አዲስ ሪፖርተር - NEWS
36.1K subscribers
17.1K photos
421 videos
22 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
በመዲናዋ ሆቴሎችን ጨምሮ የምሽት መዝናኛዎች የድምፅ ብክለት መጨመሩ ተገለፀ

የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ለቁጥጥር  የሚያመች የድምፅ ብክለት መመሪያ እያዘጋጀሁ እገኛለሁ ብሏል።

የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን  በበጀት አመቱ በ12 ሺህ 3መቶ 76 ተቋማት ላይ የክትትል እና ቁጥጥር ስራ ሰርቻለሁ ብሏል።

በመዲናዋ ሆቴሎች፣ ግሮሰሪዎች፣ የምሽት ጭፈራ ቤቶች በስፋት መኖራቸዉን ተከትሎ ህብረተሰቡ መረበሹን ቅሬታ እየቀረበ መገኘቱ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና አማካሪ አቶ አዱኛ ወንድሙ በመዲናዋ የሆቴሎችና የምሽት መዝናኛ ተቋማት መስፋፋትን ተከትሎ ከፍተኛ የድምጽ ብክለት መኖሩን ተናግረዋል።

በአገልግሎት ዘርፍ ባሉ ተቋማት ላይ ክትትል ብቻ ሳይሆን እርምጃ እየወሰድኩ ነዉ ያለዉ ባለስልጣኑ ሆቴሎች እና ግሮሰሪዎችን ጨምሮ 3 ሺህ 1መቶ 16 በሚሆኑት ላይ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ባለስልጣኑ ገልጿል።

አቶ አዱኛ ከተሰጡት የፅሁፍ ማስጠንቀቂያዎች ተሰጥቷቸዉ ያላስተካከሉ ተቋማት ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

በዚህም በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ 28ቱ ላይ የማሸግ እርምጃ እንደተወሰደ ተገልጿል።

የድምፅ ብክለት ላይ ችግሮች እንዳሉ የሚናገሩት የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና አማካሪ አቶ አዱኛ ወንድሙ፤የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲሁም የአምራች ኢንዱስትሪዎች የገንዘብ ቅጣት እንደተጣለባቸዉ አስረድተዋል።

የድምፅ ብክለት መመሪያን በማዘጋጀት ለፍትህ ሚኒስቴር መላኩን አማካሪዉ የገለፁ ሲሆን፤ አሁን ያለዉን ብክለት ጥብቅ ቁጥጥር ለማድረግ ያግዛል ተብሎ እንደታመነበት አንስተዋል።

የአዲስ አበባ አከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በተጠናቀቀው 2018 የበጀት አመት የአካባቢ ብክለትንና የአየር ንብረት ለዉጥ ስራዎችን አስመልክቶ በዛሬዉ ዕለት ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
13👍9🥱2
የመሳሪያ ዲፖ ተያዘ‼️
በሱዳን የሚንቀሳቀሰው የህወሓት አርሚ 70 በሸረሪና ግንባር አከማችቶት የነበረው የመሳሪያ ዲፖ ተያዘ‼️
ከሸረሪና ካምፕ ወጣ ብሎ 'ግዴማ' በተባለች ቦታ መጋዘን ውስጥ እንዲሁም ከመሬት በታች በኮንክሪት በተሰራ ግዙፍ ምሽግ ተጠራቅሞ የነበረ ተተኳሽ፣ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ፣ ሮኬት፣ የአጭር እና መካከለኛ ርቀት ሚሳይሎች፣ RPG-7፣ የሳተላይት ስልኮች፣ የሬዲዮ መገናኛ፣ የቅኝት ድሮኖች፣ የመኪና መለዋወጫዎች እና ለጊዜው ምንነታቸውን ለመለየት ያልተቻሉ የጦር መሳሪያዎች ገቢ መደረጋቸውን ምንጮቹ አረጋግጠዋል።

እንደ ወታደራዊ ምንጮቹ ገለፃ ከሆነ፤ በትናንትናው እለት ብቻ ከሸረሪና እና ግዴማ ካምፕ 31 ከባድ ተሳቢ ተሽከርካሪዎች ከአርሚ 70 የተማረኩ የተለያዩ ትጥቆችን ወደ ሁመራ እና ዳንሻ ከተማ ተጓጉዘዋል።
ለዚህ ዲፖ መገኘት የተማረኩ የአርሚ 70 ታጣቂዎች አስተዋጽኦ አድርገዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
42🤣22👍9👌3🤪3😢1👀1🙊1
ከላይ በምስሉ የምትመለከቷቸው ወንዶች በተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ መስረተው  በመገኘታቸው በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በባምባሲ ከተማ ፓሊስ በቁጥጥር ስር ዋሉ !   

ከማህበረሰቡ ወግና ባህል እንዲሁም እምነት ያፈነገጡ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ ።

ባምባሲ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም| ከማህበረሰቡ ወግና ባህል እንዲሁም እምነት ያፈነገጡ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ ።

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በባንቢስ ከተማበፎቶ የተመላከቱት እኒሁ ታደለ እናውጋውና በፀሎት እንየው የተባሉ ተጠርጣሪዎች በተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ በመመስረታቸው...

በማህበረሰቡ ጥቆማና ተጠርጣሪዎቹም የእምነት ቃላቸውን በሰጡት መሰረት ፖሊስ ተገቢውን የምርመራ ስራ መጀመሩንና በቀጣይ ውጤቱን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን ።

ይሄንን መሰል አፀያፊ ተግባር እንዳይከሰት መፍትሔ ግን ምን ይሆን ? በጣም አስደንጋጭ ነው ።

Via፦ የባንቢስ ከተማ አስተዳደር ኮምኒኬሽን

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
34🤣28😢17💔10🤔8🙉4👍3🙈2👀1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🌟ህልምዎን እውን ያርጉ!! ከአይሩሳሌም እና እህቷ ልምድ ይውሰዱ!!!🌟

ከሁለት ዓመት በፊት አይሩሳሌም የአላቡጋ ስታርት ዓለም አቀፍ ፕሮግራምን ተቀላቀለች፣ እዚያም የሩሲያ ቋንቋን ተምራ፣ ስኬታማ የባሪስታ ባለሙያ ከመሆኗም በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት የራሷን ሬስቶራንት ለመክፈት አቅዳለች። ​​በዚህ ስኬቷ በመነሳሳት እህቷም ፕሮግራሙን በመጠቀም በሩሲያ ውስጥ ስልጠና እና ሥራ ማግኘት ችላለች። እህትማማቾቹ ልምዳቸውን ሲያጋሩ እንደሚገልጹት ፕሮግራሙ ታላቅ የእድገት እድሎችን የሚሰጥና እንደ የጊዜ አያያዝ እና አመራር ያሉ እና ሌሎችም የግል እድገት ክህሎቶችን ለማዳበር እድል የሚፈጥር ነው።

የራስዎን ሰራ ለመጀመር ዝግጁ ነዎት?

ከ18 እስከ 22 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ወጣት ኢትዮጵያዊ ሴቶች ለዚህ ህይወትን የሚቀይር ፕሮግራም ለማመልከት ብቁ ናቸው።

ሙሉ የጥቅማጥቅም ፓኬጁ ጥሩ ደሞዝ፣ ነፃ የአየር ትኬቶች፣ የህክምና መድን እና ልዩ የሩሲያ ቋንቋ ኮርሶችን የሚያካትት ሲሆን በስምንት የተለያዩ የስራ መስኮች ላይ ማመልከት ይቻላል።

ጊዜ ሳያጠፉ ዛሬውኑ በአላቡጋ ስታርት ማመልከቻ ፖርታል https://start-alabuga.com ላይ ያመልክቱ።
8👍2🥰1🎉1
ጦርነት ከተጀመረ የኤርትራ መንግስት አይኖርም፤ ይቀየራል - ባጫ ደበሌ‼️
አምባሳደር ጄነራል ባጫ ደበሌ ጦርነት ከተቀሰቀሰ የኤርትራ መንግስት ፋፃሜ ይሆናል ሲሉ አስጠነቀቁ።

ባጫ በቀጠናው መንግስት ይቀየራል ጂኦግራፊ ይቀየራል ሲሉ የጦርነቱን ውጤት ተንብየዋል።

በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል የተወሰነ ድንበር የለም ያሉት ባጫ፣ እሱም ራሱ ችግር ይፈጥራል ነው ያሉት።

በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ጦርነት ከተጀመረ ግንባር እና ደጀን አይኖርም ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ባጫ ይህን አስተያየት የሰጡት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ውጥረት በተነገሰበት ወቅት መሆኑ አነጋጋሪ ሁኗል።

የቀድሞው የጦር አመራር የአሁኑ ዲፕሎማት ይህን ሁሉ ዛቻ መሰል አስተያየት ከሰጡ በኋላ ግን አያስፈልግም ብለዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣3617🥱7👍4
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ  በተደራጀ የኢኮኖሚ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ከዋሉት 91 ግለሰቦች መሀል ይገኙበታል ተባለ

​በጉዳዩ ላይ ከተካሄደው ምርመራ ከተገኙ ግኝቶች መካከል፡-

👉​በገቢዎች እና ጉምሩክ አስተዳደር ውስጥ የተደራጀ ህገ-ወጥ መረብ መኖሩ ተጠቁሟል።

👉​የታክስ ምዘናዎችን ማሻሻጥ፣ ሀሰተኛ ደረሰኞችን ማስተናገድ እና የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን መሰረዝ እንደ ዘዴ ጥቅም ላይ ውለዋል ተብሏል።

👉​ድርጊቶቹ የመንግስት ገቢ እንዲቀንስ ማድረጋቸው ተመልክቷል።

​በአሁኑ ወቅት ጉዳዩ በህግ አስከባሪ አካላት ተይዞ ምርመራው በዝርዝር እየተካሄደ ይገኛል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣149😡4👍3
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚደርስ መሆኑን እና አየር ኃይሉም ይህን ለማስጠበቅ አቅሙን እየገነባ እንደሚገኝ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ላይ ብቻ የሚገደብ ሳይሆን እጅግ ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚደርስ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስታወቀ። የአየር ኃይሉ ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው እንዳሉት፣ ተቋሙ ይህንን አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚመጥን ጠንካራ አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን በትጋት እየሠራ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እጅግ በጣም ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚዘልቅ ነው። አየር ኃይሉም ለዚህ አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም የሚመጥን የላቀ የመከላከል አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን እየሠራ ይገኛል።

ምክትል አዛዡ አክለውም ባላጋራ ኃይሎች የቱንም ያህል ፍላጎትና ዛቻ ቢኖራቸውም፣ የአየር ኃይሉ የመከላከል አቅም በየቀኑ እየጨመረ መምጣቱን በሚገባ ስለሚረዱት ጥቃት ከመሰንዘር መቆጠባቸውን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል፣ የአየር ኃይሉ ከአፍሪካ አገራት ጋር ሲነፃፀር አሁን ላይ ያለበት ደረጃ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት፤ በተለይም በቴክኖሎጂ፣ በእውቀት እና ራስን ችሎ በመሥራት በኩል ኢትዮጵያ ከፍተኛውን ድርሻ እንደምትይዝ አስረድተዋል።

እንደ ምክትል አዛዡ ገለጻ፣ ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ተቋሙን ለመጎብኘት የሚመጡ የልዑካን ቡድኖች በአየር ኃይሉ ውስጥ ያለውን ዘመናዊ አሠራር ሲመለከቱ ከጠበቁት በላይ ይሆንባቸዋል። በዚህም ምክንያት ከኢትዮጵያ አየር ኃይል ጋር “በጋራ እንሥራ” የሚሉ ጥያቄዎችን በስፋት የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ ከሦስት በላይ ከሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችሉ የትብብር ስምምነቶች መፈረማቸውን ጠቁመዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪2515👍4🤔1🤩1
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 118 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ እንዳገኘ አስታወቀ

የደንበኞቹ ቁጥር 5 ነጥብ 88 ሚሊዮን በላይ መሻገሩን አገልግሎቱ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም አስመልክተው  በሰጡት መግለጫ ላይ እንዳስታወቁት በበጀት አመቱ  በከተማና በገጠር የኤሌለክትሪክ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ተሰርቷል።

አዲስ የገጠር ቀበሌዎችንና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ተደራሽ ለማድረግ በተከናወነው ስራም ከዋናው ግሪድ (የኤሌክትሪክ መረብ) 179 ተጠቃሚ ማድረግ ሲቻል  ከዋናው ግሪድ የራቁ 26 የገጠር ቀበሌዎችና ከተሞችን በኦፍ ግሪድ (በፀሃይ ኃይል) አማራጭ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ከዋናው ግሪድና በኦፍ ግሪድ በጠቅላላው 205  የገጠር ቀበሌዎችና መንደሮች ተጠቃሚ እንደሆኑ አስታውቀዋል።

በበጀት አመቱ 664 ሺህ 505 አዲስ ደንበኞች  የአገልግሎት እንዳገኙ ጨምረው ገልጸዋል።

በዚህም አዲስ ቆጣሪ ያገኙትን ጨምሮ አጠቃላይ የአገልግሎቱ ደንበኞች ቁጥር 5 ነጥብ 88 ሚሊዮን በላይ መድረሱን ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡

አገልግሎቱ በ2018 በጀት ዓመት ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ፣ ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭ እና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች 118 ነጥብ 91 ቢሊዮን ብር ገቢ እንዳገኘ  ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው አስታውቀዋል።

የተገኘው ገቢም  ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 88.4 በመቶ ብልጫ እንዳለው ጠቁመዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢14🌚95👍4🙊1
በአዲግራት ከተማ ደረጃውን ያልጠበቀ የአልኮል መጠጥ ሲያሰራጩ የነበሩ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ

የዓዲግራት ከተማ ፍርድ ቤት ደረጃውን ያልጠበቀና ፈቃድ ሳይኖረው የታሸገ የአልኮል መጠጥ (አረቄ) ለህብረተሰቡ ሲያሰራጩ የነበሩ ሦስት ግለሰቦች እያንዳንዳቸው በ8 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እና በ25 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ መወሰኑን ብስራት ከአዲግራት ከተማ የኮሚኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።

ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው ግለሰቦች የዓዲግራት ከተማ ነዋሪ የሆኑት አንደኛ ተከሳሽ ኢንጂነር ዑቅባይ በርሀ ይፍጠር፣ ሁለተኛ ተከሳሽ ፅዱቅ በርሀ ይፍጠር እና ሦስተኛ ተከሳሽ ሊቀ ሁሩያን ጋይም አስገለ አለማየሁ ናቸው። ተከሳሾቹ ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም በመኖሪያ ቤት ውስጥ አረቄ በማዘጋጀትና የተለያዩ ስቲከሮችን በመጠቀም አሽገው ለህብረተሰቡ ሲያሰራጩ መቆየታቸው በምስክርነት እና በቤተ-ሙከራ በተረጋገጠ ማስረጃ ተረጋግጧል።

ድርጊቱ ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መነሻነት በዓዲግራት ከተማ የጤና ቁጥጥር መስሪያ ቤት የስራ ሃላፊ አቶ ወለገብርኤል ገብሩ እና በከተማዋ ፖሊስ ጥረት አደገኛነቱ ተረጋግጦ ወደ ፍርድ ቤት ቀርቧል።

የዓዲግራት ከተማ ዓቃቤ ህግ የተጣለውን የፅኑ እስራት ውሳኔ የተቀበለው ቢሆንም በገንዘብ መቀጮው መጠን ላይ ግን ይግባኝ ማለቱን ፍርድ ቤቱ አስታውቋል።

የፍርድ ሂደቱን ሲከታተሉ የነበሩ የጤና ቁጥጥር አካላት ህብረተሰቡ ጊዜያቸው ያለፈባቸውን እንዲሁም በህገ-ወጥ መንገድ የሚዘዋወሩ መድኃኒቶችን፣ ሳሙናዎችን፣ ቅቤ፣ ማርና ሌሎች ለምግብነት የሚውሉ ምርቶችን ሲገዛ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግና ተመሳሳይ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ሲመለከት ለሚመለከተው አካል ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።

@Addis_Reporter
11👍4👌1
የኢትዮጵያ መንግሥትና ህወሓት ለተጨማሪ ዉጊያ እየተዘጋጁ መሆናቸዉ ተነገረ‼️

የኢትዮጵያ መንግሥት ጦርና ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ታጣቂዎች ለተጨማሪ ዉጊያ የሚያደርጉት ዝግጅት መቀጠሉን የተለያዩ ወገኖች አስታወቁ።የአዉሮጳ የሰላም ተቋም መገናኛ ዘዴዎችንና ሌሎች ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበዉ የመቀሌና የአዲስ አበባ ግንኙነት ይበልጥ እየተበላሸ ነዉ።ሁለቱ ወገኖች የሚያደርጉት የጦር ኃይል ንቅናቄም ሌላ ጦርነት ሊጫር ይችላል የሚለዉን ሥጋት አንሮታል።ሁለቱ ወገኖች ልዩነታቸዉን ሰላማዊ፣ ሁሉን አካታችና ገንቢ በሆነ ዉይይት እንዲፈቱ ተቋሙ ጠይቋል።

የአይን ምሥክሮች በበኩላቸዉ የትግራይ ኃይል የሚባለዉ የታጣቂዎች ስብስብ በርካታ ተዋጊዎችን ወደ ምዕራብ ትግራይ እያዘመተ ነዉ።እንደሚሉት የትግራይ ተዋጊዎች ትግራይ ክልልን ከአፋርና ከአማራ ክልሎች ጋር በሚያዋስነዉ ድንበር አካባቢም ምሽግ እየቆፈሩ መሆኑንም የዓይን ምሥክሮች አስታዉቀዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ጦር ባንፃሩ አማራና አፋር ክልሎች ከፍተኛ የወታደራዊ ንቅናቄ እያደረገ መሆኑን የዓይን ምሥክሮች ተናግረዋል።

ከአፋር ክልል በደረሰን መረጃ መሠረት  በክልሉ የዞን አራት ተለያዩ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ተጨማሪ ወታደሮች ሠፍረዋል።ነዋሪዎቹ በሥም በዘረዘሯቸዉ ወረዳና ቀበሌዎች  ወታደሮችን ከቦታ ቦታ ማንቀሳቀሱና ተጨማሪ ኃይል ማስሩ እስከ ትናንት ማታ ድረስ ቀጥሎ ነበር።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
19👍5
በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲ ክ/ከተማ ከሰሞኑ የወጣቶች አፈሳ በከፍተኛ ሁኔታ እየተፈፀመ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀውልናል።
በዚህ የተነሳ ወጥቶ መግባት አስቸጋሪ ሆኗል ያሉ ሲሆን የተወሰኑ ወጣቶች ገንዘብ እየከፈሉ እየተለቀቁ ነው ብለዋል።

Via : አዩዘሀበሻ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
14👍6🤪5😢3💯2
ሲፒጄ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ገለልተኛ የዜና ክፍሎችን “ለመበተን ዘመቻ” እያካሄዱ ነው ሲል ከሰሰ!

ጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ቡድኑ በሐሙስ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ እነዚህ ተከታታይ ክስተቶች በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ግንባር ቀደም ነጻ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት መካከል በአንዱ ላይ የሚደረገውን ጫና በከፍተኛ ሁኔታ ማባበሳቸውን ገልጻል።

የሲፒጄ የአፍሪካ ፕሮግራም አስተባባሪ ሙቶኪ ሙሞ “በአዲስ ስታንዳርድ እና በዮናስ ከድር ላይ የተፈጸሙት እነዚህ ጥቃቶች የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት የአገሪቱን ነጻ የዜና ድርጅቶች ለመበተን የሚያካሂዱት ዘመቻ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ያሳያሉ” ብለዋል።

አስተባባሪዋ ባለሥልጣናቱ “የተቋሙን ቁሳቁሶች በአፋጣኝ እንዲመልሱ፣ ከቢሮው በግዳጅ የማስወጣት ሂደትን እንዲያስቆሙ፣ ማንኛውንም ተጨማሪ ትንኮሳ እንዲያቆሙ እና ለዮናስ እስርና ጥቃት ተጠያቂ የሆኑ አካላት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ  እንዲያደርጉ” አሳስበዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
13👍3
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ – የሚፈልጓቸውን አዳዲስ ዜናዎችን በአጭሩ እና በጥልቀት ከኛ ዘንድ ያንብቡ።

🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።

🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።

አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy

@sputnik_ethiopia
6👍2