አዲስ ሪፖርተር - NEWS
36.2K subscribers
17.1K photos
418 videos
21 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
ለምክክር ጉባዔ መጥታ ወንድ ልጅ የተገላገለችው እናት የልጇን ሥም "ኮሚሽን" አለችዉ

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተወክላ በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች።

ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራዊ ምክክሩ ላይ በመሳተፍ ላይ የነበረች የጋምቤላ ክልል ተወካይዋ ወ/ሮ ክርኑዶ ኡጁሉ ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላ ስሙም "ምክክር" መባሉ የሚታወስ ነው።

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ የመጣችው ሌላኛዋ የምክክሩ ተሳታፊ ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ በተመሳሳይ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን፥ ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች።

የመውለጃ ጊዜዬ እየደረሰ መሆኑን ባውቅም ለኢትዮጵያዊያን አብሮነትና ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ በሚመከርበት በዚህ ጉባኤ መሳተፍ አለብኝ በሚል አቋም ተገኝቻለሁ ብላለች፡፡

በጉባኤው አጀንዳዎች ላይ ለሀገራችን ይበጃል የምትለውን ሀሳብ በመስጠት ንቁ ተሳትፎ ስታደርግ የቆየች ሲሆን፥ በዚህ ታሪካዊ ወቅት ልጇን በመገላገሏ መደሰቷን ገልጻለች።

ዘገባዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሚዲያ ነዉ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣7011😡6👍3
በሩሲያ አንድ የቧንቧ ሥራ ኩባንያ የመጸዳጃ ቤት ዉሃ የመጠጣት ውድድር ማዘጋጀቱ ዉዝግብ አስነሳ
 
በሩሲያ ስታቭሮፖል የሚገኝ አንድ የቧንቧ ሥራ ኩባንያ፣ በቅርቡ "Game of Thrones" በሚል ያልተለመደ ውድድር ምክንያት በኢንተርኔት ላይ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። በዚህ ውድድር ላይ ተሳታፊዎች አዲስ ከሆኑ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫዎች ውስጥ፣ ትላልቅ የመምጠጫ ቱቦዎችን በመጠቀም "አልኮል ያልያዘ ጋዝ ያለው መጠጥ" እንዲጠጡ ይጠበቅባቸው ነበር፤ መጠጡን በፍጥነት የጨረሰውም አሸናፊ ተብሎ ተለይቷል።
 
በስታቭሮፖል ከተማ በሚገኝ የ"ዶሚክስ" መደብር ውስጥ የተካሄደው ይህ ያልተለመደ ውድድር፣ በርካታ ተሳታፊዎች የ100,000 ሩብል (1,276 የአሜሪካ ዶላር) ሽልማት ለማግኘት ሲሉ ከመጸዳጃ ቤት ጎድጓዳ ሳህን ውስጥ በፍጥነት እንዲጠጡ የሚያስገድድ ነበር። ተወዳዳሪዎቹ በሰባት ሰዎች ቡድን የተከፋፈሉ ሲሆን፣ ፈጣኑ ጠጪ ወደ ሁለተኛው ዙር ያልፍ ነበር።
 
በውድድሩ ሁለተኛ ምዕራፍ፣ ከቀዳሚው ዙር ያለፉት ሰባቱ አሸናፊዎች በተዘጋ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ላይ በተቻለ መጠን ረጅም ጊዜ መቀመጥ ነበረባቸው፤ በመጨረሻም መቀመጥ የቻለው ሰው የዚህ ያልተለመደ ዉድድር አሸናፊ ተብሎ ታዉጇል።

በቤዛዊት አራጌ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
10😡4👍2🥱2
ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 215.82 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።

ገቢው ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ33.2 በመቶ ዕድገት ያሳየ ነው።መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ለተመዘገበው ዕድገት እንደ አንድ ምክንያት የጠቀሰው የገቢ ምንጮቹ መስፋፋትን ነው።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 16፤ 2018 በሰጡት መግለጫ፤ ከዚህ ቀደም የኩባንያው የገቢ ምንጮች በሞባይል ድምጽ፣ በዳታ እና በኔትወርክ ትስስር (interconnect) ላይ ብቻ የተገደቡ እንደነበሩ አስታውሰዋል።

ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት ላገኘው ገቢ ከፍተኛውን ድርሻ ካበረከቱ የአገልግሎት ዓይነቶች መካከል የዳታ እና ኢንተርኔት አገልግሎት ይጠቀሳሉ።ሁለቱ አገልግሎቶች ከተቋሙ ገቢ ያላቸው ድርሻ 31.1 በመቶ መሆኑን ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ተናግረዋል። ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት ዓመቱ እንዳገኘው የገለጸው ያልተጣራ ትርፍም፤ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ51.9 በመቶ ከፍተኛ ዕድገት ተመዝግቦበታል።

ኩባንያው በ2018 በጀት ዓመት ያስመዘገበው ያልተጣራ ትርፍ 38.7 ቢሊዮን ነው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢176👍3🥱2🤪2
በኢትዮጵያ ብቁ የሆኑ የሂሳብ ባለሙያዎች ቁጥር ከ500 አይበልጥም ተባለ !

በኢትዮጵያ የሰለጠኑ እና  ብቁ የሆኑ የሂሳብ ባለሙያዎች ቁጥር   እጅግ አነስተኛ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በመሆኑም የተመሰከረላቸውን የሂሳብ ባሙያዎች  እጥረት ለመቅረፍ  የሚያስችል ስልጠና ኤችኤስቲ ስኪል አካዳሚ  መስጠት መጀመሩን አስታውቋል።

በተቋሙ በትምህርት እና ስልጠና ላይ ስትራቴጂክ ቢዝነስ ዩኒት ስኪል አካዳሚ ዳይሬክተር የቦርድ አባል እና የሪስክ እና ኦዲቲ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ጎበዜ ደሳለኝ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት በኢትዮጵያ  በሂሳብ አያያዝ ቴክኒካል ብቃት ብቁ የሆኑ የሒሳብ ባለሙያዎች  ቁጥር ከ500 አይበልጥም።ከዚህ ቀደም ስልጠናውን ለማግኘት ወደ ውጪ ሀገራት  መሄድ አስገዳጅ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ጎበዜ ይህንን የሚያስቀር እና ከከፍተኛ ወጪ የሚያድን ስልጠና በሀገር  ውስጥ  በድረገጽ አማካኝነት እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል

ከ12ኛ ክፍል ጀምሮ በተለያዩ የስራ ሁኔታዎችም ሆነ የትምህርት ዘርፍ ላይ የሚገኝ ማንኛውም ሰው በየትኛውም ቦታ ላይ ሆኖ ስልጠናውን መውሰድ ይችላል። በማኔጅመንት፣ በኦዲት ፋይናንስ ታክስ፣ እንዲሁም በሌሎች የሙያ ዘርፎች በ12 የትምህርት አይነቶች ስልጠናው የሚሰጥ ሲሆን ትምህርቱን ለመማር ከ12 እስከ 18  ወራት ይወስዳል

ለአንድ የትምህርት ዘርፍ የ3ሺህ ብር  የገንዘብ ክፍያ ብቻ  የሚጠየቅ መሆኑን የገለፁት አቶ ጎበዜ አስራ አንድ ድርጅቶች ስልጠናውን ይሰጣሉ ሲሉ አክለዋልከእነዚህም መካከል ሶስቱ የግል ድርጅቶች መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን  አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን  ጨምሮ ስምንቱ  ደግሞ የመንግስት ድርጅቶች ናቸው።የዩኒቨርሲቲ ተቋማት በቋሚነት ከሚሰጡት ትምህርት በተለየ መልኩ  ስልጠናውን በተግባር እንደሚሰጡ ተነግሯል

@Addis_Reporter
9👍3🎉1💊1
የአፍሪካ የሰዎችና ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያዊያን ላይ የተላለፉ ፍርዶችና የሞት ቅጣቶች እንደገና እንዲታዩ "ሁሉንም መንገዶች" እንዲጠቀምና የሞት ፍርድ የተፈረደባቸውን ኢትዮጵያዊያን ደኅንነት ለማስከበር አስፈላጊ "የዲፕሎማቲክ" እና "የቆንስላ" ርምጃዎችን እንዲወስድ ጠየቀ።

ኮሚሽኑ፣ ሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥ በበርካታ ኢትዮጵያዊያን ላይ የተጣለው የሞት ቅጣት በእጅጉ እንዳሳሰበው አስታውቋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ኢትዮጵያዊያኑ "የሕግ ውክልና" እና የፍርድ ቤት "የትርጉም አገልግሎት" እንዲያገኙና ከቤተሰባቸው ጋር እንዲገናኙ ጥረት እንዲያደርግ፤ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ፍልሠተኞችን መብት "በሁለትዮሽ ግንኙነቶች" እና በጠንካራ "የቆንስላ ድጋፎች" እንዲያስከብርም ኮሚሽኑ ጠይቋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
9👍7
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዲጂታል ገንዘቦች እና በቨርቹዋል ሀብቶች ዝውውር ላይ ጥብቅ እገዳ ጣለ

​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በህግ ከተፈቀደው ውጪ በማናቸውም የቨርቹዋል ሀብቶች ግብይት ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን አስታወቀ።

​እገዳው ቢትኮይንን ጨምሮ ሌሎች ክሪፕቶከረንሲዎችን ብቻ ሳይሆን፣ ለማንኛውም ክፍያና ኢንቨስትመንት የሚያገለግሉ በዲጂታል መልኩ የሚተላለፉ መግለጫዎችንም ያካትታል።

​በተለይም የሚከተሉት ተግባራት ሙሉ በሙሉ የተከለከሉ ናቸው ብሏል ባንኩ;

👉በቨርቹዋል ሀብት እና በመደበኛ ገንዘብ መካከል የሚደረግ መመንዘር

👉​በቨርቹዋል ሀብቶች መካከል የሚደረግ ልውውጥና ዝውውር

👉​የቨርቹዋል ሀብቶችን ማስቀመጥ፣ ማስተዳደር እና የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት

​ህብረተሰቡ ከህጋዊ ተጠያቂነት፣ ከማጭበርበር፣ ከሳይበር ጥቃት እና ከከባድ የገንዘብ ኪሳራ ለመጠበቅ ከነዚህ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠብ ባንኩ አሳስቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
10😡7🤪5👍2👌1💔1🤝1
ይድረስ ለሚመለከተው ሁሉ‼️
👉በ21ኛው ክ/ዘመን መኪና ሲገፉ/ሲጎትቱ/ ማየት አሳፋሪ ነው።
👉በሶስት አመት ይጠናቀቃል የተባለው መንገድ 8 አመት ሆነው።
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የጣርማ በር-መለያያ-ሰፌድ ሜዳ -ሞላሌ-ወገሬ የመንገድ ግንባታ ስራ ከተጀመረ ሰባት አመታት ተቆጥረዋል።

118 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍነው የጣርማ በር-መለያያ-ሰፌድ ሜዳ -ሞላሌ-ወገሬ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በ1.9 ቢሊዮን ብር የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦ የመንገድ ግንባታ ስራው የተጀመረው ታህሳስ 11/2011 ዓ.ም ነበር።
📌አሁን ላይ የመንገድ ስራው ሙሉ ለሙሉ ቆሟል፣የስራ አፈፃፀሙም ከ25% አላለፈም።
📌ይህ የዘመናት የህዝብ ጥያቄ የሆነው መንገድ ይሰራል ተብሎ የመሰረተ ድንጋይ ተጥሎ የተጀመረ ሰሞን የነበረው የህዝቡ ደስታ ወደ እርግማን ተቀይሯል፣ህዝቡም ተስፋ ቆርጧል።
📌መንገዱ ያለተለዋጭ መንገድ በየቦታው በመቆፈሩ ለጥገና አስቸጋሪ ሆኗል፣ዝናብ በጣለ ቁጥር መኪና የተባለ ሙሉ መልኩን ቀይሮ፣በጭቃ ዋና ዋኝቶ፣በህዝቡ ተገፍቶ፣ተጎትቶ ነው የሚወጣው።
📌ስራው ሳይጀመር በፊት ወደ ደብረብርሃን 4 ሰዓት ወደ አዲስ አበባ ስምንት ሰዓት ይፈጅ የነበረው መንገድ አሁን ላይ 118 ኪሎሜትር መንገድ ወደ ደብረብርሃን ለመምጣት 10 ሰዓት ይፈጃል።
📌ለግንባታው የቀረቡ ግብዓቶች ከጥቅም ውጪ ሆነዋል።
ይህ የመንገድ ስራ ከኮንትራክተር ጀምሮ ብዙ ችግሮች ቢኖሩም የሚመለከተው አካል ከህዝቡ ጋር መክሮ ዘክሮ የህዝቡን እምባ ሊያብስ የሚችል ስራ መስራት ይጠበቅበታል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
18🤣6👍4🥰1😢1
ጋምቤላ 💰 ወርቅ

ከጋምቤላ ከ7 ሺህ 98 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ሆኗል

በጋምቤላ ክልል በ2018 በጀት ዓመት 6 ሺህ ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ለማድረግ ታቅዶ፣ ከ7 ሺህ 98 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ገቢ መደረጉን የክልሉ ማዕድን ቢሮ አስታውቋል።

የተመዘገበው ውጤት ከእቅዱ በ1,098 ኪሎ ግራም፣ ከቀዳሚው ዓመት ደግሞ በ1,669 ኪሎ ግራም ብልጫ እንዳለው ተገልጿል።

በበጀት ዓመቱ በተከናወነ የማዕድን ልማትም ከ6,890 በላይ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን ቢሮው መግለጹን ኢዜአ ዘግቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
7👍5
#OpenAI

በደኅንነት ፍተሻ ወቅት የAI ሞዴል ከሙከራ ገደቡ አምልጦ በሌላ የAI ተቋም ላይ የሳይበር ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ።


የChatGPT አምራች የሆነው OpenAI እጅግ የላቁ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ሞዴሎቹ በደኅንነት ፍተሻ ወቅት ያልተጠበቀ ባህሪ በማሳየት ሌላ የAI ተቋም የሳይበር ጥቃት መፈጸማቸውን (ሀክ ማድረጋቸውን) ይፋ አድርጓል።

ኩባንያው እንደገለጸው፣ የሰው ልጅ መመሪያ ከሰጠው በኋላ ብቻውን ሊሠራ የሚችል የAI ሥርዓት ቁጥጥር በሚደረግበት አካባቢ ፍተሻ እየተደረገለት ሳለ ድክመቶችን በማግኘቱ ከሙከራ ገደቦቹ ማምለጥ ችሏል።

ጥቃቱ የደረሰው በዓለም ላይ ካሉት ትላልቅ የሰው ሠራሽ (AI) ሞዴሎች አምራች በሆነው Hugging Face ላይ ሲሆን የኮምፒውተር ሥርዓቱ ውስጥ ዘልቀው መግባት መቻላቸው ተነግሯል።

OpenAI ክስተቱ " ከዚህ በፊት ያልታየ " መሆኑን ገልጾ፣ ከHugging Face ጋር በመተባበር ምርመራ እያካሄደ መሆኑን አስታውቋል።

የHugging Face ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክሌመንት ዴላንጌም "ይህ ሁሉ በራሱ መከሰቱ በጣም አስደንጋጭ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

በሳይበር ደኅንነት ዘርፍ የሚሰሩ ባለሙያዎች ይህ ክስተት የAI አቅም በፍጥነት እየጨመረ በመምጣቱ አሁን ያሉት የደኅንነት መከላከያዎች በቂ ስለመሆናቸው አዲስ ጥያቄዎችን እንዳስነሳ ይገልጻሉ።

የSonicWall ሥራ አስፈጻሚ ስፔንሰር ስታርኪ፣ ድርጅቶች የሳይበር መከላከያቸውን ማጠናከርና ለዚህ ዘርፍ ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ክስተቱ የላቁ የAI ሥርዓቶች እየተሻሻሉ በሚሄዱበት ወቅት የደኅንነት መስፈርቶችንና የቁጥጥር ሥርዓቶችን የበለጠ ማጠናከር እንዳለባቸው የሚያሳይ አዲስ ውይይት ማስነሳቱን #ቢቢሲ ዘግቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
9🤣7👍3
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ብሄራዊ ግዴታ ተጥሏል‼️
"ማንኛውም የትግራይ ተወላጅ ጤናውና እድሜው የፈቀደለት ለተሰጠው የህልውና ጥሪ የመሳተፍ ብሔራዊ ግዴታ አለበት"።
የህወሓት አመራር አለቶ አለም ገብረዋህድ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢28👍21🤣149🤪2🤔1👀1
አስገራሚ መረጃ‼️
እስራኤል እስር ቤቶቿን በአዞ ለመጠበቅ ጉድጓድ መቆፈር ጀመረች።
👉በሀማስ እና ጋዛ እስረኞች ላይ ተጀምሯል።

የእስራኤል ሚዲያዎች እንደዘገቡት በደቡብ እስራኤል በሚገኘው የሃማስ እና የፓላስቲኒያን እስረኞች በሚገኙበትና ከፍተኛ ጥበቃ ባለው የእስር ቤት ክንፍ ዙሪያ ለአዞዎች መቀመጫ የሚሆን ጉድጓድ እየተቆፈረ ይገኛል።
እነዚህ ጉድጓዶች በኬትዚዮት እስር ቤት ዙሪያ እየተቆፈሩ ሲሆን ወደ 170 ሜትር የሚረዝሙ ይሆናሉ።

እስር ቤቱ የሚገኝበት የራማት ኔጌቭ የክልል ምክር ቤት ባለስልጣን ጉድጓዶቹ በእስር ቤቱ ውስጥ በልዩ ክንፎቹ ዙሪያ እየተቆፈሩ መሆናቸውን እና ከውጭ ማየት እንደማይቻል ተናግረዋል።

"በእርግጥ እዚያ አዞዎች ይኖሩ እንደሆነ ማንም አያውቅም፣ ነገር ግን ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው" ሲሉ ስማቸው ያልተጠቀሰ ባለስልጣን ተናግረዋል።

የእስራኤል ብሔራዊ የደህንነት ሚኒስቴር ለአዞዎች በተመደቡ ቻናሎች ላይ ሥራ መጀመሩን አረጋግጧል ሲል ጋዜጣው ዘግቧል።

የእስራኤል የእስር ቤት አገልግሎት አዞዎቹን ለመንከባከብ፣ ለመቆጣጠር እና ለማስተናገድ እቅድ አዘጋጅቷል፣ የእስር ቤቱ ኃላፊዎች ደግሞ አዞዎቹን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው ስልጠና ወስደዋል፣ ፕሮጀክቱም 21 ሚሊዮን ሰቅል (6.3 ሚሊዮን ዶላር) ተመድቧል ሲል ጋዜጣው ዘግቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
20👍8😡8😢4🤡4👀1🙉1
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ – የሚፈልጓቸውን አዳዲስ ዜናዎችን በአጭሩ እና በጥልቀት ከኛ ዘንድ ያንብቡ።

🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።

🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።

አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy

@sputnik_ethiopia
6👍2
ጦርነቱ ወደማይቀርበት ደረጃ ላይ ደርሷል
በትግራይ ድንበር ላይ የሚደረጉ ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ጦርነት የማይቀርበት ደረጃ ላይ እየደረሰ መሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶች አሉ።

🔺ዋና ዋና ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች፡

📌የሀገር መከላከያ ሰራዊት (ENDF) ከዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ጋር በተለያዩ አቅጣጫዎች ወደ ትግራይ ድንበር አካባቢ እየገቡ ይገኛሉ። ድሮኖችም መረጃ ለመሰብሰብ እና ለመከታተል በአካባቢው በተደጋጋሚ እየበረሩ ነው።

📌#ህወሃትም በራያ አካባቢ ከባድ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች እያደረገ ሲሆን አዳዲስ ሰልጣኞችን የያዙ ተሽከርካሪዎች እንደ ተጨማሪ ኃይሎች እየገቡ ይገኛሉ።
በሁለቱም ወገኖች በድንበር እና በወታደራዊ ሰፈሮች ላይ ያለው ከፍተኛ ዝግጅት ክልሉ ወደ ሌላ ጦርነት ሊገባ እንደሚችል ያሳያል።
'ትልቁ ጀግንነት ጦርነትን መጀመር ሳይሆን ማስቀረት ነው"(የቻይናዊያን አባባል)።


@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
19💔14👍6🕊5👀5🤣1🤪1
አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Photo
የራቁታቹን ፎቶ በሶሻል ሚድያ እለቃለሁ በማለት አስፈራርቶ ክብረ ንጽህና የገረሰሳ እና የግብረስጋ ድፍረት በደል ወንጀል የፈጸመው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ
 
በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 7ኛ ወንጀል ችሎት የቀረበው ተከሳሽ ፀጋዬ ሲሳይ ስዩም እንቁላል ፋብሪካ ይገዙ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው መኖሪያ ቤቱ የ14 አመት እድሜ ያላቸውን የግል ተበዳዬችን ‹‹ላስጠናችሁ›› በማለት ለእህቱ ልጅ በማስጠራት በ2018 ዓ.ም የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ስለፈጸመባቸው በዐቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶበታል፡፡
 
ተከሳሽ ግንቦት  30 ቀን 2018 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 10፡00 ሲሆን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ልዩ ቦታው እንቁላል ፋብሪካ ይገዙ ሜዳ አካባቢ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ውስጥ የ14 አመት እድሜ ያላትን የግል ተበዳይ  ‹‹ላስጠናሽ›› ብሎ በማስጠራት እና ከወንጀል ድርጊቱ በፊት ገላዋን ስትታጠብ ያነሳትን ፎቶ ‹‹ፌስቡክ ላይ እለቅብሻለሁ›› በማለት በልጅነት አእምሮዋ አስፈራርቶ የግብረ ስጋ ግንኙነት የፈጸመባት እና ክብረ ንጽህናዋ እንዲገረሰስ ያደረገ በመሆኑ በፈጸመው የግብረ ስጋ  ድፍረት ወንጀል ዐቃቤ ህግ ከሶታል፡፡
 
በሁለተኛ ክስ ተከሳሽ የወንጀል ህግ አንቀጽ 626/1/ን በመተላለፍ  ሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 11፡00 ሲሆን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ልዩ ቦታው እንቁላል ፋብሪካ ይገዙ ሜዳ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ውስጥ የ14 ዓመት እድሜ ያላትን የግል ተበዳይ ‹‹ላስጠናሽ›› ብሎ በእህቱ ልጅ በማስጠራት የግብረ ስጋ ግንኙነት የፈጸመባት እና ክብረ ንጽህናዋ እንዲገረሰስ ያደረገ በመሆኑ በግብረ ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል፡፡
 
ዐቃቤ ህግም በጉዳዩ ላይ የሰው እና የሰነድ ማሰረጃዎችን ያቀረበ ሲሆን ተከሳሽም በዐቃቤ ህግ የቀረበበትን የሰው እና የሰነድ ማሰረጃ ማሰተባበል ባለመቻሉ ድረጊቱን መፈጸሙ በማስረጃ ተረጋግጦ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎበታል  ተከሳሽ ጥፋተኛ የተባለበት ሁለቱም የወንጀል ህጎች ሲሆኑ ዐቃቤ ህግ ተከሳሽ የተከሰሰው በተደራራቢ ክሶች ስለሆነ   በወ/ህ/አንቀጽ 85 መሰረት ከብዶ እንዲወሰን ያቀረበውን ጥያቄ ፍ/ቤቱ ተቀብሎ ሀምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ወንጀለኛው የቀደመ ሪከርድ ስለሌለበት አንድ ማቅለያ በመያዝ በ10 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
16💔15😢6🤣5👍2🤯1😱1👀1