አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Video
የአሸናፊዎች አሸናፊ ውጊያ ይደረጋል‼️
ህወሃት የ 1983 ታሪክን እንደግማሁ እያለ ነው።
የሕወሓት ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር (ሞንጆሪኖ) ከሰሞኑ በአንድ መድረክ ላይ አነጋጋሪ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሁን ከተጣመርናቸው ኃይሎች ጋር መዋጋታችን አይቀርም ብለዋል፡፡ የሀላፊዋ ንግግር የጽምዶ ኃይሎችን የትብብር መሰረት የሚያናጋ ነው ተብሏል፡፡
ወይዘሮ ፈትለወርቅ ቃል በቃል የተናገሩ፡-
‹‹ዋናው ነገር ብልፅግናን ለመጣል ፍላጎት ያሳይ እንጂ የትኛውም ስብስብ እርስ በራሱ እሳትና ጭድ ቢሆንም እንኳን አብረን እንሰራለን። ብልፅግናን ከጣልን በኃላ ደግሞ የአሸናፊዎች አሸናፊ ለመለየት ሌላ ዙር ፍልሚያ ይኖረናል።
ለዚህም እየተዘጋጀን ነው፤ ይህ በተለያየ መልክ የተጀመረውን ትብብራችንን ስናየው የተለያየ ፍላጎት ያለን ሃይሎች ሆነን ነው ትብብር እየፈጠርን ያለነው። በአላማ፣ በፕሮግም፣ ወደፊት በረዥም ጊዜ እቅድ ምናምን አንድ ነን ማለት አይደለም። ትብብራችን በዛች በምታገናኘን ነገር ብቻ ነው።
እኛ ከፋኖ የምንለይበት የፖለቲካ አቋም አለን። ከሻዕቢያ ይሁን ከሌሎች የተለያዩ ሃይሎች የምንለያይባቸው መዓት ጉዳዮች አሉ። አንድ የሚያደርገን ግን የብልፅግና ስርዓት የሁላችንም ስጋት ነው የሚለው ነው። ይቺ ብቻ ናት የምታገናኘን።
እንደ ተሞክሮ ልንወስደው የሚገባን ነገር ደግሞ እንኳን አሁን በብዙ ጉዳዮች ልዩነት ካለንና በዓላማ ከማንገናኛቸው የተለያዩ ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና ኢህአዴግም እኮ ፈርሷል።
ኢህአዴግ እኮ የኦሮሞ፣የአማራ፣የደቡብ ኢትዮጵያ ሃይሎች አራት ድርጅቶች አንድ ላይ ሆነን የፈጠርነውና በፕሮግራም ወይም አላማ አንድ የነበረ ድርጅት ነበር። ግንኙነታችንም ስትራቴጂካዊ ነበር[ታክቲካል አልነበረም] ፣ በተለያየ ቋንቋ የተፃፈች አንዲት ፕሮግራም ነበር የነበረችን።
ግንባር ከመሆናችን ውጭ አንድ ድርጅት ማለት ነበርን፤ በዚህ ደረጃ የነበርን ሰዎች እኮ ተካክደናል[እንኳን ይሄ በዓላማ ከማይመስሉን ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና]›› ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር
Via :- Andafta
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ህወሃት የ 1983 ታሪክን እንደግማሁ እያለ ነው።
የሕወሓት ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር (ሞንጆሪኖ) ከሰሞኑ በአንድ መድረክ ላይ አነጋጋሪ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሁን ከተጣመርናቸው ኃይሎች ጋር መዋጋታችን አይቀርም ብለዋል፡፡ የሀላፊዋ ንግግር የጽምዶ ኃይሎችን የትብብር መሰረት የሚያናጋ ነው ተብሏል፡፡
ወይዘሮ ፈትለወርቅ ቃል በቃል የተናገሩ፡-
‹‹ዋናው ነገር ብልፅግናን ለመጣል ፍላጎት ያሳይ እንጂ የትኛውም ስብስብ እርስ በራሱ እሳትና ጭድ ቢሆንም እንኳን አብረን እንሰራለን። ብልፅግናን ከጣልን በኃላ ደግሞ የአሸናፊዎች አሸናፊ ለመለየት ሌላ ዙር ፍልሚያ ይኖረናል።
ለዚህም እየተዘጋጀን ነው፤ ይህ በተለያየ መልክ የተጀመረውን ትብብራችንን ስናየው የተለያየ ፍላጎት ያለን ሃይሎች ሆነን ነው ትብብር እየፈጠርን ያለነው። በአላማ፣ በፕሮግም፣ ወደፊት በረዥም ጊዜ እቅድ ምናምን አንድ ነን ማለት አይደለም። ትብብራችን በዛች በምታገናኘን ነገር ብቻ ነው።
እኛ ከፋኖ የምንለይበት የፖለቲካ አቋም አለን። ከሻዕቢያ ይሁን ከሌሎች የተለያዩ ሃይሎች የምንለያይባቸው መዓት ጉዳዮች አሉ። አንድ የሚያደርገን ግን የብልፅግና ስርዓት የሁላችንም ስጋት ነው የሚለው ነው። ይቺ ብቻ ናት የምታገናኘን።
እንደ ተሞክሮ ልንወስደው የሚገባን ነገር ደግሞ እንኳን አሁን በብዙ ጉዳዮች ልዩነት ካለንና በዓላማ ከማንገናኛቸው የተለያዩ ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና ኢህአዴግም እኮ ፈርሷል።
ኢህአዴግ እኮ የኦሮሞ፣የአማራ፣የደቡብ ኢትዮጵያ ሃይሎች አራት ድርጅቶች አንድ ላይ ሆነን የፈጠርነውና በፕሮግራም ወይም አላማ አንድ የነበረ ድርጅት ነበር። ግንኙነታችንም ስትራቴጂካዊ ነበር[ታክቲካል አልነበረም] ፣ በተለያየ ቋንቋ የተፃፈች አንዲት ፕሮግራም ነበር የነበረችን።
ግንባር ከመሆናችን ውጭ አንድ ድርጅት ማለት ነበርን፤ በዚህ ደረጃ የነበርን ሰዎች እኮ ተካክደናል[እንኳን ይሄ በዓላማ ከማይመስሉን ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና]›› ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር
Via :- Andafta
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣32❤16🤯7👍3👀1🤪1🙊1
🚫
ቬትናም ከ16 ዓመት በታች ያሉ ልጆች በማህበራዊ ሚዲያ ፖስት ማድረግ፣ አስተያየት መስጠትና ይዘት ማጋራት እንዳይችሉ የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አቅርባለች። ልጆች ይዘትን ማየት ብቻ ይችላሉ።
ረቂቅ ሕጉ የህጻናት አካውንት በወላጅ ወይም በአሳዳጊ መረጃ እንዲከፈት ያስገድዳል።
ባለሥልጣናት ይህ ሕግ ህጻናትን ፦
- ከስድብ ፣
- ከኦንላይን ማጭበርበር
- ከሌሎች የኢንተርኔት አደጋዎች ለመጠበቅ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ረቂቁ ገና የመጨረሻ ውሳኔ አላገኘም።
ነገር ግን ቲክቶክና ሜታ በዚህ ሀሳብ ተቃውመዋል። ሁለቱ ኩባንያዎች " ልጆች አስተያየት እንዳይሰጡ ወይም ፖስት እንዳያደርጉ መከልከል ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ይበልጣል " ያሉ ሲሆን የህጻናትን ዕድሜ ለመለየትና ለመጠበቅ የሚረዱ መረጃዎችን ያሳጣል ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ቬትናም ከ16 ዓመት በታች ያሉ ልጆች በማህበራዊ ሚዲያ ፖስት ማድረግ፣ አስተያየት መስጠትና ይዘት ማጋራት እንዳይችሉ የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አቅርባለች። ልጆች ይዘትን ማየት ብቻ ይችላሉ።
ረቂቅ ሕጉ የህጻናት አካውንት በወላጅ ወይም በአሳዳጊ መረጃ እንዲከፈት ያስገድዳል።
ባለሥልጣናት ይህ ሕግ ህጻናትን ፦
- ከስድብ ፣
- ከኦንላይን ማጭበርበር
- ከሌሎች የኢንተርኔት አደጋዎች ለመጠበቅ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ረቂቁ ገና የመጨረሻ ውሳኔ አላገኘም።
ነገር ግን ቲክቶክና ሜታ በዚህ ሀሳብ ተቃውመዋል። ሁለቱ ኩባንያዎች " ልጆች አስተያየት እንዳይሰጡ ወይም ፖስት እንዳያደርጉ መከልከል ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ይበልጣል " ያሉ ሲሆን የህጻናትን ዕድሜ ለመለየትና ለመጠበቅ የሚረዱ መረጃዎችን ያሳጣል ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍19❤13💯1🤷1
ቀይ ባህር አደጋ ላይ ወድቋል‼️
በቀይ ባሕር ላይ የመረከቦች እንቅስቃሴ በእጅጉ ቀነሰ።
ሁቲዎች ከሳውዲ ጋር የተገናኙ መርከቦች ላይ የሚሰነዘሩትን ጥቃት ማጠናከራቸውን ተከተሎ በቀይ ባሕር ላይ የመረከቦች እንቅስቃሴ በእጅጉ ቀነሰ።
የየመኑ የሁቲ ንቅናቄ በሳውዲ ዓረቢያ የነዳጅ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃቱን በአዲስ መልክ ማጠናከሩን እና ከሳውዲ ጋር ግኑኝነት ባላቸው መርከቦች ላይ የባሕር ላይ ዕገዳ መጣሉን ይታወቃል፡፡
ይህም ክስተት በዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦት እና በባሕር ደኅንነት ላይ አዲስ ስጋትን ፈጥሯል።
ሮይተርስ የመርከብ ተከታታይ መረጃዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ ትላንት ሐምሌ 20 ቀን በባቢል መንዳብ በኩል ማለፍ የቻሉት 11 የንግድ መርከቦች ብቻ እንደሆኑና ይህም በጥቂት ወራት ውስጥ ዝቅተኛው የዕለታዊ እንቅስቃሴ ቁጥር ሆኖ ተመዝግቧል።
ከእነዚህ ውስጥ ሰባቱ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች ሲሆኑ፤ ከእነዚህ መካከል ሁለቱ ወደ ሳውዲ ዓረቢያ ያንቡ ወደብ ነዳጅ ለመጫን የሚያመሩ ግዙፍ የክሩድ ነዳጅ ጫኞች ናቸው፡፡
ቀሪዎቹ አራት መርከቦች ደግሞ የሳውዲ፣ የኤምሬትስ እና የሩሲያ ነዳጅ ጭነው በዋነኝነት ወደ ቻይና እና ፓኪስታን በመጓዝ ላይ የነበሩ ናቸው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በቀይ ባሕር ላይ የመረከቦች እንቅስቃሴ በእጅጉ ቀነሰ።
ሁቲዎች ከሳውዲ ጋር የተገናኙ መርከቦች ላይ የሚሰነዘሩትን ጥቃት ማጠናከራቸውን ተከተሎ በቀይ ባሕር ላይ የመረከቦች እንቅስቃሴ በእጅጉ ቀነሰ።
የየመኑ የሁቲ ንቅናቄ በሳውዲ ዓረቢያ የነዳጅ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃቱን በአዲስ መልክ ማጠናከሩን እና ከሳውዲ ጋር ግኑኝነት ባላቸው መርከቦች ላይ የባሕር ላይ ዕገዳ መጣሉን ይታወቃል፡፡
ይህም ክስተት በዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦት እና በባሕር ደኅንነት ላይ አዲስ ስጋትን ፈጥሯል።
ሮይተርስ የመርከብ ተከታታይ መረጃዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ ትላንት ሐምሌ 20 ቀን በባቢል መንዳብ በኩል ማለፍ የቻሉት 11 የንግድ መርከቦች ብቻ እንደሆኑና ይህም በጥቂት ወራት ውስጥ ዝቅተኛው የዕለታዊ እንቅስቃሴ ቁጥር ሆኖ ተመዝግቧል።
ከእነዚህ ውስጥ ሰባቱ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች ሲሆኑ፤ ከእነዚህ መካከል ሁለቱ ወደ ሳውዲ ዓረቢያ ያንቡ ወደብ ነዳጅ ለመጫን የሚያመሩ ግዙፍ የክሩድ ነዳጅ ጫኞች ናቸው፡፡
ቀሪዎቹ አራት መርከቦች ደግሞ የሳውዲ፣ የኤምሬትስ እና የሩሲያ ነዳጅ ጭነው በዋነኝነት ወደ ቻይና እና ፓኪስታን በመጓዝ ላይ የነበሩ ናቸው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤22👍3
🚨በየ5 ደቂቃው ምስል የሚያነሳውና ሰላይ የሆነው የስማርት ፎን ምስጢር ይፋ ሆነ‼️ከሰሜን ኮሪያ በምስጢር ተሰርቆ የወጣ አንድ የስማርት ፎን ስልክ፣ የመንግስቱ አገዛዝ የዜጎቹን እያንዳንዱን እንቅስቃሴ ምን ያህል በአስፈሪ ሁኔታ እንደሚቆጣጠር ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጓል።
ቢቢሲ (BBC) በሴኡል ካለው ዴይሊ ኤንኬ (Daily NK) ከተሰኘው የመገናኛ ብዙሃን ተቀብሎ ባደረገው የቴክኒክ ምርመራ፣ ስልኩ ከተራ መገናኛ መሳሪያነት ይልቅ በኪስ የሚያዝ የወታደራዊ የሰላይ መሳሪያ ሆኖ የተሰራ መሆኑን አረጋግጧል።
ይህ ስልክ ተጠቃሚው የሚያደርገውን ማናቸውንም እንቅስቃሴ በየ5 ደቂቃው በምስጢር ፎቶ (Screenshot) በማንሳት ተጠቃሚው ሊከፍተው ወደማይችለው የተደበቀ ፎልደር ይልካል፤ ይህም መረጃ በመንግስት የደህንነት አካላት ብቻ የሚከፈትና ለቁጥጥር የሚያገለግል ነው።
በተጨማሪም ስልኩ ከማንኛውም የዓለም አቀፍ ኢንተርኔት አውታረ መረብ ጋር በፍፁም እንዳይገናኝ ተደርጎ የተዘጋ በመሆኑ ከውጭ ዓለም የሚመጣ ማናቸውንም መረጃ ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
ከዚህም በላይ ተጠቃሚዎች በሚጽፉበት ወቅት ስልኩ በራሱ የቃላት ማረምያ ስልቶችን በመጠቀም ቃላትን ይለውጣል። ለምሳሌ “ኦፓ” (Oppa - በደቡብ ኮሪያ ወንድምን ወይም ፍቅረኛን ለመጠራት የሚያገለግል ቃል) የሚለውን ወደ “ኮምሬድ” (Comrade - ጓድ)፣ እንዲሁም “ደቡብ ኮሪያ” የሚለውን ቃል ወደ “ተላላኪ ሀገር” (Puppet state) በማለት በራሱ ጊዜ አድሶ ይጽፋል።
ይህ መሳሪያ ስልክ ከመሆን ይልቅ የሰሜን ኮሪያ አገዛዝ ዜጎቹ ምን ማንበብ፣ ማወቅ፣ መጻፍ እና መናገር እንዳለባቸው ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የፈጠረው ዘመናዊ የኪስ ውስጥ የክትትልና የቁጥጥር መሳሪያ ነው ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ቢቢሲ (BBC) በሴኡል ካለው ዴይሊ ኤንኬ (Daily NK) ከተሰኘው የመገናኛ ብዙሃን ተቀብሎ ባደረገው የቴክኒክ ምርመራ፣ ስልኩ ከተራ መገናኛ መሳሪያነት ይልቅ በኪስ የሚያዝ የወታደራዊ የሰላይ መሳሪያ ሆኖ የተሰራ መሆኑን አረጋግጧል።
ይህ ስልክ ተጠቃሚው የሚያደርገውን ማናቸውንም እንቅስቃሴ በየ5 ደቂቃው በምስጢር ፎቶ (Screenshot) በማንሳት ተጠቃሚው ሊከፍተው ወደማይችለው የተደበቀ ፎልደር ይልካል፤ ይህም መረጃ በመንግስት የደህንነት አካላት ብቻ የሚከፈትና ለቁጥጥር የሚያገለግል ነው።
በተጨማሪም ስልኩ ከማንኛውም የዓለም አቀፍ ኢንተርኔት አውታረ መረብ ጋር በፍፁም እንዳይገናኝ ተደርጎ የተዘጋ በመሆኑ ከውጭ ዓለም የሚመጣ ማናቸውንም መረጃ ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
ከዚህም በላይ ተጠቃሚዎች በሚጽፉበት ወቅት ስልኩ በራሱ የቃላት ማረምያ ስልቶችን በመጠቀም ቃላትን ይለውጣል። ለምሳሌ “ኦፓ” (Oppa - በደቡብ ኮሪያ ወንድምን ወይም ፍቅረኛን ለመጠራት የሚያገለግል ቃል) የሚለውን ወደ “ኮምሬድ” (Comrade - ጓድ)፣ እንዲሁም “ደቡብ ኮሪያ” የሚለውን ቃል ወደ “ተላላኪ ሀገር” (Puppet state) በማለት በራሱ ጊዜ አድሶ ይጽፋል።
ይህ መሳሪያ ስልክ ከመሆን ይልቅ የሰሜን ኮሪያ አገዛዝ ዜጎቹ ምን ማንበብ፣ ማወቅ፣ መጻፍ እና መናገር እንዳለባቸው ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የፈጠረው ዘመናዊ የኪስ ውስጥ የክትትልና የቁጥጥር መሳሪያ ነው ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17👍3😡3🤔2😢2
አስደንጋጭ ጥናት‼️፡ ከግማሽ በላይ የሚሆኑ የኢትዮጵያ ሴቶች ሚስትን መደብደብን እንደሚያጸድቁ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ይፋ ባደረገው አዲስ የዴሞግራፊ እና የጤና ዳሰሳ ጥናት፤ ከግማሽ በላይ (55 በመቶ) የሚሆኑ ሴቶች ባል ሚስቱን ለመደብደብ አሳማኝ ምክንያት ይኖረዋል ብለው እንደሚያምኑ አመላክቷል።
ምግብ ማቃጠል፣ መጨቃጨቅ እና ልጆችን ችላ ማለትን ጨምሮ በተዘረዘሩ አምስት ሁኔታዎች ዙሪያ የተደረገው ይህ ጥናት፣ ሚስትን ለመምታት በቂ ምክንያት እንዳለ የሚያስቡ ወንዶች ቁጥር 39 በመቶ መሆኑንና ከቀድሞው ጋር ሲነጻጸር በ11 በመቶ መጨመሩን ገልጿል።
በሌላ በኩል፣ ትምህርት እና የቤተሰብ ገቢ ሲጨምር ይህንን አዝማሚያ የመቀበል አመለካከት እየቀነሰ እንደሚሄድ ጥናቱ ያሳያል።
ከሁለተኛ ደረጃ በላይ ትምህርት ካገኙ ሴቶች መካከል እንዲህ የሚያስቡት 29 በመቶው ብቻ ሲሆኑ፤ በሲዳማ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ከፍተኛው ቁጥር ሲመዘገብ፣ ሶማሌ ክልል ዝቅተኛውን አሃዝ አስመዝግቧል።
Òየቤት ውስጥ ጥቃትን ተገቢ የሚያደርጉ አመለካከቶችን ለመለወጥ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማጠናከር እና የግንዛቤ ሥራዎችን ማስፋፋት እንደ ዋና መፍትሔ ተቀምጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ይፋ ባደረገው አዲስ የዴሞግራፊ እና የጤና ዳሰሳ ጥናት፤ ከግማሽ በላይ (55 በመቶ) የሚሆኑ ሴቶች ባል ሚስቱን ለመደብደብ አሳማኝ ምክንያት ይኖረዋል ብለው እንደሚያምኑ አመላክቷል።
ምግብ ማቃጠል፣ መጨቃጨቅ እና ልጆችን ችላ ማለትን ጨምሮ በተዘረዘሩ አምስት ሁኔታዎች ዙሪያ የተደረገው ይህ ጥናት፣ ሚስትን ለመምታት በቂ ምክንያት እንዳለ የሚያስቡ ወንዶች ቁጥር 39 በመቶ መሆኑንና ከቀድሞው ጋር ሲነጻጸር በ11 በመቶ መጨመሩን ገልጿል።
በሌላ በኩል፣ ትምህርት እና የቤተሰብ ገቢ ሲጨምር ይህንን አዝማሚያ የመቀበል አመለካከት እየቀነሰ እንደሚሄድ ጥናቱ ያሳያል።
ከሁለተኛ ደረጃ በላይ ትምህርት ካገኙ ሴቶች መካከል እንዲህ የሚያስቡት 29 በመቶው ብቻ ሲሆኑ፤ በሲዳማ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ከፍተኛው ቁጥር ሲመዘገብ፣ ሶማሌ ክልል ዝቅተኛውን አሃዝ አስመዝግቧል።
Òየቤት ውስጥ ጥቃትን ተገቢ የሚያደርጉ አመለካከቶችን ለመለወጥ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማጠናከር እና የግንዛቤ ሥራዎችን ማስፋፋት እንደ ዋና መፍትሔ ተቀምጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17🤣13👍4😢3💯2
የገዛ እህቱን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ የገዛ እህቱን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱን ፖሊስ አስታውቋል።
ተከሳሹ በረከት ስዩም የተባለ ሲሆን በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ወካ አራባ ቀበሌ በ"ቡታ" ተብሎ በሚጠራ ስፍራ በሚገኘው መኖሪያ ቤት የግል ተበዳይ የሆነችውን እህቱን ረድኤት ስዩም ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀሙን ተገልጿል።
ከድርጊቱ በኋላ ለጊምቦ ወረዳ ፖሊስ ጥቆማ በመቅረቡ ፖሊስ በሰውና በሰነድ ማስረጃ ጉዳዩን አጣርቶ ለጊምቦ ወረዳ ዐቃቤ ሕግ ያስተላልፏል።
ዐቃቤ ሕጉም መዝገቡን ለፍርድ ቤት አቅርቦ ክሱን ከተመለከተ በኋላ ተከሳሹ በቀረበበት ክስ ላይ መከላከል ባለመቻሉ ጥፋተኛ መሆኑ ተረጋግጧል።
ፍርድ ቤቱ በቀረበለትን የክስ መዝገብ ተከሳሽን በ9 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ማስተላለፉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ የገዛ እህቱን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱን ፖሊስ አስታውቋል።
ተከሳሹ በረከት ስዩም የተባለ ሲሆን በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ወካ አራባ ቀበሌ በ"ቡታ" ተብሎ በሚጠራ ስፍራ በሚገኘው መኖሪያ ቤት የግል ተበዳይ የሆነችውን እህቱን ረድኤት ስዩም ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀሙን ተገልጿል።
ከድርጊቱ በኋላ ለጊምቦ ወረዳ ፖሊስ ጥቆማ በመቅረቡ ፖሊስ በሰውና በሰነድ ማስረጃ ጉዳዩን አጣርቶ ለጊምቦ ወረዳ ዐቃቤ ሕግ ያስተላልፏል።
ዐቃቤ ሕጉም መዝገቡን ለፍርድ ቤት አቅርቦ ክሱን ከተመለከተ በኋላ ተከሳሹ በቀረበበት ክስ ላይ መከላከል ባለመቻሉ ጥፋተኛ መሆኑ ተረጋግጧል።
ፍርድ ቤቱ በቀረበለትን የክስ መዝገብ ተከሳሽን በ9 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ማስተላለፉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢18❤6👍2
92 ሚሊዮን የሚጠጋ የኢትዮጵያ ሕዝብ "ጤናማ የምግብ ሥርዓት" ለመከተል አቅም እንደሌለው የተመድ የምግብ ዋስትና ሪፖርት አመለከተ።
በኢትዮጵያ ጤናማ የምግብ ሥርዓትን ለማስጠበቅ በነፍስ ወከፍ የሚወጣው ወጪ ከምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛው መኾኑን ሪፖርቱ ጠቅሷል።
ባለፈው የአውሮፓዊያን ዓመት የኢትዮጵያ የነፍስ ወከፍ ጤናማ የምግብ ወጪ 4 ነጥብ 7 ዶላር እንደነበርና ይህም ከኬንያ፣ ኡጋንዳና ታንዛኒያ የበለጠ መሆኑን ሪፖርቱ አመልክቷል።
ከአውሮፓዊያኑ 2023 እስከ 2025 60 በመቶ ኢትዮጵያዊያን "መካከለኛ" እና "ከፍተኛ" የምግብ ዋስትና እጦት ገጥሟቸው እንደነበርም ሪፖርቱ ጠቅሷል። ሪፖርቱ የትግራይ ክልልን መረጃ አላካተተም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በኢትዮጵያ ጤናማ የምግብ ሥርዓትን ለማስጠበቅ በነፍስ ወከፍ የሚወጣው ወጪ ከምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛው መኾኑን ሪፖርቱ ጠቅሷል።
ባለፈው የአውሮፓዊያን ዓመት የኢትዮጵያ የነፍስ ወከፍ ጤናማ የምግብ ወጪ 4 ነጥብ 7 ዶላር እንደነበርና ይህም ከኬንያ፣ ኡጋንዳና ታንዛኒያ የበለጠ መሆኑን ሪፖርቱ አመልክቷል።
ከአውሮፓዊያኑ 2023 እስከ 2025 60 በመቶ ኢትዮጵያዊያን "መካከለኛ" እና "ከፍተኛ" የምግብ ዋስትና እጦት ገጥሟቸው እንደነበርም ሪፖርቱ ጠቅሷል። ሪፖርቱ የትግራይ ክልልን መረጃ አላካተተም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17😢13👍6
ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 3፡30-11፡04
👉 ስካይላይት ሆቴል፣ ቱርክ ኢምባሲ፣ ቦሌ ት/ቤት፣ ኤድናሞል፣ ቦሌ ቴሌ እና አከባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 5፡40-9፡30
👉 3 ቁጥር ማዞሪያ፣ ሳሚ ካፌ፣ ጎልፍ ክለብ፣ ወይብላ ማርያም፣ አውጉስታ፣ አንፎ፣ ወይራ ኮንዶሚኒየም፣ ሞቢል፣ ራሺያ ካምፕ፣ ተዘንአ ሆስፒታል እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡30-11፡04
👉ገለን አባ ሳሙኤል፣ አቡ ሴራ፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ አርትስቲ፣ ዱከም፣ ቡራዩ ከተማ አስተዳዳር እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00-10፡00
👉ቃሊቲ ገብርኤል ቤ/ት፣ ሜድሮክ፣ ካዲስኮ፣ቃሊቲ ማረሚያ ቤት፣ ሸገር ሕንፃ፣ ቃሊቲ ፍሳሽ ማጣሪያ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00-10፡30
👉 ለገጣፎ ለገዳዲ፣ ሲዲሲ፣ ኮሰሮ፣ ኤሞሌስ ፋብሪካ፣ ካሰዴ፣ 44 ማዞሪያ፣ ሰንዳፋ ጫፍ እና አካባቢው፣
👉 ጭሮ ከተማ፣ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ፣ ሀረማያ፣ ጨላንቆ፣ በሮዳ፣ ሐድስ፣ ቆቦ፣ ከራሚሌ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ነገ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 3፡30-11፡04
👉 ስካይላይት ሆቴል፣ ቱርክ ኢምባሲ፣ ቦሌ ት/ቤት፣ ኤድናሞል፣ ቦሌ ቴሌ እና አከባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 5፡40-9፡30
👉 3 ቁጥር ማዞሪያ፣ ሳሚ ካፌ፣ ጎልፍ ክለብ፣ ወይብላ ማርያም፣ አውጉስታ፣ አንፎ፣ ወይራ ኮንዶሚኒየም፣ ሞቢል፣ ራሺያ ካምፕ፣ ተዘንአ ሆስፒታል እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡30-11፡04
👉ገለን አባ ሳሙኤል፣ አቡ ሴራ፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ አርትስቲ፣ ዱከም፣ ቡራዩ ከተማ አስተዳዳር እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00-10፡00
👉ቃሊቲ ገብርኤል ቤ/ት፣ ሜድሮክ፣ ካዲስኮ፣ቃሊቲ ማረሚያ ቤት፣ ሸገር ሕንፃ፣ ቃሊቲ ፍሳሽ ማጣሪያ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00-10፡30
👉 ለገጣፎ ለገዳዲ፣ ሲዲሲ፣ ኮሰሮ፣ ኤሞሌስ ፋብሪካ፣ ካሰዴ፣ 44 ማዞሪያ፣ ሰንዳፋ ጫፍ እና አካባቢው፣
👉 ጭሮ ከተማ፣ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ፣ ሀረማያ፣ ጨላንቆ፣ በሮዳ፣ ሐድስ፣ ቆቦ፣ ከራሚሌ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤6👍4
ለደብረብርሃን ከተማ ህዝብ እጅግ ልብ ሰባሪ ዜና ነው💔💔🥲
በዛሬው እለት አራት (4) የአንድ ቤተሰብ አባላት ግለሰቦች በመኪና አደጋ በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወታቸው እንዳለፈ ተሰምቷል።
የቁልቢ ገብርኤል ንግስ በዓልን ታድመው ወደ ቤታቸው እየተመለሱ በነበረበት ወቅት አለልቱ ላይ ነው ይህ አሳዛኝ ልብ ሰባሪ አደጋ የደረሰው🥲 ለመላው ቤተሰቦቻቸው፣ ለዘመዶቻቸው፣ ለጎረቤቶቻቸው እንዲሁም ለሚያውቋቸው ወዳጆቻቸው በሙሉ ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጣቸው እንመኛለን።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ያኑርን🥲
ሸዋ ደብረ ብርሃን
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በዛሬው እለት አራት (4) የአንድ ቤተሰብ አባላት ግለሰቦች በመኪና አደጋ በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወታቸው እንዳለፈ ተሰምቷል።
የቁልቢ ገብርኤል ንግስ በዓልን ታድመው ወደ ቤታቸው እየተመለሱ በነበረበት ወቅት አለልቱ ላይ ነው ይህ አሳዛኝ ልብ ሰባሪ አደጋ የደረሰው🥲 ለመላው ቤተሰቦቻቸው፣ ለዘመዶቻቸው፣ ለጎረቤቶቻቸው እንዲሁም ለሚያውቋቸው ወዳጆቻቸው በሙሉ ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጣቸው እንመኛለን።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ያኑርን🥲
ሸዋ ደብረ ብርሃን
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢58❤12💔10👍4🤯1
በፈረንሳይ እና በስፔን የደረሰዉ ሰደድ እሳት ተባብሶ መቀጠሉ ተነገረ
በፈረንሳይ እና በስፔን የሚነደው የሰደድ እሳት ቃጠሎ አሁንም እየቀጠለ ይገኛል፡፡በፈረንሳይ እሳት አሁን ከቦርዶ ከተማ ዳርቻ 15 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ብቻ ይገኛል።በጂሮንድ ክልል 220,000 የሚገመቱ ሰዎች አካባቢያቸዉን ለቀዉ ለመዉጣት ተገደዋል፣ 42,000 ሄክታር ያህል መሬት ሲቃጠል 240 ቤቶችም ወድመዋል።
ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ቦርዶን ከእሳቱ ለማዳን ላከናወኑት ጥረት የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሰጪዎችን አመስግነዋል፣ "መላው ሀገር ከጎናችሁ ነው" ሲሉ መናገራቸዉን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል፡፡በደቡብ ምዕራብ ፈረንሳይ የተቀሰቀሰውን ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ መቆጣጠር "ዳዊት ከጎልያድ ጋር የሚያደርገው ትግል" ዓይነት ነው ሲሉ የእሳት አደጋ መከላከያ ክፍል ቃል አቀባይ ተናግረዋል።በዚህ ሳምንት በደቡብ ምዕራብ ፈረንሳይ የሙቀት መጠኑ 39 ዲግሪ ሴልሺየስ (102 ዲግሪ ፋራናይት) ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ቢያንስ እስከ አርብ ድረስ ዝናብ አይኖርም ተብሎ ተተንብዮአል።
በስፔን ከዋና ከተማዋ ማድሪድ በስተ ምዕራብ 50 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የእሳት ቃጠሉለፐ እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ ወደ 105,000 የሚጠጉ ሰዎች በሰደድ እሳቱ ተፈናቅለዋል፣ በማድሪድ፣ በአቪላ እና በቶሌዶ ክልሎች በተነሳው የእሳት ቃጠሎ 77,000 ሄክታር አካባቢ ተጎድቷል።እሳቱ በፍጥነት እንዲሰራጭ እና በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቃጠል የሚያስችል ሞቃታማ እና ደረቅ የአየር ሁኔታ እየተፈጠረ ነው ሲሉ የአየር ንብረት ባለሙያዎች ተናግረዋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በፈረንሳይ እና በስፔን የሚነደው የሰደድ እሳት ቃጠሎ አሁንም እየቀጠለ ይገኛል፡፡በፈረንሳይ እሳት አሁን ከቦርዶ ከተማ ዳርቻ 15 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ብቻ ይገኛል።በጂሮንድ ክልል 220,000 የሚገመቱ ሰዎች አካባቢያቸዉን ለቀዉ ለመዉጣት ተገደዋል፣ 42,000 ሄክታር ያህል መሬት ሲቃጠል 240 ቤቶችም ወድመዋል።
ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ቦርዶን ከእሳቱ ለማዳን ላከናወኑት ጥረት የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሰጪዎችን አመስግነዋል፣ "መላው ሀገር ከጎናችሁ ነው" ሲሉ መናገራቸዉን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል፡፡በደቡብ ምዕራብ ፈረንሳይ የተቀሰቀሰውን ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ መቆጣጠር "ዳዊት ከጎልያድ ጋር የሚያደርገው ትግል" ዓይነት ነው ሲሉ የእሳት አደጋ መከላከያ ክፍል ቃል አቀባይ ተናግረዋል።በዚህ ሳምንት በደቡብ ምዕራብ ፈረንሳይ የሙቀት መጠኑ 39 ዲግሪ ሴልሺየስ (102 ዲግሪ ፋራናይት) ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ቢያንስ እስከ አርብ ድረስ ዝናብ አይኖርም ተብሎ ተተንብዮአል።
በስፔን ከዋና ከተማዋ ማድሪድ በስተ ምዕራብ 50 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የእሳት ቃጠሉለፐ እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ ወደ 105,000 የሚጠጉ ሰዎች በሰደድ እሳቱ ተፈናቅለዋል፣ በማድሪድ፣ በአቪላ እና በቶሌዶ ክልሎች በተነሳው የእሳት ቃጠሎ 77,000 ሄክታር አካባቢ ተጎድቷል።እሳቱ በፍጥነት እንዲሰራጭ እና በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቃጠል የሚያስችል ሞቃታማ እና ደረቅ የአየር ሁኔታ እየተፈጠረ ነው ሲሉ የአየር ንብረት ባለሙያዎች ተናግረዋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍2😱1😢1
ተጥሎ በረሃብ የሞት አፋፍ ላይ የነበረውን የሁለት ወር ሕፃን ልጅ የፖሊስ አባልዋ የራስዋን ጡት በማጥባት ከሞት ታደገችው
በጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ አንዲት እናት ጥላ የጠፋቸውንና በረሃብ የሞተት አፋፍ ላይ የደረሰን የሑለት ወር ሕፃን ልጅ የፖሊስ አባልዋ የራስዋን ጡት በማጥባት ከሞት ታደገችው።
የጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ ነዋሪዎች የተጣለና በምግብ እጦት ከሞት አፋፍ የደረሠን ልጅ አይተው ፖሊስ ጣቢያ ይዘው ይመጣሉ። ይሕ ልጅ በምግብ እጦትና በብርድ በመጎዳቱ የሞት አፋፍ ላይ ደርሷል።
ይህንን የተመለከተችው የጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ ፖሊስ አባል ረዳት ሣጅን መስከረም ስምኦን የእናትነት አንጀት አላስችል ብልዋት ጡቷን በማጥባት በሞት አፋፍ የነበረውን ልጅ ከሞት ልትታደገው መቻሏን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።ሕፃኑን ሣየው ሆዴ ስፍስፍ አለ የምትለው ረዳት ሳጅን መስከረም ስምኦን ፖሊስነት ሕይወትን መታደግ ነውና በረሐብና በብርድ የተዳከመውን ልጅ ጡቴን በማጥባት ነብስ እንዲዘራ አድርጊያለሁ በማለት ተናግራለች።
የረዳት ሳጅን መስከረም ስምኦን ተግባር ፖሊስነት ከመስዋዕትነት እስከ ሕይወት አድን ተግባር በመሆኑ ምስጋና የተቸራት ሲሆን ከሞት አፋፍ በረዳት ሣጅን መስከረም ስምኦን ጡት ነብስ የዘራው የሑለት ወር ልጆ በአሑኑ ሠዓት በመልካም ጤንነት ላይ እንዳለ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም በጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የቀርሣ ወረዳ ፖሊስ የሴቶች ና ሕፃናት ክፍል ኃላፊ ዋና ሣጅን ነይማ ጀማል ተጥሎ የተገኘ ህፃን ልጅ በረሃብ በመኖር እና በሞት መካከል መሆንኑ በመረዳት ወተት ያጋተውን ጡቷን አውጥታ በማጥባት ህይወቱን መታደጓን ብስራት ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሣል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ አንዲት እናት ጥላ የጠፋቸውንና በረሃብ የሞተት አፋፍ ላይ የደረሰን የሑለት ወር ሕፃን ልጅ የፖሊስ አባልዋ የራስዋን ጡት በማጥባት ከሞት ታደገችው።
የጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ ነዋሪዎች የተጣለና በምግብ እጦት ከሞት አፋፍ የደረሠን ልጅ አይተው ፖሊስ ጣቢያ ይዘው ይመጣሉ። ይሕ ልጅ በምግብ እጦትና በብርድ በመጎዳቱ የሞት አፋፍ ላይ ደርሷል።
ይህንን የተመለከተችው የጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ ፖሊስ አባል ረዳት ሣጅን መስከረም ስምኦን የእናትነት አንጀት አላስችል ብልዋት ጡቷን በማጥባት በሞት አፋፍ የነበረውን ልጅ ከሞት ልትታደገው መቻሏን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።ሕፃኑን ሣየው ሆዴ ስፍስፍ አለ የምትለው ረዳት ሳጅን መስከረም ስምኦን ፖሊስነት ሕይወትን መታደግ ነውና በረሐብና በብርድ የተዳከመውን ልጅ ጡቴን በማጥባት ነብስ እንዲዘራ አድርጊያለሁ በማለት ተናግራለች።
የረዳት ሳጅን መስከረም ስምኦን ተግባር ፖሊስነት ከመስዋዕትነት እስከ ሕይወት አድን ተግባር በመሆኑ ምስጋና የተቸራት ሲሆን ከሞት አፋፍ በረዳት ሣጅን መስከረም ስምኦን ጡት ነብስ የዘራው የሑለት ወር ልጆ በአሑኑ ሠዓት በመልካም ጤንነት ላይ እንዳለ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም በጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የቀርሣ ወረዳ ፖሊስ የሴቶች ና ሕፃናት ክፍል ኃላፊ ዋና ሣጅን ነይማ ጀማል ተጥሎ የተገኘ ህፃን ልጅ በረሃብ በመኖር እና በሞት መካከል መሆንኑ በመረዳት ወተት ያጋተውን ጡቷን አውጥታ በማጥባት ህይወቱን መታደጓን ብስራት ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሣል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤61👍10🥰4🎉4
በጃፓን ኩማሞቶ በሬክተር ስኬል 7.1 የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
በጃፓን ደቡባዊ የኪዩሹ ደሴት በሚገኘው ኩማሞቶ ግዛት ዛሬ የደረሰው ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ በሰዎች ሕይወት፣ በመሠረተ ልማት እና በኢንዱስትሪ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
የመጀመሪያ ግምገማዎች መንቀጥቀጡ በ6.8 እስከ 7.1 ማግኒትዩድ መካከል መለካቱን ያሳያሉ፤ ባለሥልጣናት የመጨረሻ ሳይንሳዊ ግምገማ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።
ከአደጋው በኋላ በካሺማ ከተማ የሚገኘው «ኢዮን ሞል ኩማሞቶ» ውስጥ ከባድ ፍንዳታ ተከስቶ የሕንፃው ክፍል በመፍረሱ በርካታ ሰዎች በፍርስራሹ ስር መቀራቸው ተገልጿል።
እስካሁን ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ ሰራተኞች የጠፉ ሲሆን፣ የእሳት አደጋ እና የነፍስ አድን ቡድኖች የማዳን ሥራ እያካሄዱ ነው። ፍንዳታው ከጋዝ መፍሰስ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ጥርጣሬ ቢኖርም፣ ባለሥልጣናት መንስኤውን እያጣሩ ነው።
በሌላ በኩል፣ በአካባቢው በሚገኝ የወረቀት ፋብሪካ ውስጥ የነበሩ በርካታ ሰራተኞች ያሉበት እስካሁን አልታወቀም።
በባቡር መስመሮች፣ በድልድዮች እና በመንገዶች ላይም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፤ የባቡር አገልግሎት ተቋርጧል፣ አንዳንድ ባቡሮችም ከሐዲድ ወጥተዋል። በአካባቢው የአየር ማረፊያም ለጊዜው ተዘግቷል።
የኃይል አቅርቦት በአስር ሺዎች ቤቶች ተቋርጧል፤ ከ60 በላይ የተከታታይ ንዝረቶች በመመዝገባቸውም ተጨማሪ የመሬት መንሸራተት እና የሕንፃ መውደቅ አደጋ ስለሚኖር ህዝቡ ከተጎዱ ሕንፃዎች እንዲርቅ ጥሪ ቀርቧል።
የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናኤ ታካኢቺ የመከላከያ ኃይሎችን፣ የእሳት አደጋ ባለሙያዎችን እና ሌሎች የአደጋ ምላሽ ቡድኖችን ወደ ተጎዱ አካባቢዎች መላካቸውን ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በጃፓን ደቡባዊ የኪዩሹ ደሴት በሚገኘው ኩማሞቶ ግዛት ዛሬ የደረሰው ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ በሰዎች ሕይወት፣ በመሠረተ ልማት እና በኢንዱስትሪ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
የመጀመሪያ ግምገማዎች መንቀጥቀጡ በ6.8 እስከ 7.1 ማግኒትዩድ መካከል መለካቱን ያሳያሉ፤ ባለሥልጣናት የመጨረሻ ሳይንሳዊ ግምገማ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።
ከአደጋው በኋላ በካሺማ ከተማ የሚገኘው «ኢዮን ሞል ኩማሞቶ» ውስጥ ከባድ ፍንዳታ ተከስቶ የሕንፃው ክፍል በመፍረሱ በርካታ ሰዎች በፍርስራሹ ስር መቀራቸው ተገልጿል።
እስካሁን ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ ሰራተኞች የጠፉ ሲሆን፣ የእሳት አደጋ እና የነፍስ አድን ቡድኖች የማዳን ሥራ እያካሄዱ ነው። ፍንዳታው ከጋዝ መፍሰስ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ጥርጣሬ ቢኖርም፣ ባለሥልጣናት መንስኤውን እያጣሩ ነው።
በሌላ በኩል፣ በአካባቢው በሚገኝ የወረቀት ፋብሪካ ውስጥ የነበሩ በርካታ ሰራተኞች ያሉበት እስካሁን አልታወቀም።
በባቡር መስመሮች፣ በድልድዮች እና በመንገዶች ላይም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፤ የባቡር አገልግሎት ተቋርጧል፣ አንዳንድ ባቡሮችም ከሐዲድ ወጥተዋል። በአካባቢው የአየር ማረፊያም ለጊዜው ተዘግቷል።
የኃይል አቅርቦት በአስር ሺዎች ቤቶች ተቋርጧል፤ ከ60 በላይ የተከታታይ ንዝረቶች በመመዝገባቸውም ተጨማሪ የመሬት መንሸራተት እና የሕንፃ መውደቅ አደጋ ስለሚኖር ህዝቡ ከተጎዱ ሕንፃዎች እንዲርቅ ጥሪ ቀርቧል።
የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናኤ ታካኢቺ የመከላከያ ኃይሎችን፣ የእሳት አደጋ ባለሙያዎችን እና ሌሎች የአደጋ ምላሽ ቡድኖችን ወደ ተጎዱ አካባቢዎች መላካቸውን ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤24😢14👍3
እዳ ያልከፈሉ እየተከሰሱ ነው‼️
በቴሌብር ዲጂታል ብድር ውዝፍ ዕዳ ላይ ህጋዊ እርምጃ እና ክስ መጀመሩ ተገለጸ‼️
ዳሸን ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም በቴሌብር መተግበሪያ አማካኝነት የወሰዱትን የዲጂታል ፋይናንሲንግ ብድር በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ያልከፈሉ ተበዳሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ መጀመራቸውን እና በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ክስ እየመሰረቱ እንደሚገኙ አስታወቁ።
ባንኩ ባወጣው መግለጫ እንደገለጸው፣ ተበዳሪዎች ያለባቸውን ውዝፍ ዕዳ እንዲከፍሉ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም የተደረገውን የቅጣት ክፍያ ምሕረት ተጠቅመው ዕዳቸውን ያልከፈሉ ወገኖች ላይ የህግ አካሄድ መጀመሩን ገልጿል።
በመግለጫው መሠረት፣ አስቀድሞ ለቀረበላቸው ጥሪ ምላሽ ያልሰጡ ተበዳሪዎች ላይ በፍርድ ቤት ክስ ተመስርቶ ከዋናው ዕዳ በተጨማሪ ባንኩ ለክስ ያወጣቸውን ልዩ ልዩ ወጪዎች እንዲሸፍኑ ውሳኔ እየተሰጠ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።
ዳሸን ባንክ አክሲዮን ማህበር የህዝብ ገንዘብ ለማስመለስ የጀመረውን ህጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጠቆም፣ እስካሁን የክስ መጥሪያ ያልደረሳቸው ተበዳሪዎች ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ከመሄዱ በፊት እና ተጨማሪ አላስፈላጊ እንግልት እንዲሁም ወጪ ሳይደርስባቸው ያለባቸውን ዕዳ በአስቸኳይ እንዲከፍሉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በቴሌብር ዲጂታል ብድር ውዝፍ ዕዳ ላይ ህጋዊ እርምጃ እና ክስ መጀመሩ ተገለጸ‼️
ዳሸን ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም በቴሌብር መተግበሪያ አማካኝነት የወሰዱትን የዲጂታል ፋይናንሲንግ ብድር በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ያልከፈሉ ተበዳሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ መጀመራቸውን እና በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ክስ እየመሰረቱ እንደሚገኙ አስታወቁ።
ባንኩ ባወጣው መግለጫ እንደገለጸው፣ ተበዳሪዎች ያለባቸውን ውዝፍ ዕዳ እንዲከፍሉ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም የተደረገውን የቅጣት ክፍያ ምሕረት ተጠቅመው ዕዳቸውን ያልከፈሉ ወገኖች ላይ የህግ አካሄድ መጀመሩን ገልጿል።
በመግለጫው መሠረት፣ አስቀድሞ ለቀረበላቸው ጥሪ ምላሽ ያልሰጡ ተበዳሪዎች ላይ በፍርድ ቤት ክስ ተመስርቶ ከዋናው ዕዳ በተጨማሪ ባንኩ ለክስ ያወጣቸውን ልዩ ልዩ ወጪዎች እንዲሸፍኑ ውሳኔ እየተሰጠ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።
ዳሸን ባንክ አክሲዮን ማህበር የህዝብ ገንዘብ ለማስመለስ የጀመረውን ህጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጠቆም፣ እስካሁን የክስ መጥሪያ ያልደረሳቸው ተበዳሪዎች ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ከመሄዱ በፊት እና ተጨማሪ አላስፈላጊ እንግልት እንዲሁም ወጪ ሳይደርስባቸው ያለባቸውን ዕዳ በአስቸኳይ እንዲከፍሉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤21🤪16🤣5👍2🙏2
የዘመን አቆጣጠራችን ይቀየር ተባለ‼️
በምክክሩ ላይ የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር በተመለከተ የተለያዩ አማራጮች ቀርበዋል።
በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ውስጥ የሂጅራ ወይም የእስላማዊ የዘመን አቆጣጠር ይካተት፣ «ዓመተ ምህረት» የሚለው ይቅርና አሁን ያለው የፈረንጆቹ አቆጣጠር ይቀጥል፣ እንዲሁም ከእስልምናም ሆነ ከክርስትና ሃይማኖቶች ነፃ የሆነ የዘመን አቆጣጠር እንከተል የሚሉ ምክረ ሃሳቦች መቀረባቸው ታውቋል።
በተነሱት አጀንዳዎች ላይ እስካሁን ውሳኔ ደረጃ ላይ አልተደረሰም፣የውሳኔ ሂደቱ ገና መሆኑን ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በምክክሩ ላይ የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር በተመለከተ የተለያዩ አማራጮች ቀርበዋል።
በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ውስጥ የሂጅራ ወይም የእስላማዊ የዘመን አቆጣጠር ይካተት፣ «ዓመተ ምህረት» የሚለው ይቅርና አሁን ያለው የፈረንጆቹ አቆጣጠር ይቀጥል፣ እንዲሁም ከእስልምናም ሆነ ከክርስትና ሃይማኖቶች ነፃ የሆነ የዘመን አቆጣጠር እንከተል የሚሉ ምክረ ሃሳቦች መቀረባቸው ታውቋል።
በተነሱት አጀንዳዎች ላይ እስካሁን ውሳኔ ደረጃ ላይ አልተደረሰም፣የውሳኔ ሂደቱ ገና መሆኑን ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🙉45❤29😡19👍8👀8😢5🙊3🤷♂2🤩2😱1🌚1
#በኦሮሚያ እና #በሲዳማ አዋሳኝ አካባቢዎች ዳግም በተቀሰቀሰ ግጭት የሰው ሕይወት ሲያልፍ፤ ትምህርት ቤት እና የሰብል ምርቶች ወደሙ❗❗
√.ባለፈው ሳምንት በኦሮሚያው ጊርጃ ወረዳ ጉቦ ሄማ ቀበሌ እና በምሥራቅ ሲዳማ ዞን ጭሪ ቀበሌ መካከል ባገረሸው ግጭት የ10 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን፣ በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎችን ቆስለዋል፤ እንዲሁም በበርካታ ቀበሌዎች የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል ሲሉ በሁለቱም ወገን ያሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ ግጭት በአካባቢው ላይ የነበረውን መረጋጋት በእጅጉ ማደፍረሱን ገልጸዋል።
√.የምሥራቅ ጉጂ ዞን የጊርጃ ወረዳ ነዋሪ፤ በአጠቃላይ በጉጂ በኩል ጊርጃ ወረዳ ወደ 12 የሚጠጉ ሰዎች ሲገደሉ፣ ወደ 40 የሚጠጉ ደግሞ ቆስለው በአዶላ፣ ቦሬ፣ ኩያራ፣ ሻሸመኔ፣ ወላይታ ሶዶ እና አዲስ አበባ በሚገኙ ህክምና ተቋማት በመታከም ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
√. በተጨማሪም በርካታ የመኖሪያ ቤቶች እና የጉቦ ሄማ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወድመሏ ነው የተባለው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
√.ባለፈው ሳምንት በኦሮሚያው ጊርጃ ወረዳ ጉቦ ሄማ ቀበሌ እና በምሥራቅ ሲዳማ ዞን ጭሪ ቀበሌ መካከል ባገረሸው ግጭት የ10 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን፣ በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎችን ቆስለዋል፤ እንዲሁም በበርካታ ቀበሌዎች የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል ሲሉ በሁለቱም ወገን ያሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ ግጭት በአካባቢው ላይ የነበረውን መረጋጋት በእጅጉ ማደፍረሱን ገልጸዋል።
√.የምሥራቅ ጉጂ ዞን የጊርጃ ወረዳ ነዋሪ፤ በአጠቃላይ በጉጂ በኩል ጊርጃ ወረዳ ወደ 12 የሚጠጉ ሰዎች ሲገደሉ፣ ወደ 40 የሚጠጉ ደግሞ ቆስለው በአዶላ፣ ቦሬ፣ ኩያራ፣ ሻሸመኔ፣ ወላይታ ሶዶ እና አዲስ አበባ በሚገኙ ህክምና ተቋማት በመታከም ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
√. በተጨማሪም በርካታ የመኖሪያ ቤቶች እና የጉቦ ሄማ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወድመሏ ነው የተባለው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🕊6❤3👍3
በርካታ አካባቢዎች መብራት ይቋረጣል‼️
የጥገና ሥራ ምክንያት ነገ በበርካታ አካባቢዎች የመብራት አቅርቦት ይቋረጣል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ለተወሰነ ሰዓት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።
ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
• ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
• ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል እና አካባቢያቸው።
• 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ (በከፊል)፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢያቸው።
• ማርቆስ መጋዘን፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ፣ ይመር ውኃ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
• አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
• ገላን፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ፣ ፓስታና መኮረኒ ፋብሪካ እና አካባቢያቸው።
• አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣ በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
• መቐለ (ላቺ በከፊል)፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03፣ ባህርዳር (አዲስ ዓለም)፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
• ወልዲያ፣ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊበላ፣ ገነተ ማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅ ውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢያቸው።
• ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦ ከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚካኤል፣ ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢያቸው።
በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ እና የኃይል አቅርቦቱ ወደ መደበኛ ሁኔታው እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጠይቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የጥገና ሥራ ምክንያት ነገ በበርካታ አካባቢዎች የመብራት አቅርቦት ይቋረጣል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ለተወሰነ ሰዓት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።
ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
• ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
• ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል እና አካባቢያቸው።
• 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ (በከፊል)፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢያቸው።
• ማርቆስ መጋዘን፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ፣ ይመር ውኃ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
• አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
• ገላን፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ፣ ፓስታና መኮረኒ ፋብሪካ እና አካባቢያቸው።
• አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣ በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
• መቐለ (ላቺ በከፊል)፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03፣ ባህርዳር (አዲስ ዓለም)፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
• ወልዲያ፣ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊበላ፣ ገነተ ማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅ ውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢያቸው።
• ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦ ከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚካኤል፣ ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢያቸው።
በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ እና የኃይል አቅርቦቱ ወደ መደበኛ ሁኔታው እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጠይቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13👍3🤔1😢1👀1
ኤርትራ የአየር መንገዱን ገንዘብ አልመለሰችም‼️
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤርትራ የታገደበት ገንዘብ በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው የፖለቲካ ውጥረት እና የነበረው የህግ ሂደት በመቋረጡ ምክንያት ምንም ማድረግ እንዳልተቻለና እስካሁን መፍትሔ ሳያገኝ እንደቀረ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ።
“አሁን ላይ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ግንኙነት ጤናማ አይደለም፤ በዚህ ምክንያት ምንም ዓይነት ሂደት የለም፣ ጉዳዩ ስታክ እንዳደረገ (ባለበት እንደቆመ) ነው” ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ በጊዜው ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደውት የነበረ ቢሆንም “ፖለቲካዊ ውሳኔ በመደረጉ ፍርድ ቤቱ መንቀሳቀስ አልቻለም” ብለዋል። በመሆኑም ሁኔታዎች እስኪረጋጉ ድረስ ለመጠበቅ መገደዳቸውን ተናግረዋል።
አሁን ላይ ገንዘቡ በኤርትራ ባንክ እንደሚገኝ ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ የበረራ መቋረጡም ሆነ የገንዘብ ዝውውሩ መገታት ከፖለቲካዊ ሁኔታዎች ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመዋል። አየር መንገዱ በተለያዩ ሀገራት ገንዘቦቹ እንደተያዙበት ያነሱ ሲሆን፣ በርካታ ገንዘብ በሩሲያ እንደሚገኝ በመግለጽ ይህንንም ለማውጣት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በኤርትራ ያለለወው ገንዘብ ግን እስካሁን ባለበት እንደተያዘ ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤርትራ የታገደበት ገንዘብ በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው የፖለቲካ ውጥረት እና የነበረው የህግ ሂደት በመቋረጡ ምክንያት ምንም ማድረግ እንዳልተቻለና እስካሁን መፍትሔ ሳያገኝ እንደቀረ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ።
“አሁን ላይ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ግንኙነት ጤናማ አይደለም፤ በዚህ ምክንያት ምንም ዓይነት ሂደት የለም፣ ጉዳዩ ስታክ እንዳደረገ (ባለበት እንደቆመ) ነው” ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ በጊዜው ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደውት የነበረ ቢሆንም “ፖለቲካዊ ውሳኔ በመደረጉ ፍርድ ቤቱ መንቀሳቀስ አልቻለም” ብለዋል። በመሆኑም ሁኔታዎች እስኪረጋጉ ድረስ ለመጠበቅ መገደዳቸውን ተናግረዋል።
አሁን ላይ ገንዘቡ በኤርትራ ባንክ እንደሚገኝ ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ የበረራ መቋረጡም ሆነ የገንዘብ ዝውውሩ መገታት ከፖለቲካዊ ሁኔታዎች ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመዋል። አየር መንገዱ በተለያዩ ሀገራት ገንዘቦቹ እንደተያዙበት ያነሱ ሲሆን፣ በርካታ ገንዘብ በሩሲያ እንደሚገኝ በመግለጽ ይህንንም ለማውጣት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በኤርትራ ያለለወው ገንዘብ ግን እስካሁን ባለበት እንደተያዘ ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13🙊3👍2🤪2✍1
የአበል አፈፃፀም መመሪያ‼️
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጭ እና በቅዳሜ ቀናት ለሚሰሩ ሠራተኞች የትራንስፖርት አበል አፈጻጸም መመሪያ አውጥቷል።
በመመሪያው መሠረት በቅዳሜ ቀን ለሚሰሩ ሠራተኞች በቀን 200 ብር (በወር 800 ብር) እንዲሁም በምሽት ለሚሰሩ የትራንስፖርት መመለሻ በቀን 100 ብር (በወር 2,200 ብር) ተመድቧል። በዚህም መሠረት አንድ ሠራተኛ በወር እስከ 3,000 ብር የትራንስፖርት አበል ማግኘት ይችላል።
የትራንስፖርት አበል የሚከፈለው ከመደበኛ ሰዓት በኋላ አገልግሎት ለሚሰጡ ሠራተኞች፤ በቅዳሜ ቀናት በተፈቀደ የሥራ መርሐ-ግብር መሠረት ለሚሰሩ ሠራተኞች ብቻ ነው።
- በረዥም ጊዜ ሥልጠና ወይም ትምህርት ላይ ለሚገኝ ሠራተኛ፤
- በተፈቀደው የሥራ መርሐ-ግብር መሠረት በሥራ ላይ ላልተገኘ ሠራተኛ፤
- ተቋሙ የጋራ ወይም በተናጥል ትራንስፖርት አገልግሎት ላቀረበለት ሠራተኛ እና በተመሳሳይ ዓላማ ከሌላ ምንጭ የመጓጓዣ ድጋፍ የሚያገኝ ሠራተኛ የዚህ ትራንስፖርት አበል ተጠቃሚ አይሆንም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጭ እና በቅዳሜ ቀናት ለሚሰሩ ሠራተኞች የትራንስፖርት አበል አፈጻጸም መመሪያ አውጥቷል።
በመመሪያው መሠረት በቅዳሜ ቀን ለሚሰሩ ሠራተኞች በቀን 200 ብር (በወር 800 ብር) እንዲሁም በምሽት ለሚሰሩ የትራንስፖርት መመለሻ በቀን 100 ብር (በወር 2,200 ብር) ተመድቧል። በዚህም መሠረት አንድ ሠራተኛ በወር እስከ 3,000 ብር የትራንስፖርት አበል ማግኘት ይችላል።
የትራንስፖርት አበል የሚከፈለው ከመደበኛ ሰዓት በኋላ አገልግሎት ለሚሰጡ ሠራተኞች፤ በቅዳሜ ቀናት በተፈቀደ የሥራ መርሐ-ግብር መሠረት ለሚሰሩ ሠራተኞች ብቻ ነው።
- በረዥም ጊዜ ሥልጠና ወይም ትምህርት ላይ ለሚገኝ ሠራተኛ፤
- በተፈቀደው የሥራ መርሐ-ግብር መሠረት በሥራ ላይ ላልተገኘ ሠራተኛ፤
- ተቋሙ የጋራ ወይም በተናጥል ትራንስፖርት አገልግሎት ላቀረበለት ሠራተኛ እና በተመሳሳይ ዓላማ ከሌላ ምንጭ የመጓጓዣ ድጋፍ የሚያገኝ ሠራተኛ የዚህ ትራንስፖርት አበል ተጠቃሚ አይሆንም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19👍2🥰1🤔1👌1