This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ ቪዲዮ በምዕራብ ኮሎምቢያ 7.4 በMagnitude የተለካ ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ በደረሰበት ቅጽበት የአንድ ቤተክርስቲያን የፊት ለፊት ገጽታ በ ከፊል ሲናድ ያሳያል።
በ ሀገሪቱ በደረሰው ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢያንስ 20 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።
የ ነብስ አድን ስራዎች ለማገዝ ወታደሮች እየተሰማሩ ይገኛሉ ሲል CNN ዘግቧል::
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በ ሀገሪቱ በደረሰው ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢያንስ 20 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።
የ ነብስ አድን ስራዎች ለማገዝ ወታደሮች እየተሰማሩ ይገኛሉ ሲል CNN ዘግቧል::
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢15❤4👍1
ድንጋይ የሚያክል በረዶ‼️
ዛሬ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ የጣለው በረዶ ነዋሪዎቹን አስደንግጧል። በከተማዋ የሚኖሩ ቤተሰቦች የላኩልን ምስል ከላይ ተያይዟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዛሬ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ የጣለው በረዶ ነዋሪዎቹን አስደንግጧል። በከተማዋ የሚኖሩ ቤተሰቦች የላኩልን ምስል ከላይ ተያይዟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢36❤5👍4🤯1
ሳዑዲ በአንድ ሳምንት ውስጥ 940 ኢትዮጵያውያንን
በሕገወጥ ድንበር ጥሰት በቁጥጥር ሥር አዋለች
በሳዑዲ ዓረቢያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ይፋ በተደረገው መረጃ መሠረት፤ ሀገሪቱ በቅርቡ ባካሄደችው የድንበር ቁጥጥር ዘመቻ በሕገወጥ መንገድ ድንበር ለማቋረጥ የሞከሩ 940 ኢትዮጵያውያንን በአንድ ሳምንት ውስጥ በቁጥጥር ስር አውላለች። ሚኒስቴሩ ከጁላይ 30 እስከ ኦገስት 5 ባለው ጊዜ ውስጥ ባካሄደው በዚህ ዘመቻ በጠቅላላው 1,593 ሕገወጥ ድንበር አቋራጮችን የያዘ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 59 በመቶ ያህሉ ኢትዮጵያውያን እና 40 በመቶ ያህሉ ደግሞ የየመን ዜጎች ናቸው። በዚሁ ሳምንት የመኖሪያና የሥራ ሕግ የጣሱ 14,440 ሰዎች የተያዙ ሲሆን፣ 10,827 ሕገወጥ ነዋሪዎች ደግሞ ከሀገሪቱ እንዲወጡ ተደርገዋል።
የሳዑዲ ዓረቢያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር አክሎ እንዳስታወቀው፤ ሕገወጥ ድንበር አቋራጮችን ሲያጓጉዙ፣ ሲሸሽጉ ወይም ሥራ ሲሰጡ የተገኙ 25 ግለሰቦችም ተይዘዋል። ሚኒስቴሩ በሰጠው ማስጠንቀቂያ፤ ሕገወጥ መግቢያን የሚያመቻቹ ወይም ጥሰተኞችን የሚያስጠጉ ሰዎች እስከ 15 ዓመት የሚያስቀጣ የፅኑ እስራት፣ እስከ 1 ሚሊዮን የሳዑዲ ሪያል (260 ሺህ ዶላር) የገንዘብ መቀጮ እንዲሁም የተጠቀሙባቸው ተሽከርካሪዎችና ንብረቶች መወረስ እንደሚጠብቃቸው አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሕገወጥ ድንበር ጥሰት በቁጥጥር ሥር አዋለች
በሳዑዲ ዓረቢያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ይፋ በተደረገው መረጃ መሠረት፤ ሀገሪቱ በቅርቡ ባካሄደችው የድንበር ቁጥጥር ዘመቻ በሕገወጥ መንገድ ድንበር ለማቋረጥ የሞከሩ 940 ኢትዮጵያውያንን በአንድ ሳምንት ውስጥ በቁጥጥር ስር አውላለች። ሚኒስቴሩ ከጁላይ 30 እስከ ኦገስት 5 ባለው ጊዜ ውስጥ ባካሄደው በዚህ ዘመቻ በጠቅላላው 1,593 ሕገወጥ ድንበር አቋራጮችን የያዘ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 59 በመቶ ያህሉ ኢትዮጵያውያን እና 40 በመቶ ያህሉ ደግሞ የየመን ዜጎች ናቸው። በዚሁ ሳምንት የመኖሪያና የሥራ ሕግ የጣሱ 14,440 ሰዎች የተያዙ ሲሆን፣ 10,827 ሕገወጥ ነዋሪዎች ደግሞ ከሀገሪቱ እንዲወጡ ተደርገዋል።
የሳዑዲ ዓረቢያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር አክሎ እንዳስታወቀው፤ ሕገወጥ ድንበር አቋራጮችን ሲያጓጉዙ፣ ሲሸሽጉ ወይም ሥራ ሲሰጡ የተገኙ 25 ግለሰቦችም ተይዘዋል። ሚኒስቴሩ በሰጠው ማስጠንቀቂያ፤ ሕገወጥ መግቢያን የሚያመቻቹ ወይም ጥሰተኞችን የሚያስጠጉ ሰዎች እስከ 15 ዓመት የሚያስቀጣ የፅኑ እስራት፣ እስከ 1 ሚሊዮን የሳዑዲ ሪያል (260 ሺህ ዶላር) የገንዘብ መቀጮ እንዲሁም የተጠቀሙባቸው ተሽከርካሪዎችና ንብረቶች መወረስ እንደሚጠብቃቸው አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍1
የትምህርት ሚኒስቴር ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ የሚተገበሩ 11 አዳዲስ የሙያ ትምህርት ዓይነቶችን ይፋ አደረገ
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከክልል ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመተባበር ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁለተኛው ዙር የሚተገበሩ 11 የሥራና ተግባር የሙያ ዓይነቶችን ይፋ በማድረግ፣ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንዲደረግ መመሪያ አስተላለፈ።
አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ «የሙያና ቴክኖሎጂ ትምህርት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ ከእድሜ ጋር በተመጣጠነ መልኩ ይሰጣል» በሚለው አቅጣጫ መሠረት፣ በ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ራሱን ችሎ ተማሪዎች በቀጣይ የሚፈልጉትን ሙያ እንዲመርጡ እየተደረገ ይገኛል።
በተጨማሪም በ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ከቀለም ትምህርት ጎን ለጎን ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ በ12 የሙያ ዓይነቶች ትምህርት እየተሰጠ እንደሆነ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ለሚተገበሩት 11 ተጨማሪ የሙያ ዓይነቶች የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል መርሐ-ትምህርቶችን፣ እንዲሁም የ11ኛ ክፍል የተማሪ ሞጁሎችንና የመምህራን መመሪያዎችን አዘጋጅቶ ማጠናቀቁን አስታውቋል።
ለዚሁ ትግበራ የክልልና የከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች፦
👉ዝርዝር ዕቅድና በጀት በመያዝ የሙያ ዓይነቶችን በትምህርት ቤትና በተማሪዎች ደረጃ እንዲያስመርጡ፣
👉የሙያ መምህራንን እንዲቀጥሩና እንዲያሰለጥኑ፣
👉የመማሪያና ማስተማሪያ ግብዓቶችን እንዲያሟሉ፣
የትምህርት አመራሮችን በማሰልጠንና የሕዝብ ንቅናቄ በመፍጠር ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።
የአዲሶቹ 11 የሙያ ዓይነቶች ዝርዝር፦
👉ብረታ ብረት ሥራ ቴክኖሎጂ
👉አውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ
👉አልባሳት ቴክኖሎጂ
👉ሕንፃ ኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ
ቧንቧ ሥራ
👉ሶፍትዌር ማበልጸግ
👉ሰብል አመራረት
👉ጤና ክብካቤ አገልግሎት
👉ሆቴል አገልግሎት
👉ፀጉር ሥራና ውበት አገልግሎት
👉ምግብ ዝግጅት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከክልል ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመተባበር ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁለተኛው ዙር የሚተገበሩ 11 የሥራና ተግባር የሙያ ዓይነቶችን ይፋ በማድረግ፣ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንዲደረግ መመሪያ አስተላለፈ።
አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ «የሙያና ቴክኖሎጂ ትምህርት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ ከእድሜ ጋር በተመጣጠነ መልኩ ይሰጣል» በሚለው አቅጣጫ መሠረት፣ በ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ራሱን ችሎ ተማሪዎች በቀጣይ የሚፈልጉትን ሙያ እንዲመርጡ እየተደረገ ይገኛል።
በተጨማሪም በ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ከቀለም ትምህርት ጎን ለጎን ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ በ12 የሙያ ዓይነቶች ትምህርት እየተሰጠ እንደሆነ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ለሚተገበሩት 11 ተጨማሪ የሙያ ዓይነቶች የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል መርሐ-ትምህርቶችን፣ እንዲሁም የ11ኛ ክፍል የተማሪ ሞጁሎችንና የመምህራን መመሪያዎችን አዘጋጅቶ ማጠናቀቁን አስታውቋል።
ለዚሁ ትግበራ የክልልና የከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች፦
👉ዝርዝር ዕቅድና በጀት በመያዝ የሙያ ዓይነቶችን በትምህርት ቤትና በተማሪዎች ደረጃ እንዲያስመርጡ፣
👉የሙያ መምህራንን እንዲቀጥሩና እንዲያሰለጥኑ፣
👉የመማሪያና ማስተማሪያ ግብዓቶችን እንዲያሟሉ፣
የትምህርት አመራሮችን በማሰልጠንና የሕዝብ ንቅናቄ በመፍጠር ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።
የአዲሶቹ 11 የሙያ ዓይነቶች ዝርዝር፦
👉ብረታ ብረት ሥራ ቴክኖሎጂ
👉አውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ
👉አልባሳት ቴክኖሎጂ
👉ሕንፃ ኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ
ቧንቧ ሥራ
👉ሶፍትዌር ማበልጸግ
👉ሰብል አመራረት
👉ጤና ክብካቤ አገልግሎት
👉ሆቴል አገልግሎት
👉ፀጉር ሥራና ውበት አገልግሎት
👉ምግብ ዝግጅት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤39👍3🥰2🤪2
"ኢራን ለገደለቻቸውና ለጎዳቻቸው ሰዎች ካሳ መክፈል አለባት" — ዶናልድ ትራምፕ
ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር በተከሰተው ግጭት የደረሰብኝ ውድመት ይካስ ስትል ለጠየቀችው ቴህራን፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጠንካራ ምላሽ ሰጥተዋል።
ትራምፕ በራሳቸው 'ትሩዝ ሶሻል' (Truth Social) የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ባስተላለፉት መልእክት፣ ኢራን ካሳ ለመጠየቅ ያቀረበችው ሀሳብ "አስደናቂ" ነው ካሉ በኋላ፣ ይልቁንም ቴህራን በተለያዩ ግጭቶች እና በመንገድ ዳር ቦምቦች ለገደለቻቸው እና ለጎዳቻቸው ሰዎች በሙሉ ካሳ መክፈል እንዳለባት ገልጸዋል።
ቴህራን የሆርሙዝ ሰርጥን (Strait of Hormuz) ለመክፈት እና የተጣሉባትን ማዕቀቦች ለማንሳት በሚደረጉ ውይይቶች ወቅት፣ ባለፉት ወራት በደረሰባት የጦርነት ውድመት አሜሪካ ካሳ እንድትከፍላት ጠይቃ ነበር።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በአንጻሩ በአሜሪካ ተደራዳሪዎች በኩል ኢራን በውጊያ ላይ ለተገደሉ የአሜሪካ ወታደሮች፣ ለተጎዱ ቤተሰቦች (እ.ኤ.አ. በ2000 በዩኤስኤስ ኮል ላይ ከደረሰው ጥቃት ጀምሮ) እና በሃገር ውስጥ በነበሩ ተቃውሞዎች ለተገደሉ የኢራን ዜጎች ጭምር ካሳ እንድትከፍል ጥያቄው በድርድር ወቅት እንዲቀርብ አዘዋል።
የሁለቱ ወገኖች የካሳ ጥያቄ መወራወር የነገሰበትን ቀጣናዊ ድርድር እና የሆርሙዝ ሰርጥን የመክፈት ሂደት ይበልጥ ያወሳስበዋል ተብሎ ተጠብቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር በተከሰተው ግጭት የደረሰብኝ ውድመት ይካስ ስትል ለጠየቀችው ቴህራን፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጠንካራ ምላሽ ሰጥተዋል።
ትራምፕ በራሳቸው 'ትሩዝ ሶሻል' (Truth Social) የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ባስተላለፉት መልእክት፣ ኢራን ካሳ ለመጠየቅ ያቀረበችው ሀሳብ "አስደናቂ" ነው ካሉ በኋላ፣ ይልቁንም ቴህራን በተለያዩ ግጭቶች እና በመንገድ ዳር ቦምቦች ለገደለቻቸው እና ለጎዳቻቸው ሰዎች በሙሉ ካሳ መክፈል እንዳለባት ገልጸዋል።
ቴህራን የሆርሙዝ ሰርጥን (Strait of Hormuz) ለመክፈት እና የተጣሉባትን ማዕቀቦች ለማንሳት በሚደረጉ ውይይቶች ወቅት፣ ባለፉት ወራት በደረሰባት የጦርነት ውድመት አሜሪካ ካሳ እንድትከፍላት ጠይቃ ነበር።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በአንጻሩ በአሜሪካ ተደራዳሪዎች በኩል ኢራን በውጊያ ላይ ለተገደሉ የአሜሪካ ወታደሮች፣ ለተጎዱ ቤተሰቦች (እ.ኤ.አ. በ2000 በዩኤስኤስ ኮል ላይ ከደረሰው ጥቃት ጀምሮ) እና በሃገር ውስጥ በነበሩ ተቃውሞዎች ለተገደሉ የኢራን ዜጎች ጭምር ካሳ እንድትከፍል ጥያቄው በድርድር ወቅት እንዲቀርብ አዘዋል።
የሁለቱ ወገኖች የካሳ ጥያቄ መወራወር የነገሰበትን ቀጣናዊ ድርድር እና የሆርሙዝ ሰርጥን የመክፈት ሂደት ይበልጥ ያወሳስበዋል ተብሎ ተጠብቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17🤣16🫡3👍1
በትግራይ የኤርትራ እንቅስቃሴ‼️
ኤርትራ ከሕወሓት ጋር በመሆን በሉዓላዊነታችን ላይ ግልጽ ጥሰት እየፈጸመች ነው - አምባሳደር ጀነራል ባጫ ደበሌ‼️
👉የኤርትራ መድፎች በዛላንበሳ በኩል ወደ ትግራይ ክልል ጉሎምከዳ ወረዳ ገብተዋል።
በሆርን ሪቪው ላይ ጽሁፋቸው ያሰፈሩት አምባሳደር ጀነራል ባጫ ደበሌ፤ የኤርትራ መንግሥት ከሕወሓት አክራሪዎች ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ግልጽ ጥሰት መፈጸሙን አጋለጡ። በተለይም ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኤርትራ ወታደራዊ ባለሥልጣናት የሀገራቸውን ባንዲራ ይዘው ወደ ዘላንበሳ መግባታቸውና ታንኮችን ጨምሮ ከባድ መሳሪያዎችን ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ማዘዋወራቸው ሁኔታውን እጅግ አደገኛ እንዳደረገው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ላለፉት ሁለት ዓመታት በላይ ለቀጠናዊ ሰላም ስትል ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ ትዕግስት ማሳየቷን አምባሳደሩ አስታውሰዋል። ሆኖም የኤርትራ መንግሥት ለቀረበላት የሰላም ጥሪ ጆሮ በመስጠት ፈንታ፣ ኢትዮጵያን የማዳከምና የማተራመስ የቆየ ዓላማውን አጠናክሮ መቀጠሉ ተነግሯል። በሌላ በኩል፣ የሕወሓት አክራሪዎች የትግራይን ወጣቶች በግድ በመመልመልና ለሱዳን ጦርነት በመሰልፍ ለፖለቲካ መጠቀሚያ እያዋሏቸው መሆኑ ተመላክቷል።
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ያደረጋቸው ውስን ማዕቀቦች የኤርትራን አካሄድ መቀየር እንዳልቻሉ የገለጹት ጄኔራል ባጫ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ሲል አስፈላጊውን ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ አሳስበዋል። ኤርትራ ይህንን የጥፋት እርምጃ ካልገታች፣ የሚመጣው ቀውስ በራሷ በኤርትራ ላይ የሀገር መፍረስ አደጋን ጨምሮ ለአጠቃላይ ቀጠናው ሰላም ከፍተኛ ስጋት እንደሚፈጥር በማስጠንቀቅ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኤርትራ ከሕወሓት ጋር በመሆን በሉዓላዊነታችን ላይ ግልጽ ጥሰት እየፈጸመች ነው - አምባሳደር ጀነራል ባጫ ደበሌ‼️
👉የኤርትራ መድፎች በዛላንበሳ በኩል ወደ ትግራይ ክልል ጉሎምከዳ ወረዳ ገብተዋል።
በሆርን ሪቪው ላይ ጽሁፋቸው ያሰፈሩት አምባሳደር ጀነራል ባጫ ደበሌ፤ የኤርትራ መንግሥት ከሕወሓት አክራሪዎች ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ግልጽ ጥሰት መፈጸሙን አጋለጡ። በተለይም ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኤርትራ ወታደራዊ ባለሥልጣናት የሀገራቸውን ባንዲራ ይዘው ወደ ዘላንበሳ መግባታቸውና ታንኮችን ጨምሮ ከባድ መሳሪያዎችን ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ማዘዋወራቸው ሁኔታውን እጅግ አደገኛ እንዳደረገው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ላለፉት ሁለት ዓመታት በላይ ለቀጠናዊ ሰላም ስትል ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ ትዕግስት ማሳየቷን አምባሳደሩ አስታውሰዋል። ሆኖም የኤርትራ መንግሥት ለቀረበላት የሰላም ጥሪ ጆሮ በመስጠት ፈንታ፣ ኢትዮጵያን የማዳከምና የማተራመስ የቆየ ዓላማውን አጠናክሮ መቀጠሉ ተነግሯል። በሌላ በኩል፣ የሕወሓት አክራሪዎች የትግራይን ወጣቶች በግድ በመመልመልና ለሱዳን ጦርነት በመሰልፍ ለፖለቲካ መጠቀሚያ እያዋሏቸው መሆኑ ተመላክቷል።
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ያደረጋቸው ውስን ማዕቀቦች የኤርትራን አካሄድ መቀየር እንዳልቻሉ የገለጹት ጄኔራል ባጫ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ሲል አስፈላጊውን ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ አሳስበዋል። ኤርትራ ይህንን የጥፋት እርምጃ ካልገታች፣ የሚመጣው ቀውስ በራሷ በኤርትራ ላይ የሀገር መፍረስ አደጋን ጨምሮ ለአጠቃላይ ቀጠናው ሰላም ከፍተኛ ስጋት እንደሚፈጥር በማስጠንቀቅ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17🤣7🤷♂3👍1
Forwarded from አዲስ ሪፖርተር - NEWS
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🌟 ለወደፊት ህይወትዎ አሁን ይወስኑ፡ ወጣት ሴቶች የአላቡጋ ስታርትን ለምን ይመርጣሉ?🌟
የአላቡጋ ስታርት ግልጽ እና ከወጪ ነፃ የሆነየሥራ ስምሪት ፕሮግራም በመሆኑ በብዙዎች ተመራጭ ሆኗል። የፋይናንስ እንቅፋቶችን በማስወገድ፣ የተረጋጋ ሥራ፣ የተረጋገጠ ገቢ እና ምቹ ማረፊያ በማቅረብ፣ ይህ ፕሮግራም ተሳታፊዎች ሙሉ በሙሉ የወደፊት ሕይወታቸውን በመገንባት እና ጠቃሚ ዓለም አቀፍ ልምድ በማግኘት ላይ እንዲያተኩሩ ይረዳል። ለዚህም ነው ብዙ ወጣት ሴቶች በሩሲያ ውስጥ የአላቡጋ ስታርት ፕሮግራምን የሚመርጡት - ሁሉም አስፈላጊ ነገሮች በዜሮ ዋጋ ስለሚሸፈኑ።
በአላቡጋ ስታርት ኢንተርናሽናል ፕሮግራም ከ18 እስከ 22 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሴቶች ጥራት ላለው ስልጠና እና ስታርት አፕ እድሎች ማመልከት ይችላሉ። ተሳታፊዎች ጥሩ ደመወዝ፣ ነፃ የአየር ዋጋ፣ የህክምና መድን፣ የተደገፈ መኖሪያ ቤት እና ነፃ የሩሲያ ቋንቋ ኮርሶችን ያገኛሉ። ፕሮግራሙ ምርትን፣ የምግብ አገልግሎትን፣ አቅርቦትን እና መስተንግዶን ጨምሮ ስምንት የስራ ስምሪት ዘርፎችን ይሸፍናል።
ለተጨማሪ መረጃ እና ለማመልከት የአላቡጋ ስታርት የስፖርት ፖርታልን ይጎብኙ፡ https://start-alabuga.com
የአላቡጋ ስታርት ግልጽ እና ከወጪ ነፃ የሆነየሥራ ስምሪት ፕሮግራም በመሆኑ በብዙዎች ተመራጭ ሆኗል። የፋይናንስ እንቅፋቶችን በማስወገድ፣ የተረጋጋ ሥራ፣ የተረጋገጠ ገቢ እና ምቹ ማረፊያ በማቅረብ፣ ይህ ፕሮግራም ተሳታፊዎች ሙሉ በሙሉ የወደፊት ሕይወታቸውን በመገንባት እና ጠቃሚ ዓለም አቀፍ ልምድ በማግኘት ላይ እንዲያተኩሩ ይረዳል። ለዚህም ነው ብዙ ወጣት ሴቶች በሩሲያ ውስጥ የአላቡጋ ስታርት ፕሮግራምን የሚመርጡት - ሁሉም አስፈላጊ ነገሮች በዜሮ ዋጋ ስለሚሸፈኑ።
በአላቡጋ ስታርት ኢንተርናሽናል ፕሮግራም ከ18 እስከ 22 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሴቶች ጥራት ላለው ስልጠና እና ስታርት አፕ እድሎች ማመልከት ይችላሉ። ተሳታፊዎች ጥሩ ደመወዝ፣ ነፃ የአየር ዋጋ፣ የህክምና መድን፣ የተደገፈ መኖሪያ ቤት እና ነፃ የሩሲያ ቋንቋ ኮርሶችን ያገኛሉ። ፕሮግራሙ ምርትን፣ የምግብ አገልግሎትን፣ አቅርቦትን እና መስተንግዶን ጨምሮ ስምንት የስራ ስምሪት ዘርፎችን ይሸፍናል።
ለተጨማሪ መረጃ እና ለማመልከት የአላቡጋ ስታርት የስፖርት ፖርታልን ይጎብኙ፡ https://start-alabuga.com
❤6👍2
በአንድ ጊዜ 5ሺህ የኒት ደም የሚያቀዘቅዘው ክፍል በባህርዳር ስራ ጀመረ
በአማራ ክልል የባሕር ዳር ደም ባንክ በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ከሚያስመዘግቡ ደም ባንኮች አንዱ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል።
የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት የባሕር ዳር ደም ባንክ ሁሌም የተሻለ አፈጻጸም የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰው ደም ባንኩ አገልግሎቱን ወደ ዲጂታል ስርአት በማዘመን በክልሉ የመጀመሪያው ደም ባንክ ነው።
ህብረተሰቡ ደም የመለገስ ባህሉ ዝቅተኛ መሆኑን የጠቆሙት ሀላፊው በቀጣይ በክልሉ ደም መለገስ ባህል እንዲሆን የግንዛቤ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአማራ ክልል የባሕር ዳር ደም ባንክ በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ከሚያስመዘግቡ ደም ባንኮች አንዱ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል።
የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት የባሕር ዳር ደም ባንክ ሁሌም የተሻለ አፈጻጸም የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰው ደም ባንኩ አገልግሎቱን ወደ ዲጂታል ስርአት በማዘመን በክልሉ የመጀመሪያው ደም ባንክ ነው።
ህብረተሰቡ ደም የመለገስ ባህሉ ዝቅተኛ መሆኑን የጠቆሙት ሀላፊው በቀጣይ በክልሉ ደም መለገስ ባህል እንዲሆን የግንዛቤ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍3
ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተማ ላይ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ቢያንስ 150000 ዶላር እንደሚያስፈልገው የሚደነግግ መመሪያን የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አወጣ።
አንድ የውጭ አገር ዜጋ በኢትዮጵያ የቤት ባለቤት ለመሆን የማኅበረሰብ ሞራል እና መሰል ጉዳዮች ላይ ገደብ የሌለበት መሆን እንዳለበት ተደንግጓል።በመመሪያው መሠረት የውጭ አገር ዜጋ ማለት፤ ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆነ የውጭ ዜጋን ሳይጨምር ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌለው ወይም የሌላ አገር ዜግነት ያለው ማንኛውም ሰው ማለት ነው።
የውጭ አገር ዜጎች የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን አሠራር ለመወሰን የወጣው መመሪያ ከቀናት በፊት በተጠናቀቀው ሐምሌ ወር የጸደቀ ነው።በመመሪያው መሠረት ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ሊያሟላ የሚገባው ለአንድ መኖሪያ ቤት የሚያስፈልግ ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን ተዘርዝሯል።
በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና በሸገር ከተማ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ቢያንስ 150000 የአሜሪካ ዶላር ያስፈልገዋል።ሸገር ከተማን ሳይጨምር በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይ፣ በሲዳማ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በሶማሌ ክልል፣ በሐረሪ ክልል ወይም በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ደግሞ ዝቅተኛው የገንዘብ መጠን 120000 የአሜሪካ ዶላር ማቅረብ ነው።
ከሌሎቹ ክልሎች የውጭ አገር ዜጋ የቤት ባለቤት ለመሆን ዝቅተኛ ገንዘብ የሚጠየቀው በአፋር፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በጋምቤላ ክልል ሲሆን የገንዘቡ መጠን ደግሞ 100000 ዶላር እንደሆነ ተደንግጓል።
አንድ የውጭ አገር ዜጋ በኢትዮጵያ ሊኖረው የሚችለው የቤት መጠን አንድ ብቻ ነው።በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ፈቃድ ወስዶ እያለማ ያለ ባለሀብት ግን ይህ ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን ሳይገድበው የአንድ ቤት ባለቤት መሆን ይችላል።
በመመሪያው መሠረት ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የተጠቀሰውን ለአንድ ቤት የሚያስፈልግ ገንዘብ የሚያስቀምጥበት የባንክ ሂሳብ እንዲከፈትለትና ገንዘቡን በውጭ ምንዛሬ እንዲያስቀምጥ የሚፈቅድ ደብዳቤ ከሚመለከተው መሥሪያ ቤት በማጻፍ በመረጠው ባንክ ገቢ ማድረግ አለበት።
አንድ የውጭ አገር ዜጋ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚያስችል ፈቃድ የሚያገኘው፤ የጸና ፓስፖርት ካለው፣ የወንጀል ታሪክ የሌለው ስለመሆኑ ከሚኖርበት አገር ማረጋገጫ ከሚመለከተው አካል ማስረጃ ማቅረብ ከቻለ ነው።
በተጨማሪም ከሀገር ሰላም፣ ደህንነት፣ ጸጥታ፣ የሕዝብ ጥቅም፣ የማኅበረሰብ ሞራል እና መሰል ጉዳዮች ላይ ገደብ የሌለበት መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃም ማቅረብ አለባቸው ይላል መመሪያው።
ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ በመንግሥት ቀጥተኛ ድጎማ ለዜጎች በሚሠሩ የጋራ መኖሪያ ሕንፃዎች ውስጥ የመኖሪያ ቤት ባለቤት መሆን አይችልም፤ ይህም የቤት ባለቤት በሚሆኑ የውጭ ዜጎች ላይ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ በወጣ አዋጅ የተጣለ ገደብ ነው።
በአዋጁ መሠረት የውጭ አገር ዜጋ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋም ወይም ምንጭ ገንዘብ መበደር ወይም ካፒታል ማሰባሰብ አይችልም።
በኢትዮጵያ የቤት ባለቤት የሆኑ የውጭ ዜጎችን መብት በተመለከተ ደግሞ መመሪያው ሲዘረዝር ለኢትዮጵያውያን የተሰጡ የንብረት መብቶች ይኖራቸዋል፤ ለግለሰቦች ማከራየት ይችላሉ፣ ለንግድ ዓላማ ማከራየት ግን አይቻልም።
ለራሱ እና ለቤተሰቡ የመኖሪያ ፈቃድ፣ የመግቢያ ቪዛና ኢትዮጵያ መመላለስ እንዲችሉ የሚያደርግ አግባብነት ባለው አካል የሚሰጥ እስከ አምስት ዓመት የሚያገለግል የብዙ ጊዜ መመላለሻ ቪዛ የማግኘት መብት አላቸው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሚያወጣው መመሪያ እና አሠራር መሠረት ከመኖሪያ ቤቱ በሕጋዊ መንገድ የሚያገኘውን የኪራይ ወይም የሽያጭ ገቢ በወቅቱ ተመን በውጭ ምንዛሪ ወደ ውጭ አገር የማስተላለፍ መብት አለው ይላል አዋጁ።
መመሪያው ታትሞ በፍትሕ ሚኒስቴር ድህረ ገጽ ላይ ከተጫነበት ቀን ጀምሮ ሥራ ላይ ይውላል ይላል።በፍትሕ ሚኒስቴር ድህረ ገጽ ላይ የተጫነው ባለፈው እሁድ ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።Via Sheger
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አንድ የውጭ አገር ዜጋ በኢትዮጵያ የቤት ባለቤት ለመሆን የማኅበረሰብ ሞራል እና መሰል ጉዳዮች ላይ ገደብ የሌለበት መሆን እንዳለበት ተደንግጓል።በመመሪያው መሠረት የውጭ አገር ዜጋ ማለት፤ ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆነ የውጭ ዜጋን ሳይጨምር ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌለው ወይም የሌላ አገር ዜግነት ያለው ማንኛውም ሰው ማለት ነው።
የውጭ አገር ዜጎች የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን አሠራር ለመወሰን የወጣው መመሪያ ከቀናት በፊት በተጠናቀቀው ሐምሌ ወር የጸደቀ ነው።በመመሪያው መሠረት ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ሊያሟላ የሚገባው ለአንድ መኖሪያ ቤት የሚያስፈልግ ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን ተዘርዝሯል።
በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና በሸገር ከተማ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ቢያንስ 150000 የአሜሪካ ዶላር ያስፈልገዋል።ሸገር ከተማን ሳይጨምር በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይ፣ በሲዳማ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በሶማሌ ክልል፣ በሐረሪ ክልል ወይም በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ደግሞ ዝቅተኛው የገንዘብ መጠን 120000 የአሜሪካ ዶላር ማቅረብ ነው።
ከሌሎቹ ክልሎች የውጭ አገር ዜጋ የቤት ባለቤት ለመሆን ዝቅተኛ ገንዘብ የሚጠየቀው በአፋር፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በጋምቤላ ክልል ሲሆን የገንዘቡ መጠን ደግሞ 100000 ዶላር እንደሆነ ተደንግጓል።
አንድ የውጭ አገር ዜጋ በኢትዮጵያ ሊኖረው የሚችለው የቤት መጠን አንድ ብቻ ነው።በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ፈቃድ ወስዶ እያለማ ያለ ባለሀብት ግን ይህ ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን ሳይገድበው የአንድ ቤት ባለቤት መሆን ይችላል።
በመመሪያው መሠረት ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የተጠቀሰውን ለአንድ ቤት የሚያስፈልግ ገንዘብ የሚያስቀምጥበት የባንክ ሂሳብ እንዲከፈትለትና ገንዘቡን በውጭ ምንዛሬ እንዲያስቀምጥ የሚፈቅድ ደብዳቤ ከሚመለከተው መሥሪያ ቤት በማጻፍ በመረጠው ባንክ ገቢ ማድረግ አለበት።
አንድ የውጭ አገር ዜጋ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚያስችል ፈቃድ የሚያገኘው፤ የጸና ፓስፖርት ካለው፣ የወንጀል ታሪክ የሌለው ስለመሆኑ ከሚኖርበት አገር ማረጋገጫ ከሚመለከተው አካል ማስረጃ ማቅረብ ከቻለ ነው።
በተጨማሪም ከሀገር ሰላም፣ ደህንነት፣ ጸጥታ፣ የሕዝብ ጥቅም፣ የማኅበረሰብ ሞራል እና መሰል ጉዳዮች ላይ ገደብ የሌለበት መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃም ማቅረብ አለባቸው ይላል መመሪያው።
ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ በመንግሥት ቀጥተኛ ድጎማ ለዜጎች በሚሠሩ የጋራ መኖሪያ ሕንፃዎች ውስጥ የመኖሪያ ቤት ባለቤት መሆን አይችልም፤ ይህም የቤት ባለቤት በሚሆኑ የውጭ ዜጎች ላይ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ በወጣ አዋጅ የተጣለ ገደብ ነው።
በአዋጁ መሠረት የውጭ አገር ዜጋ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋም ወይም ምንጭ ገንዘብ መበደር ወይም ካፒታል ማሰባሰብ አይችልም።
በኢትዮጵያ የቤት ባለቤት የሆኑ የውጭ ዜጎችን መብት በተመለከተ ደግሞ መመሪያው ሲዘረዝር ለኢትዮጵያውያን የተሰጡ የንብረት መብቶች ይኖራቸዋል፤ ለግለሰቦች ማከራየት ይችላሉ፣ ለንግድ ዓላማ ማከራየት ግን አይቻልም።
ለራሱ እና ለቤተሰቡ የመኖሪያ ፈቃድ፣ የመግቢያ ቪዛና ኢትዮጵያ መመላለስ እንዲችሉ የሚያደርግ አግባብነት ባለው አካል የሚሰጥ እስከ አምስት ዓመት የሚያገለግል የብዙ ጊዜ መመላለሻ ቪዛ የማግኘት መብት አላቸው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሚያወጣው መመሪያ እና አሠራር መሠረት ከመኖሪያ ቤቱ በሕጋዊ መንገድ የሚያገኘውን የኪራይ ወይም የሽያጭ ገቢ በወቅቱ ተመን በውጭ ምንዛሪ ወደ ውጭ አገር የማስተላለፍ መብት አለው ይላል አዋጁ።
መመሪያው ታትሞ በፍትሕ ሚኒስቴር ድህረ ገጽ ላይ ከተጫነበት ቀን ጀምሮ ሥራ ላይ ይውላል ይላል።በፍትሕ ሚኒስቴር ድህረ ገጽ ላይ የተጫነው ባለፈው እሁድ ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።Via Sheger
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16🤣14👍2🤯1
ከራያ በጦርነት ስጋት የሚሰደዱ ሕጻናትና ወጣቶች የአጋቾች ሰለባ እየሆኑ ነው ተባለ
ከራያ አካባቢ በጦርነት ስጋት የሚሰደዱ ወጣቶችና ሕጻናት፣ ወደ የመን በሚያደርሱ ደላሎች አማካይነት የአጋቾች ሰለባ እየሆኑ መሆኑ ተገለጸ።
በቆቦ ከተማ ከራያ አላማጣ፣ ኮረም፣ ኦፍላ፣ ዛታና አካባቢዎቻቸው በጦርነት ምክንያት ከ100 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች ይገኛሉ ተብሏል።
አብዛኞቹ ወጣቶች የሆኑት ተፈናቃዮች የምግብና የመጠለያ እጥረት በመጋፈጣቸው ወደ ውጭ ለመሰደድ እየተገደዱ መሆኑ ተመላክቷል።
ይህንን ሁኔታ የሚጠቀሙ ደላሎችም ጉዞውን በነጻ እንደሚያስጀምሩ በመናገር ወጣቶችን እንደሚያግባቡ ተገልጿል።
የመን ከደረሱ በኋላ ግን በአጋቾች እጅ በመውደቅ ከፍተኛ የገንዘብ ክፍያ እንደሚጠየቁ ተነግሯል።
የጀርመን ድምጽ ያነጋገራቸው ወጣቶች፣ በስደት ጉዞ ላይ ችግር እንደሚገጥማቸው ቢያውቁም፣ በቆቦ ከተማ ካለው ኑሮ የተሻለ እንደሚሆን በማሰብ ስደትን እንደመረጡ ገልጸዋል።
ቀደም ሲል በአብዛኛው አዋቂዎች ይሰደዱ እንደነበር የገለጹት ወጣቶቹ፣ አሁን ግን ሕጻናትና ሴቶችም በስደቱ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል።
ወጣቶቹ በቆቦ ከተማ ተረጋግተው ከመቀመጥ ይልቅ በሕገወጥ መንገድ ወደ ዓረብ ሀገራት መጓዝን እንደሚመርጡም ዘገባው አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከራያ አካባቢ በጦርነት ስጋት የሚሰደዱ ወጣቶችና ሕጻናት፣ ወደ የመን በሚያደርሱ ደላሎች አማካይነት የአጋቾች ሰለባ እየሆኑ መሆኑ ተገለጸ።
በቆቦ ከተማ ከራያ አላማጣ፣ ኮረም፣ ኦፍላ፣ ዛታና አካባቢዎቻቸው በጦርነት ምክንያት ከ100 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች ይገኛሉ ተብሏል።
አብዛኞቹ ወጣቶች የሆኑት ተፈናቃዮች የምግብና የመጠለያ እጥረት በመጋፈጣቸው ወደ ውጭ ለመሰደድ እየተገደዱ መሆኑ ተመላክቷል።
ይህንን ሁኔታ የሚጠቀሙ ደላሎችም ጉዞውን በነጻ እንደሚያስጀምሩ በመናገር ወጣቶችን እንደሚያግባቡ ተገልጿል።
የመን ከደረሱ በኋላ ግን በአጋቾች እጅ በመውደቅ ከፍተኛ የገንዘብ ክፍያ እንደሚጠየቁ ተነግሯል።
የጀርመን ድምጽ ያነጋገራቸው ወጣቶች፣ በስደት ጉዞ ላይ ችግር እንደሚገጥማቸው ቢያውቁም፣ በቆቦ ከተማ ካለው ኑሮ የተሻለ እንደሚሆን በማሰብ ስደትን እንደመረጡ ገልጸዋል።
ቀደም ሲል በአብዛኛው አዋቂዎች ይሰደዱ እንደነበር የገለጹት ወጣቶቹ፣ አሁን ግን ሕጻናትና ሴቶችም በስደቱ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል።
ወጣቶቹ በቆቦ ከተማ ተረጋግተው ከመቀመጥ ይልቅ በሕገወጥ መንገድ ወደ ዓረብ ሀገራት መጓዝን እንደሚመርጡም ዘገባው አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10😢5👍3
በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው
በኢትዮጵያ በውርስ ወይም በስጦታ በሚገኙ ገቢዎች ላይ አዲስ የታክስ ዓይነት ሊጣል መሆኑ ተገለጸ።
ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የውርስና የስጦታ ገቢዎች ለዚህ ታክስ እንደሚዳረጉ ተመልክቷል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) የአምስተኛውን ዙር የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሪፎርም ግምገማ ተከተሎ ይፋ ባደረገው ባለ 132 ገጽ ሙሉ ሪፖርት እንደጠቆመው፣ የአገሪቱ የታክስ መሠረት በጣም ጠባብ በመሆኑ መንግሥት በየዓመቱ የአገር ውስጥ ገቢውን ለማሳደግ አዳዲስ የታክስ ዓይነቶችን ለመተግበር አቅዷል።
በዚሁ ሪፖርት መሠረት በውርስና ስጦታ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ ታክስ ይጣላል።
በሲጋራ፣ በአልኮልና በነዳጅ ምርቶች ላይ የሚጣለው ታክስ እንደሚጨምር የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም አገራዊ ገቢን ከመጨመር ባለፈ ለጤና ፖሊሲዎች አተገባበር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተመልክቷል።
የኢኮኖሚ ባለሙያው አቶ ዋሲሁን በላይ በሰጡት አስተያየት፣ እነዚህ አዳዲስ የታክስ እርምጃዎች በአጠቃላይ በአገሪቱ ኢኮኖሚና በህብረተሰቡ ላይ ተጨማሪ ጫና ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
ሆኖም መንግሥት አገራዊ ገቢውን ለማሳደግ ሲል ውሳኔዎቹን በቁርጠኝነት እንደሚተገብራቸው ይጠበቃል ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በኢትዮጵያ በውርስ ወይም በስጦታ በሚገኙ ገቢዎች ላይ አዲስ የታክስ ዓይነት ሊጣል መሆኑ ተገለጸ።
ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የውርስና የስጦታ ገቢዎች ለዚህ ታክስ እንደሚዳረጉ ተመልክቷል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) የአምስተኛውን ዙር የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሪፎርም ግምገማ ተከተሎ ይፋ ባደረገው ባለ 132 ገጽ ሙሉ ሪፖርት እንደጠቆመው፣ የአገሪቱ የታክስ መሠረት በጣም ጠባብ በመሆኑ መንግሥት በየዓመቱ የአገር ውስጥ ገቢውን ለማሳደግ አዳዲስ የታክስ ዓይነቶችን ለመተግበር አቅዷል።
በዚሁ ሪፖርት መሠረት በውርስና ስጦታ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ ታክስ ይጣላል።
በሲጋራ፣ በአልኮልና በነዳጅ ምርቶች ላይ የሚጣለው ታክስ እንደሚጨምር የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም አገራዊ ገቢን ከመጨመር ባለፈ ለጤና ፖሊሲዎች አተገባበር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተመልክቷል።
የኢኮኖሚ ባለሙያው አቶ ዋሲሁን በላይ በሰጡት አስተያየት፣ እነዚህ አዳዲስ የታክስ እርምጃዎች በአጠቃላይ በአገሪቱ ኢኮኖሚና በህብረተሰቡ ላይ ተጨማሪ ጫና ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
ሆኖም መንግሥት አገራዊ ገቢውን ለማሳደግ ሲል ውሳኔዎቹን በቁርጠኝነት እንደሚተገብራቸው ይጠበቃል ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡17🤣9❤6👍3🤔2😢1💔1
በኮሎምቢያ በተከሰተ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢያንስ 132 ሰዎች ሲሞቱ 480 ተጎዱ።
በበርካታ ሕንጻዎች ፍርስራሽ ሥር ሰዎች ተቀብረዋል የሚል ስጋት በመኖሩ የሟቾች ብዛት ከ132 ሊጨምር እንደሚችልም ተገልጿል።
በኮሎምቢያ ከባድ መሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተ ሲሆን፣ ይህም በሬክተር ስኬል 7.4 ሆኖ ተመዝግቧል። በቾኮ ግዛት የተከሰተው አደጋው ከመሬት በ103 ኪሎሜትር በታች የተከሰተ እንደሆነ የአገሪቱ የጂኦሎጂካል አገልግሎት አሳውቋል።
በመሬት መንቀጥቀጥ ከ480 በላይ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል። ከመሬት መንቀጥቀጥ መነሻ 55 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ፒሬራ ከተማ የከፋው ጉዳት ተመዝግቧል።
ቢቢሲ ትክክለኛነቱን አረጋገጥኩት ያለው አንድ ቪዲዮ፣ 'ፕላዛ ቦሊቫር' በተባለው የከተማው ዋና አደባባይ የሚገኝ አንድ ሕንፃ ሲደርመስ አሳይቷል። በርካታ ሰዎች ተሰብስበውበት የነበረ ስፍራ በፍርስራሽ እና አቧራ ሲሞላም ይታያል።
በከተማው 40 ሰዎች መሞታቸውን እና 65 ሕንፃዎች መፍረሳቸውን የአካባቢው ባለሥልጣናት ተናግረዋል። በ15ቱ ሕንፃዎች ፍርስራሽ ስር ሰዎች ተቀብረው ሊሆን እንደሚችልም ይታመናል።
ከመሬት መንቀጥቀጡ መነሻ 200 ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት ላይ የምትገኘው ካሊ ከተማ ውስጥ ደግሞ 32 ሕንፃዎች ፈርሰዋል።
በቾኮ እና ቫሌ ዴል ካውካ ግዛቶች በሚገኙት ማኒዛሌስ፣ ኪብዶ እና ሜዴሊን ከተሞችም የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተዘግቧል። ንዝረቱ በጎረቤት አገራት ቬንዙዌላ፣ ኢኳዶር እና ፓናማም ደርሶባቸዋል።
የአሁኑ አደጋ የተከሰተበት ኮሎምቢያ አጎራባች በሆነችው ቬንዙዌላ ከ6 ሺሕ በላይ ሰዎች በተመሳሳይ አደጋ መሞታቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። #Bbc
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በበርካታ ሕንጻዎች ፍርስራሽ ሥር ሰዎች ተቀብረዋል የሚል ስጋት በመኖሩ የሟቾች ብዛት ከ132 ሊጨምር እንደሚችልም ተገልጿል።
በኮሎምቢያ ከባድ መሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተ ሲሆን፣ ይህም በሬክተር ስኬል 7.4 ሆኖ ተመዝግቧል። በቾኮ ግዛት የተከሰተው አደጋው ከመሬት በ103 ኪሎሜትር በታች የተከሰተ እንደሆነ የአገሪቱ የጂኦሎጂካል አገልግሎት አሳውቋል።
በመሬት መንቀጥቀጥ ከ480 በላይ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል። ከመሬት መንቀጥቀጥ መነሻ 55 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ፒሬራ ከተማ የከፋው ጉዳት ተመዝግቧል።
ቢቢሲ ትክክለኛነቱን አረጋገጥኩት ያለው አንድ ቪዲዮ፣ 'ፕላዛ ቦሊቫር' በተባለው የከተማው ዋና አደባባይ የሚገኝ አንድ ሕንፃ ሲደርመስ አሳይቷል። በርካታ ሰዎች ተሰብስበውበት የነበረ ስፍራ በፍርስራሽ እና አቧራ ሲሞላም ይታያል።
በከተማው 40 ሰዎች መሞታቸውን እና 65 ሕንፃዎች መፍረሳቸውን የአካባቢው ባለሥልጣናት ተናግረዋል። በ15ቱ ሕንፃዎች ፍርስራሽ ስር ሰዎች ተቀብረው ሊሆን እንደሚችልም ይታመናል።
ከመሬት መንቀጥቀጡ መነሻ 200 ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት ላይ የምትገኘው ካሊ ከተማ ውስጥ ደግሞ 32 ሕንፃዎች ፈርሰዋል።
በቾኮ እና ቫሌ ዴል ካውካ ግዛቶች በሚገኙት ማኒዛሌስ፣ ኪብዶ እና ሜዴሊን ከተሞችም የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተዘግቧል። ንዝረቱ በጎረቤት አገራት ቬንዙዌላ፣ ኢኳዶር እና ፓናማም ደርሶባቸዋል።
የአሁኑ አደጋ የተከሰተበት ኮሎምቢያ አጎራባች በሆነችው ቬንዙዌላ ከ6 ሺሕ በላይ ሰዎች በተመሳሳይ አደጋ መሞታቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። #Bbc
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
💔8❤6👍3
ግልገል በለስ‼️
በጋራ ግልገል በለስ ከተማን ለመቆጣጠር ሞክረዋል - የመተከል ዞን አስተዳደር‼️
የመተከል ዞን አስተዳደር የፋኖ ሀይሎችና የጉሙዝ ሀይሎች ግልገል በለስ ከተማን ዛሬ ማለትም ነሐሴ 5/2018 ከንጋቱ 12:00 ሰዓት አካባቢ ለመቆጣጠር ሞክረው እንደነበረ ገለፀ።
የዞኑ አስተዳደር ይሄ ኦፕሬሽን እንዳልተሳካና ከተማውም ወደ ቀድሞ ሰላሙ መመለሱን አስታውቋል።
በከተማዋ ዋና መንገድ መድፍ ጭምር ሲንቀሳቀስ እንደነበር የከተማዋ ነዋሪዎች ለአዩዘሀበሻ የገለፁ ሲሆን ጠዋት አካባቢ በከተማ መናኸሪያ ውስጥ ፈንጂ በማፈንዳት በርካታ ተሳፋሪዎች እንደተጎዱ እና እንዲሁም 10 ሰዎች እንደሞቱ ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል። ተጎጂዎች ፓዊ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ገልፀውልናል።
ምስል:- ከግልገል በለስ ከተማ(የመድፍ እንቅስቃሴ)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በጋራ ግልገል በለስ ከተማን ለመቆጣጠር ሞክረዋል - የመተከል ዞን አስተዳደር‼️
የመተከል ዞን አስተዳደር የፋኖ ሀይሎችና የጉሙዝ ሀይሎች ግልገል በለስ ከተማን ዛሬ ማለትም ነሐሴ 5/2018 ከንጋቱ 12:00 ሰዓት አካባቢ ለመቆጣጠር ሞክረው እንደነበረ ገለፀ።
የዞኑ አስተዳደር ይሄ ኦፕሬሽን እንዳልተሳካና ከተማውም ወደ ቀድሞ ሰላሙ መመለሱን አስታውቋል።
በከተማዋ ዋና መንገድ መድፍ ጭምር ሲንቀሳቀስ እንደነበር የከተማዋ ነዋሪዎች ለአዩዘሀበሻ የገለፁ ሲሆን ጠዋት አካባቢ በከተማ መናኸሪያ ውስጥ ፈንጂ በማፈንዳት በርካታ ተሳፋሪዎች እንደተጎዱ እና እንዲሁም 10 ሰዎች እንደሞቱ ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል። ተጎጂዎች ፓዊ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ገልፀውልናል።
ምስል:- ከግልገል በለስ ከተማ(የመድፍ እንቅስቃሴ)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16💔3👍2🤪2
ባለቤቱን በመግደል የተከሰሰው ግለሰብ በ21 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።
በአዲግራት ከተማ ቀበሌ 06 ዞን 6 ነዋሪ የሆነው አቶ ሳምሶም ሓጎስ አብርሃ የተባለው ተከሳሽ የሁለት ልጆቹ እናት የሆነችውን የ22 ዓመቷን ባለቤቱን ወይዘሮ ቅሳነት ተሾመን መጋቢት 8 ቀን 2017 ዓ.ም በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በፈፀመው አሰቃቂ የነፍስ ግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ነው በ21 አመት ከ 3 ወር ፅኑ እስራት የተቀጣው።
የምስራቅ ትግራይ ዞን ዓቃቤ ሕግ አቶ መሓሪ እንደገለፁት ተከሳሹ በከባድ የነፍስ ግድያ ወንጀል ተከሰሶ ጥፋተኛነቱ ከተረጋገጠ በኋላ ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ከዚህ ቀደም ወንጀል ፈፅሞ የማያውቅ እና ቤተሰብ አስተዳዳሪ የነበረ መሆኑን እንደ ማቅለያ እንዲሁም ሁለት የማክበጃ ነጥቦችን በመያዝ ሕግን መሰረት ያደረገ ውሳኔ ሰጥቷል ብለዋል።
በአዲግራት ከተማ የሴቶች ማህበር ሊቀመንበር እና የሴቶች ጉዳይ ፅህፈት ቤት በበኩሉ በአሁኑ ወቅት በሴቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው ጥቃት እና ነፍስ ግድያ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ገልጾ የሕግ ባለሙያዎች ግንዛቤ እንዲፈጥሩ እና ማህበራትም ተጎጂዎች ፈጣን ፍትህ የሚያገኙበትን ሁኔታ እንዲያመቻቹ ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል የተበዳይ ቤተሰቦች ፍትህ ለማግኘት ረጅም ጊዜ እንደወሰደባቸው በመግለፅ የፍርድ ቤቱን የቅጣት ውሳኔ እንዳልተቀበሉትና ደስተኛ እንዳልሆኑ መግለፃቸውን ብስራት ከአዲግራት ከተማ የኮሚኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአዲግራት ከተማ ቀበሌ 06 ዞን 6 ነዋሪ የሆነው አቶ ሳምሶም ሓጎስ አብርሃ የተባለው ተከሳሽ የሁለት ልጆቹ እናት የሆነችውን የ22 ዓመቷን ባለቤቱን ወይዘሮ ቅሳነት ተሾመን መጋቢት 8 ቀን 2017 ዓ.ም በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በፈፀመው አሰቃቂ የነፍስ ግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ነው በ21 አመት ከ 3 ወር ፅኑ እስራት የተቀጣው።
የምስራቅ ትግራይ ዞን ዓቃቤ ሕግ አቶ መሓሪ እንደገለፁት ተከሳሹ በከባድ የነፍስ ግድያ ወንጀል ተከሰሶ ጥፋተኛነቱ ከተረጋገጠ በኋላ ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ከዚህ ቀደም ወንጀል ፈፅሞ የማያውቅ እና ቤተሰብ አስተዳዳሪ የነበረ መሆኑን እንደ ማቅለያ እንዲሁም ሁለት የማክበጃ ነጥቦችን በመያዝ ሕግን መሰረት ያደረገ ውሳኔ ሰጥቷል ብለዋል።
በአዲግራት ከተማ የሴቶች ማህበር ሊቀመንበር እና የሴቶች ጉዳይ ፅህፈት ቤት በበኩሉ በአሁኑ ወቅት በሴቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው ጥቃት እና ነፍስ ግድያ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ገልጾ የሕግ ባለሙያዎች ግንዛቤ እንዲፈጥሩ እና ማህበራትም ተጎጂዎች ፈጣን ፍትህ የሚያገኙበትን ሁኔታ እንዲያመቻቹ ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል የተበዳይ ቤተሰቦች ፍትህ ለማግኘት ረጅም ጊዜ እንደወሰደባቸው በመግለፅ የፍርድ ቤቱን የቅጣት ውሳኔ እንዳልተቀበሉትና ደስተኛ እንዳልሆኑ መግለፃቸውን ብስራት ከአዲግራት ከተማ የኮሚኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13🤯4👍3
በደቡብ ትግራይ ተፈጸመ በተባለ የድሮን ጥቃት በኢትዮጵያ መንግሥት እና በትግራይ ባለሥልጣናት መካከል ያለው ውጥረት ዳግም አገረሸ
ህወሓት የፌደራል መንግሥት ኃይሎች ሰኞ ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በደቡብ ትግራይ የድሮን ጥቃት ፈጽሟል ሲል መክሰሱን ተከትሎ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና በትግራይ ክልል ባለሥልጣናት መካከል ያለው ውጥረት ዳግም ማገረሹ ተገለጸ።
በጥቃቱ በደረሰው የጉዳት መጠን እና በኢላማዎቹ ላይ የተለያዩ ዘገባዎች እየወጡ ይገኛሉ።
ጥቃቱ የተፈጸመው በአማራ ክልል አዋሳኝ አቅራቢያ በራያ አላማጣ ወረዳ መረዋ ቀበሌ ውስጥ መሆኑ ተዘግቧል።
ኤኤፍፒ (AFP) የትግራይ ባለሥልጣናትን እና የሕክምና ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ በጥቃቱ አንዲት ሴት እና ሶስት ወንዶችን ጨምሮ ሶስት የትግራይ ኃይል አባላት ቆስለዋል።
የህወሓት ምክትል ሊቀ መንበር አማኑኤል አሰፋ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በመረዋ የድሮን ጥቃት ፈጽሟል ሲሉ ለኤኤፍፒ ተናግረዋል።
ጥቃቱ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መታቱን የተናገሩ ሲሆን፣ ኤኤፍፒ ግን ይህንን መረጃ በተናጠል ማረጋገጥ አለመቻሉን ገልጻል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ህወሓት የፌደራል መንግሥት ኃይሎች ሰኞ ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በደቡብ ትግራይ የድሮን ጥቃት ፈጽሟል ሲል መክሰሱን ተከትሎ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና በትግራይ ክልል ባለሥልጣናት መካከል ያለው ውጥረት ዳግም ማገረሹ ተገለጸ።
በጥቃቱ በደረሰው የጉዳት መጠን እና በኢላማዎቹ ላይ የተለያዩ ዘገባዎች እየወጡ ይገኛሉ።
ጥቃቱ የተፈጸመው በአማራ ክልል አዋሳኝ አቅራቢያ በራያ አላማጣ ወረዳ መረዋ ቀበሌ ውስጥ መሆኑ ተዘግቧል።
ኤኤፍፒ (AFP) የትግራይ ባለሥልጣናትን እና የሕክምና ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ በጥቃቱ አንዲት ሴት እና ሶስት ወንዶችን ጨምሮ ሶስት የትግራይ ኃይል አባላት ቆስለዋል።
የህወሓት ምክትል ሊቀ መንበር አማኑኤል አሰፋ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በመረዋ የድሮን ጥቃት ፈጽሟል ሲሉ ለኤኤፍፒ ተናግረዋል።
ጥቃቱ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መታቱን የተናገሩ ሲሆን፣ ኤኤፍፒ ግን ይህንን መረጃ በተናጠል ማረጋገጥ አለመቻሉን ገልጻል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤23👍3👀1
ሶስት አሠልጣኞችና አራት አትሌቶች አሜሪካ ፖርትላንድ ላይ ኮበለሉ!
🔴 ቡድኑ በቺካጎ አድርጎ ወደ አዲስ አበባ ሲመለስ 7 የቡድኑ አባላት ከልዑካን ቡድኑ ጋር የሉም
🔴 የአሜሪካኗ ዩጂን ኦሪገን ለኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ ውጤት የሚመዘገብባት ከተማ ብቻ ሳትሆን በርካቶች የሚኮበልሉባት ታሪካዊ ከተማም ሆና ተመዝግባለች
✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት)
በአሜሪካ ኦሪገን ዩጂን ሲካሄድ የነበረው ከ20 ዓመት በታች 21ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና መጠናቀቁ ይታወሳል።
ወደ ውድድሩ ስፍራ የተጓዘችው ሀገራችን ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው 2 ወርቅ፣3 ብር እና 1 ነሃስ በድምሩ 6 ሜዳሊያ ማግኘቷም ይታወቃል።
ከወደ ኦሪገን ከደቂቃዎች በፊት የደረሠን አስደንጓጭ ዜና ለሻምፒዮናው ከተጓዙት የልዑኳን ቡድን አባላት መካከል ሰባቱ ፖሬትላንድ ላይ መኮብለላቸው ተረጋግጧል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ የልዑካን ቡድን በአሁን ሠዓት ከፖርትላንድ ተነስቶ ወደ ቺካጎ አየር ማረፊያ እየተጓዘ ሲሆን እነዚሁ ሰባቱ የቡድኑ አባላት ከልዑኳን ቡድኑ ተለይተው መቅረታቸውን ነው ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ያረጋገጠችው።
እንደ ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን ከሆነ ከሄዱት አራት አሠልጣኞች ሶስቱ ከቡድኑ ጋር ባለመመለሳቸው በአሁን ሠዓት ወደ ኢትዮጵያ በመገስገስ ላይ በሚገኘው አውሮፕላን ውስጥ አንድ አሠልጣኝ ማለትም አሠልጣኝ መሠረት ብቻ እንደሚገኝ ነው ምንጮቻችን የገለፁልን።
አትሌቶቻችን በተመለከተ አራት አትሌቶች እንደኮበለሉ የገለፁልን የመረጃ ምንጮቻችን በወኪንግ፣በ800፣በ5ሺ እና በ3ሺ መሠናክል ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ከቡድኑ ጋር አብረው እንዳልተመለሱና እንደኮበለሉ ነው የመረጃ ምንጮቻችን ጨምረው የገለፁልን።
የአትሌቶቹና የአሠልጣኞቹ ሙሉ ስም የደረሳት ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ለቤተሠቦቻቸውና ለደህንነታቸው ስትል የሁሉንም ስም ይፋ ከማድረግ ተቆጥባለች።
የአሜሪካኗ ዩጂን ኦሪገን ለኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ ውጤት የሚመዘገብባት ከተማ ቤቻ ሳትሆን በርካታ አትሌቶች፣አሠልጣኞችና አመራሮች የሚኮበልሉባት ታሪካዊ ከተማ ሆና ተመዝግባለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🔴 ቡድኑ በቺካጎ አድርጎ ወደ አዲስ አበባ ሲመለስ 7 የቡድኑ አባላት ከልዑካን ቡድኑ ጋር የሉም
🔴 የአሜሪካኗ ዩጂን ኦሪገን ለኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ ውጤት የሚመዘገብባት ከተማ ብቻ ሳትሆን በርካቶች የሚኮበልሉባት ታሪካዊ ከተማም ሆና ተመዝግባለች
✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት)
በአሜሪካ ኦሪገን ዩጂን ሲካሄድ የነበረው ከ20 ዓመት በታች 21ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና መጠናቀቁ ይታወሳል።
ወደ ውድድሩ ስፍራ የተጓዘችው ሀገራችን ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው 2 ወርቅ፣3 ብር እና 1 ነሃስ በድምሩ 6 ሜዳሊያ ማግኘቷም ይታወቃል።
ከወደ ኦሪገን ከደቂቃዎች በፊት የደረሠን አስደንጓጭ ዜና ለሻምፒዮናው ከተጓዙት የልዑኳን ቡድን አባላት መካከል ሰባቱ ፖሬትላንድ ላይ መኮብለላቸው ተረጋግጧል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ የልዑካን ቡድን በአሁን ሠዓት ከፖርትላንድ ተነስቶ ወደ ቺካጎ አየር ማረፊያ እየተጓዘ ሲሆን እነዚሁ ሰባቱ የቡድኑ አባላት ከልዑኳን ቡድኑ ተለይተው መቅረታቸውን ነው ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ያረጋገጠችው።
እንደ ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን ከሆነ ከሄዱት አራት አሠልጣኞች ሶስቱ ከቡድኑ ጋር ባለመመለሳቸው በአሁን ሠዓት ወደ ኢትዮጵያ በመገስገስ ላይ በሚገኘው አውሮፕላን ውስጥ አንድ አሠልጣኝ ማለትም አሠልጣኝ መሠረት ብቻ እንደሚገኝ ነው ምንጮቻችን የገለፁልን።
አትሌቶቻችን በተመለከተ አራት አትሌቶች እንደኮበለሉ የገለፁልን የመረጃ ምንጮቻችን በወኪንግ፣በ800፣በ5ሺ እና በ3ሺ መሠናክል ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ከቡድኑ ጋር አብረው እንዳልተመለሱና እንደኮበለሉ ነው የመረጃ ምንጮቻችን ጨምረው የገለፁልን።
የአትሌቶቹና የአሠልጣኞቹ ሙሉ ስም የደረሳት ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ለቤተሠቦቻቸውና ለደህንነታቸው ስትል የሁሉንም ስም ይፋ ከማድረግ ተቆጥባለች።
የአሜሪካኗ ዩጂን ኦሪገን ለኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ ውጤት የሚመዘገብባት ከተማ ቤቻ ሳትሆን በርካታ አትሌቶች፣አሠልጣኞችና አመራሮች የሚኮበልሉባት ታሪካዊ ከተማ ሆና ተመዝግባለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤21👌18🤣14👍6🏆2👀1🙊1
አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Photo
በአዲስ አበባ ከተማ የ26 ዓመቷ እናት አራት ህፃናትን በአንድ ጊዜ በሰላም ተገላገለች።
በአዲስ አበባ በሚገኘው ጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል የ26 ዓመቷ እናት አራት ህፃናትን በአንድ ጊዜ በሰላም መገላገሏ ተሰምቷል።
እናትየዋ አራት ፅንሶችን መፀነሷ በእርግዝና ክትትል ወቅት መለየቱን የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅና የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ዶ/ር እሸቱ ታደለ ገልጸዋል።
አራት ፅንሶችን የያዘ እርግዝና ለእናቲቱም ሆነ ለሚወለዱት ህፃናት ከፍተኛ ክትትልና ጥንቃቄ የሚፈልግ በመሆኑ የወሊድ ቀኗ ከመድረሱ ከአንድ ወር በፊት ጀምሮ በሆስፒታሉ ዋርድ እንድትቆይ ተደርጎ የሌት ተቀን ክትትል ሲደረግላት ቆይታለች።
በወሊድ ወቅትም ለአራቱ ጨቅላ ህፃናት የሚያስፈልጉ ማረፊያዎችና የድጋፍ መሳሪያዎች አስቀድመው መዘጋጀታቸውን ዶ/ር እሸቱ መግለፃቸውን ብስራት ሬዲዮ ከጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
በዶ/ር እሸቱ ታደለና በማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ናትናኤል የተመራው የህክምና ቡድን የቀዶ ጥገና ሂደቱን በስኬት ማጠናቀቁን ሆስፒታሉ አስታውቋል።እናትየው እና አራቱ ህፃናት በአሁኑ ወቅት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በሆስፒታሉ ከሦስት ዓመት በፊት የ24 ዓመቷ እናት በሪፈር ከጤና ጣቢያ መጥታ አራት ህፃናትን በሰላም መገላገሏ ተገልጿል።
ተቋሙ በዘመናዊ የህክምና ቴክኖሎጂና መሳሪያዎች የተደራጀ ሲሆን በየህክምናው ዘርፍ የተሰማሩ ስፔሻሊስቶችና ቁርጠኛ የጤና ባለሙያዎች መኖራቸው ለተሳካው የህክምና ሂደት አስተዋፅዖ አድርጓል ተብሏል።
ሆስፒታሉ በተለይም ለእናቶችና ህፃናት ጤና ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጥ እና እንደዚህ ያሉ ከፍተኛ ጥንቃቄና ልዩ ክትትል የሚፈልጉ እርግዝናዎችን በተሳካ ሁኔታ ማስተናገድ የ“እናት ጤና፣ ልጅም ደህና” የሚለውን የጤና መርህ በተግባር ማዋል አንዱ ማሳያ ነው ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአዲስ አበባ በሚገኘው ጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል የ26 ዓመቷ እናት አራት ህፃናትን በአንድ ጊዜ በሰላም መገላገሏ ተሰምቷል።
እናትየዋ አራት ፅንሶችን መፀነሷ በእርግዝና ክትትል ወቅት መለየቱን የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅና የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ዶ/ር እሸቱ ታደለ ገልጸዋል።
አራት ፅንሶችን የያዘ እርግዝና ለእናቲቱም ሆነ ለሚወለዱት ህፃናት ከፍተኛ ክትትልና ጥንቃቄ የሚፈልግ በመሆኑ የወሊድ ቀኗ ከመድረሱ ከአንድ ወር በፊት ጀምሮ በሆስፒታሉ ዋርድ እንድትቆይ ተደርጎ የሌት ተቀን ክትትል ሲደረግላት ቆይታለች።
በወሊድ ወቅትም ለአራቱ ጨቅላ ህፃናት የሚያስፈልጉ ማረፊያዎችና የድጋፍ መሳሪያዎች አስቀድመው መዘጋጀታቸውን ዶ/ር እሸቱ መግለፃቸውን ብስራት ሬዲዮ ከጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
በዶ/ር እሸቱ ታደለና በማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ናትናኤል የተመራው የህክምና ቡድን የቀዶ ጥገና ሂደቱን በስኬት ማጠናቀቁን ሆስፒታሉ አስታውቋል።እናትየው እና አራቱ ህፃናት በአሁኑ ወቅት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በሆስፒታሉ ከሦስት ዓመት በፊት የ24 ዓመቷ እናት በሪፈር ከጤና ጣቢያ መጥታ አራት ህፃናትን በሰላም መገላገሏ ተገልጿል።
ተቋሙ በዘመናዊ የህክምና ቴክኖሎጂና መሳሪያዎች የተደራጀ ሲሆን በየህክምናው ዘርፍ የተሰማሩ ስፔሻሊስቶችና ቁርጠኛ የጤና ባለሙያዎች መኖራቸው ለተሳካው የህክምና ሂደት አስተዋፅዖ አድርጓል ተብሏል።
ሆስፒታሉ በተለይም ለእናቶችና ህፃናት ጤና ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጥ እና እንደዚህ ያሉ ከፍተኛ ጥንቃቄና ልዩ ክትትል የሚፈልጉ እርግዝናዎችን በተሳካ ሁኔታ ማስተናገድ የ“እናት ጤና፣ ልጅም ደህና” የሚለውን የጤና መርህ በተግባር ማዋል አንዱ ማሳያ ነው ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤33👍12🙉9🤔3🥰1