"ኔታንያሁ ኒዮርክ ከተማ ከገቡ ይታሰራሉ" - ከንቲባ ማምዳኒ
የኒዮርክ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ የወጣውን የእስር ትዕዛዝ ተግባራዊ አደርጋለሁ አሉ።
ዓለማቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) እስራኤል በጋዛ ጦርነት የጦር ወንጀል ፈፅማለች በሚል በኔታንያሁና ሌሎች ሁለት ባለስልጣናት ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱ ይታወቃል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይ ሳምንት ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ለመወያየት ወደ አሜሪካ ይጓዛሉ።
ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያም ኔታንያሁ በሚመሯት የኒዮርክ ከተማ ከገቡ እንደሚታሰሩ ተናግረዋል።
"በጉዳዩ ዙሪያ እየተወያየን ነው፤ ግን ህግ እንደ አዲስ አይፃፍም" ሲሉ አይሲሲ ያወጣውን መመሪያ እንደሚተገብሩ ጠቁመዋል።
"በኒውዮርክ እስካለው ድረስ የከተማ ህግ አድርገው ብሎ የሚፈቅድልኝን ለማድረግ ዝግጁ ነኝ" ብለዋል። ማምዳኒ "ኔታንያሁ የጦር ወንጀል ፈፅመዋል ብየ አምናለሁ"ሲሉ ገልጸዋል።
"እሱ ባለፉት አመታት በሰራቸው ወንጀሎች መቅረብ ያለበት ሄግ በሚገኘው ፍርድቤት ነው" ብለዋል። ከንቲባ ማምዳኒ ወደ ኃላፊነት እንደመጡ ተመሳሳይ አስተያየት ሰጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ከማምዳኒ ሹመት በኋላ ወደ አሜሪካ ቢያቀኑም ኒዮርክ ከተማ ግን አልገቡም።
ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከንቲባው ወደ ሚያስተዳድሯት ኒዮርክ የሚገቡት በመጪው መስከረም ወር በሚካሄደው የተመድ አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኒዮርክ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ የወጣውን የእስር ትዕዛዝ ተግባራዊ አደርጋለሁ አሉ።
ዓለማቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) እስራኤል በጋዛ ጦርነት የጦር ወንጀል ፈፅማለች በሚል በኔታንያሁና ሌሎች ሁለት ባለስልጣናት ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱ ይታወቃል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይ ሳምንት ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ለመወያየት ወደ አሜሪካ ይጓዛሉ።
ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያም ኔታንያሁ በሚመሯት የኒዮርክ ከተማ ከገቡ እንደሚታሰሩ ተናግረዋል።
"በጉዳዩ ዙሪያ እየተወያየን ነው፤ ግን ህግ እንደ አዲስ አይፃፍም" ሲሉ አይሲሲ ያወጣውን መመሪያ እንደሚተገብሩ ጠቁመዋል።
"በኒውዮርክ እስካለው ድረስ የከተማ ህግ አድርገው ብሎ የሚፈቅድልኝን ለማድረግ ዝግጁ ነኝ" ብለዋል። ማምዳኒ "ኔታንያሁ የጦር ወንጀል ፈፅመዋል ብየ አምናለሁ"ሲሉ ገልጸዋል።
"እሱ ባለፉት አመታት በሰራቸው ወንጀሎች መቅረብ ያለበት ሄግ በሚገኘው ፍርድቤት ነው" ብለዋል። ከንቲባ ማምዳኒ ወደ ኃላፊነት እንደመጡ ተመሳሳይ አስተያየት ሰጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ከማምዳኒ ሹመት በኋላ ወደ አሜሪካ ቢያቀኑም ኒዮርክ ከተማ ግን አልገቡም።
ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከንቲባው ወደ ሚያስተዳድሯት ኒዮርክ የሚገቡት በመጪው መስከረም ወር በሚካሄደው የተመድ አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤21🤪14🤣4👍3🤷♂2😢1🙊1
የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰናል-ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል‼️
ዛሬ ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም በመቀሌ ህዝቡን እና አመራሩን ሰብስበው አወያይተዋል።
የትግራይ ህዝብ ጭቆናን የመሸከም ታሪክ የለውም ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል፤ ይልቁንም መብቶቹ ለማረጋገጥ በመደራጀት ታግሏል፣ መብቶቹን አስከብሯል እንዲሁም የሌሎች ብሔረሰቦችን መብቶች አክብሮ የመጣ ህዝብ ነው ብለዋል።
ለ17 ዓመታት በተደረገው የትጥቅ ትግል ውስጥ የትግራይ ህዝብ ከባድ መስዋእትነት በመክፈል አንባገነኑ የደርግ ስርዓት መደምሰሱን ያወሱት ዶክተር ደብረፅዮን፤ በአንባገነኑ መቃብር በሃገር ደረጃ ሰላም፣ ልማትና የዴሞክራሲ ግንባታ ማረጋገጡን ጠቅሷል፡፡
ሆኖም፣ ይህንን መቀበል ያልቻሉ ሐይሎች ጊዜና አጋጣሚውን በመጠበቅ፣ የትግራይን ህዝብ ከምድረገፅ ለማጥፋት በህዝባችን ላይ ጀኖሳይድ ፈፅሟል ያሉት ፕረዝዳንቱ፤ የትግራይ ህዝብ አንድነቱ በመጠበቅ ልህልውናው በከፈለው መስዋዕትነት ጭቆናን እና ህልውናውን ለማጥፋት ለመጣው ሐይል የማይቀበል መሆኑ በዓለም አደባባይ ያስመሰከረ እንደሆነ ጠቅሷል፡፡
የፕሪቶሪያው ስምምነት ሲፈረም፤ የትግራይ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ፣ ተፈናቃዮችን ለመመለስ እና ልማትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ተስፋ አድርገን ነበረ ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፤የፌደራል መንግሥቱ በታቀደ ሁኔታ ትግራይን ዳግም ወደ ከበባና ክልከላ በማስገባት ለዳግም ጀኖሳይድ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አብራርቷል፡፡
እንደ ትግራይ፣ ለሰላም ስንል ከፍተኛ ትዕግስትና መስዋዕትነት እየከፈልን ነው፤ ይሁን እኛ ብቻ ሰላም ስለ ፈለግን ሊሳካልን አልቻለም ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን፤ አንድነታችን አጠናክረን የትግራይ መሰረታዊ ጥያቄዎች ማረጋገጥ ብቸኛ መፍትሔ ሆኖ መገኘቱ ተናግሯል፡፡
አሁን ባለንበት ሁኔታ መቀጠል አንችልም ያሉ ሲሆን እንደህዝብ የመከተ ዓቅሞቻችን በማደራጀት ህልውናችን ለማረጋገጥ በምንወስንበት ምዕራፍ ላይ እንገኛለን ብሏል፡፡
የፌደራል መንግስቱ ለሰላም በፍጹም ዝግጁ አይደለም፤ ስለዚህ ብሔራዊ ክብራችንና ሉዓላዊነታችንን ለመመለስ እንዲሁም የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን መልሶ ለማቋቋም ትግላችንን ወደ ተጨባጭና ውጤታማ ደረጃ ማሸጋገር ይገባናል ብሏል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዛሬ ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም በመቀሌ ህዝቡን እና አመራሩን ሰብስበው አወያይተዋል።
የትግራይ ህዝብ ጭቆናን የመሸከም ታሪክ የለውም ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል፤ ይልቁንም መብቶቹ ለማረጋገጥ በመደራጀት ታግሏል፣ መብቶቹን አስከብሯል እንዲሁም የሌሎች ብሔረሰቦችን መብቶች አክብሮ የመጣ ህዝብ ነው ብለዋል።
ለ17 ዓመታት በተደረገው የትጥቅ ትግል ውስጥ የትግራይ ህዝብ ከባድ መስዋእትነት በመክፈል አንባገነኑ የደርግ ስርዓት መደምሰሱን ያወሱት ዶክተር ደብረፅዮን፤ በአንባገነኑ መቃብር በሃገር ደረጃ ሰላም፣ ልማትና የዴሞክራሲ ግንባታ ማረጋገጡን ጠቅሷል፡፡
ሆኖም፣ ይህንን መቀበል ያልቻሉ ሐይሎች ጊዜና አጋጣሚውን በመጠበቅ፣ የትግራይን ህዝብ ከምድረገፅ ለማጥፋት በህዝባችን ላይ ጀኖሳይድ ፈፅሟል ያሉት ፕረዝዳንቱ፤ የትግራይ ህዝብ አንድነቱ በመጠበቅ ልህልውናው በከፈለው መስዋዕትነት ጭቆናን እና ህልውናውን ለማጥፋት ለመጣው ሐይል የማይቀበል መሆኑ በዓለም አደባባይ ያስመሰከረ እንደሆነ ጠቅሷል፡፡
የፕሪቶሪያው ስምምነት ሲፈረም፤ የትግራይ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ፣ ተፈናቃዮችን ለመመለስ እና ልማትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ተስፋ አድርገን ነበረ ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፤የፌደራል መንግሥቱ በታቀደ ሁኔታ ትግራይን ዳግም ወደ ከበባና ክልከላ በማስገባት ለዳግም ጀኖሳይድ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አብራርቷል፡፡
እንደ ትግራይ፣ ለሰላም ስንል ከፍተኛ ትዕግስትና መስዋዕትነት እየከፈልን ነው፤ ይሁን እኛ ብቻ ሰላም ስለ ፈለግን ሊሳካልን አልቻለም ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን፤ አንድነታችን አጠናክረን የትግራይ መሰረታዊ ጥያቄዎች ማረጋገጥ ብቸኛ መፍትሔ ሆኖ መገኘቱ ተናግሯል፡፡
አሁን ባለንበት ሁኔታ መቀጠል አንችልም ያሉ ሲሆን እንደህዝብ የመከተ ዓቅሞቻችን በማደራጀት ህልውናችን ለማረጋገጥ በምንወስንበት ምዕራፍ ላይ እንገኛለን ብሏል፡፡
የፌደራል መንግስቱ ለሰላም በፍጹም ዝግጁ አይደለም፤ ስለዚህ ብሔራዊ ክብራችንና ሉዓላዊነታችንን ለመመለስ እንዲሁም የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን መልሶ ለማቋቋም ትግላችንን ወደ ተጨባጭና ውጤታማ ደረጃ ማሸጋገር ይገባናል ብሏል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19🤣8👍3🫡2🕊1🤪1😎1
መንግስት አዲስ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ታክስ ሊጥል ነው
መንግስት በ2020 በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚሆን አዲስ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ታክስ ለመጣል እየተዘጋጀ ነው። የሚኒስትሮች ምክር ቤት የህግ ረቂቁን በታህሳስ ወር መጨረሻ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሚያቀርብ ካፒታል ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል ።ታክሱ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እስከ 0.2 በመቶ ገቢ ያስገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
መንግስት በ2020 በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚሆን አዲስ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ታክስ ለመጣል እየተዘጋጀ ነው። የሚኒስትሮች ምክር ቤት የህግ ረቂቁን በታህሳስ ወር መጨረሻ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሚያቀርብ ካፒታል ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል ።ታክሱ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እስከ 0.2 በመቶ ገቢ ያስገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15🤔13👍3👀3😢2🤪2🙊2🤷♂1🤣1
65 የመንግስት ኤጀንሲዎች የቦርድ አባላት በሙሉ ከስልጣን ተነሱ
የኬንያ መንግስት በሀገሪቱ የህዝብ ተቋማት ውስጥ የነበረውን የፖለቲካ ተፅዕኖ ለመቀነስ በሚል በ65 የመንግስት ኤጀንሲዎች ውስጥ ሲያገለግሉ የነበሩ የቦርድ አባላትን በሙሉ በይፋ ማሰናበቱን አስታውቋል። ይህ እርምጃ የተወሰደው በቅርቡ ተግባራዊ በሆነው የ2025 የመንግስት ድርጅቶች ህግ (GOE Act) መሰረት መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ ለውጥ የመንግስት ድርጅቶችን አሰራር ሙያዊ እና ግልጽ ለማድረግ ያለመ ነዉ የተባለ ሲሆን ቀደም ሲል የቦርድ አባልነት ለፖለቲካዊ ሹመት ሲውል እንደነበርና ይህም ለሙስና እና ለቅልጥፍና ማጣት መንስኤ ሆኖ መቆየቱ ተገልጿል።
አዲሱ ህግ ለቦርድ አባልነት የሚወዳደሩ ሰዎች ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ በንቃት በፖለቲካ ስራ ውስጥ መሳተፍ እንደሌለባቸው ይደነግጋል። ቦርዶቹም በግልፅ እና በውድድር ሂደት በሚመረጡ ባለሙያዎች እንዲዋቀሩ ይደረጋል።
የቦርድ አባላቱ በሶስት ዓመት የስራ ዘመን የሚያገለግሉ ሲሆን፣ በድጋሚ ለአንድ ጊዜ ብቻ ሊመረጡ ይችላሉ ተብሏል። ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ይህ ለውጥ የመንግስት ተቋማትን ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ በማውጣት የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኬንያ መንግስት በሀገሪቱ የህዝብ ተቋማት ውስጥ የነበረውን የፖለቲካ ተፅዕኖ ለመቀነስ በሚል በ65 የመንግስት ኤጀንሲዎች ውስጥ ሲያገለግሉ የነበሩ የቦርድ አባላትን በሙሉ በይፋ ማሰናበቱን አስታውቋል። ይህ እርምጃ የተወሰደው በቅርቡ ተግባራዊ በሆነው የ2025 የመንግስት ድርጅቶች ህግ (GOE Act) መሰረት መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ ለውጥ የመንግስት ድርጅቶችን አሰራር ሙያዊ እና ግልጽ ለማድረግ ያለመ ነዉ የተባለ ሲሆን ቀደም ሲል የቦርድ አባልነት ለፖለቲካዊ ሹመት ሲውል እንደነበርና ይህም ለሙስና እና ለቅልጥፍና ማጣት መንስኤ ሆኖ መቆየቱ ተገልጿል።
አዲሱ ህግ ለቦርድ አባልነት የሚወዳደሩ ሰዎች ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ በንቃት በፖለቲካ ስራ ውስጥ መሳተፍ እንደሌለባቸው ይደነግጋል። ቦርዶቹም በግልፅ እና በውድድር ሂደት በሚመረጡ ባለሙያዎች እንዲዋቀሩ ይደረጋል።
የቦርድ አባላቱ በሶስት ዓመት የስራ ዘመን የሚያገለግሉ ሲሆን፣ በድጋሚ ለአንድ ጊዜ ብቻ ሊመረጡ ይችላሉ ተብሏል። ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ይህ ለውጥ የመንግስት ተቋማትን ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ በማውጣት የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍2🤣1
የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከኤርትራ እና ሶማሊያ አቻዎቻቸው ጋር በቀጣናዊ ትብብር ዙሪያ ውይይት አደረጉ - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇪🇬 ዛሬ ዕሑድ በካይሮ በተለያዩ መድረኮች በተደረጉ ስብሰባዎች፣ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ ከኤርትራ አቻቸው ኡስማን ሳሌህ እና ከሶማሊያ አቻቸው አብዱሰላም አብዲ አሊ ጋር መወያየታቸውን የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
ስብሰባዎቹ የሁለትዮሽ ግንኙነትን፣ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ማጠናከር እና በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በቅንጅት መሥራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደተደረገባቸው ሚኒስቴሩ በመግለጫው አስታውቋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🇪🇬 ዛሬ ዕሑድ በካይሮ በተለያዩ መድረኮች በተደረጉ ስብሰባዎች፣ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ ከኤርትራ አቻቸው ኡስማን ሳሌህ እና ከሶማሊያ አቻቸው አብዱሰላም አብዲ አሊ ጋር መወያየታቸውን የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
ስብሰባዎቹ የሁለትዮሽ ግንኙነትን፣ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ማጠናከር እና በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በቅንጅት መሥራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደተደረገባቸው ሚኒስቴሩ በመግለጫው አስታውቋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤18😡4👍2🤣2
ስፔን አርጀንቲናን በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች
***
የ2026 ዓለም ዋንጫ ዛሬ ፍጻሜውን ሲያገኘ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋለች። 120 ደቂቃ በወሰደው ፍጻሜ ተቀይሮ የገባው ፌራን ቶሬስ የስፔንን ግብ አስቆጥሯል።
በአርጀንቲና በኩል መደበኛ 90 ደቂቃው መጠናቀቂያ ላይ የቼልሲው አማካይ ኢንዞ ፈርናንዴዝ ፓው ኩባርሲ ላይ በሰራው ጥፋ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
የ2010 የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮኗ ስፔን በታሪኳ ለ2ኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያነሳችበት ሆኗል።
አርጀንቲና የዓለም ዋንጫን ለ2ኛ ተከታታይ ጊዜ ለመውሰድ ለፍጻሜ ብትደርስም ሳይሳካላት ቀርቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
***
የ2026 ዓለም ዋንጫ ዛሬ ፍጻሜውን ሲያገኘ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋለች። 120 ደቂቃ በወሰደው ፍጻሜ ተቀይሮ የገባው ፌራን ቶሬስ የስፔንን ግብ አስቆጥሯል።
በአርጀንቲና በኩል መደበኛ 90 ደቂቃው መጠናቀቂያ ላይ የቼልሲው አማካይ ኢንዞ ፈርናንዴዝ ፓው ኩባርሲ ላይ በሰራው ጥፋ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
የ2010 የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮኗ ስፔን በታሪኳ ለ2ኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያነሳችበት ሆኗል።
አርጀንቲና የዓለም ዋንጫን ለ2ኛ ተከታታይ ጊዜ ለመውሰድ ለፍጻሜ ብትደርስም ሳይሳካላት ቀርቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤28👍9🤪3🤷♂1🥰1😢1🎉1👌1😎1
ታክስ ሊጣል ነው‼️
መንግስት በአዲስ የተሽከርካሪ ባለቤቶች ላይ ታክስ ሊጥል ነው‼️
መንግስት በ2020 በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚሆን አዲስ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ታክስ ለመጣል እየተዘጋጀ ነው። የሚኒስትሮች ምክር ቤት የህግ ረቂቁን በታህሳስ ወር መጨረሻ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሚያቀርብ
ታውቋል።
ታክሱ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እስከ 0.2 በመቶ ገቢ ያስገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
መንግስት በአዲስ የተሽከርካሪ ባለቤቶች ላይ ታክስ ሊጥል ነው‼️
መንግስት በ2020 በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚሆን አዲስ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ታክስ ለመጣል እየተዘጋጀ ነው። የሚኒስትሮች ምክር ቤት የህግ ረቂቁን በታህሳስ ወር መጨረሻ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሚያቀርብ
ታውቋል።
ታክሱ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እስከ 0.2 በመቶ ገቢ ያስገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢12❤5👍2🤔2🤯1
የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ‼️
ለሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መናር ዋነኛው ምክንያት የቡና ነጋዴዎች ናቸው ተባለ
ኢትዮጵያ ቀዳሚ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚታየው የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መጨመር ዋነኛው ምክንያት የቡና ላኪዎች ምርቱን በተጋነነ ዋጋ ማቅረባቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ሰፊሳ አባቡ ለመናኸሪያ ሬድዮ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ለውጭ ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት የተገኘው ገቢ ከፍተኛ ቢሆንም፣ በሀገር ውስጥ ገበያ ላይ ግን የዋጋ ጭማሪ ታይቷል።
ባለስልጣኑ በዘርፉ የቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ ከአለም አቀፍ የገበያ ተመን ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት እንዳለው አስረድተዋል።
ላኪዎች እርስ በርሳቸው በመነጋገር ተቀራራቢና የተረጋጋ ዋጋ እንዲያቀርቡ በተደጋጋሚ ቢነገራቸውም፤ ወዳልተገባ የዋጋ ሽሚያ በመግባታቸው ምክንያት በገበያው ላይ አለመረጋጋት መፈጠሩን ኃላፊው ገልጸዋል።
ይህ የዋጋ መጋነን የሀገሪቱን የቡና ዘርፍ ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ባለስልጣኑ ላኪዎችን በውይይት ለማስማማት ጥረት ማድረጉን ጠቅሰዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ለሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መናር ዋነኛው ምክንያት የቡና ነጋዴዎች ናቸው ተባለ
ኢትዮጵያ ቀዳሚ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚታየው የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መጨመር ዋነኛው ምክንያት የቡና ላኪዎች ምርቱን በተጋነነ ዋጋ ማቅረባቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ሰፊሳ አባቡ ለመናኸሪያ ሬድዮ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ለውጭ ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት የተገኘው ገቢ ከፍተኛ ቢሆንም፣ በሀገር ውስጥ ገበያ ላይ ግን የዋጋ ጭማሪ ታይቷል።
ባለስልጣኑ በዘርፉ የቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ ከአለም አቀፍ የገበያ ተመን ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት እንዳለው አስረድተዋል።
ላኪዎች እርስ በርሳቸው በመነጋገር ተቀራራቢና የተረጋጋ ዋጋ እንዲያቀርቡ በተደጋጋሚ ቢነገራቸውም፤ ወዳልተገባ የዋጋ ሽሚያ በመግባታቸው ምክንያት በገበያው ላይ አለመረጋጋት መፈጠሩን ኃላፊው ገልጸዋል።
ይህ የዋጋ መጋነን የሀገሪቱን የቡና ዘርፍ ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ባለስልጣኑ ላኪዎችን በውይይት ለማስማማት ጥረት ማድረጉን ጠቅሰዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤8👍5🥰1💯1
በኢትዮጵያ መካንነት ከፍተኛ የጤና ችግር እየሆነ መምጣቱ ተነገረ
የመካንነት ችግር በሴቶች ፣በወንዶች እንዲሁም በሁለቱም አጋሮች በጋራ ሊከሰት እንደሚችል የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ።በኢትዮጵያ የመካንነት ችግር ከሚጠበቀው በላይ ከፍተኛ መሆኑን በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት እንዲሁም የመካንነት ሰብ ስፔሻሊስት ሀኪም ዶክተር በላይ ቤተማሪያም ከብስራት ሬድዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል።
ከጥንዶች መካከል ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚሆኑት በዚህ ችግር እንደሚጠቁ ተናግረዋል።በኢንፌክሽን ምክኒያት የሚከሰት የማህፀን ቱቦ መዘጋት በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር 35 በመቶ ድርሻ እንዳለዉ ሰብ ስፔሻሊስቱ አስገንዝበዋል ።በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል ይችላል።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ 20 በመቶ የሚሆነው በወንድ በኩል የሚኖር መካንነት ነው።በጭንቅላት ውስጥ የሚመረት ሆርሞን ማነስ ፣በዘር ፍሬ ላይ የሚያጋጥም ስፐርም የማምረት ችግር ፣የወንድ የዘር ቱቦ መዘጋት እንዲሁም ምክንያቱ የማይታወቅ የወንድ መካንነት ዋና ዋናዎቹ መንስኤዎች ናቸው ።
የእንቁላል መፈጠር ወይም መለቀቅ ችግር ፤ በሆርሞን መዛባት ወይም በእድሜ ምክኒያት እንቁላል በወር አበባ ዑደት ውስጥ አዘውትሮ አለመፈጠር በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር ዋነኛቹ ምክኒያቶች መሆናቸውን ዶክተር በላይ አስረድተዋል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የመካንነት ችግር በሴቶች ፣በወንዶች እንዲሁም በሁለቱም አጋሮች በጋራ ሊከሰት እንደሚችል የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ።በኢትዮጵያ የመካንነት ችግር ከሚጠበቀው በላይ ከፍተኛ መሆኑን በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት እንዲሁም የመካንነት ሰብ ስፔሻሊስት ሀኪም ዶክተር በላይ ቤተማሪያም ከብስራት ሬድዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል።
ከጥንዶች መካከል ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚሆኑት በዚህ ችግር እንደሚጠቁ ተናግረዋል።በኢንፌክሽን ምክኒያት የሚከሰት የማህፀን ቱቦ መዘጋት በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር 35 በመቶ ድርሻ እንዳለዉ ሰብ ስፔሻሊስቱ አስገንዝበዋል ።በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል ይችላል።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ 20 በመቶ የሚሆነው በወንድ በኩል የሚኖር መካንነት ነው።በጭንቅላት ውስጥ የሚመረት ሆርሞን ማነስ ፣በዘር ፍሬ ላይ የሚያጋጥም ስፐርም የማምረት ችግር ፣የወንድ የዘር ቱቦ መዘጋት እንዲሁም ምክንያቱ የማይታወቅ የወንድ መካንነት ዋና ዋናዎቹ መንስኤዎች ናቸው ።
የእንቁላል መፈጠር ወይም መለቀቅ ችግር ፤ በሆርሞን መዛባት ወይም በእድሜ ምክኒያት እንቁላል በወር አበባ ዑደት ውስጥ አዘውትሮ አለመፈጠር በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር ዋነኛቹ ምክኒያቶች መሆናቸውን ዶክተር በላይ አስረድተዋል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19👍3😱1
የመብራት ታሪፍ‼️
👉ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት አዲስ የክፍያ ታሪፍ ጭማሪ ተደርጓል።
‹‹በኤሌክትሪክ ክፍያ ላይ የታየው ለውጥ አዲስ ጭማሪ ሳይሆን ቀድሞ የተወሰነ ማስተካከያ ሂደት ነው››-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ በደንበኞች ላይ የተደረገው የታሪፍ ማስተካከያ ክፍያ ቀደም ሲል በስትራቴጂው መሠረት የተወሰነ መሆኑን አስታዉቋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሽያጭና ደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ይኸይስ ስዩም ለኢትዮ ኤፍኤም 107.8 እንደገለጹት፤ በ2017 ዓ.ም መስከረም ወር ላይ የተጀመረው የታሪፍ ማሻሻያ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ በ24 የሩብ ዓመታት ተከፋፍሎ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ይህ የታሪፍ ማስተካከያ ተቋሙ ከአራት ዓመት በኋላ የሚሰበሰበውን አጠቃላይ ክፍያ በመስከረም 2017 ዓ.ም ላይ በአንድ ጊዜ ማስከፈል የነበረበት ቢሆንም፣ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ታሳቢ በማድረግ በጥቂት በጥቂቱ ከፋፍሎ እንዲከፍል የተዘረጋ ስትራቴጂ ነው በማለት ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ ያለው ታሪፍ ዝቅተኛውን የኅብረተሰብ ክፍል በልዩ ሁኔታ ለመደገፍ የመንግሥት ድጎማ የሚደረግበት ነው ያሉ ሲሆን፣ እስከ 50 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት 96 ሳንቲም ብቻ እንዲከፍሉ እየተደረገ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዶ/ር ይኸይስ አክለውም፤ እስከ 2መቶ ኪሎ ዋት የሚጠቀም ማንኛውም ደንበኛ በትክክለኛው የታሪፍ ዋጋ ሳይሆን በድጎማ እንዲከፍል እየተደረገ ነው ብለዋል።
ደንበኞች በአንድ ወር ውስጥ በተደጋጋሚ ኃይል ሲገዙ ስለሚገጥማቸው የዋጋ ልዩነት ሲያብራሩም፤ የዋጋ አተማመን ሥርዓቱ በ30 ቀናት ውስጥ የተጠቀሙትን አጠቃላይ የኃይል መጠን በአንድ ላይ ደምሮ ስለሚያሰላው የኪሎ ዋት መጠኑ ሲጨምር ታሪፉም አብሮ እንደሚጨምር አስገንዝበዋል።
ይህንን ሁኔታ ተከትሎ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ተቋሙ በየክፍለ ከተማው ከነዋሪዎች ጋር ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶችን እያደረገ ሲሆን፣ ባለፉት 15 ቀናት ውስጥም ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለሚዲያ አካላት ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👉ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት አዲስ የክፍያ ታሪፍ ጭማሪ ተደርጓል።
‹‹በኤሌክትሪክ ክፍያ ላይ የታየው ለውጥ አዲስ ጭማሪ ሳይሆን ቀድሞ የተወሰነ ማስተካከያ ሂደት ነው››-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ በደንበኞች ላይ የተደረገው የታሪፍ ማስተካከያ ክፍያ ቀደም ሲል በስትራቴጂው መሠረት የተወሰነ መሆኑን አስታዉቋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሽያጭና ደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ይኸይስ ስዩም ለኢትዮ ኤፍኤም 107.8 እንደገለጹት፤ በ2017 ዓ.ም መስከረም ወር ላይ የተጀመረው የታሪፍ ማሻሻያ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ በ24 የሩብ ዓመታት ተከፋፍሎ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ይህ የታሪፍ ማስተካከያ ተቋሙ ከአራት ዓመት በኋላ የሚሰበሰበውን አጠቃላይ ክፍያ በመስከረም 2017 ዓ.ም ላይ በአንድ ጊዜ ማስከፈል የነበረበት ቢሆንም፣ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ታሳቢ በማድረግ በጥቂት በጥቂቱ ከፋፍሎ እንዲከፍል የተዘረጋ ስትራቴጂ ነው በማለት ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ ያለው ታሪፍ ዝቅተኛውን የኅብረተሰብ ክፍል በልዩ ሁኔታ ለመደገፍ የመንግሥት ድጎማ የሚደረግበት ነው ያሉ ሲሆን፣ እስከ 50 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት 96 ሳንቲም ብቻ እንዲከፍሉ እየተደረገ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዶ/ር ይኸይስ አክለውም፤ እስከ 2መቶ ኪሎ ዋት የሚጠቀም ማንኛውም ደንበኛ በትክክለኛው የታሪፍ ዋጋ ሳይሆን በድጎማ እንዲከፍል እየተደረገ ነው ብለዋል።
ደንበኞች በአንድ ወር ውስጥ በተደጋጋሚ ኃይል ሲገዙ ስለሚገጥማቸው የዋጋ ልዩነት ሲያብራሩም፤ የዋጋ አተማመን ሥርዓቱ በ30 ቀናት ውስጥ የተጠቀሙትን አጠቃላይ የኃይል መጠን በአንድ ላይ ደምሮ ስለሚያሰላው የኪሎ ዋት መጠኑ ሲጨምር ታሪፉም አብሮ እንደሚጨምር አስገንዝበዋል።
ይህንን ሁኔታ ተከትሎ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ተቋሙ በየክፍለ ከተማው ከነዋሪዎች ጋር ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶችን እያደረገ ሲሆን፣ ባለፉት 15 ቀናት ውስጥም ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለሚዲያ አካላት ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡21❤15👍3💊2👌1🥱1👀1🙉1
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ – የሚፈልጓቸውን አዳዲስ ዜናዎችን በአጭሩ እና በጥልቀት ከኛ ዘንድ ያንብቡ።
🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።
🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።
አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy
@sputnik_ethiopia
🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።
🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።
አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy
@sputnik_ethiopia
👍3❤1
የምግብ ዋጋ ግሽበት 15.1 በመቶ ደረሰ
የሰኔ ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 13.9 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 15.1 በመቶ የጨመረ ሲሆን በዋናነት አትክልት፣ ስጋ ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ አሳይተዋል።
ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 12.2 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንስፖርት 14.3 በመቶ፣ አልኮል መጠጦችና ትምባሆ 14.5 በመቶ፣ በኮሙዩኒኬሸን 8.9 በመቶ ፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች 12.0 በመቶ እንዲሁም ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች 17.9 በመቶ ሆነው ተመዝግበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሰኔ ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 13.9 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 15.1 በመቶ የጨመረ ሲሆን በዋናነት አትክልት፣ ስጋ ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ አሳይተዋል።
ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 12.2 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንስፖርት 14.3 በመቶ፣ አልኮል መጠጦችና ትምባሆ 14.5 በመቶ፣ በኮሙዩኒኬሸን 8.9 በመቶ ፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች 12.0 በመቶ እንዲሁም ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች 17.9 በመቶ ሆነው ተመዝግበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢11👍6❤3🤪1
አሜሪካ ወደ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈች
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍5
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ዘንድሮ ክልል አቀፉን የ8ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ 85,531 ተማሪዎች 83,342 ተማሪዎች ወይም 97.4 በመቶ ማለፋቸውን አሳውቋል።
ከ1,538 ት/ቤቶች ውስጥ 1,017 ትምህርት ቤቶች ሁሉንም ተማሪዎቻቸውን እንዳሳለፉም ያሳወቀው ክልሉ አንድም ትምህርት ቤት ተማሪ ያላሳለፈ የለም ብሏል።
ሌላው የዘንድሮው ውጤት ከ2017 ዓ.ም ጋር ሲነጻጸር በ61.5 በመቶ መሻሻሉንም ጠቁሟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከ1,538 ት/ቤቶች ውስጥ 1,017 ትምህርት ቤቶች ሁሉንም ተማሪዎቻቸውን እንዳሳለፉም ያሳወቀው ክልሉ አንድም ትምህርት ቤት ተማሪ ያላሳለፈ የለም ብሏል።
ሌላው የዘንድሮው ውጤት ከ2017 ዓ.ም ጋር ሲነጻጸር በ61.5 በመቶ መሻሻሉንም ጠቁሟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11🤣10👍4
በአከራይ ተከራይ ውል መፈጸም የሌለባቸው እና የተከለከሉ ተግባራት...
በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው።
👉የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት፤
👉በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል በአዋጁ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዝገብ፤
👉የመኖሪ ቤት ኪራይ ውል እድሳት አለማስመዝገብ፤
👉በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤
👉አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤
👉በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤
👉አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ እንዲፈፀም ማስገደድ፤
👉 በባንክ ወይሞ በሌላ ሕጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ስርዓት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈፀም
👉 ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ እና ፤
👉በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ ለመጠቀሞ ሀሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ የተከለከለ መሆኑን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው።
👉የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት፤
👉በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል በአዋጁ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዝገብ፤
👉የመኖሪ ቤት ኪራይ ውል እድሳት አለማስመዝገብ፤
👉በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤
👉አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤
👉በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤
👉አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ እንዲፈፀም ማስገደድ፤
👉 በባንክ ወይሞ በሌላ ሕጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ስርዓት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈፀም
👉 ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ እና ፤
👉በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ ለመጠቀሞ ሀሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ የተከለከለ መሆኑን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤18😡7👍2
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት፣ አስፈላጊ ማስረጃዎችን ያላሟሉ የመንግሥት ሠራተኞችን ደመወዝ እንደሚያቋርጥ አስጠነቀቀ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ የፈረሙበት ደብዳቤ፤ ከሚያዝያ ጀምሮ በመንግሥት ሠራተኞች የትምህርትና ሌሎች ማስረጃዎች ላይ ማጣራት ሲደረግ መቆየቱንና የሠራተኞች የትምህርት ማስረጃዎችና ተያያዥ መረጃዎች ተደራጅተው አለመገኘታቸውን ጠቅሷል፡፡ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በአካል ቀርቦ አስፈላጊ መረጃዎችን እስከ ሐምሌ 30 ቀን ድረስ ሞልቶ ማጠናቀቅ እንዳለበትም የክልሉ መንግሥት አሳስቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤6👍2
የ20 ዓመት ሴት ልጅ የገዛ ልጁን አስገድዶ ግብረ ስጋ ግንኘነት ያደረገው አባት በእስራት ተቀጣ
ሐምሌ 14, 2018 ዓ.ም ምዕራብ ዓባያ ወረዳ።
በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ብርብር ከተማ መንደር ሰባት ነዋሪ የሆኑት ኢንስፐክተር ግርማ ጌታቸው እና ከወ/ሮ መስከረም ሙሉጌታ የተወለደችው ልጅ ሐና ግርማ ዕድሜዋ 20 ዓመት የደረሰና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን መንግሥት ባስታጠቀው ሽጉጥ በማስፈራራት በቀን 6/9/2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ቡና እያፈለች ባለችበት ኳላ በመምጣት በጉልበት ወደ መኝታ ክፍል በማምራት የለበሰችሁን ቀምስ በማወለቅ ክብረ ንጽህና በመገርሰስ በጉልበት የግብረ ስጋ ግንኙነት ሲፈፅም ልጅቷ ባሰማችው የድረሱልኝ ጥሪ ጎረቤት በመሰማት መደፈራዋን ከአንደበቷ ሰምተው ሲያረጋግጡ ለፖሊስ ጥቆማ በማድረግ የማጣራት ስራ በመስራት በህግ ሲታይ ቆይቶ የምዕራብ አባያ ወረዳ ፍ/ቤት በተከሳሹ ላይ በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት 9 ዓመት ከ3 ወር ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል ሲል ምዕራብ ዓባያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው የዘገበው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ሐምሌ 14, 2018 ዓ.ም ምዕራብ ዓባያ ወረዳ።
በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ብርብር ከተማ መንደር ሰባት ነዋሪ የሆኑት ኢንስፐክተር ግርማ ጌታቸው እና ከወ/ሮ መስከረም ሙሉጌታ የተወለደችው ልጅ ሐና ግርማ ዕድሜዋ 20 ዓመት የደረሰና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን መንግሥት ባስታጠቀው ሽጉጥ በማስፈራራት በቀን 6/9/2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ቡና እያፈለች ባለችበት ኳላ በመምጣት በጉልበት ወደ መኝታ ክፍል በማምራት የለበሰችሁን ቀምስ በማወለቅ ክብረ ንጽህና በመገርሰስ በጉልበት የግብረ ስጋ ግንኙነት ሲፈፅም ልጅቷ ባሰማችው የድረሱልኝ ጥሪ ጎረቤት በመሰማት መደፈራዋን ከአንደበቷ ሰምተው ሲያረጋግጡ ለፖሊስ ጥቆማ በማድረግ የማጣራት ስራ በመስራት በህግ ሲታይ ቆይቶ የምዕራብ አባያ ወረዳ ፍ/ቤት በተከሳሹ ላይ በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት 9 ዓመት ከ3 ወር ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል ሲል ምዕራብ ዓባያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው የዘገበው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
💔30😡23🙉9❤8👍2😱2🤯1😢1👀1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የጦርነት ድባብ እየተሰማ ነው‼️
በትግራይ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ከባለፈው እሁድ ጀምሮ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
ህዝቡ እና ወጣቱ ለጦርነት እንዲዘጋጅ ከሁሉም አመራሮች በግልጽ እየተነገራቸው ይገኛል።
የህወሓት ዋና ፀሃፊ የሆኑት ፈትለወርቅ (ሞንጀሪኖ) ባካሄዱበት ስብሰባ ላይ "አዲስ አበባ እስክንገባ ብቻችን እንሸከመዋለን ማለት አይደለም፥ ብዙ አጋሮች አሉን ። አዲስ አበባ በር ላይ ፋኖ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አለ ስለዚህ ብዙ ወዳጆች አሉን” ሲሉ ተደምጠዋል።
ሰላም ለሀገራችን🕊🕊
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በትግራይ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ከባለፈው እሁድ ጀምሮ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
ህዝቡ እና ወጣቱ ለጦርነት እንዲዘጋጅ ከሁሉም አመራሮች በግልጽ እየተነገራቸው ይገኛል።
የህወሓት ዋና ፀሃፊ የሆኑት ፈትለወርቅ (ሞንጀሪኖ) ባካሄዱበት ስብሰባ ላይ "አዲስ አበባ እስክንገባ ብቻችን እንሸከመዋለን ማለት አይደለም፥ ብዙ አጋሮች አሉን ። አዲስ አበባ በር ላይ ፋኖ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አለ ስለዚህ ብዙ ወዳጆች አሉን” ሲሉ ተደምጠዋል።
ሰላም ለሀገራችን🕊🕊
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤46👍12🫡6🤣5🙉5🤯4🕊4👀1🙊1