አዲስ ሪፖርተር - NEWS
36.1K subscribers
17.1K photos
421 videos
22 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
ሲፒጄ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ገለልተኛ የዜና ክፍሎችን “ለመበተን ዘመቻ” እያካሄዱ ነው ሲል ከሰሰ!

ጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ቡድኑ በሐሙስ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ እነዚህ ተከታታይ ክስተቶች በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ግንባር ቀደም ነጻ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት መካከል በአንዱ ላይ የሚደረገውን ጫና በከፍተኛ ሁኔታ ማባበሳቸውን ገልጻል።

የሲፒጄ የአፍሪካ ፕሮግራም አስተባባሪ ሙቶኪ ሙሞ “በአዲስ ስታንዳርድ እና በዮናስ ከድር ላይ የተፈጸሙት እነዚህ ጥቃቶች የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት የአገሪቱን ነጻ የዜና ድርጅቶች ለመበተን የሚያካሂዱት ዘመቻ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ያሳያሉ” ብለዋል።

አስተባባሪዋ ባለሥልጣናቱ “የተቋሙን ቁሳቁሶች በአፋጣኝ እንዲመልሱ፣ ከቢሮው በግዳጅ የማስወጣት ሂደትን እንዲያስቆሙ፣ ማንኛውንም ተጨማሪ ትንኮሳ እንዲያቆሙ እና ለዮናስ እስርና ጥቃት ተጠያቂ የሆኑ አካላት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ  እንዲያደርጉ” አሳስበዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
13👍3
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ – የሚፈልጓቸውን አዳዲስ ዜናዎችን በአጭሩ እና በጥልቀት ከኛ ዘንድ ያንብቡ።

🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።

🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።

አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy

@sputnik_ethiopia
6👍2
የከባድ መሳሪያ ተኩስ‼️
በራያ ግንባር የሚንቀሳቀሰውና ከሰሞኑ ከባድ መሳሪያዎችን እና ተጨማሪ ታጣቂዎችን ሲያጠጋ የነበረው የህወሃት አርሚ 33 እና 44  ዓዲጉደም ➡️ ደቡብ ወጀራት ➡️ኮንካ ➡️ጎነቕ ➡️ቶንሳ ➡️ንፋሮ መጋለ መስመር በዓዲቀይሕ ወደ ገራርሳ እና ቶንሳ አሁን ዛሬ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ላይ በትግራይ ሰላም ሰራዊት ላይ የከባድ መሳሪያ ተኩስ መጀመሩን ምንጮቻችን ገልፀዋል።

እራሱን 'የትግራይ ሰላም ሰራዊት' በሚል የተደራጀው ታጣቂ ሀይል ወደ መቀሌ ለመግባት ዝግጁ መሆኑን ከሳምንት በፊት አሳውቆ ነበር።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍157👀6🕊2🥱1🤪1
በአርባምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት የመብራት ምሰሶ ላይ ጉዳት ያደረሰው አሽከርካሪ 1 ሚሊዮን ብር ተቀጣ

በአርባምንጭ ከተማ በኮሪደር ልማት ሥራ የተተከለ ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ምሰሶ (ፖል) በመግጨት ውድመት ያደረሰ አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ውሎ 1 ሚሊዮን ብር እንዲቀጣና የወደመውን ሀብት በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ ተወሰነ።

በከተማዋ ሲቀላ ክፍለ ከተማ አሽከርካሪው ተሽከርካሪ ለማንቀሳቀስ ባልተፈቀደ ቦታ ላይ በማሽከርከር በከፍተኛ ወጪ የተተከለውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በመግጨት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።

ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ የአርባምንጭ ከተማ ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ከከተማው ትራፊክ ፖሊስ ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል ጥፋተኛውን አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል።

የከተማው ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰራዊት ገዛኸኝ እንዳስታወቁት፣ በቸልተኝነት በሚፈጸሙ ጥፋቶች የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት እንዳይባክን እና አስተማሪ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ሲባል የተሰበረውንና የወደመውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ።

ጥፋተኛውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ከነዋሪዎች የተገኘው የጥቆማ ትብብር ከፍተኛ ሚና እንደነበረው የገለጹት አቶ ሰራዊት፣ ለኅብረተሰቡ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ኃላፊው አክለውም ለከተማዋ እድገትና ለነዋሪዎች ምቾት በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የኮሪደር ልማት ሥራዎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በሚያበላሹ ወይም ሕግ በሚተላለፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስበዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣16🤯1410😢5👍3🙉2🥰1🤪1
አቃቢ ህግ አቅርቦት የነበረው አቤቱታ ውድቅ ተደረገ

በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች የዋስትና መብታቸው ተነስቶ ጉዳያቸውን በእስር ላይ ሆነው እንዲከታተሉ አቃቢ ህግ አቅርቦት የነበረው አቤቱታ ውድቅ እንዲደረግ እና በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ብይን ተሰጠ።

አቃቢ ህግ በከፍተኛ የኢንቨስትመንት ማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙ ተከሳሾች እና ጠበቃቸው፣ የተከሰሱበት የክስ መዝገቡ በክርክር ሂደት ላይ የሚገኝ እና በችሎት ውሳኔ ያልተሰጠበት ሆኖ እያለ በሚዲያ ላይ በመቅረብ ከክሱ አውድ ውጪ የሆነ ማብራሪያ በመስጠታቸው የፍትሕ ሂደቱን ተጽዕኖ ውስጥ ለመክተት እና ምስክሮችን ላይ ተጽዕኖ ለማድረግ ሞክረዋል በሚል የዋስትና መብታቸው ተነስቶ ከማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የሚል አቤቱታ አቅርቦ ነበር።

በተጨማሪም ዘገባው የተጫነበት ሚዲያ ይቅርታ እንዲጠይቅ እና ቪዲዮውን እንዲያወርድ ፣ በወንጀል ህግ አንቀጽ 457 ስር በቀጥታ እንዲቀጡ እንዲወሰን የሚሉ አቤቱታዎችንም አቃቢ ህግ አካቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
11👍4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ማስጠንቀቂያ ፦ ይህ ቪዲዮ አስደንጋጭ እና ለአንዳንድ ተመልካቾች ሊረብሽ የሚችል ምስል ይዟል። ከመመልከትዎ በፊት ጥንቃቄ ያድርጉ።

በታይላንድ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ ግዛት እየተካሄደ በነበረ የእግር ኳስ ውድድር ላይ አንድ እግር ኳስ ተጫዋች በመብረቅ ተመትቶ ህይወቱን አጥቷል።

ጨዋታው በከባድ ዝናብ እየተካሄደ ባለበት ወቅት ነው መብረቅ በሜዳው ላይ በመውረድ ተጫዋቹን የመታው።

ከአደጋው በኋላ ተመልካቾች እንዲሁም የድንገተኛ አደጋ ሰራተኞች እርዳታ ቢያደርጉም፣ ወደ ሆስፒታል ቢወስዱም ህይወቱን ማትረፍ አልተቻለም።

ባለሥልጣናት በአደጋው ተጨማሪ 12 ሰዎች በቃጠሎ መቁሰላቸውን ገልጸዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢3212👍2🤯1
ብዙ ስፍራዎች ኤርትራ ውስጥ በአፋን ኦሮሞ ይጠራሉ- ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ ለኦቢኤን።
📌በ1512 ዓ.ም የባሕረ ነጋሽ (የዛሬዋ ኤርትራ) ንጉሥ የነበረው 'ዶሪ' ኦሮሞ እንደነበር፣ በተጨማሪም 'ባሬንቱ' የተሰኘው ትልቅ ከተማ እና እንደ አምባ ሶይራና አምባ ደብራ ያሉ ተራራዎች ስያሜያቸው የኦሮሞ ሥረ-መሠረት እንዳለው አስረድተዋል።
📌በ1499 ዘርፀድንግል የኦሮሞ ሰራዊትን ይዞ እስከ ምፅዋ ታግሏል ብለዋል።
📌ኦሮሞ ደሙን ያላፈሰሰበት አጥንቱን ያልከሰከሰበት የኢትዮጵያ ግዛት የለም ብለዋል።
📌ኦሮሞ በታሪኩ የተቃወመው የተበላሸ አስተዳደርን እንጂ ኢትዮጵያን አይደለም ብለዋል።
📌ኦሮሞ ነፃ ወጥቷል፤ ግራ፣ ቀኝ፣ ኋላ፣ ፊት ማየት አያስፈልግም። ኦሮሞን ነፃ ለማውጣት ዛሬ መታገል ሞኝነት ነው"ሲሉ ተደምጠዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🥱33🙉18🤪1510👍8🤣4😱1👀1🙊1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🌟ህልምዎን እውን ያርጉ!! ከአይሩሳሌም እና እህቷ ልምድ ይውሰዱ!!!🌟

ከሁለት ዓመት በፊት አይሩሳሌም የአላቡጋ ስታርት ዓለም አቀፍ ፕሮግራምን ተቀላቀለች፣ እዚያም የሩሲያ ቋንቋን ተምራ፣ ስኬታማ የባሪስታ ባለሙያ ከመሆኗም በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት የራሷን ሬስቶራንት ለመክፈት አቅዳለች። ​​በዚህ ስኬቷ በመነሳሳት እህቷም ፕሮግራሙን በመጠቀም በሩሲያ ውስጥ ስልጠና እና ሥራ ማግኘት ችላለች። እህትማማቾቹ ልምዳቸውን ሲያጋሩ እንደሚገልጹት ፕሮግራሙ ታላቅ የእድገት እድሎችን የሚሰጥና እንደ የጊዜ አያያዝ እና አመራር ያሉ እና ሌሎችም የግል እድገት ክህሎቶችን ለማዳበር እድል የሚፈጥር ነው።

የራስዎን ሰራ ለመጀመር ዝግጁ ነዎት?

ከ18 እስከ 22 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ወጣት ኢትዮጵያዊ ሴቶች ለዚህ ህይወትን የሚቀይር ፕሮግራም ለማመልከት ብቁ ናቸው።

ሙሉ የጥቅማጥቅም ፓኬጁ ጥሩ ደሞዝ፣ ነፃ የአየር ትኬቶች፣ የህክምና መድን እና ልዩ የሩሲያ ቋንቋ ኮርሶችን የሚያካትት ሲሆን በስምንት የተለያዩ የስራ መስኮች ላይ ማመልከት ይቻላል።

ጊዜ ሳያጠፉ ዛሬውኑ በአላቡጋ ስታርት ማመልከቻ ፖርታል https://start-alabuga.com ላይ ያመልክቱ።
7
#የጉድሀገር

የጆኒ እና ሴዶ MMA ፍልሚያ መግቢያ ትኬት VVIP 100 ሺ ብር መሆኑ ተገለፀ።

የቲኬት ዓይነቶች እና ዋጋ፦

1. VVIP Ringside - 100,000 የኢትዮጵይ ብር

* ልዩ የሪንግ አጠገብ መቀመጫ
* ያልተገደበ የምግብ እና የመጠጥ አገልግሎት
* ወደ ተወዳዳሪዎች ልብስ መቀየሪያ ክፍል የመግባት እድል

2. VVIP Premium - 50,000 የኢትዮጵይ ብር

* 2ኛ ተከታታይ ረድፍ መቀመጫ
* 2 የምግብ እና 10 የመጠጥ ኩፖኖች

3. VVIP Normal - 30,000 የኢትዮጵይ ብር

* ከ 3ኛ እስከ 5ኛ ረድፍ መቀመጫዎች
* 2 የምግብ እና 7 የመጠጥ ኩፖኖች

4. VIP - 20,000 የኢትዮጵይ ብር

* 1 የምግብ እና 4 የመጠጥ ኩፖኖች

5. Regular - 10,000 የኢትዮጵይ ብር

6. Early Bird - 4,000 የኢትዮጵይ ብር

ጉርሻ page

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣6512👍4👀2🤪1🙊1😡1
በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ባለፈው ሰኞ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) አባላት አቶ አበበ አካሉ እና አቶ ይስሀቅ ወልዳይ እንዲሁም የፓርቲው ጠበቃ አቶ አበራ ንጉስ ላይ ፍርድ ቤት የ12 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቀደ።

የምርመራ ጊዜውን የፈቀደው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ልደታ ምድብ፣ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። ችሎቱ ለዛሬ ቀጥሮ ተጠርጣሪዎች ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ነበር።

ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ከማስተላለፉ አስቀድሞ፤ ፖሊስ በጊዜ ቀጠሮ ማመልከቻው ያካተተውን እና ተጠርጣሪዎች ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ጋር ያደረጓቸውን ቃለ ምልልሶች ሊንኮች በትላንትናው ዕለት እንዲያቀርቡ ትዕዛዝ መስጠቱ ይታወሳል።

የፌደራል ፖሊስ ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ማመልከቻ ላይ ተጠርጣሪዎቹ “የብሔር እና የሃይማኖት ግጭትን ለመፍጠር በማሰብ በውጭ ሀገር በሚገኙ መገናኛ ብዙኃን ሀሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ሲያሰራጩ ነበር” የሚል ውንጀላ አቅርቦ ነበር።

ከመገናኛ ብዙሃኑ መካከል በፖሊስ ማመልከቻ ላይ በስም የተጠቀሱት አንከር ሚዲያ፣ ኢትዮ ፎረም እና ኢትዮ 360 መገናኛ ብዙሃን ናቸው።

ከመገናኛ ብዙሃን ጋር የተደረጉ ቃለ ምልልሶችን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት፤ ፖሊስ ሊንኮቹን ለችሎቱ ማቅረቡን የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል።

ተጠርጣሪዎቹ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ጋር አድርገዋቸዋል የተባሉትን ቃለ ምልልሶች ያደመጠው ፍርድ ቤቱ፤ ንግግሮቹ በሽብር ወንጀል ለመጠርጠር “መነሻ ይሆናሉ” ማለቱን አቶ ሰለሞን አስረድተዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡87👍2😢2🎉1
ሸረሪና‼️
ባሳለፍነው ሳምንት ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም ከንጋቱ 11:45 ጀምሮ በሱዳን ድንበር ሸረሪና አካባቢ የሚንቀሳቀሰው የህወሓት አርሚ 70 (በዋናነት ኮር 131) ሁመራን ለመቆጣጠር በመከላከያ ሠራዊት ላይ ተኩስ መክፈቱን ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊት በወሰደው የአፀፋ ምላሽ አንድ ሙሉ የተከማቸ የመሳሪያ ዲፖን በቁጥጥር ሥር አውሏል፣በርካታ ታጣቂዎች ተማርከዋል፣በርካታ ታጣቂዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፣በርካታ ሎጀስቲክ ወድሟል።
ሸረሪና እና አካባቢው ሙሉ ለሙሉ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ውሏል።
አሁን ላይ በአካባቢው ከፍተኛ አሰሳ እየተካሄደ ሲሆን በተለይ የመሳሪያ ማከማቻዎች በቁጥጥር ሥር እየዋሉ ይገኛሉ።
ከላይ የሚታዩት ምስሎች ከስፍራው የደረሱን ምስሎች ሲሆኑ በመከላከያ ሠራዊት የተማረኩ የአርሚ 70 ታጣቂዎችን፣ መሳሪያዎችን እንዲሁም ተሽከርካሪዎችን የሚሳይ ነው።

Via : አዩዘሀበሻ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
28👍12😢2🤣2🤔1👀1🤪1💊1🙊1
አሜሪካ የኤምባሲዎቿን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ልትቀንስ ነው

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአፍሪካ አህጉር ውስጥ የቪዛ ማመልከቻዎችን የሚያስተናግዱ ኤምባሲዎቹንና ቆንስላዎቹን ቁጥር ከ50 ወደ 20 ዝቅ ለማድረግ ማቀዱ ተሰምቷል።

ይህ የተቋማት ውህደትና ቅነሳ ውሳኔ በተለይም በትራምፕ አስተዳደር እየተተገበረ ያለው ጥብቅ የኢሚግሬሽን ቁጥጥር አካል ሲሆን፣ በመጪዎቹ ሳምንታት ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
10👍4
በኮሬ ዞን የገዛ ባሏን የገደለችው ግለሰብ በእስራት ተቀጣች
 
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ሳርማለ ወረዳ ደርባ ማናና ቀበሌ ልዩ ቦታዉ ወካለ ወይም ወይዶ ተብሎ በሚጠራ ቦታ ነው የወንጀል ድርጊቱ ተፈጽሟል።ተከሳሽ  ተስፋይነሽ ዘለቀ የተባለች ሲሆን  ከምሽቱ 2:00 ሰዓት አከባቢ  ድርጊቱን ፈጽማለች።
 
ተከሳሽ ከትዳር አጋሯ  ሳሪያ ጋር በተነሳ አለመግባባት ምክንያት ምሽት ላይ ከቤት ወጥታ እንደተሰወረች ተገልጿል።የትዳር አጋሯም ተከሳሽን  ለመፈለግ ወደ ጎረቤት ቤት ሲሄድ  ወደዚያ አልመጣችም የሚል ምላሽ ያገኛል። በመቀጠልም ወደ መኖሪያ ቤቱ ተመልሶ በጓሮ በኩል ባትሪ እያበራ ሲፈልጋት ተከሳሽ ተደብቃ በነበረችበት ቦታ አጠገቧ እያለፈ እያለ ይዛዉ በነበረው ቆጮ መቁረጫ የቀኝ አንገቱን  አንድ ጊዜ በመቁረጥ  ህይወቱ እንዲያልፍ ማድረጉን የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ሲዳሞ ማዳሞ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
 
ፖሊስም ተከሳሽን በቁጥጥር ስር በማዋል የክስ መዝገቧን ለአቃቤ ህግ ያቀርባል።አቃቤ ህግም ተከሳሽ በፈፀመችው ከባድ የሰዉ ግድያ ወንጀል ክስ መስርቶ ለፍርድ ቤት ያቀርባል።
 
ፍርድ ቤቱም ተከሻሽ ጥፋተኛ መሆኗን በቀረበለት የክስ መዝገብ በማጣራት   በ20 ዓመት ጽኑ እስራት እንድትቀጣ  ወስኖባታል ሲሉ ምክትል ኮማንደር ሲዳሞ ማዳሞ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
 
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
11😢10👍2
የመጸዳጃ ቤት እና ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ የሚለቁ ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች እስከ 3 መቶ ሺህ ብር ድረስ እየተቀጡ መሆኑ ተነገረ
 
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ከመኖሪያ ቤት የመጸዳጃ ቤት ወይም ማንኛውንም ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቁ ወይም መስመሩን አገናኝተው ወንዙን የበከሉ ድርጅቶች እና ግለሰቦችን ከ150 ሺህ እስከ 3 መቶ ሺህ ብር እየቀጣ ይገኛል።
 
የባለስልጣኑ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ወቅቱ የክረምት ወቅት በመሆኑ ዝናብ በሚዘንብበት ወቅት ከግለሰቦች መኖሪያ እንዲሁም ከድርጅቶች የመጸዳጃ ቤት ወይም ማንኛውም ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻን ወደ ወንዝ የሚለቁ እንዲሁም አካባቢን የሚበክሉ ግለሰቦች በባለስልጣኑ ደንቡ መሠረት እስከ 300 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት ይጣልባቸዋል።
 
ይህንን ህግ ጥሰው የተገኙ አካላት አሁን ላይ እየተቀጡ እንደሚገኙ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።በተጨማሪም ህብረተሰቡ ለማንኛውም አይነት የደንብ መተላለፍ በነፃ ስልክ 9995 መረጃና ጥቆማ እንዲሰጥ አቶ የምስራች ጨምረው ገልፀዋል።
 
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
23🙉5👍2😢1🤣1