የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ‼️
ለሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መናር ዋነኛው ምክንያት የቡና ነጋዴዎች ናቸው ተባለ
ኢትዮጵያ ቀዳሚ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚታየው የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መጨመር ዋነኛው ምክንያት የቡና ላኪዎች ምርቱን በተጋነነ ዋጋ ማቅረባቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ሰፊሳ አባቡ ለመናኸሪያ ሬድዮ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ለውጭ ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት የተገኘው ገቢ ከፍተኛ ቢሆንም፣ በሀገር ውስጥ ገበያ ላይ ግን የዋጋ ጭማሪ ታይቷል።
ባለስልጣኑ በዘርፉ የቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ ከአለም አቀፍ የገበያ ተመን ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት እንዳለው አስረድተዋል።
ላኪዎች እርስ በርሳቸው በመነጋገር ተቀራራቢና የተረጋጋ ዋጋ እንዲያቀርቡ በተደጋጋሚ ቢነገራቸውም፤ ወዳልተገባ የዋጋ ሽሚያ በመግባታቸው ምክንያት በገበያው ላይ አለመረጋጋት መፈጠሩን ኃላፊው ገልጸዋል።
ይህ የዋጋ መጋነን የሀገሪቱን የቡና ዘርፍ ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ባለስልጣኑ ላኪዎችን በውይይት ለማስማማት ጥረት ማድረጉን ጠቅሰዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ለሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መናር ዋነኛው ምክንያት የቡና ነጋዴዎች ናቸው ተባለ
ኢትዮጵያ ቀዳሚ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚታየው የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መጨመር ዋነኛው ምክንያት የቡና ላኪዎች ምርቱን በተጋነነ ዋጋ ማቅረባቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ሰፊሳ አባቡ ለመናኸሪያ ሬድዮ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ለውጭ ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት የተገኘው ገቢ ከፍተኛ ቢሆንም፣ በሀገር ውስጥ ገበያ ላይ ግን የዋጋ ጭማሪ ታይቷል።
ባለስልጣኑ በዘርፉ የቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ ከአለም አቀፍ የገበያ ተመን ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት እንዳለው አስረድተዋል።
ላኪዎች እርስ በርሳቸው በመነጋገር ተቀራራቢና የተረጋጋ ዋጋ እንዲያቀርቡ በተደጋጋሚ ቢነገራቸውም፤ ወዳልተገባ የዋጋ ሽሚያ በመግባታቸው ምክንያት በገበያው ላይ አለመረጋጋት መፈጠሩን ኃላፊው ገልጸዋል።
ይህ የዋጋ መጋነን የሀገሪቱን የቡና ዘርፍ ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ባለስልጣኑ ላኪዎችን በውይይት ለማስማማት ጥረት ማድረጉን ጠቅሰዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤8👍5🥰1💯1
በኢትዮጵያ መካንነት ከፍተኛ የጤና ችግር እየሆነ መምጣቱ ተነገረ
የመካንነት ችግር በሴቶች ፣በወንዶች እንዲሁም በሁለቱም አጋሮች በጋራ ሊከሰት እንደሚችል የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ።በኢትዮጵያ የመካንነት ችግር ከሚጠበቀው በላይ ከፍተኛ መሆኑን በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት እንዲሁም የመካንነት ሰብ ስፔሻሊስት ሀኪም ዶክተር በላይ ቤተማሪያም ከብስራት ሬድዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል።
ከጥንዶች መካከል ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚሆኑት በዚህ ችግር እንደሚጠቁ ተናግረዋል።በኢንፌክሽን ምክኒያት የሚከሰት የማህፀን ቱቦ መዘጋት በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር 35 በመቶ ድርሻ እንዳለዉ ሰብ ስፔሻሊስቱ አስገንዝበዋል ።በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል ይችላል።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ 20 በመቶ የሚሆነው በወንድ በኩል የሚኖር መካንነት ነው።በጭንቅላት ውስጥ የሚመረት ሆርሞን ማነስ ፣በዘር ፍሬ ላይ የሚያጋጥም ስፐርም የማምረት ችግር ፣የወንድ የዘር ቱቦ መዘጋት እንዲሁም ምክንያቱ የማይታወቅ የወንድ መካንነት ዋና ዋናዎቹ መንስኤዎች ናቸው ።
የእንቁላል መፈጠር ወይም መለቀቅ ችግር ፤ በሆርሞን መዛባት ወይም በእድሜ ምክኒያት እንቁላል በወር አበባ ዑደት ውስጥ አዘውትሮ አለመፈጠር በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር ዋነኛቹ ምክኒያቶች መሆናቸውን ዶክተር በላይ አስረድተዋል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የመካንነት ችግር በሴቶች ፣በወንዶች እንዲሁም በሁለቱም አጋሮች በጋራ ሊከሰት እንደሚችል የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ።በኢትዮጵያ የመካንነት ችግር ከሚጠበቀው በላይ ከፍተኛ መሆኑን በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት እንዲሁም የመካንነት ሰብ ስፔሻሊስት ሀኪም ዶክተር በላይ ቤተማሪያም ከብስራት ሬድዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል።
ከጥንዶች መካከል ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚሆኑት በዚህ ችግር እንደሚጠቁ ተናግረዋል።በኢንፌክሽን ምክኒያት የሚከሰት የማህፀን ቱቦ መዘጋት በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር 35 በመቶ ድርሻ እንዳለዉ ሰብ ስፔሻሊስቱ አስገንዝበዋል ።በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል ይችላል።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ 20 በመቶ የሚሆነው በወንድ በኩል የሚኖር መካንነት ነው።በጭንቅላት ውስጥ የሚመረት ሆርሞን ማነስ ፣በዘር ፍሬ ላይ የሚያጋጥም ስፐርም የማምረት ችግር ፣የወንድ የዘር ቱቦ መዘጋት እንዲሁም ምክንያቱ የማይታወቅ የወንድ መካንነት ዋና ዋናዎቹ መንስኤዎች ናቸው ።
የእንቁላል መፈጠር ወይም መለቀቅ ችግር ፤ በሆርሞን መዛባት ወይም በእድሜ ምክኒያት እንቁላል በወር አበባ ዑደት ውስጥ አዘውትሮ አለመፈጠር በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር ዋነኛቹ ምክኒያቶች መሆናቸውን ዶክተር በላይ አስረድተዋል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19👍3😱1
የመብራት ታሪፍ‼️
👉ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት አዲስ የክፍያ ታሪፍ ጭማሪ ተደርጓል።
‹‹በኤሌክትሪክ ክፍያ ላይ የታየው ለውጥ አዲስ ጭማሪ ሳይሆን ቀድሞ የተወሰነ ማስተካከያ ሂደት ነው››-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ በደንበኞች ላይ የተደረገው የታሪፍ ማስተካከያ ክፍያ ቀደም ሲል በስትራቴጂው መሠረት የተወሰነ መሆኑን አስታዉቋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሽያጭና ደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ይኸይስ ስዩም ለኢትዮ ኤፍኤም 107.8 እንደገለጹት፤ በ2017 ዓ.ም መስከረም ወር ላይ የተጀመረው የታሪፍ ማሻሻያ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ በ24 የሩብ ዓመታት ተከፋፍሎ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ይህ የታሪፍ ማስተካከያ ተቋሙ ከአራት ዓመት በኋላ የሚሰበሰበውን አጠቃላይ ክፍያ በመስከረም 2017 ዓ.ም ላይ በአንድ ጊዜ ማስከፈል የነበረበት ቢሆንም፣ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ታሳቢ በማድረግ በጥቂት በጥቂቱ ከፋፍሎ እንዲከፍል የተዘረጋ ስትራቴጂ ነው በማለት ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ ያለው ታሪፍ ዝቅተኛውን የኅብረተሰብ ክፍል በልዩ ሁኔታ ለመደገፍ የመንግሥት ድጎማ የሚደረግበት ነው ያሉ ሲሆን፣ እስከ 50 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት 96 ሳንቲም ብቻ እንዲከፍሉ እየተደረገ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዶ/ር ይኸይስ አክለውም፤ እስከ 2መቶ ኪሎ ዋት የሚጠቀም ማንኛውም ደንበኛ በትክክለኛው የታሪፍ ዋጋ ሳይሆን በድጎማ እንዲከፍል እየተደረገ ነው ብለዋል።
ደንበኞች በአንድ ወር ውስጥ በተደጋጋሚ ኃይል ሲገዙ ስለሚገጥማቸው የዋጋ ልዩነት ሲያብራሩም፤ የዋጋ አተማመን ሥርዓቱ በ30 ቀናት ውስጥ የተጠቀሙትን አጠቃላይ የኃይል መጠን በአንድ ላይ ደምሮ ስለሚያሰላው የኪሎ ዋት መጠኑ ሲጨምር ታሪፉም አብሮ እንደሚጨምር አስገንዝበዋል።
ይህንን ሁኔታ ተከትሎ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ተቋሙ በየክፍለ ከተማው ከነዋሪዎች ጋር ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶችን እያደረገ ሲሆን፣ ባለፉት 15 ቀናት ውስጥም ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለሚዲያ አካላት ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👉ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት አዲስ የክፍያ ታሪፍ ጭማሪ ተደርጓል።
‹‹በኤሌክትሪክ ክፍያ ላይ የታየው ለውጥ አዲስ ጭማሪ ሳይሆን ቀድሞ የተወሰነ ማስተካከያ ሂደት ነው››-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ በደንበኞች ላይ የተደረገው የታሪፍ ማስተካከያ ክፍያ ቀደም ሲል በስትራቴጂው መሠረት የተወሰነ መሆኑን አስታዉቋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሽያጭና ደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ይኸይስ ስዩም ለኢትዮ ኤፍኤም 107.8 እንደገለጹት፤ በ2017 ዓ.ም መስከረም ወር ላይ የተጀመረው የታሪፍ ማሻሻያ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ በ24 የሩብ ዓመታት ተከፋፍሎ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ይህ የታሪፍ ማስተካከያ ተቋሙ ከአራት ዓመት በኋላ የሚሰበሰበውን አጠቃላይ ክፍያ በመስከረም 2017 ዓ.ም ላይ በአንድ ጊዜ ማስከፈል የነበረበት ቢሆንም፣ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ታሳቢ በማድረግ በጥቂት በጥቂቱ ከፋፍሎ እንዲከፍል የተዘረጋ ስትራቴጂ ነው በማለት ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ ያለው ታሪፍ ዝቅተኛውን የኅብረተሰብ ክፍል በልዩ ሁኔታ ለመደገፍ የመንግሥት ድጎማ የሚደረግበት ነው ያሉ ሲሆን፣ እስከ 50 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት 96 ሳንቲም ብቻ እንዲከፍሉ እየተደረገ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዶ/ር ይኸይስ አክለውም፤ እስከ 2መቶ ኪሎ ዋት የሚጠቀም ማንኛውም ደንበኛ በትክክለኛው የታሪፍ ዋጋ ሳይሆን በድጎማ እንዲከፍል እየተደረገ ነው ብለዋል።
ደንበኞች በአንድ ወር ውስጥ በተደጋጋሚ ኃይል ሲገዙ ስለሚገጥማቸው የዋጋ ልዩነት ሲያብራሩም፤ የዋጋ አተማመን ሥርዓቱ በ30 ቀናት ውስጥ የተጠቀሙትን አጠቃላይ የኃይል መጠን በአንድ ላይ ደምሮ ስለሚያሰላው የኪሎ ዋት መጠኑ ሲጨምር ታሪፉም አብሮ እንደሚጨምር አስገንዝበዋል።
ይህንን ሁኔታ ተከትሎ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ተቋሙ በየክፍለ ከተማው ከነዋሪዎች ጋር ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶችን እያደረገ ሲሆን፣ ባለፉት 15 ቀናት ውስጥም ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለሚዲያ አካላት ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡21❤15👍3💊2👌1🥱1👀1🙉1
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ – የሚፈልጓቸውን አዳዲስ ዜናዎችን በአጭሩ እና በጥልቀት ከኛ ዘንድ ያንብቡ።
🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።
🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።
አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy
@sputnik_ethiopia
🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።
🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።
አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy
@sputnik_ethiopia
👍3❤1
የምግብ ዋጋ ግሽበት 15.1 በመቶ ደረሰ
የሰኔ ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 13.9 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 15.1 በመቶ የጨመረ ሲሆን በዋናነት አትክልት፣ ስጋ ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ አሳይተዋል።
ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 12.2 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንስፖርት 14.3 በመቶ፣ አልኮል መጠጦችና ትምባሆ 14.5 በመቶ፣ በኮሙዩኒኬሸን 8.9 በመቶ ፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች 12.0 በመቶ እንዲሁም ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች 17.9 በመቶ ሆነው ተመዝግበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሰኔ ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 13.9 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 15.1 በመቶ የጨመረ ሲሆን በዋናነት አትክልት፣ ስጋ ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ አሳይተዋል።
ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 12.2 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንስፖርት 14.3 በመቶ፣ አልኮል መጠጦችና ትምባሆ 14.5 በመቶ፣ በኮሙዩኒኬሸን 8.9 በመቶ ፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች 12.0 በመቶ እንዲሁም ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች 17.9 በመቶ ሆነው ተመዝግበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢11👍6❤3🤪1
አሜሪካ ወደ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈች
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍5
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ዘንድሮ ክልል አቀፉን የ8ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ 85,531 ተማሪዎች 83,342 ተማሪዎች ወይም 97.4 በመቶ ማለፋቸውን አሳውቋል።
ከ1,538 ት/ቤቶች ውስጥ 1,017 ትምህርት ቤቶች ሁሉንም ተማሪዎቻቸውን እንዳሳለፉም ያሳወቀው ክልሉ አንድም ትምህርት ቤት ተማሪ ያላሳለፈ የለም ብሏል።
ሌላው የዘንድሮው ውጤት ከ2017 ዓ.ም ጋር ሲነጻጸር በ61.5 በመቶ መሻሻሉንም ጠቁሟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከ1,538 ት/ቤቶች ውስጥ 1,017 ትምህርት ቤቶች ሁሉንም ተማሪዎቻቸውን እንዳሳለፉም ያሳወቀው ክልሉ አንድም ትምህርት ቤት ተማሪ ያላሳለፈ የለም ብሏል።
ሌላው የዘንድሮው ውጤት ከ2017 ዓ.ም ጋር ሲነጻጸር በ61.5 በመቶ መሻሻሉንም ጠቁሟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11🤣10👍4
በአከራይ ተከራይ ውል መፈጸም የሌለባቸው እና የተከለከሉ ተግባራት...
በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው።
👉የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት፤
👉በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል በአዋጁ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዝገብ፤
👉የመኖሪ ቤት ኪራይ ውል እድሳት አለማስመዝገብ፤
👉በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤
👉አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤
👉በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤
👉አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ እንዲፈፀም ማስገደድ፤
👉 በባንክ ወይሞ በሌላ ሕጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ስርዓት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈፀም
👉 ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ እና ፤
👉በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ ለመጠቀሞ ሀሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ የተከለከለ መሆኑን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው።
👉የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት፤
👉በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል በአዋጁ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዝገብ፤
👉የመኖሪ ቤት ኪራይ ውል እድሳት አለማስመዝገብ፤
👉በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤
👉አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤
👉በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤
👉አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ እንዲፈፀም ማስገደድ፤
👉 በባንክ ወይሞ በሌላ ሕጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ስርዓት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈፀም
👉 ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ እና ፤
👉በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ ለመጠቀሞ ሀሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ የተከለከለ መሆኑን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤18😡7👍2
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት፣ አስፈላጊ ማስረጃዎችን ያላሟሉ የመንግሥት ሠራተኞችን ደመወዝ እንደሚያቋርጥ አስጠነቀቀ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ የፈረሙበት ደብዳቤ፤ ከሚያዝያ ጀምሮ በመንግሥት ሠራተኞች የትምህርትና ሌሎች ማስረጃዎች ላይ ማጣራት ሲደረግ መቆየቱንና የሠራተኞች የትምህርት ማስረጃዎችና ተያያዥ መረጃዎች ተደራጅተው አለመገኘታቸውን ጠቅሷል፡፡ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በአካል ቀርቦ አስፈላጊ መረጃዎችን እስከ ሐምሌ 30 ቀን ድረስ ሞልቶ ማጠናቀቅ እንዳለበትም የክልሉ መንግሥት አሳስቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤6👍2
የ20 ዓመት ሴት ልጅ የገዛ ልጁን አስገድዶ ግብረ ስጋ ግንኘነት ያደረገው አባት በእስራት ተቀጣ
ሐምሌ 14, 2018 ዓ.ም ምዕራብ ዓባያ ወረዳ።
በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ብርብር ከተማ መንደር ሰባት ነዋሪ የሆኑት ኢንስፐክተር ግርማ ጌታቸው እና ከወ/ሮ መስከረም ሙሉጌታ የተወለደችው ልጅ ሐና ግርማ ዕድሜዋ 20 ዓመት የደረሰና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን መንግሥት ባስታጠቀው ሽጉጥ በማስፈራራት በቀን 6/9/2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ቡና እያፈለች ባለችበት ኳላ በመምጣት በጉልበት ወደ መኝታ ክፍል በማምራት የለበሰችሁን ቀምስ በማወለቅ ክብረ ንጽህና በመገርሰስ በጉልበት የግብረ ስጋ ግንኙነት ሲፈፅም ልጅቷ ባሰማችው የድረሱልኝ ጥሪ ጎረቤት በመሰማት መደፈራዋን ከአንደበቷ ሰምተው ሲያረጋግጡ ለፖሊስ ጥቆማ በማድረግ የማጣራት ስራ በመስራት በህግ ሲታይ ቆይቶ የምዕራብ አባያ ወረዳ ፍ/ቤት በተከሳሹ ላይ በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት 9 ዓመት ከ3 ወር ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል ሲል ምዕራብ ዓባያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው የዘገበው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ሐምሌ 14, 2018 ዓ.ም ምዕራብ ዓባያ ወረዳ።
በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ብርብር ከተማ መንደር ሰባት ነዋሪ የሆኑት ኢንስፐክተር ግርማ ጌታቸው እና ከወ/ሮ መስከረም ሙሉጌታ የተወለደችው ልጅ ሐና ግርማ ዕድሜዋ 20 ዓመት የደረሰና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን መንግሥት ባስታጠቀው ሽጉጥ በማስፈራራት በቀን 6/9/2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ቡና እያፈለች ባለችበት ኳላ በመምጣት በጉልበት ወደ መኝታ ክፍል በማምራት የለበሰችሁን ቀምስ በማወለቅ ክብረ ንጽህና በመገርሰስ በጉልበት የግብረ ስጋ ግንኙነት ሲፈፅም ልጅቷ ባሰማችው የድረሱልኝ ጥሪ ጎረቤት በመሰማት መደፈራዋን ከአንደበቷ ሰምተው ሲያረጋግጡ ለፖሊስ ጥቆማ በማድረግ የማጣራት ስራ በመስራት በህግ ሲታይ ቆይቶ የምዕራብ አባያ ወረዳ ፍ/ቤት በተከሳሹ ላይ በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት 9 ዓመት ከ3 ወር ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል ሲል ምዕራብ ዓባያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው የዘገበው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
💔30😡23🙉9❤8👍2😱2🤯1😢1👀1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የጦርነት ድባብ እየተሰማ ነው‼️
በትግራይ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ከባለፈው እሁድ ጀምሮ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
ህዝቡ እና ወጣቱ ለጦርነት እንዲዘጋጅ ከሁሉም አመራሮች በግልጽ እየተነገራቸው ይገኛል።
የህወሓት ዋና ፀሃፊ የሆኑት ፈትለወርቅ (ሞንጀሪኖ) ባካሄዱበት ስብሰባ ላይ "አዲስ አበባ እስክንገባ ብቻችን እንሸከመዋለን ማለት አይደለም፥ ብዙ አጋሮች አሉን ። አዲስ አበባ በር ላይ ፋኖ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አለ ስለዚህ ብዙ ወዳጆች አሉን” ሲሉ ተደምጠዋል።
ሰላም ለሀገራችን🕊🕊
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በትግራይ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ከባለፈው እሁድ ጀምሮ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
ህዝቡ እና ወጣቱ ለጦርነት እንዲዘጋጅ ከሁሉም አመራሮች በግልጽ እየተነገራቸው ይገኛል።
የህወሓት ዋና ፀሃፊ የሆኑት ፈትለወርቅ (ሞንጀሪኖ) ባካሄዱበት ስብሰባ ላይ "አዲስ አበባ እስክንገባ ብቻችን እንሸከመዋለን ማለት አይደለም፥ ብዙ አጋሮች አሉን ። አዲስ አበባ በር ላይ ፋኖ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አለ ስለዚህ ብዙ ወዳጆች አሉን” ሲሉ ተደምጠዋል።
ሰላም ለሀገራችን🕊🕊
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤46👍12🫡6🤣5🙉5🤯4🕊4👀1🙊1
እየተባባሰ የመጣው የኦንላይን ማጭበርበር
በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰው እፈልጋለሁ " በሚሉ መልዕክቶች ተጠቃሚዎችን በማታለል እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ እያሳጡ መሆናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ እንዳሉት፣ አጭበርባሪዎቹ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ቴሌግራምን በመጠቀም የውሸት ማንነት በመፍጠር ተጎጂዎችን ያጠምዳሉ።
" ሀብታም ነኝ "፣ " ከሁሉም አንተን/አንቺን መርጫለሁ " የሚሉ መልዕክቶችም ከሚጠቀሙባቸው የማጭበርበሪያ ስልቶች መካከል ናቸው።
ከተጎጂዎች ጋር ግንኙነታቸውን ካጠናከሩ በኋላ፣ ሌላ ሰው በተለየ ስልክ ቁጥር በመደወል " የላክነው ዕቃ ጉምሩክ ደርሷል፤ ነገር ግን ዶላር ወይም ወርቅ ስላለበት ክፍያ ያስፈልጋል " በማለት የታሸገ ዕቃ ፎቶ በመላክ ገንዘብ እንዲልኩ እንደሚያደርጉ ተገልጿል።
በዚህ ሂደት ከ500 ሺህ እና ከዛ በላይ ገንዘብ ሰዎች እንደሚጭበረበሩ አመልክተዋል።
ወ/ሮ እጣወርቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች " ከሁሉም ሰው እኔ ለምን ተመረጥኩ ? " እና " ለስጦታ እንዴት ክፍያ ይጠየቃል ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ራሳቸውን በመጠየቅ ከመሰል ማጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል።
የኦንላይን ማጭበርበር ወንጀል እየተስፋፋ ሲሆን፣ ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ጉዳት ያስከተሉ ከ80 በላይ ዋና ዋና የክስ መዝገቦች በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ መመስረታቸው ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰው እፈልጋለሁ " በሚሉ መልዕክቶች ተጠቃሚዎችን በማታለል እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ እያሳጡ መሆናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ እንዳሉት፣ አጭበርባሪዎቹ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ቴሌግራምን በመጠቀም የውሸት ማንነት በመፍጠር ተጎጂዎችን ያጠምዳሉ።
" ሀብታም ነኝ "፣ " ከሁሉም አንተን/አንቺን መርጫለሁ " የሚሉ መልዕክቶችም ከሚጠቀሙባቸው የማጭበርበሪያ ስልቶች መካከል ናቸው።
ከተጎጂዎች ጋር ግንኙነታቸውን ካጠናከሩ በኋላ፣ ሌላ ሰው በተለየ ስልክ ቁጥር በመደወል " የላክነው ዕቃ ጉምሩክ ደርሷል፤ ነገር ግን ዶላር ወይም ወርቅ ስላለበት ክፍያ ያስፈልጋል " በማለት የታሸገ ዕቃ ፎቶ በመላክ ገንዘብ እንዲልኩ እንደሚያደርጉ ተገልጿል።
በዚህ ሂደት ከ500 ሺህ እና ከዛ በላይ ገንዘብ ሰዎች እንደሚጭበረበሩ አመልክተዋል።
ወ/ሮ እጣወርቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች " ከሁሉም ሰው እኔ ለምን ተመረጥኩ ? " እና " ለስጦታ እንዴት ክፍያ ይጠየቃል ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ራሳቸውን በመጠየቅ ከመሰል ማጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል።
የኦንላይን ማጭበርበር ወንጀል እየተስፋፋ ሲሆን፣ ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ጉዳት ያስከተሉ ከ80 በላይ ዋና ዋና የክስ መዝገቦች በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ መመስረታቸው ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤3👍3👀2
የነዳጅ ቦቴ ባለንብረቶች ከገበያ ልንወጣ እንችላለን ሲሉ ስጋታቸውን ገለጹ
በሀገሪቱ እየታየ ያለው የመለዋወጫ እቃዎች ዋጋ መናር እና የታሪፍ ማሻሻያ አለመደረግ አክሳሪ እንደሆነባቸው የገለጹት የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች፣ ችግሩ ባልተፈታበት ሁኔታ ስራቸውን ማስቀጠል አስቸጋሪ እንደሆነባቸው በመግለጽ ከገበያው የመወጣት ስጋት እንደደቀነባቸው አስታወቁ።
የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር የነዳጅ ፍላጎት እድገትን እና የወጡ ወጪዎችን ያገናዘበ የታሪፍ ማሻሻያ እንዲደረግ ተደጋጋሚ ጥናቶችን ማቅረቡን ያስታወሰ ቢሆንም፣ በመንግስት በኩል ግን እስካሁን አዎንታዊ ምላሽ ማግኘት አለመቻሉን ገልጿል።
የማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ ፀጋ አስማረ እንደገለጹት፤ ጥናቱ ዝም ብሎ የቀረበ ሳይሆን ከነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን፣ ከትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር እንዲሁም ከንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተወጣጡ ባለሙያዎች ጋር በጥጋቢ ሁኔታ ተጠናቆ የቀረበ ነው። ሆኖም ምላሽ በመዘግየቱ አባላቱ ለአላስፈላጊ ክሳራ መዳረጋቸውን አብራርተዋል።
ከታሪፍ መዘገየት በተጨማሪ ባለንብረቶች ሌላ አጣብቂኝ ውስጥ የከተታቸው አሽከርካሪዎች ከባለንብረቱ እውቅና ውጪ በሚፈጽሙት የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ምክንያት ተሽከርካሪዎች እና ነዳጅ የመወረስ እርምጃ እየተወሰደባቸው ይገኛል ብለዋል።
ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ትራንስፖርት ባለንብረቶች ማህበር አባላቱን በመጥራት በዘርፉ በተደቀኑ ዘርፈ-ብዙ ችግሮች እና በቀጣይ የጋራ አቋሞች ዙሪያ የምክክር ስብሰባ አካሂዷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሀገሪቱ እየታየ ያለው የመለዋወጫ እቃዎች ዋጋ መናር እና የታሪፍ ማሻሻያ አለመደረግ አክሳሪ እንደሆነባቸው የገለጹት የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች፣ ችግሩ ባልተፈታበት ሁኔታ ስራቸውን ማስቀጠል አስቸጋሪ እንደሆነባቸው በመግለጽ ከገበያው የመወጣት ስጋት እንደደቀነባቸው አስታወቁ።
የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር የነዳጅ ፍላጎት እድገትን እና የወጡ ወጪዎችን ያገናዘበ የታሪፍ ማሻሻያ እንዲደረግ ተደጋጋሚ ጥናቶችን ማቅረቡን ያስታወሰ ቢሆንም፣ በመንግስት በኩል ግን እስካሁን አዎንታዊ ምላሽ ማግኘት አለመቻሉን ገልጿል።
የማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ ፀጋ አስማረ እንደገለጹት፤ ጥናቱ ዝም ብሎ የቀረበ ሳይሆን ከነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን፣ ከትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር እንዲሁም ከንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተወጣጡ ባለሙያዎች ጋር በጥጋቢ ሁኔታ ተጠናቆ የቀረበ ነው። ሆኖም ምላሽ በመዘግየቱ አባላቱ ለአላስፈላጊ ክሳራ መዳረጋቸውን አብራርተዋል።
ከታሪፍ መዘገየት በተጨማሪ ባለንብረቶች ሌላ አጣብቂኝ ውስጥ የከተታቸው አሽከርካሪዎች ከባለንብረቱ እውቅና ውጪ በሚፈጽሙት የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ምክንያት ተሽከርካሪዎች እና ነዳጅ የመወረስ እርምጃ እየተወሰደባቸው ይገኛል ብለዋል።
ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ትራንስፖርት ባለንብረቶች ማህበር አባላቱን በመጥራት በዘርፉ በተደቀኑ ዘርፈ-ብዙ ችግሮች እና በቀጣይ የጋራ አቋሞች ዙሪያ የምክክር ስብሰባ አካሂዷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤5👍4
አስቸኳይ መረጃ ‼️
በመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ላይ የተከለከሉ ዋና ዋና ተግባራት ይፋ ሆኑ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል አፈጻጸም ላይ በአከራዮችና በተከራዮች ዘንድ የተከለከሉ ተግባራትን አስመልካች መረጃ ይፋ አድርጓል።
እንደ ቢሮው ማስታወቂያ፤ በሁለቱ ወገኖች መካከል በሚደረግ ማንኛውም የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ውስጥ የሚከተሉትን ድርጊቶች መፈጸም በሕግ የተከለከለ ነው፡
❌ በሕግ የተከለከሉ ተግባራት፡
1 ያለ ውል ማከራየት፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየት እና ማከራየት፤
2 የጊዜ ገደብ ማሳለፍ፡ በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የኪራይ ውሉን በአዋጁ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዘገብ፤
3 ውል አለማደስ፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እድሳትን በወቅቱ አለማስመዘገብ፤
4 ሕገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪ፡ በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤
5 ያለጊዜው ከቤት ማስወጣት፡ በአዋጁ ከሚፈቀደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ተከራይን ከቤት ማስወጣት፤
6 ያለ ማስጠንቀቂያ ውል ማቋረጥ፡ በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጡ ውል ማቋረጥ፤
7 ከመጠን በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ፡ በአዋጁ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ (አድቫንስ) እንዲፈጸም ማስገደድ፤
8 በጥሬ ገንዘብ ክፍያ መፈጸም፡ የቤት ኪራይ ክፍያን በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ (ዲጂታል) መንገድ አለመፈጸም፤
9 ቤትን ያለ አገልግሎት ባዶውን ማስቀመጥ፡ ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየን የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ ቤትን ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ፤
10 ሐሰተኛ መረጃ ማቅረብ፡ በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ ለመጠቀም ሐሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ።
መረጃው ለአከራዮችና ለተከራዮች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ይተባበሩ!
Via የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ላይ የተከለከሉ ዋና ዋና ተግባራት ይፋ ሆኑ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል አፈጻጸም ላይ በአከራዮችና በተከራዮች ዘንድ የተከለከሉ ተግባራትን አስመልካች መረጃ ይፋ አድርጓል።
እንደ ቢሮው ማስታወቂያ፤ በሁለቱ ወገኖች መካከል በሚደረግ ማንኛውም የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ውስጥ የሚከተሉትን ድርጊቶች መፈጸም በሕግ የተከለከለ ነው፡
❌ በሕግ የተከለከሉ ተግባራት፡
1 ያለ ውል ማከራየት፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየት እና ማከራየት፤
2 የጊዜ ገደብ ማሳለፍ፡ በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የኪራይ ውሉን በአዋጁ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዘገብ፤
3 ውል አለማደስ፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እድሳትን በወቅቱ አለማስመዘገብ፤
4 ሕገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪ፡ በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤
5 ያለጊዜው ከቤት ማስወጣት፡ በአዋጁ ከሚፈቀደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ተከራይን ከቤት ማስወጣት፤
6 ያለ ማስጠንቀቂያ ውል ማቋረጥ፡ በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጡ ውል ማቋረጥ፤
7 ከመጠን በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ፡ በአዋጁ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ (አድቫንስ) እንዲፈጸም ማስገደድ፤
8 በጥሬ ገንዘብ ክፍያ መፈጸም፡ የቤት ኪራይ ክፍያን በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ (ዲጂታል) መንገድ አለመፈጸም፤
9 ቤትን ያለ አገልግሎት ባዶውን ማስቀመጥ፡ ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየን የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ ቤትን ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ፤
10 ሐሰተኛ መረጃ ማቅረብ፡ በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ ለመጠቀም ሐሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ።
መረጃው ለአከራዮችና ለተከራዮች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ይተባበሩ!
Via የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13👍8✍1🥰1👌1
ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት የ2 ዓመት ህፃን እንዳትጮህ አፉን በማፈን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
በአሶሳ ዞን ባምባሲ ወረዳ ኤዳ ዳቡስ ቀበሌ ጎጥ አንድ በሚባል አካባቢ ነው የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ተከሳሽ አወድ አልሀሪብ የተባለ ሲሆን ግንቦት 16 ቀን 2018 ከረፍዱ 4፡00 ሰዓት የወንጀል ድርጊቱን ፈፅሟል።
የ2 አመት ህፃን የሆነችውን ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት እናቷ ውሃ ልትቀዳ መሄዷን በማረጋገጥ ወደ ራሱ መኖሪያ ቤት ከወሰዳት በኋላ አፏን በማፈን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀሙን ተናግረዋል፡፡
የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች በማስደገፍ ለዐቃቤ ህግ ያቀርባል ዐቃቤ ህጉም ተከሳሹ በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 627(1) ስር በተደነገገው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ክስ በመመስረት ለባምባሲ ወረዳ ፍርድ ቤት ያቀርባል፡፡
ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተከሳሹን ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ የወንጀሉን ክብደትና የቅጣት ማክበጃ እና ማቅለያ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው ችሎት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲሉ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአሶሳ ዞን ባምባሲ ወረዳ ኤዳ ዳቡስ ቀበሌ ጎጥ አንድ በሚባል አካባቢ ነው የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ተከሳሽ አወድ አልሀሪብ የተባለ ሲሆን ግንቦት 16 ቀን 2018 ከረፍዱ 4፡00 ሰዓት የወንጀል ድርጊቱን ፈፅሟል።
የ2 አመት ህፃን የሆነችውን ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት እናቷ ውሃ ልትቀዳ መሄዷን በማረጋገጥ ወደ ራሱ መኖሪያ ቤት ከወሰዳት በኋላ አፏን በማፈን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀሙን ተናግረዋል፡፡
የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች በማስደገፍ ለዐቃቤ ህግ ያቀርባል ዐቃቤ ህጉም ተከሳሹ በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 627(1) ስር በተደነገገው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ክስ በመመስረት ለባምባሲ ወረዳ ፍርድ ቤት ያቀርባል፡፡
ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተከሳሹን ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ የወንጀሉን ክብደትና የቅጣት ማክበጃ እና ማቅለያ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው ችሎት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲሉ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡17💔13❤12🤯3👍2😱2😢1
አሜሪካ ለኢትዮጵያ የስንዴ እና ማሽላ እርዳታ ላከች
የአሜሪካ መንግሥት ወደ 47,000 ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ የምግብ እህል የጫነ የጭነት መርከብ ወደ ኢትዮጵያ እየተጓዘ መሆኑን አስታወቀ።
በ”ሰላም ለምግብ” መርሃ ግብር የተላከው ይህ እርዳታ 37,700 ቶን ማሽላ እና 9,200 ቶን ስንዴን ያካተተ ነው።
ይህ እርዳታ የተላከው የኢትዮጵያ መንግሥት በስንዴ ምርት ራሱን መቻሉን እና ወደ ውጭ መላክ መጀመሩን በተደጋጋሚ ከገለጸበት ማግስት ነው።
ይሁን እንጂ፣ የአሜሪካ የግብርና መምሪያ በቅርቡ ይፋ ባደረገው ሪፖርት፣ የኢትዮጵያ የስንዴ ፍላጎት በየጊዜው እያደገ በመሆኑ፣ ሀገሪቱ አሁንም ወደ 1.4 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ የስንዴ ምርት ከውጭ ማስመጣት እንደምትፈልግ ያሳያል።
ከዚህ በተጨማሪ፣ በግጭት፣ በመፈናቀል እና በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በኢትዮጵያ የሰብአዊ እርዳታ ፍላጎት አሁንም ከፍተኛ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ይህ የአሜሪካ እርዳታ የሀገሪቱን የስንዴ ራስን የመቻል ጥያቄዎች እና የሰብአዊ ድጋፍ አስፈላጊነትን ዳግም አነጋጋሪ አድርጎታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአሜሪካ መንግሥት ወደ 47,000 ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ የምግብ እህል የጫነ የጭነት መርከብ ወደ ኢትዮጵያ እየተጓዘ መሆኑን አስታወቀ።
በ”ሰላም ለምግብ” መርሃ ግብር የተላከው ይህ እርዳታ 37,700 ቶን ማሽላ እና 9,200 ቶን ስንዴን ያካተተ ነው።
ይህ እርዳታ የተላከው የኢትዮጵያ መንግሥት በስንዴ ምርት ራሱን መቻሉን እና ወደ ውጭ መላክ መጀመሩን በተደጋጋሚ ከገለጸበት ማግስት ነው።
ይሁን እንጂ፣ የአሜሪካ የግብርና መምሪያ በቅርቡ ይፋ ባደረገው ሪፖርት፣ የኢትዮጵያ የስንዴ ፍላጎት በየጊዜው እያደገ በመሆኑ፣ ሀገሪቱ አሁንም ወደ 1.4 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ የስንዴ ምርት ከውጭ ማስመጣት እንደምትፈልግ ያሳያል።
ከዚህ በተጨማሪ፣ በግጭት፣ በመፈናቀል እና በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በኢትዮጵያ የሰብአዊ እርዳታ ፍላጎት አሁንም ከፍተኛ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ይህ የአሜሪካ እርዳታ የሀገሪቱን የስንዴ ራስን የመቻል ጥያቄዎች እና የሰብአዊ ድጋፍ አስፈላጊነትን ዳግም አነጋጋሪ አድርጎታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣74❤12🌚5🤩3👍2🙏1
የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናን ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ ተመዛኞች በሙሉ
የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ ጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2018 ዓ.ም የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለመስጠት ተመዛኞች ከሰኔ 30/2018ዓ.ም ጀምሮ መረጃችሁን በማስተሳሰር ላይ እንደምትገኙ ይታወቃል፡፡
ስለዚህም መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ማስተሳሰር የምትችሉት እስከ ሃምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑን ተገንዝባችሁ ይህንን https://hple.moh.gov.et/ ማስፈንጠሪያ/Link/ በመጫን የብሄራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (National ID FAN 16 Digit) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
▪ ይህ መረጃን የማስተሳሰር ሂደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሂደት እንደሚቀጥል እናሳውቃለን፡፡
▪ በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን የሚጠበቅባችሁ መሆኑን አሳስቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ ጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2018 ዓ.ም የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለመስጠት ተመዛኞች ከሰኔ 30/2018ዓ.ም ጀምሮ መረጃችሁን በማስተሳሰር ላይ እንደምትገኙ ይታወቃል፡፡
ስለዚህም መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ማስተሳሰር የምትችሉት እስከ ሃምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑን ተገንዝባችሁ ይህንን https://hple.moh.gov.et/ ማስፈንጠሪያ/Link/ በመጫን የብሄራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (National ID FAN 16 Digit) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
▪ ይህ መረጃን የማስተሳሰር ሂደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሂደት እንደሚቀጥል እናሳውቃለን፡፡
▪ በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን የሚጠበቅባችሁ መሆኑን አሳስቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤5👍2
ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ታጥረው የተተዉ መሬቶች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ታጥረው ያለምንም አገልግሎት የተቀመጡ መሬቶችን በማጣራት በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል።
ከንቲባዋ ይህን ያስታወቁት፣ በከተማ አስተዳደሩ የአምስት ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድና የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ነው።
እንደ ከንቲባዋ ገለጻ፣ አዲስ አበባ መሬት ታጥሮ የሚቀመጥባት ከተማ መሆን እንደሌለባት ቀደም ሲል የተደረሰውን ስምምነት የሚጥሱ አካላት ተጨማሪ ዕድል እንደማይሰጣቸው አስጠንቅቀዋል።
በሌላ በኩል፣ በከተማዋ የሰላምና ደህንነት ሁኔታ የተረጋጋ መሆኑን በመግለጽ፣ በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶች ያለ የደህንነት ችግር በሰላም መጠናቀቃቸውን አስታውሰዋል።
በተጨማሪም፣ የከተማዋ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት መዘመኑ ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው፣ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጥናት መሠረት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በአፍሪካ ከተመረጡ ስድስት ምርጥ ከተሞች መካከል በአሠራር ደረጃ አንደኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አክለውም፣ በጤናው ዘርፍ የሕክምና ባለሙያዎች የሙያ ሥነ-ምግባርና የአገልግሎት ጥራት መሻሻሉን፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ የጤና አገልግሎትና የመሠረተ ልማት ሥራዎችም ከቀደሙት ዓመታት ጋር ሲነጻጸሩ በእጥፍ መጨመራቸውን ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ታጥረው ያለምንም አገልግሎት የተቀመጡ መሬቶችን በማጣራት በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል።
ከንቲባዋ ይህን ያስታወቁት፣ በከተማ አስተዳደሩ የአምስት ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድና የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ነው።
እንደ ከንቲባዋ ገለጻ፣ አዲስ አበባ መሬት ታጥሮ የሚቀመጥባት ከተማ መሆን እንደሌለባት ቀደም ሲል የተደረሰውን ስምምነት የሚጥሱ አካላት ተጨማሪ ዕድል እንደማይሰጣቸው አስጠንቅቀዋል።
በሌላ በኩል፣ በከተማዋ የሰላምና ደህንነት ሁኔታ የተረጋጋ መሆኑን በመግለጽ፣ በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶች ያለ የደህንነት ችግር በሰላም መጠናቀቃቸውን አስታውሰዋል።
በተጨማሪም፣ የከተማዋ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት መዘመኑ ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው፣ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጥናት መሠረት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በአፍሪካ ከተመረጡ ስድስት ምርጥ ከተሞች መካከል በአሠራር ደረጃ አንደኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አክለውም፣ በጤናው ዘርፍ የሕክምና ባለሙያዎች የሙያ ሥነ-ምግባርና የአገልግሎት ጥራት መሻሻሉን፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ የጤና አገልግሎትና የመሠረተ ልማት ሥራዎችም ከቀደሙት ዓመታት ጋር ሲነጻጸሩ በእጥፍ መጨመራቸውን ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20🤪4🤣3👍2🤔1
" ከሰሞኑን ለ15 ቀናት በቆየ ኦፕሬሽን በአዲስ አበባ፣ በሐረሪና በሌሎች አካባቢዎች ነው የተያዙት " - አቶ ጃይላን አብዲ
"እጅግ አደገኛ ናቸው" የተባሉ ሰው አዘዋዋሪዎች መያዛቸውን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ " ከ60 በላይ ስደተኞች ለሞት እና በርካታ ሴቶች ለመደፈር ተጠያቂ ናቸው " ያላቸውን አደገኛ 17 ተጠርጣሪ የሰዎች አዘዋዋሪዎች መያዙን አስታውቋል።
ፖሊስ እንደገለጸው፣ በ"መሐመድ ጣሂር አደም (ወርዲ)" የሚመራው ቡድን ሰዎችን ከኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በደላሎች አማካኝነት በመልመል በጂቡቲና በየመን በኩል በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ያዘዋውር ነበር።
እነዚህ አደገኛ የሰው አዘዋዋሪዎች ከ40,000 በላይ ሰዎች እንዳዘዋወሩ እና ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ እንደሰበሰቡ ተገልጿል።
ተጎጂዎች በየመን ውስጥ በመጋዘኖች ታግተው ድብደባ፣ ማሰቃየት እና ሌሎች ኢሰብአዊ ድርጊቶች እንደተፈጸሙባቸው ሲገለጽ፣ ቤተሰቦቻቸውን ገንዘብ እንዲልኩ ለማስገደድ የስቃይ ቪዲዮዎች ይላኩ እንደነበር ተጠቁሟል።
በምርመራውም ከ60 በላይ ሰዎች መሞታቸውና በርካታ ሴቶች መደፈራቸው መረጋገጡን ፖሊስ ገልጿል።
የፌደራል ፖሊስ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ጄይላን አብዲ፣ ተጠርጣሪዎቹ ሰሞኑን ለ15 ቀናት በቆየ ኦፕሬሽን በአዲስ አበባ፣ በሐረሪና በሌሎች አካባቢዎች መያዛቸውን ለቢቢሲ አማርኛ ተናግረዋል።
ፖሊስ የተጠርጣሪዎቹ የምርመራ ፋይል ለፍትሕ ሚኒስቴር መተላለፉን ገልጿል።
በስማቸው የነበሩ ቤቶች ፣ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶችም መታገዳቸው ታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
"እጅግ አደገኛ ናቸው" የተባሉ ሰው አዘዋዋሪዎች መያዛቸውን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ " ከ60 በላይ ስደተኞች ለሞት እና በርካታ ሴቶች ለመደፈር ተጠያቂ ናቸው " ያላቸውን አደገኛ 17 ተጠርጣሪ የሰዎች አዘዋዋሪዎች መያዙን አስታውቋል።
ፖሊስ እንደገለጸው፣ በ"መሐመድ ጣሂር አደም (ወርዲ)" የሚመራው ቡድን ሰዎችን ከኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በደላሎች አማካኝነት በመልመል በጂቡቲና በየመን በኩል በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ያዘዋውር ነበር።
እነዚህ አደገኛ የሰው አዘዋዋሪዎች ከ40,000 በላይ ሰዎች እንዳዘዋወሩ እና ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ እንደሰበሰቡ ተገልጿል።
ተጎጂዎች በየመን ውስጥ በመጋዘኖች ታግተው ድብደባ፣ ማሰቃየት እና ሌሎች ኢሰብአዊ ድርጊቶች እንደተፈጸሙባቸው ሲገለጽ፣ ቤተሰቦቻቸውን ገንዘብ እንዲልኩ ለማስገደድ የስቃይ ቪዲዮዎች ይላኩ እንደነበር ተጠቁሟል።
በምርመራውም ከ60 በላይ ሰዎች መሞታቸውና በርካታ ሴቶች መደፈራቸው መረጋገጡን ፖሊስ ገልጿል።
የፌደራል ፖሊስ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ጄይላን አብዲ፣ ተጠርጣሪዎቹ ሰሞኑን ለ15 ቀናት በቆየ ኦፕሬሽን በአዲስ አበባ፣ በሐረሪና በሌሎች አካባቢዎች መያዛቸውን ለቢቢሲ አማርኛ ተናግረዋል።
ፖሊስ የተጠርጣሪዎቹ የምርመራ ፋይል ለፍትሕ ሚኒስቴር መተላለፉን ገልጿል።
በስማቸው የነበሩ ቤቶች ፣ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶችም መታገዳቸው ታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍8🥰1👌1🤣1