አዲስ ሪፖርተር - NEWS
36.1K subscribers
17.2K photos
421 videos
22 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
ኢዜማ ከሀገራዊ ምክክሩ ምን ይፈልጋል?

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) መሪ አቶ እዮብ መሳፍንት ፓርቲያቸው ወደ ሀገራዊ ምክክሩ መድረክ የገባው ለአጭር ጊዜ የሥልጣን መጋራት ስምምነት ሳይሆን መሠረታዊና ሥርዓታዊ ለውጥ ለማምጣት ታግሎ ለመለወጥ መሆኑን አሳሰቡ።

መሪው አክለውም ኢዜማ እስከ ምክክሩ መዝጊያ ቀን ድረስ በማይበገር አቋም የዜግነት ፖለቲካን፣ የነፃና ገለልተኛ መንግሥታዊ ተቋማትን ግንባታ እንዲሁም በብቃት ላይ የተመሠረተ ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ሥርዓት መዘርጋትን እንደ ዋና መሠረታዊ ምሰሶዎች አድርጎ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

  ትውልዱን ከግጭትና ከመከፋፈል አዙሪት ነፃ ለማውጣትና ጠንካራ ሀገራዊ ሥርዓት ለመገንባት እነዚህን መርሆዎች እውን ማድረግ እንደሚያስፈልግ የጠቆሙት አቶ እዮብ፣ የዜጋ ክብር ፍጹምና የማይደፈር የሆነባትን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ በጋራ እውን እስከሚደረግ ድረስ ፓርቲያቸው ያለማቋረጥ እንደሚታገል አጽንኦት ሰጥተዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
19🤣5👍4
ከ2010 በኋላ የወጡ አብዛኛዎቹ አዋጆች በችኮላ የተዘጋጁ በመሆናቸው በተደጋጋሚ እንዲሸሻሉ መደረጋቸው በጥናት ተመላከተ

ከ2010 ዓ.ም. በኋላ የወጡ አብዛኛዎቹ አዋጆች በችኮላ የተዘጋጁ በመሆናቸው ለተደጋጋሚ ማሻሻያ መጋለጣቸውንና ከአዋጆቹ ድንጋጌዎች ጋር የሚጋጩ ደንቦችና መመሪያዎች እንዲወጡ ምክንያት መሆናቸውን የፌደራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ጥናት አመላከተ።

ኢንስቲትዩቱ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከሌሎች አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር ባካሄዳቸው አምስት ጥናቶች ላይ ባደረገው የማጽደቂያ ዓውደ ጥናት ግኝቶቹን አቅርቧል።

ጥናቱ ከ2010 እስከ 2018 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጡ ሁሉንም አዋጆች የሸፈነ ሲሆን፣ በሀገሪቱ የሕግ አወጣጥ ሥርዓት መረጋጋትን የሚመለከት የተለየ ፖሊሲ እንደሌለ ጠቁሟል።

ለአብነትም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን እንደገና ለማቋቋም የወጣው አዋጅ በተመሳሳይ ዓመት በሌላ አዋጅ መሻሻሉንና ከሁለት ዓመት በኋላም በ2015 ዓ.ም. እንደገና መሻሻሉን ጥናቱ አመላክቷል።

በተጨማሪም አንዳንድ አዋጆች ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚጋጩ ድንጋጌዎች እንዳሏቸው ጥናቱ ጠቁሟል።

በሕገ መንግሥቱ ውስጥም አሻሚ ቃላት፣ ግልጽነት የጎደላቸው አንቀጾችና አንዳንድ የሚጋጩ መርሆዎች መኖራቸውን ጥናቱ አመላክቶ፣ የሕገ መንግሥቱ ትርጓሜ ጉዳይ በጥናት እንዲታይ ምክረ ሃሳብ አቅርቧል።

ደንቦችና መመሪያዎች በየጊዜው ሲሻሻሉም በቂ ጥናትና ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ ጥናቱ አሳስቧል።ዘገባው የሪፖርተር ነው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
6👍4
የኤሌክትሪክ ኃይል አዲስ ኃይል ማስገቢያ የዱቤ ክፍያ ወለድ ሙሉ በሙሉ ተነሳ‼️

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አዲስ ኃይል ማስገቢያ ክፍያን በዱቤ ለሚከፍሉ ደንበኞች ይጠየቅ የነበረውን ከ3 እስከ 9 በመቶ የወለድ ክፍያ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጅነር ጌቱ ገረመው አስታወቁ።

ቀደም ሲል የዱቤ ክፍያ ጊዜው እስከ 24 ወራት ሲሆን፣ ከ6 ወራት በላይ ለሚቆይ ክፍያ ወለድ ይጣል ነበር።

አሁን ወለዱ መነሳቱ ክፍያውን በአንድ ጊዜ መፈጸም ለማይችሉ ዜጎች የምስራች መሆኑንና አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ከሰኔ 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በተጀመረው የአዲስ ቆጣሪ የዱቤ አሰራር በሁለት ሳምንታት ብቻ 19,231 አዳዲስ ደንበኞች ኤሌክትሪክ ማግኘት ችለዋል።

ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት 664,505 አዳዲስ ደንበኞችን ያገናኘ ሲሆን፣ በ2019 ዓ.ም. ደግሞ 1.1 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞችን ለማገናኘት አቅዷል።

ኢንጅነር ጌቱ እንደገለጹት፣ አገልግሎቱ በ70 ዓመታት ታሪኩ 5.88 ሚሊዮን ደንበኞችን ማገናኘት ችሏል፤ አሁን ግን በዓመት እስከ 1 ሚሊዮን ደንበኞችን የማገናኘት አቅም ላይ ደርሷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
11👍4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🌟 ለወደፊት ህይወትዎ አሁን ይወስኑ፡ ወጣት ሴቶች የአላቡጋ ስታርትን ለምን ይመርጣሉ?🌟

የአላቡጋ ስታርት ግልጽ እና ከወጪ ነፃ የሆነየሥራ ስምሪት ፕሮግራም በመሆኑ በብዙዎች ተመራጭ ሆኗል። የፋይናንስ እንቅፋቶችን በማስወገድ፣ የተረጋጋ ሥራ፣ የተረጋገጠ ገቢ እና ምቹ ማረፊያ በማቅረብ፣ ይህ ፕሮግራም ተሳታፊዎች ሙሉ በሙሉ የወደፊት ሕይወታቸውን በመገንባት እና ጠቃሚ ዓለም አቀፍ ልምድ በማግኘት ላይ እንዲያተኩሩ ይረዳል። ለዚህም ነው ብዙ ወጣት ሴቶች በሩሲያ ውስጥ የአላቡጋ ስታርት ፕሮግራምን የሚመርጡት - ሁሉም አስፈላጊ ነገሮች በዜሮ ዋጋ ስለሚሸፈኑ።

በአላቡጋ ስታርት ኢንተርናሽናል ፕሮግራም ከ18 እስከ 22 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሴቶች ጥራት ላለው ስልጠና እና ስታርት አፕ እድሎች ማመልከት ይችላሉ። ተሳታፊዎች ጥሩ ደመወዝ፣ ነፃ የአየር ዋጋ፣ የህክምና መድን፣ የተደገፈ መኖሪያ ቤት እና ነፃ የሩሲያ ቋንቋ ኮርሶችን ያገኛሉ። ፕሮግራሙ ምርትን፣ የምግብ አገልግሎትን፣ አቅርቦትን እና መስተንግዶን ጨምሮ ስምንት የስራ ስምሪት ዘርፎችን ይሸፍናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለማመልከት የአላቡጋ ስታርት የስፖርት ፖርታልን ይጎብኙ፡ https://start-alabuga.com
5
693 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከፌደራልና ከክልል ፖሊስ አባላት ጋር በመሆን ከሀምሌ 23 እስከ ሀምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው ክትትል የተያዙት 648 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር የገቢ እንዲሁም 44 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የሚገመቱ የወጭ ኮንትሮባንድ እቃዎች ናቸው፡፡

በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አዳዲስና ልባሽ ጨርቆች፣ የግብርና ምርቶች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድኃኒት፣ ማዕድናት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳትና የውጭ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን ባከናወነው ክትትል ህብረተሰቡ ከፍተኛ ትብብር ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን፥ በፍተሻ፣ በጥቆማና በበረራ ከተያዙ የኮንትሮባንድ እቃዎች በተጨማሪ ሲያዘዋውሩ የተገኙ 30 ተጠርጣሪዎችና 17 ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን ተጽእኖ ለመከላከል ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
12👍4
ተጨማሪ መረጃ‼️
ዛሬ ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት አካባቢ በራያ አላማጣ ወረዳ በመረዋ ንዑስ ወረዳ የተፈፀመው የድሮን ጥቃት በአራት ዙር መሆኑን የአካባቢው ምንጮች ገልፀውልናል።
እንደ የአካባቢው ምንጮች ገለጻ፣ ጥቃቱ:-
📌በመረዋ 2ኛ ደረጃ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተሰበሰቡ ታጣቂዎች ላይ
▪️📌በችግኝ ጣቢያው አካባቢ በተሰበሰቡ ታጣቂዎች ላይ
📌ከቤተ-ክርስቲያን አለፍ ብሎ ባለው ዋርካ (ዳዕሮ) ዛፍ ስር በተሰበሰቡ ታጣቂዎች ላይ
📌ሚይ ሓርማዝ በሚገኙ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው የተፈፀመው።
ጥቃቱ በአራት ዙር የተፈፀመ ሲሆን ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ታጣቂዎች ተሰውተዋል።
የተጎዱ ታጣቂዎች ደግሞ ወደ አላማጣ ለህክምና ተወስደዋል። መረዋ አካባቢ በሚገኝ በአንድ የቤተክርስቲያን ዋሻ ውስጥ የህክምና አገልግሎት መስጫ አዘጋጅተው ነበር ተብሏል።

Via : አዩዘሀበሻ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
13👍8
ውጊያውን አናንዛዛውም:-ጄኔራል ባጫ ደበሌ‼️
'ሱዳኖች  ጦርነት እጀምራለሁ ብለው ካሰቡ አናንዛዛውም‼️
የሱዳን መንግስት በራሱ ጦርነት ነው ያለው። የሱዳን መንግስት  የራሱን ጦርነት ሳይጨርስ ወደ ኢትዮጵያ  የሚያልፍ ከሆነ እድሜው አጭር ነው፣ይጠፋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ያለውን ሙሉ  አቅምና ሃይሉን ተጠቅሞ መጨረስ ነው የሚፈልገው።እንደ በፊቱ የሚንዛዛበት ምክንያት የለም። ጀመርክ በአጭር ግዜ መጨረስ ነው፣ እንደበፊቱ ምሽግ ይዘህ ደጀን ይዘህ፣እረፍት አድርገህ እንደገና ላደራጅ...ወዘተ በሚል የምትሮጥበት አይደለም። ውጊያው በቴክኔሎጂ ነው'ሲሉ ተደምጠዋል።

Via : አዩዘሀበሻ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪37👍2212🫡2
የዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካ በሐምሌ ወር ለአውሮፓ ትልቁ የጄት ነዳጅ አቅራቢ መሆን ቻለ

የናይጄሪያው አሊኮ ዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካ በሐምሌ ወር ብቻ ለአውሮፓ ከገባው አጠቃላይ የጄት ነዳጅ ውስጥ አምስተኛውን ድርሻ በመያዝ (ከ2.06 ሚሊዮን ቶን ውስጥ ከ400 ሺህ በላይ ቶን በማቅረብ) ለአሁኑ ወርም ከአሜሪካ እና ከመካከለኛው ምስራቅ ቀድሞ የአውሮፓ ትልቁ የውጭ አቅራቢ መሆን መቻሉ ተገለፀ።


ይህ አፈጻጸም የተመዘገበው በፋብሪካው ላይ በተከሰተ የቴክኒክ ችግር ምክንያት የጥገና ሥራዎች ተከናውነው የነዳጅ ማጣሪያ አቅሙ ከነበረበት በቀን ከ600 ሺህ በላይ ወደ 350 ሺህ ቀንሶ በነበረበት ወቅት ጭምር ነው። በሆርሙዝ ሰርጥ ዙሪያ የተፈጠሩ መስተጓጎሎች እና የአውሮፓ አገራት የኃይል አቅርቦታቸውን ለማብዛት ያላቸው ፍላጎት ለዚህ ስኬት መሠረት ሆኗል።

የፋብሪካው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዴቪድ በርድ እንዳሉት ተቋሙ የናፍጣ እና ቤንዚን ምርቶችን ወደ ውጭ መላክ ጀምሯል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ፋብሪካው በጥቅምት ወር 5 ቢሊዮን ዶላር ለመሰብሰብ የአክሲዮን ሽያጭ እንደሚያካሂድ ይጠበቃል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
16
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
 
ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፡-

ከጠዋቱ 2፡00-11፡00

👉  ጎፋ መብራት ኮንዶሚኒየም፣ ጉራጌ ሰፈር፣ ናሰው ሪልስቴት፣ ጎፋ ካምፕ ፣ ሀዋርያው ቸርች ፣ ኪዳነ-ምህረት ቤተ-ክርስቲያን እና አካባቢው፣

👉መካኒሳ አረቄ ፋብሪካ ቆሬ አደባባይ ፣ አሚጎ ኮንዶሚንየም በከፊል፣ ፋና ት/ቤት እና አካባቢው፣

ከረፋዱ 4፡00-11፡00

👉የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋራጅ አካባቢ፣ ማዕድን ሚኒስቴር ፣ ላምበረት መናሀሪያ እና አካባቢው፣

👉ጉርድ  ሾላ ቴሌ ፣ የካ ሞሰብ ፣ ትምህርት መሳሪያዎች ፣ ጃክሮስ አደባባይ ፣ ሜታ ቢራ ፋብሪካ እና አካባቢው፣

ከጠዋቱ 2፡30-11፡30

👉ባህርዳር ቀበሌ11፣ ማራኪ ቴሌ፣ ማራኪ ቀበሌ ቢሮ፣ ቀበሌ16፣ ሕዳሴ፣ መኮድ ኮንዶሚኒየም ፣ ጭሮ፣ ጨለንቆ፣ ቀርሳ፣ ቁልቢ፣ ኮሮሚ፣ ላንጌ እና አካባቢው

ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን ።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
9😢1
ለታሪካዊው ኢትዮጵያ ሆቴል ዘመናዊ ህንጻ ሊገነባለት ነው

አዲስ አበባ ብሔራዊ ቴአትር አካባቢ የሚገኘው አንጋፋው የኢትዮጵያ ሆቴል ሊፈርርስ መሆኑ ተሰማ። ከዚህ ቀደም የሆቴሉ ጀርባ ያለው የስብሰባ አዳራሽ መፍረስ የጀመረ ሲሆን፣ ዋናው ሕንፃም በቅርቡ ሙሉ በሙሉ እንደሚፈርስ ተገልጿል። በቅጥር ግቢው ውስጥ የነበሩ ሰባት የንግድ ሱቆችም አስቀድመው ተነስተዋል።

ይህንን ባለ አምስት ፎቅ ሆቴል ባለሃብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ በ2002 ዓ.ም በ94 ሚሊዮን ብር ገዝተውት ነበር። አሁን ላይ በቦታው ላይ ዘመናዊ ሕንፃ ለመገንባት ታቅዷል። ሆቴሉ ሲፈርስ 140 ሠራተኞች ሥራቸውን እንደማያጡና በባለቤቱ ሌሎች ኩባንያዎች ውስጥ እንደሚዛወሩ ተነግሯል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
20🤯8👍2😢1🎉1🤪1
የኢትዮጵያ አየር መንገድ  ምዝገባ ተጀመረ!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ አስተናጋጅ እና የአውሮፕላን ጥገና ቦታዎች ምዝገባ ዛሬ ተጀምሯል።

እስከ ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው በዚህ በኦንላይን ምዝገባ አመልካቾች የትምህርት ማስረጃዎቻቸውን እና መታወቂያቸውን በተለዩ ሁለት የፒዲኤፍ (PDF) ፋይሎች አዘጋጅተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

​የምዝገባ ሂደቱ ሙሉ በሙሉ በኢንተርኔት የሚከናወን ቢሆንም የጽሁፍ ፈተና እና የኢንተርቪው ሂደቶች በአዲስ አበባ ብቻ የሚሰጡ በመሆናቸው የክፍለ ሀገር  አመልካቾች ይህንን ታሳቢ ማድረግ አለባቸው።

የፋይል መጠኑም ከ1 ሜጋባይት መብለጥ የሌለበት ሲሆን ዝርዝር መረጃዎችን እና የአመዘጋገብ ቅደም ተከተሎችን በኩባንያው ይፋዊ ድረ-ገጽ  ይከታተሉ።

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
25
በኩርሙክ የጅምላ መቃብር ተገኘ‼️
በኢትዮጵያ ድንበር በሱዳን ብሉ ናይል ክልል በምትገኘው ኩርሙክ ከተማ የ25 ሰላማዊ ሰዎችን አስከሬን የያዘ የጅምላ መቃብር መገኘቱን የከተማዋ ባለሥልጣን አስታወቁ።

በመቃብሩ የተገኙት አስከሬኖች የሴቶች፣ የሕፃናት እና የሆስፒታል ሠራተኞች መሆናቸው ተገልጿል። የኩርሙክ ከተማ ኮሚሽነር አብደል አቲ ሞሐመድ አል-ፋኪ እንዳሉት፣ የሱዳን ሠራዊት ከተማዋን ከፈጣን ድጋፍ ኃይሎች (RSF) ነፃ ካወጣ ከአንድ ወር በኋላ በተካሄደ የማጽዳት ሥራ ወቅት በከተማዋ ሰሜን ምሥራቃዊ ክፍል መቃብሩ ተገኝቷል።

ባለሥልጣኑ እንደገለጹት፣ ተጎጂዎቹ በከተማዋ ላይ ጥቃት በተፈጸመበት ወቅት RSF የአጥፍቶ ጠፊ ድሮኖችን ለማስወንጨፍ ይጠቀምበት ከነበረው ጄበል ፋንካት ኮረብታ አቅራቢያ መገኘታቸውን ተናግረዋል።

የጅምላ መቃብሩ መገኘቱ በሱዳን በቀጠለው ጦርነት በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸሙ ከባድ ጥሰቶች እና የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች እየተጋለጡ መሆናቸውን ያሳያል። በኩርሙክ የተገኘው መቃብር ከዚህ ቀደም በካርቱምና በጌዚራ ግዛቶች ከተገኙ ተመሳሳይ የጅምላ መቃብሮች ጋር ተያይዞ በሱዳን ጦርነት የሚደርሰውን የሰላማዊ ሰዎች ሰቆቃ እንደገና አጉልቶ አሳይቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
13😢8💔7👍2
የጦርነት ዝግጅቱ‼️
ህወሃት በራያ የጦርነት ዝግጁትን ወደ መጨረሻ ምዕራፍ እያደረሰ ይገኛል።
በዚህም በሁሉም አካባቢዎች የሚደረጉ ስብሰባዎች ከቀትር ወደ ማታ እንዲሸጋገሩ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ለራያ አዘቦ 1,000 ሊትር ነዳጅ እና ለመኮኒ ከተማ 3,000 ሊትር ነዳጅ እንዲከፋፈል ገልጿል።
እንስሳትን ጨምሮ የስንቅ አቅርቦት፣ውሃ የሚያቀርቡ ቦቢዎች እንዲሁም ለቀብር የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች እስከ ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም እንዲዘጋጅ ለሁሉም አመራሮቹ ትዕዛዝ መስጠቱ ታውቋል።
ጦርነት ይብቃ፣ ችግሮች በውይይት ይፈቱ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
26🤔5👍2😢2
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ የተፈፀመ‼️
ተመስገን ጌታቸው፣ ይታገሱ አሰግደው እና ግዛው ግርማዬ የተባሉ ሶስት ግልሰቦች ከተሳፈሩበት የሕዝብ ማጓጓዣ መኪና ላይ “ፋኖ ናችሁ” በሚል ውንጀላ ተገደው እንዲወርዱ ከተደረጉ በኋላ መገደላቸውን የአካባቢው ምንጮች ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

ድርጊቱ የተፈጸመው አገና በተባለችው ልዩ ቦታ ሲሆን ወንጀሉን የፈጸሙት የመንግስት ኃይሎች ከአካባቢው የአበሽጌ አገና ፖሊስ እና ሚሊሻ አባላት ጋር በመተባበር እንደሆነ ተጠቅሷል።

ግለሰቦቹ የተለያዩ ወንጀሎችን እንደፈፀሙና የተያዙትም ከአካባቢው ለማምለጥ በሚሞክሩበት ጊዜ መሆኑንና ከተያዙ በኋላ እንዲረሸኑ መደረጉን የአካባቢው ምንጮች ይገልፃሉ።
Via:- መሰረት ሚዲያ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡50😢1411💔5🙉41👍1🍾1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ ቪዲዮ በምዕራብ ኮሎምቢያ 7.4 በMagnitude የተለካ ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ በደረሰበት ቅጽበት የአንድ ቤተክርስቲያን የፊት ለፊት ገጽታ በ ከፊል ሲናድ ያሳያል።

በ ሀገሪቱ በደረሰው ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢያንስ 20 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።

የ ነብስ አድን  ስራዎች ለማገዝ ወታደሮች እየተሰማሩ ይገኛሉ ሲል CNN ዘግቧል::

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢154👍1
ድንጋይ የሚያክል በረዶ‼️
ዛሬ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ የጣለው በረዶ ነዋሪዎቹን አስደንግጧል። በከተማዋ የሚኖሩ ቤተሰቦች የላኩልን ምስል ከላይ ተያይዟል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢365👍4🤯1
ሳዑዲ በአንድ ሳምንት ውስጥ 940 ኢትዮጵያውያንን
በሕገወጥ ድንበር ጥሰት በቁጥጥር ሥር አዋለች

በሳዑዲ ዓረቢያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ይፋ በተደረገው መረጃ መሠረት፤ ሀገሪቱ በቅርቡ ባካሄደችው የድንበር ቁጥጥር ዘመቻ በሕገወጥ መንገድ ድንበር ለማቋረጥ የሞከሩ 940 ኢትዮጵያውያንን በአንድ ሳምንት ውስጥ በቁጥጥር ስር አውላለች። ሚኒስቴሩ ከጁላይ 30 እስከ ኦገስት 5 ባለው ጊዜ ውስጥ ባካሄደው በዚህ ዘመቻ በጠቅላላው 1,593 ሕገወጥ ድንበር አቋራጮችን የያዘ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 59 በመቶ ያህሉ ኢትዮጵያውያን እና 40 በመቶ ያህሉ ደግሞ የየመን ዜጎች ናቸው። በዚሁ ሳምንት የመኖሪያና የሥራ ሕግ የጣሱ 14,440 ሰዎች የተያዙ ሲሆን፣ 10,827 ሕገወጥ ነዋሪዎች ደግሞ ከሀገሪቱ እንዲወጡ ተደርገዋል።

የሳዑዲ ዓረቢያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር አክሎ እንዳስታወቀው፤ ሕገወጥ ድንበር አቋራጮችን ሲያጓጉዙ፣ ሲሸሽጉ ወይም ሥራ ሲሰጡ የተገኙ 25 ግለሰቦችም ተይዘዋል። ሚኒስቴሩ በሰጠው ማስጠንቀቂያ፤ ሕገወጥ መግቢያን የሚያመቻቹ ወይም ጥሰተኞችን የሚያስጠጉ ሰዎች እስከ 15 ዓመት የሚያስቀጣ የፅኑ እስራት፣ እስከ 1 ሚሊዮን የሳዑዲ ሪያል (260 ሺህ ዶላር) የገንዘብ መቀጮ እንዲሁም የተጠቀሙባቸው ተሽከርካሪዎችና ንብረቶች መወረስ እንደሚጠብቃቸው አስታውቋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
9👍1