስራ ልምድ ፡ 0_5አመት
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ ፡ እሪል እስቴት ሴልስ
👉የት ደረጃ ፡ ዲፕ/ዲግሪ
👉የስራ ልምድ ፡ 0-2
👉ደሞዝ ፡  9000-50000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ ፡ ሁለገብ ሰራተኛ
👉የደረጃ ፡- 8_10
👉የስራ ልምድ ፡- 0አመት
👉ደሞወዝ :- 10000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ ፡ reception
👉የት ደረጃ ፡ 10/12
👉የስራ ልምድ ፡ 0-2
👉ደሞዝ 8000/15000
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ፦#ተላላኪና ፅዳት ለባንክ
👉የት/ደረጃ፦8/12 /ዲፕ
👉 የሰራ ልምድ 0 አመት
👉ደሞዝ:- በስምምነት
👉የስራ ቦታ: በሰፈር አቅራብያ
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉የስራ መደብ ፡ ጉዳይ አስፈፃሚ ፖስተኛ
👉የት ደረጃ ፡ 10/12/"Dip
👉ፆታ: ሴ/ወ
👉የስራ ልምድ ፡ 0-2አመት
👉ደሞዝ ፡  15000+
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
👉መረጃና መዝገበ አያያዝ 
👉 የት ደረጃ ፡ dip-degree
👉የስራ ልምድ ፡ 0_1አመት
👉ደሞዝ ፡  13500
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ለበለጠ መረጃ 👇👇👇👇
አድራሻ:-  መገናኛ ደራርቱ ህንፃ ወደ 24 በሚወስደው መንገድ  መብራቱን ተሻግሮ ሰኒ ህንፃ 3 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 305  👇👇👇👇👇
         ☎️ 0907362385
         ☎️  0909174853
     
👍32
የምሽቱ ትልቁን ፍልሚያ ጆኒ አሸነፈ

በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ሲካሄድ የሰነበተው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ኮከቦች ምሽት በጉጉት በተጠበቀውና በዋናው የዋንጫ ፍልሚያ (Main Event) በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል!

በሚድል ዌይት (Middleweight MMA Bout) ዘርፍ በጆኒ እና በሴዶ መካከል የተደረገው ይህ አስደናቂና አቃጣጣኝ ፍልሚያ የመላው ተመልካች ቀልብ የሳበ ነበር።

በከፍተኛ የኤምኤምኤ (MMA) ቴክኒክ፣ የላቀ ብቃትና ፍጹም የድል ወኔ ተጋጣሚውን ሴዶን ያሸነፈው ጆኒ፡ የምሽቱን ትልቅ ድል በመቀዳጀት አዲሱ የ ETFC 2 ቻምፒዮን (Champion) በመሆን ዘውዱን ደፍቷል!

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍11🤣42🤪2🎉1😡1
የገቢዎች ሚኒስቴር የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች የ2018 በጀት ዓመት የሂሳብ ሪፖርት ሲያቀርቡ፣ ለእያንዳንዱ የንግድ ስራ መስክ በተናጠል እና ሁሉንም የንግድ መስኮች ያካተተ የተጠቃለለ ሪፖርት ማቅረብ እንዳለባቸው አውቀው ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳሰበ።

የገቢዎች ሚኒስቴር፣ ከአንድ በላይ የንግድ መስክ ላይ ለተሰማሩ የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች ለእያንዳንዱ የንግድ ዘርፍ የተለየ የሂሳብ መዝገብ መያዝ እንዳለባቸው አውቀው ዝግጅት እንዲያደርጉ ጠይቋል።

ይህ አሰራር ተግባራዊ የሚደረገው በገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 አንቀጽ 86 እና በሠንጠረዥ "ሐ" በተቀመጠው ድንጋጌ መሠረት ነው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter