በኮንታ ልዩ ወረዳ እናትን ገድሎ ልጃቸውን የደፈረው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ
በኮንታ ልዩ ወረዳ የግንባ አጋሬ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ አብርሃም አመለ ቦንጆሬ፣ በፈጸማቸው ሶስት ከባድ ወንጀሎች በሞት እንዲቀጣ የኮንታ ልዩ ወረዳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላለፈ።
ተከሳሹ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከገበያ ስትመለስ የነበረችውን የ15 ዓመት ታዳጊ ጠልፎ ወደ ጫካ በመውሰድ ሊደፍራት ሲታገል፣ የልጇን ጩኸት ሰምታ የደረሰችውን እናት ወይዘሮ አይናቴ ኬቶን በጩቤ ወግቶ በመግደል ገደል ውስጥ ወርውሯታል።
ተከሳሹ እናትን በዚህ አሰቃቂ ሁኔታ ካደባየ በኋላ የጠለፋትን ታዳጊ ልጅ አስገድዶ መድፈሩን የፖሊስ የምርመራ ውጤት እና የዐቃቤ ህግ ማስረጃዎች አረጋግጠዋል።
በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባስቻለው ችሎት፣ ተከሳሹ በፈጸማቸው በጭካኔ የመግደል፣ በታዳጊ ልጅ ጠለፋ እና በአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች ጥፋተኛ በማለቱ የሞት ቅጣት እንዲወሰንበት አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በኮንታ ልዩ ወረዳ የግንባ አጋሬ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ አብርሃም አመለ ቦንጆሬ፣ በፈጸማቸው ሶስት ከባድ ወንጀሎች በሞት እንዲቀጣ የኮንታ ልዩ ወረዳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላለፈ።
ተከሳሹ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከገበያ ስትመለስ የነበረችውን የ15 ዓመት ታዳጊ ጠልፎ ወደ ጫካ በመውሰድ ሊደፍራት ሲታገል፣ የልጇን ጩኸት ሰምታ የደረሰችውን እናት ወይዘሮ አይናቴ ኬቶን በጩቤ ወግቶ በመግደል ገደል ውስጥ ወርውሯታል።
ተከሳሹ እናትን በዚህ አሰቃቂ ሁኔታ ካደባየ በኋላ የጠለፋትን ታዳጊ ልጅ አስገድዶ መድፈሩን የፖሊስ የምርመራ ውጤት እና የዐቃቤ ህግ ማስረጃዎች አረጋግጠዋል።
በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባስቻለው ችሎት፣ ተከሳሹ በፈጸማቸው በጭካኔ የመግደል፣ በታዳጊ ልጅ ጠለፋ እና በአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች ጥፋተኛ በማለቱ የሞት ቅጣት እንዲወሰንበት አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤22🙉13🤯10💯8🫡3👍2🤔2😢1
ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ ጄኤፍኤም 106.7 የብሮድካስት አዋጅ ቁጥር 1238/2013 እና የፈቃድ ውል ስምምነቱን አልጠበቀም ሲል አስታውቋል።
ጣቢያው 60% የሚሆነውን ስርጭት ለፈቃድ አካባቢው የማዋል፣ ህዝብን የሚያስተምሩና የሚያዝናኑ ፕሮግራሞችን የማቅረብ፣ እንዲሁም ሀገራዊ እና ህገ-መንግስታዊ እሴቶችን የማጠናከር ግዴታዎቹን አልተወጣም ተብሏል።
ባለሥልጣኑ በተደጋጋሚ የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቢሰጥም መሻሻል ባለመታየቱ እርምጃው ሊወሰድበት ችሏል።
በዚህም መሠረት የሬዲዮ ጣቢያው ከተሰጡት ማስጠንቀቂያዎች በኋላ አስፈላጊዎቹን ግዴታዎች ሙሉ ለሙሉ አሟልቶ እስኪገኝ ድረስ ለቀጣዮቹ 6 ወራት ከስርጭት ሙሉ በሙሉ ታግዷል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣንም ለጄኤፍኤም የተመደበው 106.7 የሬድዮ ሞገድ እግድ ፀንቶ እስከሚቆይበት ጊዜ ድረስ ፍሪኩዌንሲውን ጥቅም ላይ ማዋል እንደማይቻል ለጣቢያው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ ጄኤፍኤም 106.7 የብሮድካስት አዋጅ ቁጥር 1238/2013 እና የፈቃድ ውል ስምምነቱን አልጠበቀም ሲል አስታውቋል።
ጣቢያው 60% የሚሆነውን ስርጭት ለፈቃድ አካባቢው የማዋል፣ ህዝብን የሚያስተምሩና የሚያዝናኑ ፕሮግራሞችን የማቅረብ፣ እንዲሁም ሀገራዊ እና ህገ-መንግስታዊ እሴቶችን የማጠናከር ግዴታዎቹን አልተወጣም ተብሏል።
ባለሥልጣኑ በተደጋጋሚ የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቢሰጥም መሻሻል ባለመታየቱ እርምጃው ሊወሰድበት ችሏል።
በዚህም መሠረት የሬዲዮ ጣቢያው ከተሰጡት ማስጠንቀቂያዎች በኋላ አስፈላጊዎቹን ግዴታዎች ሙሉ ለሙሉ አሟልቶ እስኪገኝ ድረስ ለቀጣዮቹ 6 ወራት ከስርጭት ሙሉ በሙሉ ታግዷል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣንም ለጄኤፍኤም የተመደበው 106.7 የሬድዮ ሞገድ እግድ ፀንቶ እስከሚቆይበት ጊዜ ድረስ ፍሪኩዌንሲውን ጥቅም ላይ ማዋል እንደማይቻል ለጣቢያው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡20❤11👍4🤷♂3🤡2🤔1
ኢትዮጵያ መብራት አቋረጠችብች-ሱዳን‼️
የሱዳን የኢነርጂ እና ነዳጅ ሚኒስቴር በትናትናው ዕለት ሀምሌ 14/2018 ዓ.ም እንዳስታወቀው 'በመላ ሀገሪቱ የሚታየው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ በበርካታ ምክንያቶች የተከሰተ መሆኑን ጠቅሶ ከእነዚህም መካከል ከኢትዮጵያ ጋር በተዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በኩል የሚደረገው የኤሌክትሪክ አቅርቦት መቋረጥ በዋናው መስመር ላይ ጉዳት መድረሱን ሌላኛው ፈተና መሆኑን ገልጿል። ሚኒስትሩ በካርቱም ከፍተኛ የተባለ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ችግር መፈጠሩን ጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሱዳን የኢነርጂ እና ነዳጅ ሚኒስቴር በትናትናው ዕለት ሀምሌ 14/2018 ዓ.ም እንዳስታወቀው 'በመላ ሀገሪቱ የሚታየው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ በበርካታ ምክንያቶች የተከሰተ መሆኑን ጠቅሶ ከእነዚህም መካከል ከኢትዮጵያ ጋር በተዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በኩል የሚደረገው የኤሌክትሪክ አቅርቦት መቋረጥ በዋናው መስመር ላይ ጉዳት መድረሱን ሌላኛው ፈተና መሆኑን ገልጿል። ሚኒስትሩ በካርቱም ከፍተኛ የተባለ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ችግር መፈጠሩን ጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣25❤14👍4🤔1🤪1
የድሮን ጥቃት‼️
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️
በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰላም በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በሚገኘው ዓባይ ገዳመ አስቀጤስ የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ምክንያት በገዳሙ ውስጥ የሚኖሩ 2 ሴቶች ወዲያው ህይወታቸው ማለፉን እና ሌሎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል።
ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው የፋኖ ሀይሎች ከትመዋል በሚል ነው ተብሏል።
ሰላም ለሀገራችን🕊🕊
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️
በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰላም በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በሚገኘው ዓባይ ገዳመ አስቀጤስ የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ምክንያት በገዳሙ ውስጥ የሚኖሩ 2 ሴቶች ወዲያው ህይወታቸው ማለፉን እና ሌሎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል።
ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው የፋኖ ሀይሎች ከትመዋል በሚል ነው ተብሏል።
ሰላም ለሀገራችን🕊🕊
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢57💔28❤15😱3
የዝናብ ሁኔታ‼️
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ።
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ።
ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል።
በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን ይኖራቸዋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል።
ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ።
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ።
ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል።
በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን ይኖራቸዋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል።
ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13👍7
ብሄራዊ ባንክ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ሊያካሂድ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ2019 ዓ.ም የፋይናንስ ዓመት የመጀመሪያው ሩብ በንግድ ባንኮች በኩል 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ወደ ገበያው ለማስገባት አቅዷል።
ማዕከላዊ ባንኩ በነሐሴ እና መስከረም ወራት አራት መደበኛ የውጭ ምንዛሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ ገልጿል።
በእያንዳንዱ ጨረታም 125 ሚሊዮን ዶላር ለንግድ ባንኮች እንደሚቀርብ አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ2019 ዓ.ም የፋይናንስ ዓመት የመጀመሪያው ሩብ በንግድ ባንኮች በኩል 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ወደ ገበያው ለማስገባት አቅዷል።
ማዕከላዊ ባንኩ በነሐሴ እና መስከረም ወራት አራት መደበኛ የውጭ ምንዛሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ ገልጿል።
በእያንዳንዱ ጨረታም 125 ሚሊዮን ዶላር ለንግድ ባንኮች እንደሚቀርብ አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤4👍3
በትግራይ በረዶ አዘል ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ቀጠፈ
በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ ተቃራኒ የአየር ሁኔታዎች በሕዝብና በግብርና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆናቸው ተገልጿል።
በአንድ በኩል በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ሲቀጥፍ፣ በአዝርእትና በመስኖ ላይም ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል። በሌላ በኩል ደግሞ 176 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳላገኙ ተገልጿል።
በማዕከላዊ ዞን ወረዳ ቀይሕ ተኽሊ ዶክተር አታኽልቲ ቀበሌ ገበሬ ማህበር፣ ለሁለት ሰዓታት ያለማቋረጥ የዘነበው በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ከመቅጠፉ በተጨማሪ በአዝርእትና በመስኖ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
በተመሳሳይ በዞኑ ወረዳ አሕፈሮም ሴሮ ቀበሌ የዘነበው ብርቱ ዝናብም በአዝርእትና በአትክልት ላይ ጉዳት ማድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።
በሌላ በኩል የትግራይ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ጥበቃ ቢሮ ሐምሌ 13፣ 2018 ዓ.ም. ባወጣው መረጃ፣ በክልሉ ከሚገኙ 600 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት መካከል 176 በሚሆኑት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳልዘነበ አስታውቋል።
ይህ ሁኔታ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ከመጠን ያለፈ ዝናብ ጉዳት እያደረሰ ሲሆን፣ በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ የዝናብ እጥረት በእርሻ ሥራና በምርት ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ያሳያል።#ቲክቫህ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ ተቃራኒ የአየር ሁኔታዎች በሕዝብና በግብርና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆናቸው ተገልጿል።
በአንድ በኩል በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ሲቀጥፍ፣ በአዝርእትና በመስኖ ላይም ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል። በሌላ በኩል ደግሞ 176 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳላገኙ ተገልጿል።
በማዕከላዊ ዞን ወረዳ ቀይሕ ተኽሊ ዶክተር አታኽልቲ ቀበሌ ገበሬ ማህበር፣ ለሁለት ሰዓታት ያለማቋረጥ የዘነበው በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ከመቅጠፉ በተጨማሪ በአዝርእትና በመስኖ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
በተመሳሳይ በዞኑ ወረዳ አሕፈሮም ሴሮ ቀበሌ የዘነበው ብርቱ ዝናብም በአዝርእትና በአትክልት ላይ ጉዳት ማድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።
በሌላ በኩል የትግራይ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ጥበቃ ቢሮ ሐምሌ 13፣ 2018 ዓ.ም. ባወጣው መረጃ፣ በክልሉ ከሚገኙ 600 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት መካከል 176 በሚሆኑት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳልዘነበ አስታውቋል።
ይህ ሁኔታ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ከመጠን ያለፈ ዝናብ ጉዳት እያደረሰ ሲሆን፣ በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ የዝናብ እጥረት በእርሻ ሥራና በምርት ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ያሳያል።#ቲክቫህ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10😢9👍2
መረጃ‼️
59 በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድ ክፍል ቤት ውስጥ እንደሚኖር የፌደራል ስታትስቲክስ አገልግሎት ከአውሮፓዊያኑ 2024 እስከ 2025 ያካሄደው ጥናት አመለከተ።
የመኖሪያ ቤቶች መጨናነቅ በተለይ በከተሞች አካባቢ እንዲባባስ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገው ያልተቋረጠ ፍልሠት መኾኑን ዋዜማ ከጥናቱ ላይ ተመልክታለች።
በተጠቀሠው ጊዜ ውስጥ በጥናቱ 31 በመቶ የሴቶች እና 24 በመቶ የወንዶች ፍልሠት ተመዝግቧል።
የተሻለ የሥራ ዕድል፣ ትምህርትና የመሠረተ ልማት አቅርቦትን ፍለጋ የሚደረገው ፍልሠት፣ በከተሞች ላይ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ጫና በመፍጠሩ በባለ ሁለት ክፍል ቤቶች የሚኖሩ ዜጎች ድርሻ 31 በመቶ መድረሱን ሪፖርቱ ያትቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
59 በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድ ክፍል ቤት ውስጥ እንደሚኖር የፌደራል ስታትስቲክስ አገልግሎት ከአውሮፓዊያኑ 2024 እስከ 2025 ያካሄደው ጥናት አመለከተ።
የመኖሪያ ቤቶች መጨናነቅ በተለይ በከተሞች አካባቢ እንዲባባስ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገው ያልተቋረጠ ፍልሠት መኾኑን ዋዜማ ከጥናቱ ላይ ተመልክታለች።
በተጠቀሠው ጊዜ ውስጥ በጥናቱ 31 በመቶ የሴቶች እና 24 በመቶ የወንዶች ፍልሠት ተመዝግቧል።
የተሻለ የሥራ ዕድል፣ ትምህርትና የመሠረተ ልማት አቅርቦትን ፍለጋ የሚደረገው ፍልሠት፣ በከተሞች ላይ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ጫና በመፍጠሩ በባለ ሁለት ክፍል ቤቶች የሚኖሩ ዜጎች ድርሻ 31 በመቶ መድረሱን ሪፖርቱ ያትቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢20❤7👍3🤣2
አብይ አህመድ ስለ ህወሃት‼️👇
ህወሓት አዲስ ነገር ለመስማት እና ለማየት ፍላጎት የለውም'-ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)‼️
ህወሃት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብና ሀሳብ የታጠረ ድርጅት ነው።
ይህ ብቻ ሳይሆን ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ እርምጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፣አሁንም እየወሰደ ይገኛል።
ይህ ደግሞ ጤና ያለው ድርጅት ባህሪ አይደለም።
አዲስ ነገር ለመስማት ጆሮ የለውም፣አዲስ ነገር ለማየት አይን የለውም፣ፍላጎትም የለውም።
አዲስ ነገር ለመስማት ዝግጁ ያልሆነ ድርጅት ለህዝቡ ጥሩ ስራ ይሰራል ተብሎ አይጠበቅም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ሐምሌ 15 ስለህወሓት በትግርኛ ከተናገሩት ተተርጉሞ የተወሰደ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ህወሓት አዲስ ነገር ለመስማት እና ለማየት ፍላጎት የለውም'-ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)‼️
ህወሃት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብና ሀሳብ የታጠረ ድርጅት ነው።
ይህ ብቻ ሳይሆን ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ እርምጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፣አሁንም እየወሰደ ይገኛል።
ይህ ደግሞ ጤና ያለው ድርጅት ባህሪ አይደለም።
አዲስ ነገር ለመስማት ጆሮ የለውም፣አዲስ ነገር ለማየት አይን የለውም፣ፍላጎትም የለውም።
አዲስ ነገር ለመስማት ዝግጁ ያልሆነ ድርጅት ለህዝቡ ጥሩ ስራ ይሰራል ተብሎ አይጠበቅም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ሐምሌ 15 ስለህወሓት በትግርኛ ከተናገሩት ተተርጉሞ የተወሰደ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤25🤣21🤪4👍3
#የውቅያኖስ ወለል ምስጢር፦ የዓለምን ኢንተርኔት የሚያንቀሳቅሱት የባህር ስር መስመሮች❗❗
ብዙዎቻችን በየቀኑ በስልካችን የምንጠቀመው ኢንተርኔት፣ ማህበራዊ ሚዲያ እና ዓለም አቀፍ የመረጃ ፍሰት በሳተላይት በኩል በአየር ላይ የሚጓዝ ቢመስለንም፣ እውነታው ግን ከዚህ እጅግ የራቀ ነው።
የዓለማችን 99 በመቶ የሚያህለው የኢንተርኔት ዳታ የሚጓዘው በጨለማውና በጥቁሩ የውቅያኖሶች ወለል ላይ በተዘረጉ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮች በኩል ነው። በዓለም ዙሪያ በውቅያኖሶች ስር የተዘረጉት እነዚህ ከ550 በላይ ንቁ ካብሎች ከ1.4 ሚሊዮን ኪሎሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን፣ በሴኮንድ በመቶ ቴራባይት የሚቆጥር ዳታ የሚያስተላልፉት እነዚህ መስመሮች እንደተጠበቀው ትልቅ ሳይሆኑ የመጠጥ ውሃ ማስተላለፊያ ወይም የጓሮ ቧንቧ ያህል ውፍረት ብቻ ያላቸው ናቸው።
በኬብሉ መሃል የሚገኙት የመረጃ ማስተላለፊያ የብርጭቆ ጫፎች ወይም ቀጫጭን የብርጭቆ ገመዶች የሰው ፀጉር ያህል ቀጫጭን ሲሆኑ፣ መረጃን በብርሃን ፍጥነት ያጓጉዛሉ።እነዚህ መስመሮች ለአደጋ ተጋላጭነታቸው ከፍተኛ በመሆኑ በየዓመቱ በአማካይ ከ100 በላይ የመቆረጥ አደጋዎች ያጋጥሟቸዋል ተብሏል።
የመርከብ መልሕቆች መሬት ሲቧጥጡ፣ የባህር ስር የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት ወይም አልፎ አልፎ የሻርክ አሳዎች ሲነክሷቸው መስመሮቹ የሚበጠሱ ሲሆን፣ አንድ የባህር ስር ኬብል ከተቋረጠ የሙሉ ሀገር ወይም ቀጠና ኢንተርኔት ሙሉ በሙሉ ሊቋረጥ ወይም ሊዘገይ ይችላል ነው የተባለው።
በአሁኑ ወቅት እንደ Google፣ Meta፣ Microsoft እና Amazon ያሉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የራሳቸውን የባህር ስር ኬብሎች በመዘርጋት የዓለምን የመረጃ መረብ በባለቤትነት እየተቆጣጠሩት ይገኛሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ብዙዎቻችን በየቀኑ በስልካችን የምንጠቀመው ኢንተርኔት፣ ማህበራዊ ሚዲያ እና ዓለም አቀፍ የመረጃ ፍሰት በሳተላይት በኩል በአየር ላይ የሚጓዝ ቢመስለንም፣ እውነታው ግን ከዚህ እጅግ የራቀ ነው።
የዓለማችን 99 በመቶ የሚያህለው የኢንተርኔት ዳታ የሚጓዘው በጨለማውና በጥቁሩ የውቅያኖሶች ወለል ላይ በተዘረጉ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮች በኩል ነው። በዓለም ዙሪያ በውቅያኖሶች ስር የተዘረጉት እነዚህ ከ550 በላይ ንቁ ካብሎች ከ1.4 ሚሊዮን ኪሎሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን፣ በሴኮንድ በመቶ ቴራባይት የሚቆጥር ዳታ የሚያስተላልፉት እነዚህ መስመሮች እንደተጠበቀው ትልቅ ሳይሆኑ የመጠጥ ውሃ ማስተላለፊያ ወይም የጓሮ ቧንቧ ያህል ውፍረት ብቻ ያላቸው ናቸው።
በኬብሉ መሃል የሚገኙት የመረጃ ማስተላለፊያ የብርጭቆ ጫፎች ወይም ቀጫጭን የብርጭቆ ገመዶች የሰው ፀጉር ያህል ቀጫጭን ሲሆኑ፣ መረጃን በብርሃን ፍጥነት ያጓጉዛሉ።እነዚህ መስመሮች ለአደጋ ተጋላጭነታቸው ከፍተኛ በመሆኑ በየዓመቱ በአማካይ ከ100 በላይ የመቆረጥ አደጋዎች ያጋጥሟቸዋል ተብሏል።
የመርከብ መልሕቆች መሬት ሲቧጥጡ፣ የባህር ስር የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት ወይም አልፎ አልፎ የሻርክ አሳዎች ሲነክሷቸው መስመሮቹ የሚበጠሱ ሲሆን፣ አንድ የባህር ስር ኬብል ከተቋረጠ የሙሉ ሀገር ወይም ቀጠና ኢንተርኔት ሙሉ በሙሉ ሊቋረጥ ወይም ሊዘገይ ይችላል ነው የተባለው።
በአሁኑ ወቅት እንደ Google፣ Meta፣ Microsoft እና Amazon ያሉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የራሳቸውን የባህር ስር ኬብሎች በመዘርጋት የዓለምን የመረጃ መረብ በባለቤትነት እየተቆጣጠሩት ይገኛሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤22👍5
በወላይታ ሶዶ ከተማ ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወሰደ
በወላይታ ሶዶ ከተማ በህግ የተከለከለውን ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን የከተማው የአካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ጽ/ቤት አስታውቋል።እርምጃው በአብዛኛው በሱቆችና በንግድ ተቋማት ላይ የተወሰደ ሲሆን ከየካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው ክትትል የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።
የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ ለማ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1387/2017ን በመተላለፍ ፌስታል በመያዝ እና ለንግድ አገልግሎት ጥቅም ላይ ሲያውሉ በተገኙ 130 አካላት ላይ በህጉ መሠረት እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል።በቅርቡ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል አንድ ነጋዴ 17 ኩንታል ማዳበሪያ ይዞ በመገኘቱ የተወረሰበት ሲሆን በ50 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ጨምር እንዲቀጣ ተደርጓል።
በመሆኑም ግለሰቦችና ተቋማት ፌስታል መጠቀም በህግ የተከለከለ ተግባር መሆኑን በመገንዘብ ህጉን ሊያከብሩ ይገባል ሲሉ አቶ ጴጥሮስ ለማ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።በአዋጁ መሰረት ፌስታል ይዞ የተገኘ ግለሰብ በ2 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ይቀጣል።እንዲሁም በተቋም ደረጃ ፌስታል ያከማቸ፣ የሸጠ ወይም ለንግድ ዓላማ እንደ እቃ መያዣ ያቀረበ ተቋም እስከ 200 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና ባለንብረቶችም እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚቀጡ በአዋጁ ተጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በወላይታ ሶዶ ከተማ በህግ የተከለከለውን ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን የከተማው የአካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ጽ/ቤት አስታውቋል።እርምጃው በአብዛኛው በሱቆችና በንግድ ተቋማት ላይ የተወሰደ ሲሆን ከየካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው ክትትል የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።
የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ ለማ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1387/2017ን በመተላለፍ ፌስታል በመያዝ እና ለንግድ አገልግሎት ጥቅም ላይ ሲያውሉ በተገኙ 130 አካላት ላይ በህጉ መሠረት እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል።በቅርቡ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል አንድ ነጋዴ 17 ኩንታል ማዳበሪያ ይዞ በመገኘቱ የተወረሰበት ሲሆን በ50 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ጨምር እንዲቀጣ ተደርጓል።
በመሆኑም ግለሰቦችና ተቋማት ፌስታል መጠቀም በህግ የተከለከለ ተግባር መሆኑን በመገንዘብ ህጉን ሊያከብሩ ይገባል ሲሉ አቶ ጴጥሮስ ለማ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።በአዋጁ መሰረት ፌስታል ይዞ የተገኘ ግለሰብ በ2 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ይቀጣል።እንዲሁም በተቋም ደረጃ ፌስታል ያከማቸ፣ የሸጠ ወይም ለንግድ ዓላማ እንደ እቃ መያዣ ያቀረበ ተቋም እስከ 200 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና ባለንብረቶችም እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚቀጡ በአዋጁ ተጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16🤪12👍2🤯1
ሰበር መረጃ‼️
የኢትዮጵያን መንግስት ለመጣል ያለመ ስብሰባ በኤርትራ ድንበር ተደረገ፣ስብሰባውን የመሩት አቶ አማኑኤል አሰፋ ናቸው።
ሕወሓት የብልጽግናን መንግስት አስወግዳለሁ እያለ ነው፡፡ ቡድኑ ካለፈው እሁድ አንስቶ 'ህልውናችን የሚረጋገጠው በብልጽግና መቃብር ላይ ነው' በሚል መሪቃል ስብሰባዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡ በእነዚህ ስብሰባዎች ላይ ከወትሮው በተለየ መልኩ የሕወሓት አመራሮች ‹‹ብልጽግናን ከስልጣን ማስወገድ አለብን›› በማለት በግላጭ እየተናገሩ ነው፡፡
በሚዲያዎቻቸውም የፌደራል መንግስቱን 'ጄንኖሳይዳዊ አገዛዝ' የሚል ስያሜ ሰጥተው በትግራይ ቴሌቪዥን ጭምር ዜና መስራት ጀምረዋል። የፌደራል መንግሥቱ ለህወሓት የጦርነት ጉሰማ በቀጥታ የሰጠው ምላሽ የለም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያን መንግስት ለመጣል ያለመ ስብሰባ በኤርትራ ድንበር ተደረገ፣ስብሰባውን የመሩት አቶ አማኑኤል አሰፋ ናቸው።
ሕወሓት የብልጽግናን መንግስት አስወግዳለሁ እያለ ነው፡፡ ቡድኑ ካለፈው እሁድ አንስቶ 'ህልውናችን የሚረጋገጠው በብልጽግና መቃብር ላይ ነው' በሚል መሪቃል ስብሰባዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡ በእነዚህ ስብሰባዎች ላይ ከወትሮው በተለየ መልኩ የሕወሓት አመራሮች ‹‹ብልጽግናን ከስልጣን ማስወገድ አለብን›› በማለት በግላጭ እየተናገሩ ነው፡፡
በሚዲያዎቻቸውም የፌደራል መንግስቱን 'ጄንኖሳይዳዊ አገዛዝ' የሚል ስያሜ ሰጥተው በትግራይ ቴሌቪዥን ጭምር ዜና መስራት ጀምረዋል። የፌደራል መንግሥቱ ለህወሓት የጦርነት ጉሰማ በቀጥታ የሰጠው ምላሽ የለም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍48🤪17❤9👌4🥰2🕊2👀1
ጄነራል ታደሰ ወረደ ወዴት ተሰወሩ❓
የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ በመቀሌ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መሰወራቸው ተሰማ። እስከ ማክሰኞ ጠዋት ድረስ መኖሪያ ቤታቸው በከፍተኛ ሁኔታ የሚጠበቅና በጥበቃ ተሽከርካሪዎች የተከበበ የነበረ ቢሆንም፣ ከማክሰኞ ምሽት ጀምሮ ግን አብረዋቸው የነበሩ ጥበቃዎችና ሰራተኞች ከአካባቢው ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል።
ጄነራሉ ከጥቂት ቀናት በፊት ከአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር እንዳይገናኙ በትግራይ ጸጥታ ቢሮ ተከልክለው እንደነበርና ቤተሰቦቻቸውም ስለ ደህንነታቸው ስጋት አድሮባቸው እንደነበር ይታወቃል።
ጄነራል ታደሰ ወረደ በፌደራል መንግሥት ዳግም በተሾሙ በጥቂት ቀናት ውስጥ በሕወሓት ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው የሚታወስ ነው። ከኃላፊነታቸው ከመነሳታቸው በፊትም ጊዜያዊ አስተዳደሩን በኃይል ለመገልበጥ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ክልሉን ወደ አዲስ ጦርነት እንደሚያስገባ አስጠንቅቀው ነበር።
በአሁኑ ወቅት በሕወሓት እና በፌደራል መንግሥት መካከል ያለው የፖለቲካ ውጥረት በጨመረበት ሁኔታ፣ የጄነራሉ ከአካባቢው መሰወር በትግራይ ክልል አዲስ የጸጥታ ስጋት ደቅኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ በመቀሌ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መሰወራቸው ተሰማ። እስከ ማክሰኞ ጠዋት ድረስ መኖሪያ ቤታቸው በከፍተኛ ሁኔታ የሚጠበቅና በጥበቃ ተሽከርካሪዎች የተከበበ የነበረ ቢሆንም፣ ከማክሰኞ ምሽት ጀምሮ ግን አብረዋቸው የነበሩ ጥበቃዎችና ሰራተኞች ከአካባቢው ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል።
ጄነራሉ ከጥቂት ቀናት በፊት ከአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር እንዳይገናኙ በትግራይ ጸጥታ ቢሮ ተከልክለው እንደነበርና ቤተሰቦቻቸውም ስለ ደህንነታቸው ስጋት አድሮባቸው እንደነበር ይታወቃል።
ጄነራል ታደሰ ወረደ በፌደራል መንግሥት ዳግም በተሾሙ በጥቂት ቀናት ውስጥ በሕወሓት ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው የሚታወስ ነው። ከኃላፊነታቸው ከመነሳታቸው በፊትም ጊዜያዊ አስተዳደሩን በኃይል ለመገልበጥ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ክልሉን ወደ አዲስ ጦርነት እንደሚያስገባ አስጠንቅቀው ነበር።
በአሁኑ ወቅት በሕወሓት እና በፌደራል መንግሥት መካከል ያለው የፖለቲካ ውጥረት በጨመረበት ሁኔታ፣ የጄነራሉ ከአካባቢው መሰወር በትግራይ ክልል አዲስ የጸጥታ ስጋት ደቅኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍3😢1🎉1🤪1
ለምክክር ጉባዔ መጥታ ወንድ ልጅ የተገላገለችው እናት የልጇን ሥም "ኮሚሽን" አለችዉ
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተወክላ በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች።
ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራዊ ምክክሩ ላይ በመሳተፍ ላይ የነበረች የጋምቤላ ክልል ተወካይዋ ወ/ሮ ክርኑዶ ኡጁሉ ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላ ስሙም "ምክክር" መባሉ የሚታወስ ነው።
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ የመጣችው ሌላኛዋ የምክክሩ ተሳታፊ ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ በተመሳሳይ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን፥ ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች።
የመውለጃ ጊዜዬ እየደረሰ መሆኑን ባውቅም ለኢትዮጵያዊያን አብሮነትና ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ በሚመከርበት በዚህ ጉባኤ መሳተፍ አለብኝ በሚል አቋም ተገኝቻለሁ ብላለች፡፡
በጉባኤው አጀንዳዎች ላይ ለሀገራችን ይበጃል የምትለውን ሀሳብ በመስጠት ንቁ ተሳትፎ ስታደርግ የቆየች ሲሆን፥ በዚህ ታሪካዊ ወቅት ልጇን በመገላገሏ መደሰቷን ገልጻለች።
ዘገባዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሚዲያ ነዉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተወክላ በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች።
ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራዊ ምክክሩ ላይ በመሳተፍ ላይ የነበረች የጋምቤላ ክልል ተወካይዋ ወ/ሮ ክርኑዶ ኡጁሉ ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላ ስሙም "ምክክር" መባሉ የሚታወስ ነው።
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ የመጣችው ሌላኛዋ የምክክሩ ተሳታፊ ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ በተመሳሳይ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን፥ ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች።
የመውለጃ ጊዜዬ እየደረሰ መሆኑን ባውቅም ለኢትዮጵያዊያን አብሮነትና ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ በሚመከርበት በዚህ ጉባኤ መሳተፍ አለብኝ በሚል አቋም ተገኝቻለሁ ብላለች፡፡
በጉባኤው አጀንዳዎች ላይ ለሀገራችን ይበጃል የምትለውን ሀሳብ በመስጠት ንቁ ተሳትፎ ስታደርግ የቆየች ሲሆን፥ በዚህ ታሪካዊ ወቅት ልጇን በመገላገሏ መደሰቷን ገልጻለች።
ዘገባዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሚዲያ ነዉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣70❤11😡6👍3