የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን፣ ሁሉም የበይነ መረብ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ሊያስገድድ መኾኑን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ፣ የበይነ መረብ ጣቢያዎች ተመዝግበው ብቻ እንዲሠሩ ለማስቻል የመገናኛ ብዙኀን ዋጁን ለማሻሻል ቅድመ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝም ገልጧል።
አዋጁ፣ የበይነ መረብ ጣቢያዎች ምዝገባ በፈቃደኝነት ላይ ብቻ እንዲኾን የሚፈቅድ ነው።
በዚህ ምክንያት፣ ፌስቡክን፣ ቲክቶክን እና ዩትዩብን በመሳሰሉ የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ይዘቶችን የሚያስተላልፉ አብዛኞቹ ድርጅቶችና ግለሰቦች የምዝገባ የምስክር ወረቀት ሳይወስዱና እውቅናና ፈቃድ ሳያገኙ እየሠሩ እንደሚገኙ ባለሥልጣኑ ጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ባለስልጣኑ፣ የበይነ መረብ ጣቢያዎች ተመዝግበው ብቻ እንዲሠሩ ለማስቻል የመገናኛ ብዙኀን ዋጁን ለማሻሻል ቅድመ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝም ገልጧል።
አዋጁ፣ የበይነ መረብ ጣቢያዎች ምዝገባ በፈቃደኝነት ላይ ብቻ እንዲኾን የሚፈቅድ ነው።
በዚህ ምክንያት፣ ፌስቡክን፣ ቲክቶክን እና ዩትዩብን በመሳሰሉ የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ይዘቶችን የሚያስተላልፉ አብዛኞቹ ድርጅቶችና ግለሰቦች የምዝገባ የምስክር ወረቀት ሳይወስዱና እውቅናና ፈቃድ ሳያገኙ እየሠሩ እንደሚገኙ ባለሥልጣኑ ጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10😱4👍3
ትምህርት ሚኒስቴር በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና አዲስ ማዕቀፍ አዘጋጅቷል።
ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ፣ ከአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር ተያይዞ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ማስገባት መቋረጡን አስታውሷል፡፡
ይሁን እንጂ በቀጣይ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት በተዘጋጀ የስልጠና ማዕቀፍ፣ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል።
በ2018 ዓ.ም የክረምት ስልጠናውን ለመስጠት ስምንት አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች መመረጣቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
ለክረምት ስልጠናው የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች፦
1. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
3. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
4. መቐለ ዩኒቨርሲቲ
5. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
7. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
8. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
ተቋማት እና የስልጠናው አሰጣጥ አግባብነት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከሚገለጽ ድረስ ከላይ ከተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በክረምት መምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መስጠት የማይቻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
ከ2011 ዓ.ም በፊት ስልጠና ጀምረው ያላጠናቀቁ መምህራን ከዚህ በፊት በተሰጠው ውሳኔ መሰረት እንዲያጠናቅቁ እንዲደረግ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ደብዳቤ ይገልጻል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ፣ ከአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር ተያይዞ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ማስገባት መቋረጡን አስታውሷል፡፡
ይሁን እንጂ በቀጣይ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት በተዘጋጀ የስልጠና ማዕቀፍ፣ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል።
በ2018 ዓ.ም የክረምት ስልጠናውን ለመስጠት ስምንት አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች መመረጣቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
ለክረምት ስልጠናው የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች፦
1. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
3. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
4. መቐለ ዩኒቨርሲቲ
5. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
7. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
8. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
ተቋማት እና የስልጠናው አሰጣጥ አግባብነት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከሚገለጽ ድረስ ከላይ ከተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በክረምት መምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መስጠት የማይቻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
ከ2011 ዓ.ም በፊት ስልጠና ጀምረው ያላጠናቀቁ መምህራን ከዚህ በፊት በተሰጠው ውሳኔ መሰረት እንዲያጠናቅቁ እንዲደረግ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ደብዳቤ ይገልጻል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍10❤6😢1
ለአንድ ቴሌቪዥን 850 ብር ታክስ‼️
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከፌዴራል መገናኛ ብዙሃን ነው የተላክነው እያሉ ቤት ለቤት በመዞር የዲሽ ሳህን እየቆጠሩ በአንድ ቴሌቪዥን 850 ብር ከእያንዳንዱ ሰው ታክስ እያስከፈሉ መሆኑን ነዋሪዎቹ ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን አመታዊ የቴሌቪዥን ግብር 120 ሲሆን ከመብራት ክፍያ ጋር አስር አስር ብር በየወሩ እንዲከፈል ተደርጓል። የአሁኑ ክፍያ መንግስት ያውቀዋል? የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከፌዴራል መገናኛ ብዙሃን ነው የተላክነው እያሉ ቤት ለቤት በመዞር የዲሽ ሳህን እየቆጠሩ በአንድ ቴሌቪዥን 850 ብር ከእያንዳንዱ ሰው ታክስ እያስከፈሉ መሆኑን ነዋሪዎቹ ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን አመታዊ የቴሌቪዥን ግብር 120 ሲሆን ከመብራት ክፍያ ጋር አስር አስር ብር በየወሩ እንዲከፈል ተደርጓል። የአሁኑ ክፍያ መንግስት ያውቀዋል? የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10👍3
3.69 ቢሊዮን ብር ያባከነው ተቋም‼
የፌዴራል ዋና ኦዲተር በ2018-2025 እ.ኤ.አ በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ስር በተከናወኑት የዌልመል እና የጨልጨል የመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ ባካሄደው የክዋኔ ኦዲት፣ ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ ብክነትና የውል ጥሰት መፈጸሙን ይፋ አደረገ።
ዋና ዋና የኦዲት ግኝቶች፦
📌የገንዘብ ብክነት፦ "የዋጋ ማስተካከያ አይፈቀድም" የሚለው የውል ድንጋጌ ተጥሶ በተደረጉ ማሻሻያዎች 3.69 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ወጪ ተደርጓል።
📌የቅንጡ መኪናዎች ግዢ፦ በጨልጨል ፕሮጀክት ውስጥ በውል ያልተካተቱ፣ ከ132 ሚሊዮን ብር በላይ የፈጁ የ2023 ሞዴል ቅንጡ ተሽከርካሪዎች (V6 እና Toyota Prado) ተገዝተው በተቋራጩ እጅ እንዲገቡ ተደርጓል።
📌የሰነድ ማጭበርበር፦ የ75 ሚሊዮን ብር የመስክ ተሽከርካሪዎች ግዢ የተጠናቀቀ ግንባታ ተደርጎ በተጭበረበረ ጊዜያዊ የክፍያ ማረጋገጫ ተፈጽሟል።
📌 ከፍተኛ መዘግየት፦ ፕሮጀክቶቹ ያለ አዋጭነት ጥናት በመጀመራቸውና በደካማ ክትትል ምክንያት ከ38 ወራት በላይ የዘገዩ ቢሆንም፣ በሚኒስቴሩ በኩል ምንም ዓይነት የመዘግየት ቅጣት አልተጣለም።
👉👉ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የተሰጡትን የማስተካከያ ምክረ-ሃሳቦች በአስቸኳይ ተግባራዊ ካላደረገ፣ ጉዳዩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የሕግና የወንጀል ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ዋና ኦዲተሩ ማስጠንቀቁን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የፌዴራል ዋና ኦዲተር በ2018-2025 እ.ኤ.አ በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ስር በተከናወኑት የዌልመል እና የጨልጨል የመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ ባካሄደው የክዋኔ ኦዲት፣ ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ ብክነትና የውል ጥሰት መፈጸሙን ይፋ አደረገ።
ዋና ዋና የኦዲት ግኝቶች፦
📌የገንዘብ ብክነት፦ "የዋጋ ማስተካከያ አይፈቀድም" የሚለው የውል ድንጋጌ ተጥሶ በተደረጉ ማሻሻያዎች 3.69 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ወጪ ተደርጓል።
📌የቅንጡ መኪናዎች ግዢ፦ በጨልጨል ፕሮጀክት ውስጥ በውል ያልተካተቱ፣ ከ132 ሚሊዮን ብር በላይ የፈጁ የ2023 ሞዴል ቅንጡ ተሽከርካሪዎች (V6 እና Toyota Prado) ተገዝተው በተቋራጩ እጅ እንዲገቡ ተደርጓል።
📌የሰነድ ማጭበርበር፦ የ75 ሚሊዮን ብር የመስክ ተሽከርካሪዎች ግዢ የተጠናቀቀ ግንባታ ተደርጎ በተጭበረበረ ጊዜያዊ የክፍያ ማረጋገጫ ተፈጽሟል።
📌 ከፍተኛ መዘግየት፦ ፕሮጀክቶቹ ያለ አዋጭነት ጥናት በመጀመራቸውና በደካማ ክትትል ምክንያት ከ38 ወራት በላይ የዘገዩ ቢሆንም፣ በሚኒስቴሩ በኩል ምንም ዓይነት የመዘግየት ቅጣት አልተጣለም።
👉👉ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የተሰጡትን የማስተካከያ ምክረ-ሃሳቦች በአስቸኳይ ተግባራዊ ካላደረገ፣ ጉዳዩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የሕግና የወንጀል ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ዋና ኦዲተሩ ማስጠንቀቁን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍5😢1
የአፍሪካ የገንዘብ ሚኒስትሮችና የባንክ ገዥዎች በባንጁል የጋራ መግለጫ አወጡ
የአፍሪካ ሀገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች እና የባንክ ገዥዎች ዓመታዊ ስብሰባ በባንጁል ተካሂዷል ። በስብሰባው ላይ የተሳተፉት የብሬተን ዉድስ ተቋማት የአፍሪካ ገዥዎች፣ አህጉሪቱን ወደ ተሻለ ኢኮኖሚያዊ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ቁርጠኝነቶችን ይፋ አድርገዋል።
የገንዘብ ሚኒስትሮቹ በዋናነት የሀገር ውስጥ የገቢ አሰባሰብን ማጠናከር፣ የመንግስት የገንዘብ አያያዝን ማሻሻል፣ የካፒታል ገበያዎችን ማሳደግ እንዲሁም ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋት የጋራ ግባቸው መሆኑን አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) እና የዓለም ባንክ (WBG) አፍሪካ የግብር ስርዓቷን ለማዘመን፣ ህገ-ወጥ የገንዘብ ፍሰትን ለመግታት እና በዲጂታላይዜሽን የታገዘ የግብር አስተዳደር ለመገንባት እያደረጉት ያለውን ጥረት በልዩ ትኩረት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል።
የአፍሪካን መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ለማረጋገጥና የዕዳ ተጋላጭነትን ለመቋቋም፣ ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ምንጭ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ፤ ተቋማቱ በግሉ ዘርፍ ልማትና በተቋማዊ የመቋቋም አቅም ግንባታ ረገድ የሚያደርጉት ድጋፍ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአፍሪካ ሀገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች እና የባንክ ገዥዎች ዓመታዊ ስብሰባ በባንጁል ተካሂዷል ። በስብሰባው ላይ የተሳተፉት የብሬተን ዉድስ ተቋማት የአፍሪካ ገዥዎች፣ አህጉሪቱን ወደ ተሻለ ኢኮኖሚያዊ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ቁርጠኝነቶችን ይፋ አድርገዋል።
የገንዘብ ሚኒስትሮቹ በዋናነት የሀገር ውስጥ የገቢ አሰባሰብን ማጠናከር፣ የመንግስት የገንዘብ አያያዝን ማሻሻል፣ የካፒታል ገበያዎችን ማሳደግ እንዲሁም ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋት የጋራ ግባቸው መሆኑን አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) እና የዓለም ባንክ (WBG) አፍሪካ የግብር ስርዓቷን ለማዘመን፣ ህገ-ወጥ የገንዘብ ፍሰትን ለመግታት እና በዲጂታላይዜሽን የታገዘ የግብር አስተዳደር ለመገንባት እያደረጉት ያለውን ጥረት በልዩ ትኩረት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል።
የአፍሪካን መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ለማረጋገጥና የዕዳ ተጋላጭነትን ለመቋቋም፣ ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ምንጭ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ፤ ተቋማቱ በግሉ ዘርፍ ልማትና በተቋማዊ የመቋቋም አቅም ግንባታ ረገድ የሚያደርጉት ድጋፍ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7👍2🤯1
አከራዮች ላይ ከተማ አስተዳደሩ የማያዳግም እርምጃ እወስዳለሁ አለ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
በተለይም ተከራዮችን “ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ” በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ”ድርብ ውል” አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
በተለይም ተከራዮችን “ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ” በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ”ድርብ ውል” አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍3🤪3
"የትራፊክ መጨናነቅ ስለሚያጋጥም አማራጭ መንገዶች ተጠቀሙ" - ትራፊክ ማኔጅመንት
ነገ ሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል።
ለዚሁ ጉባኤ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የጉባኤው ተሳታፊዎች አዲስ አበባ ይገኛሉ።
የጉባኤው ተሳታፊዎች በሲኤምሲ መስመር የተባበሩት አደባባይ ወደ ሚገኘው አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር ጠዋት እና ማታ ሲገቡና ሲወጡ የሚጓዙባቸው መስመሮች ማለትም ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በሳህሊተ ምህረት እንዲሁም ከኢትዮ ቻይና መስመር በሳህሊተ ምህረት እስከ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር የትራፊክ መጨናነቅ እንደሚያጋጥም የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አሳውቋል።
በመሆኑም ከነገ ጀምሮ ጉባኤው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ በመስመሮቹ የሚጓዙ አሽከርካሪዎች አስቀድመው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ከወዲሁ መልዕክት ተላልፏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ነገ ሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል።
ለዚሁ ጉባኤ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የጉባኤው ተሳታፊዎች አዲስ አበባ ይገኛሉ።
የጉባኤው ተሳታፊዎች በሲኤምሲ መስመር የተባበሩት አደባባይ ወደ ሚገኘው አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር ጠዋት እና ማታ ሲገቡና ሲወጡ የሚጓዙባቸው መስመሮች ማለትም ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በሳህሊተ ምህረት እንዲሁም ከኢትዮ ቻይና መስመር በሳህሊተ ምህረት እስከ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር የትራፊክ መጨናነቅ እንደሚያጋጥም የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አሳውቋል።
በመሆኑም ከነገ ጀምሮ ጉባኤው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ በመስመሮቹ የሚጓዙ አሽከርካሪዎች አስቀድመው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ከወዲሁ መልዕክት ተላልፏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤5👍3🤪3
አሳሳቢ እየሆነ የመጣው ማጅራት መቺነት‼️
በመዲናዋ አዲስ አበባ በተለይም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ ሰሚት፣ ገርጂ እና አካባቢው ከመቼውም ጊዜ በላይ የተበራከተው የማጅራት መምታት እና የንጥቂያ ወንጀል የነዋሪውን ደህንነት ክፉኛ እየፈተነ ይገኛል። የወንጀሉ ገጽታ እና የጸጥታ አካላት እየወሰዱት ያለው እርምጃ ነዋሪዎችን እና የፖሊስ ኃላፊዎችን እያወዛገበ ሲሆን፣ የህዝቡን ስጋት እና የፖሊስን ምላሽ እንደሚከተለው አጠናቅረነዋል።
እንደ ነዋሪዎች እና ስማቸው እንዳይጠቀስ ከፈለጉ የውስጥ ፖሊስ አባላት ዘ-ሐበሻ ባገኘው መረጃ፣ የዘረፋው ወንጀል መልኩን ቀይሮ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ለወትሮው በምሽት ይፈጸም የነበረው ማጅራት መምታት፣ አሁን የክረምቱን መግባት እና የጠዋቱን ጨለማ እንደ ሽፋን በመጠቀም ወደ ማለዳ ተሸጋግሯል።
የዚህ አዲስ የማለዳ ላይ ጥቃት ዋነኛ ሰለባ እየሆኑ ያሉት ደግሞ፣ ጠዋት በጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን የሚያመሩ አረጋውያን እናቶች ናቸው። ይህ በየዕለቱ እየተፈጸመ ያለ አስነዋሪ ድርጊት ቢሆንም፣ የፖሊስ የበላይ ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት ከማሰብ ይልቅ ጉዳዩን አድበስብሶ ማለፍን መርጠዋል የሚል ጠንካራ ወቀሳ ከውስጥ ምንጮች ቀርቧል። "የህዝቡ ስቃይ ዝም ተብሎ ስለታለፈ እና ኃላፊዎች እርምጃ ባለመውሰዳቸው መረጃውን ለሚዲያ አድርሰናል" ያሉት የውስጥ ምንጮች፣ ተቋማዊ ቸልተኝነት መኖሩን በጽኑ ተችተዋል።
በተነሳው የ"ቸልተኝነት እና የዝምታ" ክስ ላይ ምላሽ የሰጡን የፖሊስ ኃላፊዎች፣ ተቋሙ በምንም መልኩ ዝምታን እንዳልመረጠ አስታውቀዋል። ኃላፊው ለቀረበባቸው ወቀሳ በሰጡት ምላሽ፣ ፖሊስ ወንጀለኞች በስፋት ይንቀሳቀሱባቸዋል የተባሉትን ሰሚት፣ ገርጂ እና 'ጥላሁን' የተባሉ አካባቢዎችን ለይቶ ሰፊ የጸጥታ ማስከበር አሰሳ እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ወንጀለኞች የሚሰባሰቡባቸውን ህገ-ወጥ የሺሻ ቤቶችን የማፍረስ ስራ እየተሰራ ሲሆን፣ በአንድ ቀን በተደረገ ኦፕሬሽን ብቻ 80 ያህል የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ማስመለስ መቻሉን ፖሊስ በምላሹ አስረድቷል። ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት ድረስ የዘለቀ ጥብቅ አሰሳ በየቀኑ እየተካሄደ መሆኑንም አክለዋል።
ከዚህ ቀደም የነበሩ አመራሮች የጸጥታ ስራዎችን ለሚዲያ ፍጆታ ይጠቀሙበት እንደነበር የወቀሱት ኃላፊው፣ "አሁን ያለው የጸጥታ መዋቅር ማወናበድ ሳይሆን በተጨባጭ ወንጀልን ከስረ-መሰረቱ ለማጥፋት ትልቅ ኦፕሬሽን እየሰራ ስለሆነ ነው እንጂ የተኛንበት ጊዜ የለም" ሲሉ ተከራክረዋል።
በፖሊስ ኃላፊው ምላሽ ውስጥ ጎልቶ የወጣው ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ በነዚህ አካባቢዎች ያለው የውጭ ዜጎች ወንጀል ተሳትፎ ነው። ከዩጋንዳ፣ ናይጄሪያ እና ሌሎችም ሀገራት የመጡ፣ እንዲሁም ህጋዊ የጉዞ ሰነድ የሌላቸው በርካታ ስደተኞች በአካባቢው ተሰባስበው ይገኛሉ። እነዚህ የውጭ ዜጎች በስርቆት፣ በዝሙት አዳሪነት እና በተለያዩ ወንጀሎች ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውንና ፖሊስም ህጋዊ እርምጃ እየወሰደባቸው መሆኑ ተጠቁሟል።
የህዝቡን የዕለት ተዕለት ስቃይ እና የፖሊስን ሪፖርት ጎን ለጎን ስንመዝነው፣ አንድ ትልቅ የአሰራር እና የትኩረት ክፍተት ይታያል። በአንድ በኩል ህዝቡ እና አረጋውያን እናቶች ጥቃት እየደረሰባቸው ያለው በማለዳው (ጠዋት) የጨለማ ሰዓት መሆኑን እያማረሩ ነው። በሌላ በኩል ግን ፖሊስ ትልቅ እርምጃ እየወሰድኩ ነው ብሎ ያቀረበው ማስረጃ "ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት" የሚያደርገውን አሰሳ ነው። ይህ የሚያሳየው ወንጀለኞቹ የፖሊስን የጥበቃ ሰዓት ክፍተት አጥንተው የዘረፋ ሰዓታቸውን ወደ ጠዋት ማለዳ ሲያሸጋግሩ፣ ፖሊስ ግን አሁንም ትኩረቱን ምሽት ላይ ብቻ ማድረጉን ነው።
ፖሊስ "ለሚዲያ ፍጆታ ሳይሆን በተግባር እየሰራሁ ነው" ማለቱ የሚበረታታ ቢሆንም ስኬቱ ሊለካ የሚገባው በተያዙ ስልኮች ብዛት ብቻ ሳይሆን በማለዳ ወደ ቤተክርስቲያን እና ወደ ስራ የሚወጣው ነዋሪ በሚያገኘው የደህንነት ዋስትና ነው። በመሆኑም የጸጥታ አካላት የኦፕሬሽን ስልታቸውን እና የሰዓት ስምሪታቸውን ነዋሪው እየተጠቃበት ካለው የማለዳ ሰዓት ጋር ሊያስተካክሉ ይገባል። ፖሊስ አደረግኩት የሚለው ኦፕሬሽን በተግባር የህዝቡን ስጋት እስካላቀለለ ድረስ፣ "ቸልተኝነት አለ" የሚለው የህዝብ ቅሬታ መቀጠሉ አይቀርም።
#ዘሐበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በመዲናዋ አዲስ አበባ በተለይም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ ሰሚት፣ ገርጂ እና አካባቢው ከመቼውም ጊዜ በላይ የተበራከተው የማጅራት መምታት እና የንጥቂያ ወንጀል የነዋሪውን ደህንነት ክፉኛ እየፈተነ ይገኛል። የወንጀሉ ገጽታ እና የጸጥታ አካላት እየወሰዱት ያለው እርምጃ ነዋሪዎችን እና የፖሊስ ኃላፊዎችን እያወዛገበ ሲሆን፣ የህዝቡን ስጋት እና የፖሊስን ምላሽ እንደሚከተለው አጠናቅረነዋል።
እንደ ነዋሪዎች እና ስማቸው እንዳይጠቀስ ከፈለጉ የውስጥ ፖሊስ አባላት ዘ-ሐበሻ ባገኘው መረጃ፣ የዘረፋው ወንጀል መልኩን ቀይሮ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ለወትሮው በምሽት ይፈጸም የነበረው ማጅራት መምታት፣ አሁን የክረምቱን መግባት እና የጠዋቱን ጨለማ እንደ ሽፋን በመጠቀም ወደ ማለዳ ተሸጋግሯል።
የዚህ አዲስ የማለዳ ላይ ጥቃት ዋነኛ ሰለባ እየሆኑ ያሉት ደግሞ፣ ጠዋት በጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን የሚያመሩ አረጋውያን እናቶች ናቸው። ይህ በየዕለቱ እየተፈጸመ ያለ አስነዋሪ ድርጊት ቢሆንም፣ የፖሊስ የበላይ ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት ከማሰብ ይልቅ ጉዳዩን አድበስብሶ ማለፍን መርጠዋል የሚል ጠንካራ ወቀሳ ከውስጥ ምንጮች ቀርቧል። "የህዝቡ ስቃይ ዝም ተብሎ ስለታለፈ እና ኃላፊዎች እርምጃ ባለመውሰዳቸው መረጃውን ለሚዲያ አድርሰናል" ያሉት የውስጥ ምንጮች፣ ተቋማዊ ቸልተኝነት መኖሩን በጽኑ ተችተዋል።
በተነሳው የ"ቸልተኝነት እና የዝምታ" ክስ ላይ ምላሽ የሰጡን የፖሊስ ኃላፊዎች፣ ተቋሙ በምንም መልኩ ዝምታን እንዳልመረጠ አስታውቀዋል። ኃላፊው ለቀረበባቸው ወቀሳ በሰጡት ምላሽ፣ ፖሊስ ወንጀለኞች በስፋት ይንቀሳቀሱባቸዋል የተባሉትን ሰሚት፣ ገርጂ እና 'ጥላሁን' የተባሉ አካባቢዎችን ለይቶ ሰፊ የጸጥታ ማስከበር አሰሳ እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ወንጀለኞች የሚሰባሰቡባቸውን ህገ-ወጥ የሺሻ ቤቶችን የማፍረስ ስራ እየተሰራ ሲሆን፣ በአንድ ቀን በተደረገ ኦፕሬሽን ብቻ 80 ያህል የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ማስመለስ መቻሉን ፖሊስ በምላሹ አስረድቷል። ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት ድረስ የዘለቀ ጥብቅ አሰሳ በየቀኑ እየተካሄደ መሆኑንም አክለዋል።
ከዚህ ቀደም የነበሩ አመራሮች የጸጥታ ስራዎችን ለሚዲያ ፍጆታ ይጠቀሙበት እንደነበር የወቀሱት ኃላፊው፣ "አሁን ያለው የጸጥታ መዋቅር ማወናበድ ሳይሆን በተጨባጭ ወንጀልን ከስረ-መሰረቱ ለማጥፋት ትልቅ ኦፕሬሽን እየሰራ ስለሆነ ነው እንጂ የተኛንበት ጊዜ የለም" ሲሉ ተከራክረዋል።
በፖሊስ ኃላፊው ምላሽ ውስጥ ጎልቶ የወጣው ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ በነዚህ አካባቢዎች ያለው የውጭ ዜጎች ወንጀል ተሳትፎ ነው። ከዩጋንዳ፣ ናይጄሪያ እና ሌሎችም ሀገራት የመጡ፣ እንዲሁም ህጋዊ የጉዞ ሰነድ የሌላቸው በርካታ ስደተኞች በአካባቢው ተሰባስበው ይገኛሉ። እነዚህ የውጭ ዜጎች በስርቆት፣ በዝሙት አዳሪነት እና በተለያዩ ወንጀሎች ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውንና ፖሊስም ህጋዊ እርምጃ እየወሰደባቸው መሆኑ ተጠቁሟል።
የህዝቡን የዕለት ተዕለት ስቃይ እና የፖሊስን ሪፖርት ጎን ለጎን ስንመዝነው፣ አንድ ትልቅ የአሰራር እና የትኩረት ክፍተት ይታያል። በአንድ በኩል ህዝቡ እና አረጋውያን እናቶች ጥቃት እየደረሰባቸው ያለው በማለዳው (ጠዋት) የጨለማ ሰዓት መሆኑን እያማረሩ ነው። በሌላ በኩል ግን ፖሊስ ትልቅ እርምጃ እየወሰድኩ ነው ብሎ ያቀረበው ማስረጃ "ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት" የሚያደርገውን አሰሳ ነው። ይህ የሚያሳየው ወንጀለኞቹ የፖሊስን የጥበቃ ሰዓት ክፍተት አጥንተው የዘረፋ ሰዓታቸውን ወደ ጠዋት ማለዳ ሲያሸጋግሩ፣ ፖሊስ ግን አሁንም ትኩረቱን ምሽት ላይ ብቻ ማድረጉን ነው።
ፖሊስ "ለሚዲያ ፍጆታ ሳይሆን በተግባር እየሰራሁ ነው" ማለቱ የሚበረታታ ቢሆንም ስኬቱ ሊለካ የሚገባው በተያዙ ስልኮች ብዛት ብቻ ሳይሆን በማለዳ ወደ ቤተክርስቲያን እና ወደ ስራ የሚወጣው ነዋሪ በሚያገኘው የደህንነት ዋስትና ነው። በመሆኑም የጸጥታ አካላት የኦፕሬሽን ስልታቸውን እና የሰዓት ስምሪታቸውን ነዋሪው እየተጠቃበት ካለው የማለዳ ሰዓት ጋር ሊያስተካክሉ ይገባል። ፖሊስ አደረግኩት የሚለው ኦፕሬሽን በተግባር የህዝቡን ስጋት እስካላቀለለ ድረስ፣ "ቸልተኝነት አለ" የሚለው የህዝብ ቅሬታ መቀጠሉ አይቀርም።
#ዘሐበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17👍5
ህወሓት ዳግም ያቋቋመው የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ሀገራዊ የምክክር መድረኩን ውድቅ በማድረግ በሂደቱ ላይ እንደማይሳተፍ አስታወቀ
በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሃት) ዳግም የተቋቋመው የትግራይ ክልላዊ መንግሥት እየተካሄደ ያለውን ሀገራዊ የምክክር ሂደት ውድቅ ማድረጉን ያስታወቀ ሲሆን፥ «ተቀባይነት የሌለው» ሲል በገለጸው የውይይት መድረክ ላይ የክልሉ መንግሥትም ሆነ የትግራይ ሕዝብ አልተወከሉም ብሏል።
የትግራይ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ትናንት ባወጣው መግለጫ፥ መድረኩ የትግራይ ሕዝብ የሚጋፈጣቸውን መሠረታዊ ጥያቄዎች መመለስ አልቻለም በሚል አስተዳደሩ በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ላይ እንደማይሳተፍ አስታውቋል። ቢሮው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የፌዴራል መንግሥት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ቁልፍ ድንጋጌዎችን ተግባራዊ አላደረገም ሲል የከሰሰ ሲሆን፥ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ቢፈረምም ትግራይ አሁንም ከባድ ሰብአዊ፣ ፖለቲካዊ እና የደኅንነት ተግዳሮቶች እየገጠሟት ይገኛል ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሃት) ዳግም የተቋቋመው የትግራይ ክልላዊ መንግሥት እየተካሄደ ያለውን ሀገራዊ የምክክር ሂደት ውድቅ ማድረጉን ያስታወቀ ሲሆን፥ «ተቀባይነት የሌለው» ሲል በገለጸው የውይይት መድረክ ላይ የክልሉ መንግሥትም ሆነ የትግራይ ሕዝብ አልተወከሉም ብሏል።
የትግራይ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ትናንት ባወጣው መግለጫ፥ መድረኩ የትግራይ ሕዝብ የሚጋፈጣቸውን መሠረታዊ ጥያቄዎች መመለስ አልቻለም በሚል አስተዳደሩ በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ላይ እንደማይሳተፍ አስታውቋል። ቢሮው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የፌዴራል መንግሥት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ቁልፍ ድንጋጌዎችን ተግባራዊ አላደረገም ሲል የከሰሰ ሲሆን፥ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ቢፈረምም ትግራይ አሁንም ከባድ ሰብአዊ፣ ፖለቲካዊ እና የደኅንነት ተግዳሮቶች እየገጠሟት ይገኛል ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15🤪7👍5🤣3🤯2
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አጋሮች የቀነሰባቸውን 2.8 በመቶ ድርሻ መልሰው የመግዛት መብት እንዳላቸው ተገለጸ
ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚንቀሳቀሰው ቅርንጫፍ ኩባንያው ያደረገውን ተጨማሪ የካፒታል ኢንቨስትመንት ተከትሎ፣ ሌሎች አብረውት ኢንቨስት ያደረጉ አጋሮቹ ያጡትን የ2.78 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ መልሰው የመግዛት መብታቸው የተጠበቀ መሆኑን አስታወቀ።
የቴሌኮም ኩባንያው እና ደቡብ አፍሪካዊው የእናት ኩባንያው ቮዳኮም ግሩፕ ‘ቮዳፋሚሊ ኢትዮጵያ ሆልዲንግ’ በተሰኘው የኢንቨስትመንት ተቋማቸው አማካኝነት፣ እስከ እኤአ መጋቢት 2026 በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 21.3 ቢሊዮን የኬንያ ሺሊንግ የሚያወጣ የካፒታል ማሰባሰቢያ ጥሪ ላይ ብቻቸውን ተሳትፈዋል።
ይህንን የካፒታል ማሳደግ ጥሪ ሳፋሪኮም እና ቮዳኮም ብቻቸውን በመሸፈናቸው በኢትዮጵያው ኩባንያ ውስጥ የነበራቸውን ጥምር ድርሻ ከ57.41 በመቶ ወደ 60.19 በመቶ ከፍ ማድረግ ችለዋል። ይህ እርምጃ እንደ ሱሚቶሞ ኮርፖሬሽን ፣ ብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ያሉትን ሌሎች አጋር ኩባንያዎች የነበራቸውን የባለቤትነት ድርሻ እንዲቀንስ አድርጎት ነበር።
ይሁን እንጂ ሳፋሪኮም አጋሮቹ የተዳከመውን ድርሻቸውን ወደነበረበት ለመመለስና ያጡትን የ2.78 በመቶ ድርሻ መልሰው መግዛት የሚችሉበት ሕጋዊ መብት እንዳላቸው በይፋ አረጋግጧል።
ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን የኔትወርክ ተደራሽነት ለማስፋፋት እና የንግድ እንቅስቃሴውን ለማጠናከር ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እያፈሰሰ የሚገኝ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እስከ መጋቢት 2027 ዓ.ም ድረስ ወጪና ገቢውን አጣጥሞ ሙሉ በሙሉ ትርፋማ መሆን እንደሚጀምር ግምቱን አስቀምጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚንቀሳቀሰው ቅርንጫፍ ኩባንያው ያደረገውን ተጨማሪ የካፒታል ኢንቨስትመንት ተከትሎ፣ ሌሎች አብረውት ኢንቨስት ያደረጉ አጋሮቹ ያጡትን የ2.78 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ መልሰው የመግዛት መብታቸው የተጠበቀ መሆኑን አስታወቀ።
የቴሌኮም ኩባንያው እና ደቡብ አፍሪካዊው የእናት ኩባንያው ቮዳኮም ግሩፕ ‘ቮዳፋሚሊ ኢትዮጵያ ሆልዲንግ’ በተሰኘው የኢንቨስትመንት ተቋማቸው አማካኝነት፣ እስከ እኤአ መጋቢት 2026 በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 21.3 ቢሊዮን የኬንያ ሺሊንግ የሚያወጣ የካፒታል ማሰባሰቢያ ጥሪ ላይ ብቻቸውን ተሳትፈዋል።
ይህንን የካፒታል ማሳደግ ጥሪ ሳፋሪኮም እና ቮዳኮም ብቻቸውን በመሸፈናቸው በኢትዮጵያው ኩባንያ ውስጥ የነበራቸውን ጥምር ድርሻ ከ57.41 በመቶ ወደ 60.19 በመቶ ከፍ ማድረግ ችለዋል። ይህ እርምጃ እንደ ሱሚቶሞ ኮርፖሬሽን ፣ ብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ያሉትን ሌሎች አጋር ኩባንያዎች የነበራቸውን የባለቤትነት ድርሻ እንዲቀንስ አድርጎት ነበር።
ይሁን እንጂ ሳፋሪኮም አጋሮቹ የተዳከመውን ድርሻቸውን ወደነበረበት ለመመለስና ያጡትን የ2.78 በመቶ ድርሻ መልሰው መግዛት የሚችሉበት ሕጋዊ መብት እንዳላቸው በይፋ አረጋግጧል።
ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን የኔትወርክ ተደራሽነት ለማስፋፋት እና የንግድ እንቅስቃሴውን ለማጠናከር ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እያፈሰሰ የሚገኝ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እስከ መጋቢት 2027 ዓ.ም ድረስ ወጪና ገቢውን አጣጥሞ ሙሉ በሙሉ ትርፋማ መሆን እንደሚጀምር ግምቱን አስቀምጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12👍7
የአዲስ አበባ ታክሲዎች ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት ክፍያ እንዲሰበስቡ ተወሰነ
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከተወሰነው ታሪፍ በላይ እንዲሚያስከፍሉ ከማኅበረሰቡ የሚነሳውን ቅሬታ ለመፍታት ክፍያው ከመነሻው እንዲሰበሰብ የሚያስገድድ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስታውቋል።
አሽከርካሪዎች በታሪፍ መመሪያው መሠረት ብቻ ከመነሻው የትራንስፖርት ክፍያ እንዲሰበስቡ ለማስቻል ተቆጣጣሪዎች በመነሻ መጫኛ ቦታዎች ላይ ተመድበው ሥራ መጀመራቸውን የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ተናግረዋል።
ይህ አሠራር በጉዞ ወቅት "ሒሳብ ጨምሩ" በሚል ከአሽከርካሪዎች የሚነሳውን አግባብነት የሌለው ጥያቄ ለመግታት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል።
ይሁን እንጂ አዲሱ አሠራር ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ አንዳንድ ተግዳሮቶች መፈጠራቸውን የቢሮው ኃላፊዎች ጠቁመዋል።
በከተማዋ በሚገኙ መነሻዎች ላይ ክፍያውን አስቀድሞ በመሰብሰብ ሂደት የተወሰነ ጊዜ እየወሰደ መሆኑ በማኅበረሰቡ በኩል ቅሬታ መፍጠሩ ተገልጿል።
በተመሳሳይ አንዳንድ አሽከርካሪዎች መንገድ ከጀመሩ በኋላ ታሪፍ የመጨመር አዝማሚያዎችን እያሳዩ መሆናቸውን ቢሮው አስታውቋል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ ማኅበረሰቡ የጉዳዩን ፋይዳ በመገንዘብ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግና ህገ-ወጥ አሽከርካሪዎችን በተመለከተ ጥቆማዎችን በመስጠት የዜግነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አቶ ዳኛቸው አሳስበዋል።
በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም ያለ ረዳት በሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ሲገለጽ መቆየቱ የሚታወስ ቢሆንም፤ ቢሮው በአሁኑ ወቅት ትኩረቱን አዲሱ የአሠራር ሥርዓት ላይ ማድረጉን አመልክቷል።
ይሁን እንጂ የረዳት አጠቃቀምን በተመለከተ ግልጽና ወጥ የሆነ የአሠራር ሥርዓት እንደሚያስፈልግ አቶ ዳኛቸው ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከተወሰነው ታሪፍ በላይ እንዲሚያስከፍሉ ከማኅበረሰቡ የሚነሳውን ቅሬታ ለመፍታት ክፍያው ከመነሻው እንዲሰበሰብ የሚያስገድድ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስታውቋል።
አሽከርካሪዎች በታሪፍ መመሪያው መሠረት ብቻ ከመነሻው የትራንስፖርት ክፍያ እንዲሰበስቡ ለማስቻል ተቆጣጣሪዎች በመነሻ መጫኛ ቦታዎች ላይ ተመድበው ሥራ መጀመራቸውን የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ተናግረዋል።
ይህ አሠራር በጉዞ ወቅት "ሒሳብ ጨምሩ" በሚል ከአሽከርካሪዎች የሚነሳውን አግባብነት የሌለው ጥያቄ ለመግታት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል።
ይሁን እንጂ አዲሱ አሠራር ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ አንዳንድ ተግዳሮቶች መፈጠራቸውን የቢሮው ኃላፊዎች ጠቁመዋል።
በከተማዋ በሚገኙ መነሻዎች ላይ ክፍያውን አስቀድሞ በመሰብሰብ ሂደት የተወሰነ ጊዜ እየወሰደ መሆኑ በማኅበረሰቡ በኩል ቅሬታ መፍጠሩ ተገልጿል።
በተመሳሳይ አንዳንድ አሽከርካሪዎች መንገድ ከጀመሩ በኋላ ታሪፍ የመጨመር አዝማሚያዎችን እያሳዩ መሆናቸውን ቢሮው አስታውቋል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ ማኅበረሰቡ የጉዳዩን ፋይዳ በመገንዘብ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግና ህገ-ወጥ አሽከርካሪዎችን በተመለከተ ጥቆማዎችን በመስጠት የዜግነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አቶ ዳኛቸው አሳስበዋል።
በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም ያለ ረዳት በሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ሲገለጽ መቆየቱ የሚታወስ ቢሆንም፤ ቢሮው በአሁኑ ወቅት ትኩረቱን አዲሱ የአሠራር ሥርዓት ላይ ማድረጉን አመልክቷል።
ይሁን እንጂ የረዳት አጠቃቀምን በተመለከተ ግልጽና ወጥ የሆነ የአሠራር ሥርዓት እንደሚያስፈልግ አቶ ዳኛቸው ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤35👍9🤔1
ኢትዮጵያ ዛሬ 180 ሚሊየን ዶላር (29 ቢሊየን ብር) እዳዋን ዘጭ አድርጋ እንደምትከፍል የሚጠበቅበት ቀን ነው!
👉ሌላ 100 ሚሊየን ዶላር ሊኖር ይችላል
ኢትዮጵያ እና የዩሮቦንድ ባለይዞታዎች ከሰሞኑ በደረሱበት የቴክኒክ ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ካለባት እዳ ውስጥ 180 ሚሊየን ዶላሩን ዛሬ መክፈል ይጠበቅባታል፡፡
የእዳ መልሶ ማዋቀር ስምምነቱ ሲደረስ ከታህሳስ 2016 እስከ ታህሳስ 2017 ዓም መከፈል የሚገባቸው ሶስት የወለድ ክፍያዎች በጥቅሉ 100 ሚሊየን ዶላር በአንዴ መከፈል የሚገባው መሆኑ ይታወሳል፡፡
በመርህ ደረጃ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ቀሪ
👉100 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2027
👉300 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2028
👉300 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2029 የሚከፈል ይሆናል።
አሁን ጥያቄው የዛሬውን እሺ ያንን የሚያክል ገንዘብ በአንዴ የመክፈል አቅም ይኖረናል ወይ? ነው ጥያቄው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👉ሌላ 100 ሚሊየን ዶላር ሊኖር ይችላል
ኢትዮጵያ እና የዩሮቦንድ ባለይዞታዎች ከሰሞኑ በደረሱበት የቴክኒክ ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ካለባት እዳ ውስጥ 180 ሚሊየን ዶላሩን ዛሬ መክፈል ይጠበቅባታል፡፡
የእዳ መልሶ ማዋቀር ስምምነቱ ሲደረስ ከታህሳስ 2016 እስከ ታህሳስ 2017 ዓም መከፈል የሚገባቸው ሶስት የወለድ ክፍያዎች በጥቅሉ 100 ሚሊየን ዶላር በአንዴ መከፈል የሚገባው መሆኑ ይታወሳል፡፡
በመርህ ደረጃ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ቀሪ
👉100 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2027
👉300 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2028
👉300 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2029 የሚከፈል ይሆናል።
አሁን ጥያቄው የዛሬውን እሺ ያንን የሚያክል ገንዘብ በአንዴ የመክፈል አቅም ይኖረናል ወይ? ነው ጥያቄው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7😢7👍4👀1🤪1
ያልተመረጠ መንግሥት ከቀይ ባሕር አባሮናል‼️
‹‹በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች መልዕክት አለኝ›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ
‹‹በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች መልዕክት አለኝ፤ ከብቱን መርጠን የምንገዛ እኛ ነን፤ የቅርጫውን ባለቤት የምንወስን እኛ ነን፤ የተረፈንን የማንፈልገውን ካልሆነ በቀር የትኛውን አሞራ በጉልበት ከየትኛውም የቅርጫ መደብ ላይ አንዲት ኪሎ ስጋ መውሰድ እንደማይችል ላረጋግጥላቸው እፈልጋለሁ፤ ስንፈልግ ለማጋት ዝግጁ ነን፤ ከፍቃዳችን ውጪ ግን ለሺህ አመታት የኖረች ኢትዮጵያን አሁን ባለው ፕሮፓጋንዳ ትዘናጋለች ጥቅሟን አሳልፋ ትሰጣለች ብሎ ማሰብ ከንቱ ምኞት ነው›› ያሉ ሲሆን ‹ያልተመረጠ መንግሥት በሸፍጥ ከቀይ ባህር አባረረን ብለዋል።
‹‹ኢትዮጵያ ለዘመናት ያስከበረችውን ቀይ ባህር ያልተመረጠ መንግሥት በሸፍጥ የጂኦግራፊ እስረኛ ያደረገበት ምክንያት በውስጣችን ያለ ስንፍና እንጂ የኢትዮጵያን መሻት እና ጥቅም ማስቆም የሚችል ኃይል ስለነበረ አይደለም›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በአገራዊ ምክክር ጉባኤ መክፈቻ ላይ ከተናገሩት ተቀንጭቦ የተወሰደ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
‹‹በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች መልዕክት አለኝ›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ
‹‹በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች መልዕክት አለኝ፤ ከብቱን መርጠን የምንገዛ እኛ ነን፤ የቅርጫውን ባለቤት የምንወስን እኛ ነን፤ የተረፈንን የማንፈልገውን ካልሆነ በቀር የትኛውን አሞራ በጉልበት ከየትኛውም የቅርጫ መደብ ላይ አንዲት ኪሎ ስጋ መውሰድ እንደማይችል ላረጋግጥላቸው እፈልጋለሁ፤ ስንፈልግ ለማጋት ዝግጁ ነን፤ ከፍቃዳችን ውጪ ግን ለሺህ አመታት የኖረች ኢትዮጵያን አሁን ባለው ፕሮፓጋንዳ ትዘናጋለች ጥቅሟን አሳልፋ ትሰጣለች ብሎ ማሰብ ከንቱ ምኞት ነው›› ያሉ ሲሆን ‹ያልተመረጠ መንግሥት በሸፍጥ ከቀይ ባህር አባረረን ብለዋል።
‹‹ኢትዮጵያ ለዘመናት ያስከበረችውን ቀይ ባህር ያልተመረጠ መንግሥት በሸፍጥ የጂኦግራፊ እስረኛ ያደረገበት ምክንያት በውስጣችን ያለ ስንፍና እንጂ የኢትዮጵያን መሻት እና ጥቅም ማስቆም የሚችል ኃይል ስለነበረ አይደለም›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በአገራዊ ምክክር ጉባኤ መክፈቻ ላይ ከተናገሩት ተቀንጭቦ የተወሰደ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20🤪19👍6🤔2😎2
የአውሮፓ ህብረት በሱዳን ወርቅ ላይ ማዕቀብ ጣለ
የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት የሀገሪቱን የጦርነት ኢኮኖሚ ለማዳከም እና የቀጠለውን ግጭት የገንዘብ ምንጭ ለመቀነስ ከሱዳን የሚመጣን ወርቅ መግዛት፣ ማስገባት (ማስመጣት) ወይም ማጓጓዝ ላይ ነው ማዕቀብ የጣለው።
ማዕቀቡ ከሱዳን የሚመጣን ወርቅ መግዛት፣ ወደ ሀገር ማስገባት ወይም ማጓጓዝ ላይ የተጣለ ሙሉ እገዳ ሲሆን ለወርቅ ማዕድን ማውጣት እና ማጣራት ሂደት ውስጥ በስፋት ጥቅም ላይ የሚውሉትን ሜርኩሪ እና ሲያናይድ ኬሚካሎችን ለሱዳን መሸጥ፣ ማቅረብ፣ ማስተላለፍ ወይም መላክ ይከለክላል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ከወርቅ እና ከእነዚህ ኬሚካሎች አቅርቦት ጋር የተያያዙ ቴክኒካዊ እገዛ፣ የፋይናንስ ድጋፍ ማድረግ ህብረቱ አግዷል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት የሀገሪቱን የጦርነት ኢኮኖሚ ለማዳከም እና የቀጠለውን ግጭት የገንዘብ ምንጭ ለመቀነስ ከሱዳን የሚመጣን ወርቅ መግዛት፣ ማስገባት (ማስመጣት) ወይም ማጓጓዝ ላይ ነው ማዕቀብ የጣለው።
ማዕቀቡ ከሱዳን የሚመጣን ወርቅ መግዛት፣ ወደ ሀገር ማስገባት ወይም ማጓጓዝ ላይ የተጣለ ሙሉ እገዳ ሲሆን ለወርቅ ማዕድን ማውጣት እና ማጣራት ሂደት ውስጥ በስፋት ጥቅም ላይ የሚውሉትን ሜርኩሪ እና ሲያናይድ ኬሚካሎችን ለሱዳን መሸጥ፣ ማቅረብ፣ ማስተላለፍ ወይም መላክ ይከለክላል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ከወርቅ እና ከእነዚህ ኬሚካሎች አቅርቦት ጋር የተያያዙ ቴክኒካዊ እገዛ፣ የፋይናንስ ድጋፍ ማድረግ ህብረቱ አግዷል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍3
ያገለገሉ ንብረቶችን በመሸጥ ከ411.5 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱ ተነገረ
የመንግስት ግዥ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት ካከናወናቸው ተግባራት መካከል በሽያጭ ከተወገዱ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች እና ልዩ ልዩ ንብረቶች ከ411.5 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን አስታወቀ። ይህ የተገኘው ገቢ የዕቅዱን 103 ፐርሰንት ያሳካ ሲሆን በአገልግሎቱ ታሪክ ከፍተኛው ሆኖ መመዝገብ ተመላክቷል።
የአገልግሎቱ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ረድኤት ተክሉ በበጀት ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ እንደገለጹት፥ ተቋሙ በስትራቴጂ እና በማዕቀፍ ስምምነት ግዥ 15.6 ቢሊየን ብር የሚያወጡ 74 ውሎችን ተፈራርሟል።
በተጨማሪም ለማዕቀፍ ስምምነት ዕቃዎች ግዥ ከ9.2 ቢሊየን ብር በላይ ለአሸናፊ ተጫራቾች የአሸናፊነት ደብዳቤ ተሰጥቶ ውል እንደተገባ አስረድተዋል።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ አስማረ ይገዙ በበኩላቸው፥ በ2018 በጀት ዓመት ያልተከናወኑ ተግባራትን በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውስጥ በማካተት፣ አሰራርን በማዘመን እና ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ በማድረግ ከአሁኑ በበለጠ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባም ዋና ዳይሬክተሩ አሳስበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የመንግስት ግዥ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት ካከናወናቸው ተግባራት መካከል በሽያጭ ከተወገዱ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች እና ልዩ ልዩ ንብረቶች ከ411.5 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን አስታወቀ። ይህ የተገኘው ገቢ የዕቅዱን 103 ፐርሰንት ያሳካ ሲሆን በአገልግሎቱ ታሪክ ከፍተኛው ሆኖ መመዝገብ ተመላክቷል።
የአገልግሎቱ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ረድኤት ተክሉ በበጀት ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ እንደገለጹት፥ ተቋሙ በስትራቴጂ እና በማዕቀፍ ስምምነት ግዥ 15.6 ቢሊየን ብር የሚያወጡ 74 ውሎችን ተፈራርሟል።
በተጨማሪም ለማዕቀፍ ስምምነት ዕቃዎች ግዥ ከ9.2 ቢሊየን ብር በላይ ለአሸናፊ ተጫራቾች የአሸናፊነት ደብዳቤ ተሰጥቶ ውል እንደተገባ አስረድተዋል።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ አስማረ ይገዙ በበኩላቸው፥ በ2018 በጀት ዓመት ያልተከናወኑ ተግባራትን በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውስጥ በማካተት፣ አሰራርን በማዘመን እና ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ በማድረግ ከአሁኑ በበለጠ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባም ዋና ዳይሬክተሩ አሳስበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11🤣6👍3
“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል፤ ያደፈጡ፣ የሚነቁ፣ የዘመናት ያልተቋረጠ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ።
ኢትዮጵያ “በቀጣይ” አዲስ ህገ መንግስት ሊኖራት እንደሚችልም ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 8፤ በይፋ በተከፈተው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጥተዋል።
ጠ/ሚኒስትሩ በዚሁ ንግግራቸው ከሀገራዊ ጉባኤው የሚጠበቁ ጉዳዮችን እና በምክክሩ ይሳካሉ ብለው የሚጠብቋቸውን ጉዳዮች አንስተዋል።
“አሁን የምንመካከረው ስለ ትላንትናው አይደለም። የትላንትን ችግር ፈተን ለነገ መልካም መሰረት ለማኖር ነው” ሲሉ አብይ ከሀገራዊ ጉባኤው የሚጠበቀውን አመልክተዋል።
“የአሜሪካ ህገ መንግስት በ55 ሰዎች ቢሰራም ልባም ነበሩና ለምዕተ ዓመታት የሚቆይ ስራ ሰርተዋል። የእኛ አራት ሺህ ሰዎች ከእነሱ በላይ፣ ከእነሱ በተሻለ ጊዜ ይበልጥ ልባም ሆነው፣ ሁሉን ወገን፣ መላው ኢትዮጵያን የሚሰበስብ ምክክር ቢያደርጉ፤ በቀጣይ የሚኖረን ህገመንግስት ከዚህ ቀደም እንደለመድነው የመጣ ሁሉ የሚቀደው ሳይሆን፤ እኛ በአራት ሺህ ጀምረናል፣ በ10 ሺህ ምክክር ሳይደርግ፤ አንድም ሰው መቀየር አይችልም ማለት ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል።
ጠ/ሚኒስትሩ ስለ ቀይ ባህር ጉዳይ በተለይ ሲናገሩ፣ "ኢትዮጵያ ለሺ ዘመናት ያስተዳደረችውን፣ በባለቤትነት የያዘችውን፣ ለራሷም ለከባቢውም መጠቀሚያ ያኖረችውን ቀይ ባህር ያልተመረጠ መንግስት፣ ያልተወያየ መንግስት በሸፍጥ ኢትዮጵያን የጂኦግራፊ እስረኛ እንዲያደርግ ያደረገበት ዋናው ምክንያት በውስጥ ያለን ስንፍና እንጂ የኢትዮጵያን መሻትና ጥቅም ማስቆም የሚችል ኃይል ስለነበረ፣ ስላለ፣ ስለሚኖር አይደለም " ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኢትዮጵያ “በቀጣይ” አዲስ ህገ መንግስት ሊኖራት እንደሚችልም ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 8፤ በይፋ በተከፈተው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጥተዋል።
ጠ/ሚኒስትሩ በዚሁ ንግግራቸው ከሀገራዊ ጉባኤው የሚጠበቁ ጉዳዮችን እና በምክክሩ ይሳካሉ ብለው የሚጠብቋቸውን ጉዳዮች አንስተዋል።
“አሁን የምንመካከረው ስለ ትላንትናው አይደለም። የትላንትን ችግር ፈተን ለነገ መልካም መሰረት ለማኖር ነው” ሲሉ አብይ ከሀገራዊ ጉባኤው የሚጠበቀውን አመልክተዋል።
“የአሜሪካ ህገ መንግስት በ55 ሰዎች ቢሰራም ልባም ነበሩና ለምዕተ ዓመታት የሚቆይ ስራ ሰርተዋል። የእኛ አራት ሺህ ሰዎች ከእነሱ በላይ፣ ከእነሱ በተሻለ ጊዜ ይበልጥ ልባም ሆነው፣ ሁሉን ወገን፣ መላው ኢትዮጵያን የሚሰበስብ ምክክር ቢያደርጉ፤ በቀጣይ የሚኖረን ህገመንግስት ከዚህ ቀደም እንደለመድነው የመጣ ሁሉ የሚቀደው ሳይሆን፤ እኛ በአራት ሺህ ጀምረናል፣ በ10 ሺህ ምክክር ሳይደርግ፤ አንድም ሰው መቀየር አይችልም ማለት ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል።
ጠ/ሚኒስትሩ ስለ ቀይ ባህር ጉዳይ በተለይ ሲናገሩ፣ "ኢትዮጵያ ለሺ ዘመናት ያስተዳደረችውን፣ በባለቤትነት የያዘችውን፣ ለራሷም ለከባቢውም መጠቀሚያ ያኖረችውን ቀይ ባህር ያልተመረጠ መንግስት፣ ያልተወያየ መንግስት በሸፍጥ ኢትዮጵያን የጂኦግራፊ እስረኛ እንዲያደርግ ያደረገበት ዋናው ምክንያት በውስጥ ያለን ስንፍና እንጂ የኢትዮጵያን መሻትና ጥቅም ማስቆም የሚችል ኃይል ስለነበረ፣ ስላለ፣ ስለሚኖር አይደለም " ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20🤣8👍4🤔1🤪1
#እጅግ በጣም አስቸኳይ መልዕክት‼️
ከዲፕሎማ ወደ ድግሪ ትምህርታቸውን በክረምት መርሃግብር ለመማር ዕድል የሚያገኙ መምህራን በሐምሌ 11/2018 የ12 ክፍል ተማሪዎች በተፈተኑበት ማዕከላት ፈተና ስለሚሰጥ በቶሎ ተዘጋጅተው ወደ ማዕከላቱ እንዲደርሱ ደብዳቤ ተጽፏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከዲፕሎማ ወደ ድግሪ ትምህርታቸውን በክረምት መርሃግብር ለመማር ዕድል የሚያገኙ መምህራን በሐምሌ 11/2018 የ12 ክፍል ተማሪዎች በተፈተኑበት ማዕከላት ፈተና ስለሚሰጥ በቶሎ ተዘጋጅተው ወደ ማዕከላቱ እንዲደርሱ ደብዳቤ ተጽፏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7👍5🥰1