አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Photo
#ቢሾፍቱ‼️
አሜሪካ በኢትዮጵያ አየር መንገድ 12.5 ቢሊዮን ዶላር የቢሾፍቱ አዲስ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአሜሪካ ኩባንያዎች እንዲሳተፉ ደጅ እየጠናች ነው።
አሜሪካ በቢሾፍቱ እየተገነባ ባለው አዲሱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአሜሪካ ኩባንያዎች ተሳትፎ እንዲኖራቸው እየሰራች መሆኗን የአሜሪካ የንግድ መምሪያ ከፍተኛ ኃላፊ ማርክ ሚቼል ተናግረዋል።
ሚቼል እንዳሉት፣ ዋሽንግተን በፕሮጀክቱ ውስጥ የአሜሪካ ኩባንያዎች ተሳትፎ እንዲረጋገጥ " በቅርበት እየሰራች " ሲሆን፣ ይህም በአፍሪካ የመሠረተ ልማትና የኢንቨስትመንት ተፅዕኖ ለማሳደግ አሜሪካ ከቻይናና ከሌሎች ኃያላን ሀገራት ጋር እያደረገችው ያለው ፉክክር አካል መሆኑን አመልክተዋል።
እሳቸው ይህን ያሉት በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሎጂስቲክስና ኮሙኒኬሽን ሲምፖዚየም ወቅት በቪዲዮ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃላፊዎችም ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል።
ሚቼል የአሜሪካ ኩባንያዎች በፕሮጀክቱ ውስጥ በትክክል ምን ዓይነት ሚና እንደሚኖራቸው በይፋ ባይገልጹም፣ ትብብሩ ወደፊት በGE Aerospace ሞተሮች የሚንቀሳቀሱ ተጨማሪ የቦይንግ አውሮፕላኖች ግዥ ሊያመራ እንደሚችል ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ አየር መንገድ በሚያዝያ ወር ተጨማሪ 6 የቦይንግ 787-9 Dreamliner አውሮፕላኖችን ለመግዛት ስምምነት የፈረመ ሲሆን ይህም ከዚህ ቀደም ከታዘዡ 20 አውሮፕላኖች ተጨማሪ ነው።
ከወራት በፊት በቢሾፍቱ የተጀመረው እጅግ ግዙፉ ፕሮጀክት በ2030 ሲጠናቀቅ " የአፍሪካ ዱባይ " እንዲሆን ታቅዷል።
ከአበዳሪዎች አንዱ የአፍሪካ ልማት ባንክ ለፕሮጀክቱ 500 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ቃል የገባ ሲሆን ከጠቅላላው ወጪ 8.7 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ማሰባሰብ ሂደትንም እየመራ ነው።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የአሜሪካ የፋይናንስ ተቋማት በፕሮጀክቱ ለመሳተፍ ፍላጎታቸውን መግለጻቸውን ተናግረው ነበር።
በተጨማሪም፥ አሜሪካ ከኢትዮጵያ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ኢንስቲትዩት ጋር ትብብሯን ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ሚቼል ገልጸው፣ ይህም የአሜሪካ የAI ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ እና ወደ አፍሪካ ገበያ እንዲስፋፋ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑን አስታውቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አሜሪካ በኢትዮጵያ አየር መንገድ 12.5 ቢሊዮን ዶላር የቢሾፍቱ አዲስ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአሜሪካ ኩባንያዎች እንዲሳተፉ ደጅ እየጠናች ነው።
አሜሪካ በቢሾፍቱ እየተገነባ ባለው አዲሱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአሜሪካ ኩባንያዎች ተሳትፎ እንዲኖራቸው እየሰራች መሆኗን የአሜሪካ የንግድ መምሪያ ከፍተኛ ኃላፊ ማርክ ሚቼል ተናግረዋል።
ሚቼል እንዳሉት፣ ዋሽንግተን በፕሮጀክቱ ውስጥ የአሜሪካ ኩባንያዎች ተሳትፎ እንዲረጋገጥ " በቅርበት እየሰራች " ሲሆን፣ ይህም በአፍሪካ የመሠረተ ልማትና የኢንቨስትመንት ተፅዕኖ ለማሳደግ አሜሪካ ከቻይናና ከሌሎች ኃያላን ሀገራት ጋር እያደረገችው ያለው ፉክክር አካል መሆኑን አመልክተዋል።
እሳቸው ይህን ያሉት በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሎጂስቲክስና ኮሙኒኬሽን ሲምፖዚየም ወቅት በቪዲዮ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃላፊዎችም ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል።
ሚቼል የአሜሪካ ኩባንያዎች በፕሮጀክቱ ውስጥ በትክክል ምን ዓይነት ሚና እንደሚኖራቸው በይፋ ባይገልጹም፣ ትብብሩ ወደፊት በGE Aerospace ሞተሮች የሚንቀሳቀሱ ተጨማሪ የቦይንግ አውሮፕላኖች ግዥ ሊያመራ እንደሚችል ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ አየር መንገድ በሚያዝያ ወር ተጨማሪ 6 የቦይንግ 787-9 Dreamliner አውሮፕላኖችን ለመግዛት ስምምነት የፈረመ ሲሆን ይህም ከዚህ ቀደም ከታዘዡ 20 አውሮፕላኖች ተጨማሪ ነው።
ከወራት በፊት በቢሾፍቱ የተጀመረው እጅግ ግዙፉ ፕሮጀክት በ2030 ሲጠናቀቅ " የአፍሪካ ዱባይ " እንዲሆን ታቅዷል።
ከአበዳሪዎች አንዱ የአፍሪካ ልማት ባንክ ለፕሮጀክቱ 500 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ቃል የገባ ሲሆን ከጠቅላላው ወጪ 8.7 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ማሰባሰብ ሂደትንም እየመራ ነው።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የአሜሪካ የፋይናንስ ተቋማት በፕሮጀክቱ ለመሳተፍ ፍላጎታቸውን መግለጻቸውን ተናግረው ነበር።
በተጨማሪም፥ አሜሪካ ከኢትዮጵያ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ኢንስቲትዩት ጋር ትብብሯን ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ሚቼል ገልጸው፣ ይህም የአሜሪካ የAI ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ እና ወደ አፍሪካ ገበያ እንዲስፋፋ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑን አስታውቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤24🤪9🙊4👍3😎1
“በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል”ዳቪድ ማልፓስ
የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዳቪድ ማልፓስ የኢትዮጵያ ብር መዳከም እና የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያዎች ድህነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማባባሳቸውን በመግለጽ፤ በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች «ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል» ሲሉ ተናግረዋል።
በተቃራኒው ጥቂት ቡድኖች የውጭ ምንዛሬን እና የሀገር ውስጥ ብድርን በልዩ ሁኔታ ማግኘት በመቻላቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ማልፓስ፤ ስታንሊ ፊሸር መታሰቢያ በተሰኘ መድረክ ላይ ባቀረቡት የፖሊሲ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን በዋና ምሳሌነት የተጠቀሙ ሲሆን፥ ሀገሪቱ የእርሻ መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የውኃ፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና የሰው ኃይል አቅም ያላት በመሆኗ «ትልቅ የእድገት አቅም» ያላት ሀገር እንደሆነች ገልጸዋል።(AS)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዳቪድ ማልፓስ የኢትዮጵያ ብር መዳከም እና የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያዎች ድህነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማባባሳቸውን በመግለጽ፤ በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች «ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል» ሲሉ ተናግረዋል።
በተቃራኒው ጥቂት ቡድኖች የውጭ ምንዛሬን እና የሀገር ውስጥ ብድርን በልዩ ሁኔታ ማግኘት በመቻላቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ማልፓስ፤ ስታንሊ ፊሸር መታሰቢያ በተሰኘ መድረክ ላይ ባቀረቡት የፖሊሲ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን በዋና ምሳሌነት የተጠቀሙ ሲሆን፥ ሀገሪቱ የእርሻ መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የውኃ፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና የሰው ኃይል አቅም ያላት በመሆኗ «ትልቅ የእድገት አቅም» ያላት ሀገር እንደሆነች ገልጸዋል።(AS)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍22❤21😢5🙏1
የጦርነት ውጤት አስከፊ ነው‼️
ዛሬ በሸረሪና የተፈፀመው እልቂት ዘግናኝ ነው።
የህወሓት አርሚ 70 ታጣቂዎች በሸረሪና ግንባር ወደ ሁመራ ለመግባት ጥቃት የፈፀሙት ከታች የተዘረዘሩትን ሎጀስቲክ፣የሰው ሀይል እና መሳሪያ በመያዝ ነው።
- ዙ-23 03 በፓትሮል የተጫነ
- 107 ሮኬት 01
- ኮርኔት 02
- ሞርታር-120 01
- ሞርታር-82 01
- ሞርታር (ልዩ) 02 [በምርመራ ላይ ነው]
- ድሽቃ 09
- የድሽቃ ሆ/እግር 01
- RPG 06
- ብሬን 54
- ስናይፐር 05
- ክላሽ 1347
- ሬድዮ 183
- ኦራል 02
- ፓትሮል 02
- ጄኔሬተር 02
ይህንን ጥቃት ተከትሎ በአካባቢው የሚገኘው መከላከያ ሰራዊት በወሰደው የአፀፋ ጥቃት:-
- የተማረከ 01 ሻለቃ አዛዥ
- የተማረከ 141 ታጣቂ እና የተለያየ የአመራር
- የተገደለ እና የቆሰለ 1000+ መሆናቸውን የአዩዘሀበሻ ምንጮች አረጋግጠዋል።
የተለያዩ ትጥቆች፣ የሕክምና ቁሳቁስ፣ ተተኳሾች፣ የደረት ትጥቆች፣ መድኃኒቶች፣ የመኪና መለዋወጫ፣ ነዳጅ ዘይትን ጨምሮ የጥይት ዴፖዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ሸረሪና እና አካባቢው ሙሉ ለሙሉ በመከላከያ ቁጥጥር ስር መሆኑ ተረጋግጧል። ተኩሱ ሙሉ ለሙሉ ቆሟል።
በዚሁ በቃ ይበለን።
Via : አዩዘሀበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዛሬ በሸረሪና የተፈፀመው እልቂት ዘግናኝ ነው።
የህወሓት አርሚ 70 ታጣቂዎች በሸረሪና ግንባር ወደ ሁመራ ለመግባት ጥቃት የፈፀሙት ከታች የተዘረዘሩትን ሎጀስቲክ፣የሰው ሀይል እና መሳሪያ በመያዝ ነው።
- ዙ-23 03 በፓትሮል የተጫነ
- 107 ሮኬት 01
- ኮርኔት 02
- ሞርታር-120 01
- ሞርታር-82 01
- ሞርታር (ልዩ) 02 [በምርመራ ላይ ነው]
- ድሽቃ 09
- የድሽቃ ሆ/እግር 01
- RPG 06
- ብሬን 54
- ስናይፐር 05
- ክላሽ 1347
- ሬድዮ 183
- ኦራል 02
- ፓትሮል 02
- ጄኔሬተር 02
ይህንን ጥቃት ተከትሎ በአካባቢው የሚገኘው መከላከያ ሰራዊት በወሰደው የአፀፋ ጥቃት:-
- የተማረከ 01 ሻለቃ አዛዥ
- የተማረከ 141 ታጣቂ እና የተለያየ የአመራር
- የተገደለ እና የቆሰለ 1000+ መሆናቸውን የአዩዘሀበሻ ምንጮች አረጋግጠዋል።
የተለያዩ ትጥቆች፣ የሕክምና ቁሳቁስ፣ ተተኳሾች፣ የደረት ትጥቆች፣ መድኃኒቶች፣ የመኪና መለዋወጫ፣ ነዳጅ ዘይትን ጨምሮ የጥይት ዴፖዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ሸረሪና እና አካባቢው ሙሉ ለሙሉ በመከላከያ ቁጥጥር ስር መሆኑ ተረጋግጧል። ተኩሱ ሙሉ ለሙሉ ቆሟል።
በዚሁ በቃ ይበለን።
Via : አዩዘሀበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤51💔18👍11🕊6✍3👀2🙈2😢1🙊1
በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ ያለው የክረምት ሁኔታ ከላይ በምስል የተያያዘውን ይመስላል፣ ምንም ዝናብ የለም።
የፓስፍክ ውቂያኖስ ሙቀት ባልተለመደ ሁነታ በመጨመሩ ምክንያት በሰሜን፣ በመካከለኛና ምስራቅ አከባቢ የዘንድሮው የክረምት ዝናብ አጭር መሆኑና ክረምቱም ቶሎ እንደሚወጣ የኢትዮጵያ ሜትሮዎሎጂ ማስታወቁ አይዘነጋም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የፓስፍክ ውቂያኖስ ሙቀት ባልተለመደ ሁነታ በመጨመሩ ምክንያት በሰሜን፣ በመካከለኛና ምስራቅ አከባቢ የዘንድሮው የክረምት ዝናብ አጭር መሆኑና ክረምቱም ቶሎ እንደሚወጣ የኢትዮጵያ ሜትሮዎሎጂ ማስታወቁ አይዘነጋም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
💔13😢12👍4❤3🙊2
ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡30-8፡30
👉 ቱሉዲምቱ ኮንዶሚኒየም፣ ዓለም ባንክ 700 ማህበራት ቤቶች፣ ገላን እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 12፡00 - 4፡00
👉 በመቀሌ ቀበሌ 14፣ 15 ፣ 17 ፣ መቀሌ ተክላይማኖት እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡30-10፡00
👉 አዋሽ መልካሳ እና አከባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00-7፡00
👉 በበህዳር ሪጅን አዲስ ዓለም፣ ኦቪድ ኮኒስትረክሽን፣ ሰማታት፣ ግዮን ት/ቤት፣ ሚሊኒየም ት/ቤት፣ ናይል ቪው ሆቴል እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ነገ ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡30-8፡30
👉 ቱሉዲምቱ ኮንዶሚኒየም፣ ዓለም ባንክ 700 ማህበራት ቤቶች፣ ገላን እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 12፡00 - 4፡00
👉 በመቀሌ ቀበሌ 14፣ 15 ፣ 17 ፣ መቀሌ ተክላይማኖት እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡30-10፡00
👉 አዋሽ መልካሳ እና አከባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00-7፡00
👉 በበህዳር ሪጅን አዲስ ዓለም፣ ኦቪድ ኮኒስትረክሽን፣ ሰማታት፣ ግዮን ት/ቤት፣ ሚሊኒየም ት/ቤት፣ ናይል ቪው ሆቴል እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍2
#USA 🇺🇸 #VISA
አሜሪካ ለቪዛ የምትይዘውን ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ዶላር ልታሳድግ ነው።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የበርካታ አገራት ዜጎች ቪዛ ሲያመለክቱ ያስይዙት የነበረውን ገንዘብ ከ15 ሺህ ዶላር ወደ 20 ሺህ ዶላር (3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) ከፍ በማድረግ ቋሚ ሊያደርግ ነው።
መሥሪያ ቤቱ እንደገለፀው መርሃ ግብሩ የቢዝነስ እና የቱሪስት (ቢ1 እና ቢ2) ቪዛ አመልካቾች ላይ ተግባራዊ የሚሆን ነው።
ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ አሜሪካ ውስጥ ከቆዩ ገንዘቡ ተመላሽ እንዳይሆን የሚያደርገው ይህ አሠራር ተግባራዊ ይሆንባቸዋል ከተባሉ አብዛኞቹ ከአፍሪካ ከሆኑ 50 አገራት መካከል ፦
- #ኢትዮጵያ፣
- ጂቡቲ፣
- ናይጄሪያ፣
- ሴኔጋል፣
- ኡጋንዳ፣
- ታንዛኒያ ይገኙበታል።
ይህ በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው የተሻሻለው ፕሮግራም፣ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ የሚቆዩ ጎብኝዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ መሠረት አመልካቾች እንደ ኤምባሲው ኦፊሰሮች ውሳኔ ለቪዛ እስከ 20 ሺህ ዶላር (ከ3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) የሚደርስ ገንዘብ እንዲያስይዙ ሊጠይቁ ይችላሉ።
አሜሪካ ውስጥ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ዜጎች ባሏቸው አገራት እና የአገር ውስጥ ሰነዶች ላይ የላላ ቁጥጥር በሚያደርጉ አገራት የቪዛ ማስያዣ የሙከራ መርሃ ግብር ተግባራዊ ማድረግ የጀመረችው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ነበር።
መርሃ ግብሩ ለአንድ ዓመት የሚቆይ የነበረ ሲሆን የተቀመጠለት ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ ነው አዲሱ መመሪያ የወጣው።
በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው ይህ አዲሱ የቪዛ ማስያዣ ገንዘብ ፕሮግራም ቋሚ እንደሚሆንም ተገልጿል።
በተጠናቀቀው የሙከራ መርሃ ግብር መሠረት አመልካቾች ከ5 ሺህ ፣ ከ10 ሺህ እስከ 15 ሺህ ዶላር ድረስ እንዲያስይዙ ይጠየቁ የነበረ ሲሆን በአዲሱ ፕሮግራም አነስተኛው 5 ሺህ ዶላር ከዝርዝሩ ወጥቶ፣ ከፍተኛው የማስያዣ ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ከፍ ተደርጓል።
በአዲሱ መርሃ ግብር ከተካተቱ 50 አገራት መካከል 30ዎቹ የሚገኙት በአፍሪካ ውስጥ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አሜሪካ ለቪዛ የምትይዘውን ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ዶላር ልታሳድግ ነው።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የበርካታ አገራት ዜጎች ቪዛ ሲያመለክቱ ያስይዙት የነበረውን ገንዘብ ከ15 ሺህ ዶላር ወደ 20 ሺህ ዶላር (3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) ከፍ በማድረግ ቋሚ ሊያደርግ ነው።
መሥሪያ ቤቱ እንደገለፀው መርሃ ግብሩ የቢዝነስ እና የቱሪስት (ቢ1 እና ቢ2) ቪዛ አመልካቾች ላይ ተግባራዊ የሚሆን ነው።
ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ አሜሪካ ውስጥ ከቆዩ ገንዘቡ ተመላሽ እንዳይሆን የሚያደርገው ይህ አሠራር ተግባራዊ ይሆንባቸዋል ከተባሉ አብዛኞቹ ከአፍሪካ ከሆኑ 50 አገራት መካከል ፦
- #ኢትዮጵያ፣
- ጂቡቲ፣
- ናይጄሪያ፣
- ሴኔጋል፣
- ኡጋንዳ፣
- ታንዛኒያ ይገኙበታል።
ይህ በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው የተሻሻለው ፕሮግራም፣ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ የሚቆዩ ጎብኝዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ መሠረት አመልካቾች እንደ ኤምባሲው ኦፊሰሮች ውሳኔ ለቪዛ እስከ 20 ሺህ ዶላር (ከ3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) የሚደርስ ገንዘብ እንዲያስይዙ ሊጠይቁ ይችላሉ።
አሜሪካ ውስጥ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ዜጎች ባሏቸው አገራት እና የአገር ውስጥ ሰነዶች ላይ የላላ ቁጥጥር በሚያደርጉ አገራት የቪዛ ማስያዣ የሙከራ መርሃ ግብር ተግባራዊ ማድረግ የጀመረችው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ነበር።
መርሃ ግብሩ ለአንድ ዓመት የሚቆይ የነበረ ሲሆን የተቀመጠለት ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ ነው አዲሱ መመሪያ የወጣው።
በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው ይህ አዲሱ የቪዛ ማስያዣ ገንዘብ ፕሮግራም ቋሚ እንደሚሆንም ተገልጿል።
በተጠናቀቀው የሙከራ መርሃ ግብር መሠረት አመልካቾች ከ5 ሺህ ፣ ከ10 ሺህ እስከ 15 ሺህ ዶላር ድረስ እንዲያስይዙ ይጠየቁ የነበረ ሲሆን በአዲሱ ፕሮግራም አነስተኛው 5 ሺህ ዶላር ከዝርዝሩ ወጥቶ፣ ከፍተኛው የማስያዣ ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ከፍ ተደርጓል።
በአዲሱ መርሃ ግብር ከተካተቱ 50 አገራት መካከል 30ዎቹ የሚገኙት በአፍሪካ ውስጥ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20🤪5😢3👍2
የሼክ መሐመድ አልአሙዲ ሀብት 10.1 ቢሊዮን ዶላር ደረሰ፤ በብሉምበርግ የዓለም ቢሊየነሮች ዝርዝር 375ኛ ደረጃን ያዙ
የትውልደ ኢትዮጵያዊው ባለሀብት ሼክ መሐመድ አልአሙዲ የተጣራ ሀብት 10.1 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን ተከትሎ በብሉምበርግ የዓለም ቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ በድጋሚ ተካተዋል።
ዛሬ ኦገስት 1፣ 2026 ይፋ በሆነው የብሉምበርግ ዝርዝር መሠረት፣ አልአሙዲ በዓለም 375ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። በ2026 ብቻ የሀብታቸው መጠን በ1.67 ቢሊዮን ዶላር፣ ወይም በ19.7 በመቶ አድጓል። በቅርብ ጊዜም በአንድ ቀን ብቻ 33.7 ሚሊዮን ዶላር መጨመሩ ተመዝግቧል።
የብሉምበርግ ግምገማ እንደሚያሳየው፣ የአልአሙዲ ሀብት መጨመር ከኢነርጂ፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከመሠረተ ልማት እና ከሌሎች የንግድ ንብረቶቻቸው ዋጋ መጨመር ጋር የተያያዘ ነው። ከዚህ ቀደም ከዋና ንብረቶቻቸው መካከል የነበረው የስዊድኑ ፕሪም (Preem) የነዳጅ ማጣሪያ ኩባንያ ግን ለVARO Energy ከተላለፈ በኋላ በአሁኑ ጊዜ VAROPreem በተባለ የተዋሃደ ኩባንያ ስር ይገኛል።
በሌላ በኩል፣ ብሉምበርግ የአልአሙዲን ሀብት ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደደረሰ ቢገልጽም፣ በፎርብስ 2026 ዓመታዊ የዓለም ቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ ግን ስማቸው አልተካተተም። ይህም ሁለቱ ተቋማት የቢሊየነሮችን ሀብት በሚገምቱበት የመረጃ ምንጭና የግምገማ ዘዴ ልዩነት መኖሩን ያሳያል።
በብሉምበርግ የወጣው አዲሱ መረጃ የሚያመለክተው፣ ሼክ መሐመድ አልአሙዲ ከቀደሙት ዓመታት የሀብት መቀነስ በኋላ በድጋሚ ወደ 10 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሀብት ደረጃ መመለሳቸውን ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የትውልደ ኢትዮጵያዊው ባለሀብት ሼክ መሐመድ አልአሙዲ የተጣራ ሀብት 10.1 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን ተከትሎ በብሉምበርግ የዓለም ቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ በድጋሚ ተካተዋል።
ዛሬ ኦገስት 1፣ 2026 ይፋ በሆነው የብሉምበርግ ዝርዝር መሠረት፣ አልአሙዲ በዓለም 375ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። በ2026 ብቻ የሀብታቸው መጠን በ1.67 ቢሊዮን ዶላር፣ ወይም በ19.7 በመቶ አድጓል። በቅርብ ጊዜም በአንድ ቀን ብቻ 33.7 ሚሊዮን ዶላር መጨመሩ ተመዝግቧል።
የብሉምበርግ ግምገማ እንደሚያሳየው፣ የአልአሙዲ ሀብት መጨመር ከኢነርጂ፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከመሠረተ ልማት እና ከሌሎች የንግድ ንብረቶቻቸው ዋጋ መጨመር ጋር የተያያዘ ነው። ከዚህ ቀደም ከዋና ንብረቶቻቸው መካከል የነበረው የስዊድኑ ፕሪም (Preem) የነዳጅ ማጣሪያ ኩባንያ ግን ለVARO Energy ከተላለፈ በኋላ በአሁኑ ጊዜ VAROPreem በተባለ የተዋሃደ ኩባንያ ስር ይገኛል።
በሌላ በኩል፣ ብሉምበርግ የአልአሙዲን ሀብት ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደደረሰ ቢገልጽም፣ በፎርብስ 2026 ዓመታዊ የዓለም ቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ ግን ስማቸው አልተካተተም። ይህም ሁለቱ ተቋማት የቢሊየነሮችን ሀብት በሚገምቱበት የመረጃ ምንጭና የግምገማ ዘዴ ልዩነት መኖሩን ያሳያል።
በብሉምበርግ የወጣው አዲሱ መረጃ የሚያመለክተው፣ ሼክ መሐመድ አልአሙዲ ከቀደሙት ዓመታት የሀብት መቀነስ በኋላ በድጋሚ ወደ 10 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሀብት ደረጃ መመለሳቸውን ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤25👍8🫡1
በአማራ ክልል የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።
በክልሉ 173,699 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን፤ 135,003 (77.72%) ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት በማስመዝገብ ማለፋቸውን የክልሉ ትምህርሮ አሳውቋል።
ውጤት ለማየት 👇
https://amhara.ministry.et/#/result
አድራሻውን ከተጫኑ በኋላ የተማሪውን መለያ ቁጥር እና ስም በአማርኛ በማስገባት 'Check your result' የሚለውን በመጫን ውጤትዎን ማየት ይችላሉ፡፡
በቴሌግራም ቦት ለማየት 👇
@emacs_ministry_result_qmt_bot
የቴሌግራም ቦት ላይ ከገቡ በኋላ Start የሚለውን ይጫኑ፣ ክፍልዎን ይምረጡ፣ ከዚያም ክልልዎን ይምረጡ፣ የምዝገባ መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስምን በማስገባት ውጤትዎን ማየት ይችላሉ።
ቅሬታ ለማቅረብ 👇 https://amhara.ministry.et/#/complaint
VPN የምትጠቀሙ ከሆነ በቅድሚያ ማጥፋት ይኖርባችኋል፡፡
በክልሉ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም ይፋ እንደሚደረግ ቢሮው ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በክልሉ 173,699 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን፤ 135,003 (77.72%) ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት በማስመዝገብ ማለፋቸውን የክልሉ ትምህርሮ አሳውቋል።
ውጤት ለማየት 👇
https://amhara.ministry.et/#/result
አድራሻውን ከተጫኑ በኋላ የተማሪውን መለያ ቁጥር እና ስም በአማርኛ በማስገባት 'Check your result' የሚለውን በመጫን ውጤትዎን ማየት ይችላሉ፡፡
በቴሌግራም ቦት ለማየት 👇
@emacs_ministry_result_qmt_bot
የቴሌግራም ቦት ላይ ከገቡ በኋላ Start የሚለውን ይጫኑ፣ ክፍልዎን ይምረጡ፣ ከዚያም ክልልዎን ይምረጡ፣ የምዝገባ መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስምን በማስገባት ውጤትዎን ማየት ይችላሉ።
ቅሬታ ለማቅረብ 👇 https://amhara.ministry.et/#/complaint
VPN የምትጠቀሙ ከሆነ በቅድሚያ ማጥፋት ይኖርባችኋል፡፡
በክልሉ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም ይፋ እንደሚደረግ ቢሮው ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤8😢3👍2
በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ተማሪዎች እና የሚያስተምሩ መምህራን ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ እንዲዘዋወሩ ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ።
በትግራይ በሚገኙ አራት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ የተወሰኑ ተማሪዎች እና መምህራን በክልሉ ባለው የጸጥታ ስጋት ምክንያት ወደ ሌሎች የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲዛወሩ ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኝ ተሰምቷል።
በመቐለ፣ አክሱም፣ ዓዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች እና የሚያስተምሩ መምህራን ጥያቄያቸውን ለመንግሥት እያቀረቡ ነው።
ተማሪዎች እና መምህራን በክልሉ በሚታየው የጸጥታ ስጋት ምክንያት የቅሬታ ጥያቄ እያስገቡ ሲሆን፤ እስካሁን ከትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠ የዝውውር ውሳኔም ሆነ የተገባ ቃል አለመኖሩን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝዳንት ሓየሎም ስዩም ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በትግራይ በሚገኙ አራት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ የተወሰኑ ተማሪዎች እና መምህራን በክልሉ ባለው የጸጥታ ስጋት ምክንያት ወደ ሌሎች የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲዛወሩ ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኝ ተሰምቷል።
በመቐለ፣ አክሱም፣ ዓዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች እና የሚያስተምሩ መምህራን ጥያቄያቸውን ለመንግሥት እያቀረቡ ነው።
ተማሪዎች እና መምህራን በክልሉ በሚታየው የጸጥታ ስጋት ምክንያት የቅሬታ ጥያቄ እያስገቡ ሲሆን፤ እስካሁን ከትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠ የዝውውር ውሳኔም ሆነ የተገባ ቃል አለመኖሩን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝዳንት ሓየሎም ስዩም ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤8👍6🤔2
የማስታወቂያ ግብዣ
የተከበራችሁ ቤተሰቦች ከ35,000 በላይ ተከታይ ባለው እና በደቂቃዎች ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝ ባለው በዚህ የቴሌግራም ቻናል ላይ ምርትና አገልግሎታችሁን ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንድታስተዋውቁ በአክብሮት ተጋብዛችኋል‼
✔Youtube ቻናል …
✔የትምህርት ተቋማት…...
✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…...
✔የትራንስፖርት አገልግሎት…....
✔ኤጀንሲዎች……
✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች......
✔ሌሎችም የምትሰጧቸውን አገልግሎቶች.....ማስተዋወቅ የምትፈልጉ በዚህ በኩል ኑ 👇
መልዕክት መቀበያ:—@Addis_reporter_bot
የተከበራችሁ ቤተሰቦች ከ35,000 በላይ ተከታይ ባለው እና በደቂቃዎች ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝ ባለው በዚህ የቴሌግራም ቻናል ላይ ምርትና አገልግሎታችሁን ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንድታስተዋውቁ በአክብሮት ተጋብዛችኋል‼
✔Youtube ቻናል …
✔የትምህርት ተቋማት…...
✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…...
✔የትራንስፖርት አገልግሎት…....
✔ኤጀንሲዎች……
✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች......
✔ሌሎችም የምትሰጧቸውን አገልግሎቶች.....ማስተዋወቅ የምትፈልጉ በዚህ በኩል ኑ 👇
መልዕክት መቀበያ:—@Addis_reporter_bot
👍4❤2
የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት እና በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ አማካሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የትግራይ ሰራዊት አመራሮችና አባላት በጥቂት የህወሓት ፖለቲከኞች ተገፋፍተው ክልሉን ዳግም ወደ እልቂት ከመክተት እንዲቆጠቡ አሳሰቡ።
አቶ ጌታቸው በኤክስ ገጻቸው የደብረ ጽዮንን ንግግር አያይዘው ባሰራጩት እጅግ ነቀፋ የበዛበት መልእክት፣ የህወሓት አመራሮች የትግራይን ህዝብ አንድነት በመበተን እንዲሁም በፋኖ፣ በሱዳኑ ጄኔራል አል-ቡርሃን እና በኤርትራ መንግስት (ሻዕቢያ) ላይ ተማምነው ዳግም ጦርነት ለመክፈት የሚያደርጉት ፉከራ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ገልጸዋል። በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ በወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ) እና በቀድሞው የደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ መሪነት፣ በጉልበት "አራት ኪሎ እንመለሳለን" በማለት የሚያልሙትን "ቅዠት" በአስቸኳይ እንዲያቆሙ አስጠንቅቀዋል።
ከፌደራል መንግስቱ ጋር በቅርበት እየሰሩ የሚገኙት አቶ ጌታቸው፣ የትግራይ ሰራዊት ከምንም በላይ የህዝቡን ደህንነት እንዲያስቀድም ጥሪ አቅርበዋል። አቅም እያለ የህዝቡን የህልውና ጥያቄዎች መመለስ የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሰራዊቱ በህይወቱና በአካሉ ላይ እየተቆመረበት ያለውን ኃይል 'ይበቃል' ሊለው እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመጨረሻም "በሐውልቲ (የህወሓት ጽህፈት ቤት) የመሸገው የብጥብጥ ቡድን" ሲሉ የጠሯቸው እነዚህ አካላት፣ በፉከራና በውጭ ኃይሎች ድጋፍ ላይ በመተማመን የዲፕሎማሲ በሮችን ከዘጉ በኋላ፣ አሁን መሬት ላይ ያለው እውነት ሲከብዳቸው "ዓለም ይድረስልኝ" እያሉ መጮሃቸው ማመዛዘን የጎደለው የፖለቲካ ኪሳራ መሆኑን በአጽንኦት ተችተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አቶ ጌታቸው በኤክስ ገጻቸው የደብረ ጽዮንን ንግግር አያይዘው ባሰራጩት እጅግ ነቀፋ የበዛበት መልእክት፣ የህወሓት አመራሮች የትግራይን ህዝብ አንድነት በመበተን እንዲሁም በፋኖ፣ በሱዳኑ ጄኔራል አል-ቡርሃን እና በኤርትራ መንግስት (ሻዕቢያ) ላይ ተማምነው ዳግም ጦርነት ለመክፈት የሚያደርጉት ፉከራ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ገልጸዋል። በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ በወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ) እና በቀድሞው የደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ መሪነት፣ በጉልበት "አራት ኪሎ እንመለሳለን" በማለት የሚያልሙትን "ቅዠት" በአስቸኳይ እንዲያቆሙ አስጠንቅቀዋል።
ከፌደራል መንግስቱ ጋር በቅርበት እየሰሩ የሚገኙት አቶ ጌታቸው፣ የትግራይ ሰራዊት ከምንም በላይ የህዝቡን ደህንነት እንዲያስቀድም ጥሪ አቅርበዋል። አቅም እያለ የህዝቡን የህልውና ጥያቄዎች መመለስ የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሰራዊቱ በህይወቱና በአካሉ ላይ እየተቆመረበት ያለውን ኃይል 'ይበቃል' ሊለው እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመጨረሻም "በሐውልቲ (የህወሓት ጽህፈት ቤት) የመሸገው የብጥብጥ ቡድን" ሲሉ የጠሯቸው እነዚህ አካላት፣ በፉከራና በውጭ ኃይሎች ድጋፍ ላይ በመተማመን የዲፕሎማሲ በሮችን ከዘጉ በኋላ፣ አሁን መሬት ላይ ያለው እውነት ሲከብዳቸው "ዓለም ይድረስልኝ" እያሉ መጮሃቸው ማመዛዘን የጎደለው የፖለቲካ ኪሳራ መሆኑን በአጽንኦት ተችተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍6🤣3🤪3🙊1
በመከላከያ ሠራዊትና በትግራይ የጸጥታ ኃይሎች መካከል ሸረሪና በተባለ ቦታ የተጀመረው ውጊያ መቆሙን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ማንነታቸው ያልተገለጸ የመረጃ ምንጮች ዋቢ አድርጎ ዘገበ። ከኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው ሸረሪና የተባለ ቦታ ውጊያ የተቀሰቀሰው ትላንት ቅዳሜ ከማለዳው 12 ሰዓት ገደማ እንደሆነ አንድ ስማቸው ያልተገለጸ የህወሓት አባል መናገራቸውን የዜና ወኪሉ ዘግቧል።
በከባድ የጦር መሣሪያ እና በድሮን ጭምር የተደረገው ውጊያው ከ23 ሰዓታት ገደማ በኋላ እንደቆመ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዋቢ ያደረጋቸው የመረጃ ምንጭ ተናግረዋል። በግጭቱ ምን ያክል ሰዎች እንደተገደሉ ወይም እንደቆሰሉ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ሌላ የጸጥታ የመረጃ ምንጭ በእርግጥም ውጊያው እንደቆመ ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል። ይሁንና ከህወሓት በኩል የቀረበው መረጃ ትክክለኛ መሆኑን በገለልተኝነት እንዳላረጋገጠ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት በዘገባው ጠቁሟል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተሰረዘው ህወሓት የሚመራው የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ትላንት ቅዳሜ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት ከማለዳ ጀምሮ በሸረሪና በኩል ውጊያ ጀምሯል በማለት ወንጅሎ ነበር። የፌድራል መንግሥት ግን ስለ ጉዳዩ በይፋ የሰጠው ማብራሪያም ሆነ ምላሽ የለም። ይሁንና የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትሩ አብርሀም በላይ በተረጋገጠ የፌስቡክ ገጻቸው ባሠፈሩት ጽሁፍ ህወሓትን በሸረሪና በኩል ጦርነት በመክፈት ወንጅለዋል።
በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና በትግራይ የጸጥታ ኃይሎች መካከል ሐምሌ 25 ቀን 2018 ውጊያ መቀስቀሱ የተሰማው በአዲስ አበባና በመቐለ በሚገኙ ባለሥልጣናት መካከል ያለው ውጥረት በኃይል በተባባሰበት ወቅት ነው።
@Addis_Reporter
በከባድ የጦር መሣሪያ እና በድሮን ጭምር የተደረገው ውጊያው ከ23 ሰዓታት ገደማ በኋላ እንደቆመ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዋቢ ያደረጋቸው የመረጃ ምንጭ ተናግረዋል። በግጭቱ ምን ያክል ሰዎች እንደተገደሉ ወይም እንደቆሰሉ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ሌላ የጸጥታ የመረጃ ምንጭ በእርግጥም ውጊያው እንደቆመ ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል። ይሁንና ከህወሓት በኩል የቀረበው መረጃ ትክክለኛ መሆኑን በገለልተኝነት እንዳላረጋገጠ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት በዘገባው ጠቁሟል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተሰረዘው ህወሓት የሚመራው የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ትላንት ቅዳሜ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት ከማለዳ ጀምሮ በሸረሪና በኩል ውጊያ ጀምሯል በማለት ወንጅሎ ነበር። የፌድራል መንግሥት ግን ስለ ጉዳዩ በይፋ የሰጠው ማብራሪያም ሆነ ምላሽ የለም። ይሁንና የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትሩ አብርሀም በላይ በተረጋገጠ የፌስቡክ ገጻቸው ባሠፈሩት ጽሁፍ ህወሓትን በሸረሪና በኩል ጦርነት በመክፈት ወንጅለዋል።
በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና በትግራይ የጸጥታ ኃይሎች መካከል ሐምሌ 25 ቀን 2018 ውጊያ መቀስቀሱ የተሰማው በአዲስ አበባና በመቐለ በሚገኙ ባለሥልጣናት መካከል ያለው ውጥረት በኃይል በተባባሰበት ወቅት ነው።
@Addis_Reporter
❤28👍5🤯1
AAU ከ500 በላይ ሰራተኞቹን አሰናበተ‼️
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙሉ የራስ-ገዝነት መብቱን ለመተግበር ባደረገው የመዋቅር ማስተካከያ ምክንያት ከ500 በላይ አስተዳደራዊ ሰራተኞች እና 50 መምህራን ያለ ምደባ ቀርተዋል።
ይሁን እንጂ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ማንም ሰራተኛ እንዳልተባረረ ገልጸው፣ የተጎዱት በጡረታ፣ በካሳ ወይም በቅርቡ በሚጀመሩ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንደሚካተቱ አረጋግጠዋል።
ምደባው ለአስተዳደር ሰራተኞች በፈተና፣ ለመምህራን ደግሞ በትምህርት ዝግጅት አግባብነት ላይ ተመስርቶ የተከናወነ ነው።
በሀገሪቱ ከሚገኙ 46 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመጀመሪያው ሞዴል የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም እርምጃ፣ ቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ ለሚዘጋጁት እንደ ጂማ፣ መቐለ፣ ባህር ዳር እና ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች ትልቅ ማሳያ እንደሚሆን ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙሉ የራስ-ገዝነት መብቱን ለመተግበር ባደረገው የመዋቅር ማስተካከያ ምክንያት ከ500 በላይ አስተዳደራዊ ሰራተኞች እና 50 መምህራን ያለ ምደባ ቀርተዋል።
ይሁን እንጂ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ማንም ሰራተኛ እንዳልተባረረ ገልጸው፣ የተጎዱት በጡረታ፣ በካሳ ወይም በቅርቡ በሚጀመሩ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንደሚካተቱ አረጋግጠዋል።
ምደባው ለአስተዳደር ሰራተኞች በፈተና፣ ለመምህራን ደግሞ በትምህርት ዝግጅት አግባብነት ላይ ተመስርቶ የተከናወነ ነው።
በሀገሪቱ ከሚገኙ 46 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመጀመሪያው ሞዴል የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም እርምጃ፣ ቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ ለሚዘጋጁት እንደ ጂማ፣ መቐለ፣ ባህር ዳር እና ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች ትልቅ ማሳያ እንደሚሆን ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢19❤18😡8👍5👀3🤔2🤪2🙊2🙉1
የኤርትራ ሰራዊት አቀባበል‼️
በዛሬው ዕለት ሐምሌ 26 በትግራይ ክልል በጉሎምከዳ ወረዳ ዝባን ሁጻ በተባለ ስፍራ የኤርትራ ሰራዊት እና ወታደራዊ መሪዎች በህወሓት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
በአካባቢው በጋራ ወታደራዊ ቅስቀሳ አካሂደዋል፣የኤርትራ ሰራዊት በይፋ ሲጨፍሩ ታይተዋል።
ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በአሁኑ ወቅት በስፍራው የድሮን የስለላ እንቅስቃሴዎችም እየተካሄዱ ይገኛሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በዛሬው ዕለት ሐምሌ 26 በትግራይ ክልል በጉሎምከዳ ወረዳ ዝባን ሁጻ በተባለ ስፍራ የኤርትራ ሰራዊት እና ወታደራዊ መሪዎች በህወሓት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
በአካባቢው በጋራ ወታደራዊ ቅስቀሳ አካሂደዋል፣የኤርትራ ሰራዊት በይፋ ሲጨፍሩ ታይተዋል።
ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በአሁኑ ወቅት በስፍራው የድሮን የስለላ እንቅስቃሴዎችም እየተካሄዱ ይገኛሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤31🤪15👍8😢5👀5🤣1🙈1🙊1
ትርፍ አንጀት ምንድን ነው?
በተለምዶ ትርፍ አንጀት እየተባለ የሚጠራው ችግር የሚከሰተው አፔንዲክስ (ትርፍ አንጀት) ሚባለው ትንሽ የአንጀት አካል ሲያብጥ ወይም ሲቆጣ ነው። ይህ ችግር በፍጥነት ካልታከሙ ሊፈነዳ እና አደገኛ ኢንፌክሽን ሊያስከትል ይችላል።
የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ምንድን ነው?
የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ትርፍ አንጀት ለማስወገድ የሚደረግ ቀዶ ጥገና ሲሆን ለትርፍ አንጀት ችግር በጣም የተለመደው ሕክምና ነው። ቀዶ ሕክምናው በክፍት (open) መንገድ ወይም በላፓሮስኮፒ ሊሰራ ይችላል።
🚨 የትርፍ አንጀት አደገኛ ምልክቶች፡
👉 ከታች በቀኝ በኩል ባለው የሆድ ክፍል ላይ ድንገተኛ እና ከባድ ህመም ፣
🔹ማቅለሽለሽ እና ማስታወክ ፣
🔹ትኩሳት እና ብርድ ብርድ ማለት፣
🔹 የምግብ ፍላጎት ማጣት እና
🔹 በእንቅስቃሴ የሚባባስ ህመም ሲኖር በፍጥነት ወደ ህክምና መሄድ ያስፈልጋል።
✨ የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ለምን ያስፈልጋል?
✅ ትርፍ አንጀት እንዳይፈነዳ እና
✅ ከባድ ኢንፌክሽን እንዳይፈጠር እንዲሁም
✅ በፍጥነት ለማገገም ይህ ቀዶ ህክምና ያስፈልጋል።
ከቀዶ ጥገናው በኋላ ምን ማድረግ ያስፈልጋል?
🔹 በቀላሉ ሊፈጩ የሚችሉ ምግቦችን መመገብ፣
🔹 ረጋ ያለ እንቅስቃሴ ማድረግ፣
🔹 እረፍት ማድረግ እና
🔹 ውሃ በደንብ መጠጣት ቶሎ ለማገገም ይረዳል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በተለምዶ ትርፍ አንጀት እየተባለ የሚጠራው ችግር የሚከሰተው አፔንዲክስ (ትርፍ አንጀት) ሚባለው ትንሽ የአንጀት አካል ሲያብጥ ወይም ሲቆጣ ነው። ይህ ችግር በፍጥነት ካልታከሙ ሊፈነዳ እና አደገኛ ኢንፌክሽን ሊያስከትል ይችላል።
የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ምንድን ነው?
የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ትርፍ አንጀት ለማስወገድ የሚደረግ ቀዶ ጥገና ሲሆን ለትርፍ አንጀት ችግር በጣም የተለመደው ሕክምና ነው። ቀዶ ሕክምናው በክፍት (open) መንገድ ወይም በላፓሮስኮፒ ሊሰራ ይችላል።
🚨 የትርፍ አንጀት አደገኛ ምልክቶች፡
👉 ከታች በቀኝ በኩል ባለው የሆድ ክፍል ላይ ድንገተኛ እና ከባድ ህመም ፣
🔹ማቅለሽለሽ እና ማስታወክ ፣
🔹ትኩሳት እና ብርድ ብርድ ማለት፣
🔹 የምግብ ፍላጎት ማጣት እና
🔹 በእንቅስቃሴ የሚባባስ ህመም ሲኖር በፍጥነት ወደ ህክምና መሄድ ያስፈልጋል።
✨ የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ለምን ያስፈልጋል?
✅ ትርፍ አንጀት እንዳይፈነዳ እና
✅ ከባድ ኢንፌክሽን እንዳይፈጠር እንዲሁም
✅ በፍጥነት ለማገገም ይህ ቀዶ ህክምና ያስፈልጋል።
ከቀዶ ጥገናው በኋላ ምን ማድረግ ያስፈልጋል?
🔹 በቀላሉ ሊፈጩ የሚችሉ ምግቦችን መመገብ፣
🔹 ረጋ ያለ እንቅስቃሴ ማድረግ፣
🔹 እረፍት ማድረግ እና
🔹 ውሃ በደንብ መጠጣት ቶሎ ለማገገም ይረዳል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20👍19
ራያ‼️
ህወሓት በራያ ጨርጨር የነበረውን ሰራዊት እና መካናይዝድ ጦር ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም ለሊቱን በባቡር መስመሩ ወደ አፋር ድንበር ሲያስጠጋ አድሯል።
ሁሉም የሰራዊት አባላት ስልካቸውን እንዲያስረክቡ ታዘዋል።
ህዝቡ በመኪና የሚያደርጋቸውን እንቅስቃሴዎች እንዲያቆም አዟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ህወሓት በራያ ጨርጨር የነበረውን ሰራዊት እና መካናይዝድ ጦር ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም ለሊቱን በባቡር መስመሩ ወደ አፋር ድንበር ሲያስጠጋ አድሯል።
ሁሉም የሰራዊት አባላት ስልካቸውን እንዲያስረክቡ ታዘዋል።
ህዝቡ በመኪና የሚያደርጋቸውን እንቅስቃሴዎች እንዲያቆም አዟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17👍5🤡5🤯3🕊2👀1