በሳዑዲ አረቢያ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ጉዳይ በቅርበት እየተከታተልኩ ነው፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ በሳዑዲ አረቢያ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ፣ በተለይም የሕግ ሂደቶችና የፍርድ እርምጃዎችን እየጠበቁ ካሉ ዜጎች ጋር በተያያዘ ከሚመለከታቸው የሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየተሳተፈ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት በውጭ አገር ለሚኖሩ ዜጎቹ ደህንነት፣ ጥበቃ እና ቆንስላዊ ድጋፍ ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል ያለው ሚኒስቴሩ፣ በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ጋር በከፍተኛ የመንግሥት የሥልጣን እርከን ግንኙነቱን ቀጥሏል ብሏል፡፡
በተጨማሪም ሚኒስቴሩ በሪያድ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና በጅዳ በሚገኘው ጠቅላላ ቆንስላ በኩል፣ ዜጎች ሰብዓዊ አያያዝ እንዲደረግላቸው፣ የቆንስላ ድጋፍ እንዲያገኙ እና አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች ተገቢው መፍትሔ እንዲፈለግ ከሚመለከታቸው የሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር መደበኛ እና ገንቢ ግንኙነት እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ በሳዑዲ አረቢያ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ፣ በተለይም የሕግ ሂደቶችና የፍርድ እርምጃዎችን እየጠበቁ ካሉ ዜጎች ጋር በተያያዘ ከሚመለከታቸው የሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየተሳተፈ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት በውጭ አገር ለሚኖሩ ዜጎቹ ደህንነት፣ ጥበቃ እና ቆንስላዊ ድጋፍ ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል ያለው ሚኒስቴሩ፣ በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ጋር በከፍተኛ የመንግሥት የሥልጣን እርከን ግንኙነቱን ቀጥሏል ብሏል፡፡
በተጨማሪም ሚኒስቴሩ በሪያድ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና በጅዳ በሚገኘው ጠቅላላ ቆንስላ በኩል፣ ዜጎች ሰብዓዊ አያያዝ እንዲደረግላቸው፣ የቆንስላ ድጋፍ እንዲያገኙ እና አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች ተገቢው መፍትሔ እንዲፈለግ ከሚመለከታቸው የሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር መደበኛ እና ገንቢ ግንኙነት እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤4👍2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በቦሌ አትላስ አካባቢ በጣለው ከባድ ዝናብና ንፋስ በአንድ ተሽከርካሪ ላይ ጉዳት ደረሰ
በትናንትናው ዕለት ከላይ በቪዲዮ እንደምትመለከቱት በአስደንጋጭ ሁኔታበዋና ከተማዋ ቦሌ አትላስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጣለው ኃይለኛ ዝናብ እና በነፈሰው ብርቱ ንፋስ ምክንያት...
ከአንድ የግንባታ ቦታ ላይ የብረት ቁሳቁሶች ተፈንቅለው በመውደቃቸው በአቅራቢያው በነበረ ዘመናዊ መኪና ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ታውቋል።
ምንም እንኳን በንብረት ላይ አደጋው ጉዳት ቢያስከትልም፣ በአምላክ ምስጋና ይግባና በአደጋው ወቅት በሰው ሕይወትም ሆነ አካል ላይ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደሌለ ተረጋግጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በትናንትናው ዕለት ከላይ በቪዲዮ እንደምትመለከቱት በአስደንጋጭ ሁኔታበዋና ከተማዋ ቦሌ አትላስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጣለው ኃይለኛ ዝናብ እና በነፈሰው ብርቱ ንፋስ ምክንያት...
ከአንድ የግንባታ ቦታ ላይ የብረት ቁሳቁሶች ተፈንቅለው በመውደቃቸው በአቅራቢያው በነበረ ዘመናዊ መኪና ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ታውቋል።
ምንም እንኳን በንብረት ላይ አደጋው ጉዳት ቢያስከትልም፣ በአምላክ ምስጋና ይግባና በአደጋው ወቅት በሰው ሕይወትም ሆነ አካል ላይ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደሌለ ተረጋግጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20👍5👀2🤔1🙏1
የቤት ኪራይ አልቀመስ ብሏል‼️
በአዲስ አበባ ከተማ እያጋጠመ ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ መናር ከነዋሪዎች የመክፈል አቅም በላይ እየሆነና ጣሪያ እየነካ መምጣቱ ተሰምቷል።
በአሁኑ ወቅት በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ እያሻቀበ የሚገኝ ሲሆን፣ ለአንድ መደበኛ ክፍል ቤት ከ25 ሺህ እስከ 30 ሺህ የኢትዮጵያ ብር እየተጠየቀ ይገኛል።
ባለ ሁለት እና ባለ ሦስት መኝታ ክፍሎች ደግሞ ዋጋቸው በአስገራሚ ሁኔታ ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ለነዋሪዎች ለመጥራት እንኳ የሚያስፈራ ደረጃ ላይ መድረሱ ተነግሯል።
ይህ የቤት ኪራይ ዋጋ በዚህ ፍጥነት ሊያሽቀበቅብ የቻለባቸው ዋነኛ ምክንያቶች በሀገሪቱ ከተለያዩ አካባቢዎች በጸጥታና አለመረጋጋት ምክንያት ደኅንነት ፍለጋ ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ የሚደረገው ፍልሰት በከተማዋ ያለውን የቤት ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደጉ ነው።
በተጨማሪም በከተማዋ ለኮሪደርና ለተለያዩ ልማቶች ተብለው በርካታ መኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸውን ተከትሎ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች በአንድ ጊዜ ወደ ኪራይ ገበያው እንዲገቡ መገደዳቸው በአቅርቦትና ፍላጎት መካከል ከፍተኛ አለመጣጣም ፈጥሯል።
ይህ ተደራራቢ ጫና ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸውን የከተማዋን ነዋሪዎች ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እየዳረጋቸው ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአዲስ አበባ ከተማ እያጋጠመ ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ መናር ከነዋሪዎች የመክፈል አቅም በላይ እየሆነና ጣሪያ እየነካ መምጣቱ ተሰምቷል።
በአሁኑ ወቅት በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ እያሻቀበ የሚገኝ ሲሆን፣ ለአንድ መደበኛ ክፍል ቤት ከ25 ሺህ እስከ 30 ሺህ የኢትዮጵያ ብር እየተጠየቀ ይገኛል።
ባለ ሁለት እና ባለ ሦስት መኝታ ክፍሎች ደግሞ ዋጋቸው በአስገራሚ ሁኔታ ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ለነዋሪዎች ለመጥራት እንኳ የሚያስፈራ ደረጃ ላይ መድረሱ ተነግሯል።
ይህ የቤት ኪራይ ዋጋ በዚህ ፍጥነት ሊያሽቀበቅብ የቻለባቸው ዋነኛ ምክንያቶች በሀገሪቱ ከተለያዩ አካባቢዎች በጸጥታና አለመረጋጋት ምክንያት ደኅንነት ፍለጋ ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ የሚደረገው ፍልሰት በከተማዋ ያለውን የቤት ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደጉ ነው።
በተጨማሪም በከተማዋ ለኮሪደርና ለተለያዩ ልማቶች ተብለው በርካታ መኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸውን ተከትሎ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች በአንድ ጊዜ ወደ ኪራይ ገበያው እንዲገቡ መገደዳቸው በአቅርቦትና ፍላጎት መካከል ከፍተኛ አለመጣጣም ፈጥሯል።
ይህ ተደራራቢ ጫና ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸውን የከተማዋን ነዋሪዎች ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እየዳረጋቸው ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢41❤17👍2
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ – የሚፈልጓቸውን አዳዲስ ዜናዎችን በአጭሩ እና በጥልቀት ከኛ ዘንድ ያንብቡ።
🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።
🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።
አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy
@sputnik_ethiopia
🔸 ትኩስ ትኩስ እና የሚፈልጓቸውን መረጃዎችን በፎቶ እና በቪዲዮ ይመልከቱ።
🔸 ለውድ ጊዜዎት ዋጋ እንሰጣለን።እርሶም ዋጋ ከሰጡ ፣ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይቀላለሉ: ያልተነገረውን እንናገራለን፤ያልተሰማውን እናበስራለን።
አሁኑኑ ይቀላቀሉን : https://t.me/+C_9-IRD5_Ws0MDgy
@sputnik_ethiopia
👍3❤2
የባንኮች የማበደር ገደብ ተነሳ‼
የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (ቁጥር 7) ስብሰባ ዋና ዋና ውሳኔዎችና የኢኮኖሚ አፈጻጸም አጭር መግለጫ:-
፩. ዋና ዋና የፖሊሲ ውሳኔዎች
📌የብድር ገደብ መነሳት፦ በባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብ (Credit Cap) ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል።
📌 የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ማሻሻያ፦ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ (Policy Rate) በ1.0 በመቶ ነጥብ ከፍ በማለት ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ እንዲያድግ ተደርጓል።
📌 የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ግዴታ (FX Surrender)፦ ላኪዎችና የውጭ ምንዛሬ አስገኚዎች ለባንኮች ገቢ የሚያደርጉት የውጭ ምንዛሬ ግዴታ ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ እንዲል ተወስኗል።
📌 የኮሚሽን ምጣኔ ቅነሳ፦ ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግዢ ጋር ተያይዞ የሚያስከፍሉት የኮሚሽን ምጣኔ ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።
፪. የኢኮኖሚ አፈጻጸም ማጠቃለያ
📌 የኢኮኖሚ ዕድገት፦ በ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድገት 9.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
📌የዋጋ ግሽበት፦ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም. ወደ 13.4 በመቶ ዝቅ ብሏል።
📌 የበጀት ጉድለት፦ የአገሪቱ የበጀት ጉድለት ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አንጻር ወደ 0.9 በመቶ ወርዷል።
📌 የውጭ ኢኮኖሚ ክምችት፦ አጠቃላይ የውጭ ክፍያ ሚዛን ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማሻሻያው ከመደረጉ በፊት ከነበረው አንጻር በ20 እጥፍ አድጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (ቁጥር 7) ስብሰባ ዋና ዋና ውሳኔዎችና የኢኮኖሚ አፈጻጸም አጭር መግለጫ:-
፩. ዋና ዋና የፖሊሲ ውሳኔዎች
📌የብድር ገደብ መነሳት፦ በባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብ (Credit Cap) ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል።
📌 የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ማሻሻያ፦ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ (Policy Rate) በ1.0 በመቶ ነጥብ ከፍ በማለት ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ እንዲያድግ ተደርጓል።
📌 የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ግዴታ (FX Surrender)፦ ላኪዎችና የውጭ ምንዛሬ አስገኚዎች ለባንኮች ገቢ የሚያደርጉት የውጭ ምንዛሬ ግዴታ ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ እንዲል ተወስኗል።
📌 የኮሚሽን ምጣኔ ቅነሳ፦ ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግዢ ጋር ተያይዞ የሚያስከፍሉት የኮሚሽን ምጣኔ ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።
፪. የኢኮኖሚ አፈጻጸም ማጠቃለያ
📌 የኢኮኖሚ ዕድገት፦ በ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድገት 9.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
📌የዋጋ ግሽበት፦ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም. ወደ 13.4 በመቶ ዝቅ ብሏል።
📌 የበጀት ጉድለት፦ የአገሪቱ የበጀት ጉድለት ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አንጻር ወደ 0.9 በመቶ ወርዷል።
📌 የውጭ ኢኮኖሚ ክምችት፦ አጠቃላይ የውጭ ክፍያ ሚዛን ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማሻሻያው ከመደረጉ በፊት ከነበረው አንጻር በ20 እጥፍ አድጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍2
አሜሪካ ለሆርሙዝ ክፍያ ልጠይቅ‼️
ትራምፕ "አሜሪካ የሆርሙዝ ሰርጥ ጠባቂ' አድርገው ማወጃቸውን አስታወቁ።
በዚህም ለሆርሙዝ ሰርጥ ደህንነት ሲባል ዓለም አቀፍ የባህር ላይ ትራንስፖርት 20% ክፍያ እንዲፈጽም አዘዋል። ኢራን በበኩሏ ከራሷ ውጪ ማንም የሆርሙዝ ሰርጥ ደህንነት ጠባቂ እንደማይሆን ገልፃለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ትራምፕ "አሜሪካ የሆርሙዝ ሰርጥ ጠባቂ' አድርገው ማወጃቸውን አስታወቁ።
በዚህም ለሆርሙዝ ሰርጥ ደህንነት ሲባል ዓለም አቀፍ የባህር ላይ ትራንስፖርት 20% ክፍያ እንዲፈጽም አዘዋል። ኢራን በበኩሏ ከራሷ ውጪ ማንም የሆርሙዝ ሰርጥ ደህንነት ጠባቂ እንደማይሆን ገልፃለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍5👀3🤡2🥱1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሟቹ የቀድሞ የኳታር አሚር ለቅሶ ለመድረስ ዶሃ ገቡ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ፣ የቀድሞው የኳታር አሚር ሼክ ሃማድ ቢን ኸሊፋ አል ታኒ ከዚህ ዓለም በሞት መለየትን ተከትሎ የተሰማቸውን ሐዘን ለመግለጽ ዛሬ ሰኞ ዶሃ መድረሳቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩና ልዑካን ቡድናቸው ሃማድ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፤ በኳታር ትራንስፖርት ሚኒስትር ሼክ መሐመድ ቢን አብዱላህ እና በኳታር የኢትዮጵያ አምባሳደር ፈይሰል ኢብራሂም አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ “የእሳቸው ማለፍ ለአፍሪካም ሆነ ለመላው ቀጣና ትልቅ ኪሳራ ነው” ነው ሲሉ የኢሚሩ ሕልፈተ ሕይወት በተሰማ ጊዜ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት የሐዘን መልዕክት ገልጸዋል ሲል ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ፣ የቀድሞው የኳታር አሚር ሼክ ሃማድ ቢን ኸሊፋ አል ታኒ ከዚህ ዓለም በሞት መለየትን ተከትሎ የተሰማቸውን ሐዘን ለመግለጽ ዛሬ ሰኞ ዶሃ መድረሳቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩና ልዑካን ቡድናቸው ሃማድ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፤ በኳታር ትራንስፖርት ሚኒስትር ሼክ መሐመድ ቢን አብዱላህ እና በኳታር የኢትዮጵያ አምባሳደር ፈይሰል ኢብራሂም አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ “የእሳቸው ማለፍ ለአፍሪካም ሆነ ለመላው ቀጣና ትልቅ ኪሳራ ነው” ነው ሲሉ የኢሚሩ ሕልፈተ ሕይወት በተሰማ ጊዜ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት የሐዘን መልዕክት ገልጸዋል ሲል ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪27❤17👍4🤣4🥱1
የምርጫ ቀን ስለሆነ መንግስትም የለም በማለት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በጽኑ እስራት ተቀጣ
አቶ አክሊሉ አለማየሁ የተባለው ግለሰብ በኣሪ ዞን በደቡብ ኣሪ ወረዳ ሲዶ ቀበሌ ልዩ ስሙ ደብተር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዕድሜዋ 15 ዓመት የሚሆናትን ታዳጊ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፍዱ 4 ሰዓት ገደማ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፅሟል።
ተከሳሹ 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሚካሄድበት ዕለት ተበዳይን መንገድ ላይ ጠብቋት ዛሬ የምርጫ ቀን ስለሆነ መንግስትም የለም በማለት አንድ ጊዜ ወገቧ ላይ እና አንድ ጊዜ ትከሻዋ ላይ በመምታት እራሷን ከሳተች በኋላ ያለፍላጎቷ የግብረ ስጋ ግንኙነት ፈፅሞባታል።
የወረዳው ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ብርቱ ክትትል በማድረግ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር በማዋል የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን አደራጅቶ መዝገቡን ለወረዳው ዐቃቤ ህግ ልኳል።
የወረዳው ፍትህ ጽ/ቤት ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ዐቃቤ ህግ ከፖሊስ መዝገቡን ተመልክቶ ክስ መመስረቱን የአሪ ዞን ደቡብ አሪ ወረዳ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ ጉዶ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።ክሱ የቀረበለት የደቡብ ኣሪ ወረዳ ፍርድ ቤት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት በ12 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ወስኗል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አቶ አክሊሉ አለማየሁ የተባለው ግለሰብ በኣሪ ዞን በደቡብ ኣሪ ወረዳ ሲዶ ቀበሌ ልዩ ስሙ ደብተር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዕድሜዋ 15 ዓመት የሚሆናትን ታዳጊ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፍዱ 4 ሰዓት ገደማ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፅሟል።
ተከሳሹ 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሚካሄድበት ዕለት ተበዳይን መንገድ ላይ ጠብቋት ዛሬ የምርጫ ቀን ስለሆነ መንግስትም የለም በማለት አንድ ጊዜ ወገቧ ላይ እና አንድ ጊዜ ትከሻዋ ላይ በመምታት እራሷን ከሳተች በኋላ ያለፍላጎቷ የግብረ ስጋ ግንኙነት ፈፅሞባታል።
የወረዳው ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ብርቱ ክትትል በማድረግ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር በማዋል የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን አደራጅቶ መዝገቡን ለወረዳው ዐቃቤ ህግ ልኳል።
የወረዳው ፍትህ ጽ/ቤት ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ዐቃቤ ህግ ከፖሊስ መዝገቡን ተመልክቶ ክስ መመስረቱን የአሪ ዞን ደቡብ አሪ ወረዳ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ ጉዶ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።ክሱ የቀረበለት የደቡብ ኣሪ ወረዳ ፍርድ ቤት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት በ12 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ወስኗል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤔12❤5👍3
የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን፣ ሁሉም የበይነ መረብ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ሊያስገድድ መኾኑን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ፣ የበይነ መረብ ጣቢያዎች ተመዝግበው ብቻ እንዲሠሩ ለማስቻል የመገናኛ ብዙኀን ዋጁን ለማሻሻል ቅድመ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝም ገልጧል።
አዋጁ፣ የበይነ መረብ ጣቢያዎች ምዝገባ በፈቃደኝነት ላይ ብቻ እንዲኾን የሚፈቅድ ነው።
በዚህ ምክንያት፣ ፌስቡክን፣ ቲክቶክን እና ዩትዩብን በመሳሰሉ የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ይዘቶችን የሚያስተላልፉ አብዛኞቹ ድርጅቶችና ግለሰቦች የምዝገባ የምስክር ወረቀት ሳይወስዱና እውቅናና ፈቃድ ሳያገኙ እየሠሩ እንደሚገኙ ባለሥልጣኑ ጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ባለስልጣኑ፣ የበይነ መረብ ጣቢያዎች ተመዝግበው ብቻ እንዲሠሩ ለማስቻል የመገናኛ ብዙኀን ዋጁን ለማሻሻል ቅድመ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝም ገልጧል።
አዋጁ፣ የበይነ መረብ ጣቢያዎች ምዝገባ በፈቃደኝነት ላይ ብቻ እንዲኾን የሚፈቅድ ነው።
በዚህ ምክንያት፣ ፌስቡክን፣ ቲክቶክን እና ዩትዩብን በመሳሰሉ የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ይዘቶችን የሚያስተላልፉ አብዛኞቹ ድርጅቶችና ግለሰቦች የምዝገባ የምስክር ወረቀት ሳይወስዱና እውቅናና ፈቃድ ሳያገኙ እየሠሩ እንደሚገኙ ባለሥልጣኑ ጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10😱4👍3
ትምህርት ሚኒስቴር በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና አዲስ ማዕቀፍ አዘጋጅቷል።
ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ፣ ከአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር ተያይዞ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ማስገባት መቋረጡን አስታውሷል፡፡
ይሁን እንጂ በቀጣይ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት በተዘጋጀ የስልጠና ማዕቀፍ፣ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል።
በ2018 ዓ.ም የክረምት ስልጠናውን ለመስጠት ስምንት አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች መመረጣቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
ለክረምት ስልጠናው የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች፦
1. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
3. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
4. መቐለ ዩኒቨርሲቲ
5. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
7. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
8. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
ተቋማት እና የስልጠናው አሰጣጥ አግባብነት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከሚገለጽ ድረስ ከላይ ከተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በክረምት መምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መስጠት የማይቻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
ከ2011 ዓ.ም በፊት ስልጠና ጀምረው ያላጠናቀቁ መምህራን ከዚህ በፊት በተሰጠው ውሳኔ መሰረት እንዲያጠናቅቁ እንዲደረግ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ደብዳቤ ይገልጻል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ፣ ከአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር ተያይዞ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ማስገባት መቋረጡን አስታውሷል፡፡
ይሁን እንጂ በቀጣይ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት በተዘጋጀ የስልጠና ማዕቀፍ፣ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል።
በ2018 ዓ.ም የክረምት ስልጠናውን ለመስጠት ስምንት አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች መመረጣቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
ለክረምት ስልጠናው የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች፦
1. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
3. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
4. መቐለ ዩኒቨርሲቲ
5. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
7. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
8. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
ተቋማት እና የስልጠናው አሰጣጥ አግባብነት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከሚገለጽ ድረስ ከላይ ከተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በክረምት መምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መስጠት የማይቻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
ከ2011 ዓ.ም በፊት ስልጠና ጀምረው ያላጠናቀቁ መምህራን ከዚህ በፊት በተሰጠው ውሳኔ መሰረት እንዲያጠናቅቁ እንዲደረግ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ደብዳቤ ይገልጻል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍10❤6😢1
ለአንድ ቴሌቪዥን 850 ብር ታክስ‼️
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከፌዴራል መገናኛ ብዙሃን ነው የተላክነው እያሉ ቤት ለቤት በመዞር የዲሽ ሳህን እየቆጠሩ በአንድ ቴሌቪዥን 850 ብር ከእያንዳንዱ ሰው ታክስ እያስከፈሉ መሆኑን ነዋሪዎቹ ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን አመታዊ የቴሌቪዥን ግብር 120 ሲሆን ከመብራት ክፍያ ጋር አስር አስር ብር በየወሩ እንዲከፈል ተደርጓል። የአሁኑ ክፍያ መንግስት ያውቀዋል? የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከፌዴራል መገናኛ ብዙሃን ነው የተላክነው እያሉ ቤት ለቤት በመዞር የዲሽ ሳህን እየቆጠሩ በአንድ ቴሌቪዥን 850 ብር ከእያንዳንዱ ሰው ታክስ እያስከፈሉ መሆኑን ነዋሪዎቹ ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን አመታዊ የቴሌቪዥን ግብር 120 ሲሆን ከመብራት ክፍያ ጋር አስር አስር ብር በየወሩ እንዲከፈል ተደርጓል። የአሁኑ ክፍያ መንግስት ያውቀዋል? የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10👍3
3.69 ቢሊዮን ብር ያባከነው ተቋም‼
የፌዴራል ዋና ኦዲተር በ2018-2025 እ.ኤ.አ በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ስር በተከናወኑት የዌልመል እና የጨልጨል የመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ ባካሄደው የክዋኔ ኦዲት፣ ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ ብክነትና የውል ጥሰት መፈጸሙን ይፋ አደረገ።
ዋና ዋና የኦዲት ግኝቶች፦
📌የገንዘብ ብክነት፦ "የዋጋ ማስተካከያ አይፈቀድም" የሚለው የውል ድንጋጌ ተጥሶ በተደረጉ ማሻሻያዎች 3.69 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ወጪ ተደርጓል።
📌የቅንጡ መኪናዎች ግዢ፦ በጨልጨል ፕሮጀክት ውስጥ በውል ያልተካተቱ፣ ከ132 ሚሊዮን ብር በላይ የፈጁ የ2023 ሞዴል ቅንጡ ተሽከርካሪዎች (V6 እና Toyota Prado) ተገዝተው በተቋራጩ እጅ እንዲገቡ ተደርጓል።
📌የሰነድ ማጭበርበር፦ የ75 ሚሊዮን ብር የመስክ ተሽከርካሪዎች ግዢ የተጠናቀቀ ግንባታ ተደርጎ በተጭበረበረ ጊዜያዊ የክፍያ ማረጋገጫ ተፈጽሟል።
📌 ከፍተኛ መዘግየት፦ ፕሮጀክቶቹ ያለ አዋጭነት ጥናት በመጀመራቸውና በደካማ ክትትል ምክንያት ከ38 ወራት በላይ የዘገዩ ቢሆንም፣ በሚኒስቴሩ በኩል ምንም ዓይነት የመዘግየት ቅጣት አልተጣለም።
👉👉ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የተሰጡትን የማስተካከያ ምክረ-ሃሳቦች በአስቸኳይ ተግባራዊ ካላደረገ፣ ጉዳዩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የሕግና የወንጀል ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ዋና ኦዲተሩ ማስጠንቀቁን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የፌዴራል ዋና ኦዲተር በ2018-2025 እ.ኤ.አ በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ስር በተከናወኑት የዌልመል እና የጨልጨል የመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ ባካሄደው የክዋኔ ኦዲት፣ ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ ብክነትና የውል ጥሰት መፈጸሙን ይፋ አደረገ።
ዋና ዋና የኦዲት ግኝቶች፦
📌የገንዘብ ብክነት፦ "የዋጋ ማስተካከያ አይፈቀድም" የሚለው የውል ድንጋጌ ተጥሶ በተደረጉ ማሻሻያዎች 3.69 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ወጪ ተደርጓል።
📌የቅንጡ መኪናዎች ግዢ፦ በጨልጨል ፕሮጀክት ውስጥ በውል ያልተካተቱ፣ ከ132 ሚሊዮን ብር በላይ የፈጁ የ2023 ሞዴል ቅንጡ ተሽከርካሪዎች (V6 እና Toyota Prado) ተገዝተው በተቋራጩ እጅ እንዲገቡ ተደርጓል።
📌የሰነድ ማጭበርበር፦ የ75 ሚሊዮን ብር የመስክ ተሽከርካሪዎች ግዢ የተጠናቀቀ ግንባታ ተደርጎ በተጭበረበረ ጊዜያዊ የክፍያ ማረጋገጫ ተፈጽሟል።
📌 ከፍተኛ መዘግየት፦ ፕሮጀክቶቹ ያለ አዋጭነት ጥናት በመጀመራቸውና በደካማ ክትትል ምክንያት ከ38 ወራት በላይ የዘገዩ ቢሆንም፣ በሚኒስቴሩ በኩል ምንም ዓይነት የመዘግየት ቅጣት አልተጣለም።
👉👉ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የተሰጡትን የማስተካከያ ምክረ-ሃሳቦች በአስቸኳይ ተግባራዊ ካላደረገ፣ ጉዳዩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የሕግና የወንጀል ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ዋና ኦዲተሩ ማስጠንቀቁን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍5😢1
የአፍሪካ የገንዘብ ሚኒስትሮችና የባንክ ገዥዎች በባንጁል የጋራ መግለጫ አወጡ
የአፍሪካ ሀገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች እና የባንክ ገዥዎች ዓመታዊ ስብሰባ በባንጁል ተካሂዷል ። በስብሰባው ላይ የተሳተፉት የብሬተን ዉድስ ተቋማት የአፍሪካ ገዥዎች፣ አህጉሪቱን ወደ ተሻለ ኢኮኖሚያዊ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ቁርጠኝነቶችን ይፋ አድርገዋል።
የገንዘብ ሚኒስትሮቹ በዋናነት የሀገር ውስጥ የገቢ አሰባሰብን ማጠናከር፣ የመንግስት የገንዘብ አያያዝን ማሻሻል፣ የካፒታል ገበያዎችን ማሳደግ እንዲሁም ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋት የጋራ ግባቸው መሆኑን አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) እና የዓለም ባንክ (WBG) አፍሪካ የግብር ስርዓቷን ለማዘመን፣ ህገ-ወጥ የገንዘብ ፍሰትን ለመግታት እና በዲጂታላይዜሽን የታገዘ የግብር አስተዳደር ለመገንባት እያደረጉት ያለውን ጥረት በልዩ ትኩረት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል።
የአፍሪካን መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ለማረጋገጥና የዕዳ ተጋላጭነትን ለመቋቋም፣ ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ምንጭ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ፤ ተቋማቱ በግሉ ዘርፍ ልማትና በተቋማዊ የመቋቋም አቅም ግንባታ ረገድ የሚያደርጉት ድጋፍ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአፍሪካ ሀገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች እና የባንክ ገዥዎች ዓመታዊ ስብሰባ በባንጁል ተካሂዷል ። በስብሰባው ላይ የተሳተፉት የብሬተን ዉድስ ተቋማት የአፍሪካ ገዥዎች፣ አህጉሪቱን ወደ ተሻለ ኢኮኖሚያዊ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ቁርጠኝነቶችን ይፋ አድርገዋል።
የገንዘብ ሚኒስትሮቹ በዋናነት የሀገር ውስጥ የገቢ አሰባሰብን ማጠናከር፣ የመንግስት የገንዘብ አያያዝን ማሻሻል፣ የካፒታል ገበያዎችን ማሳደግ እንዲሁም ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋት የጋራ ግባቸው መሆኑን አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) እና የዓለም ባንክ (WBG) አፍሪካ የግብር ስርዓቷን ለማዘመን፣ ህገ-ወጥ የገንዘብ ፍሰትን ለመግታት እና በዲጂታላይዜሽን የታገዘ የግብር አስተዳደር ለመገንባት እያደረጉት ያለውን ጥረት በልዩ ትኩረት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል።
የአፍሪካን መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ለማረጋገጥና የዕዳ ተጋላጭነትን ለመቋቋም፣ ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ምንጭ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ፤ ተቋማቱ በግሉ ዘርፍ ልማትና በተቋማዊ የመቋቋም አቅም ግንባታ ረገድ የሚያደርጉት ድጋፍ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7👍2🤯1
አከራዮች ላይ ከተማ አስተዳደሩ የማያዳግም እርምጃ እወስዳለሁ አለ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
በተለይም ተከራዮችን “ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ” በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ”ድርብ ውል” አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
በተለይም ተከራዮችን “ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ” በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ”ድርብ ውል” አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍3🤪3
"የትራፊክ መጨናነቅ ስለሚያጋጥም አማራጭ መንገዶች ተጠቀሙ" - ትራፊክ ማኔጅመንት
ነገ ሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል።
ለዚሁ ጉባኤ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የጉባኤው ተሳታፊዎች አዲስ አበባ ይገኛሉ።
የጉባኤው ተሳታፊዎች በሲኤምሲ መስመር የተባበሩት አደባባይ ወደ ሚገኘው አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር ጠዋት እና ማታ ሲገቡና ሲወጡ የሚጓዙባቸው መስመሮች ማለትም ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በሳህሊተ ምህረት እንዲሁም ከኢትዮ ቻይና መስመር በሳህሊተ ምህረት እስከ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር የትራፊክ መጨናነቅ እንደሚያጋጥም የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አሳውቋል።
በመሆኑም ከነገ ጀምሮ ጉባኤው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ በመስመሮቹ የሚጓዙ አሽከርካሪዎች አስቀድመው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ከወዲሁ መልዕክት ተላልፏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ነገ ሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል።
ለዚሁ ጉባኤ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የጉባኤው ተሳታፊዎች አዲስ አበባ ይገኛሉ።
የጉባኤው ተሳታፊዎች በሲኤምሲ መስመር የተባበሩት አደባባይ ወደ ሚገኘው አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር ጠዋት እና ማታ ሲገቡና ሲወጡ የሚጓዙባቸው መስመሮች ማለትም ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በሳህሊተ ምህረት እንዲሁም ከኢትዮ ቻይና መስመር በሳህሊተ ምህረት እስከ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር የትራፊክ መጨናነቅ እንደሚያጋጥም የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አሳውቋል።
በመሆኑም ከነገ ጀምሮ ጉባኤው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ በመስመሮቹ የሚጓዙ አሽከርካሪዎች አስቀድመው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ከወዲሁ መልዕክት ተላልፏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤5👍3🤪3
አሳሳቢ እየሆነ የመጣው ማጅራት መቺነት‼️
በመዲናዋ አዲስ አበባ በተለይም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ ሰሚት፣ ገርጂ እና አካባቢው ከመቼውም ጊዜ በላይ የተበራከተው የማጅራት መምታት እና የንጥቂያ ወንጀል የነዋሪውን ደህንነት ክፉኛ እየፈተነ ይገኛል። የወንጀሉ ገጽታ እና የጸጥታ አካላት እየወሰዱት ያለው እርምጃ ነዋሪዎችን እና የፖሊስ ኃላፊዎችን እያወዛገበ ሲሆን፣ የህዝቡን ስጋት እና የፖሊስን ምላሽ እንደሚከተለው አጠናቅረነዋል።
እንደ ነዋሪዎች እና ስማቸው እንዳይጠቀስ ከፈለጉ የውስጥ ፖሊስ አባላት ዘ-ሐበሻ ባገኘው መረጃ፣ የዘረፋው ወንጀል መልኩን ቀይሮ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ለወትሮው በምሽት ይፈጸም የነበረው ማጅራት መምታት፣ አሁን የክረምቱን መግባት እና የጠዋቱን ጨለማ እንደ ሽፋን በመጠቀም ወደ ማለዳ ተሸጋግሯል።
የዚህ አዲስ የማለዳ ላይ ጥቃት ዋነኛ ሰለባ እየሆኑ ያሉት ደግሞ፣ ጠዋት በጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን የሚያመሩ አረጋውያን እናቶች ናቸው። ይህ በየዕለቱ እየተፈጸመ ያለ አስነዋሪ ድርጊት ቢሆንም፣ የፖሊስ የበላይ ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት ከማሰብ ይልቅ ጉዳዩን አድበስብሶ ማለፍን መርጠዋል የሚል ጠንካራ ወቀሳ ከውስጥ ምንጮች ቀርቧል። "የህዝቡ ስቃይ ዝም ተብሎ ስለታለፈ እና ኃላፊዎች እርምጃ ባለመውሰዳቸው መረጃውን ለሚዲያ አድርሰናል" ያሉት የውስጥ ምንጮች፣ ተቋማዊ ቸልተኝነት መኖሩን በጽኑ ተችተዋል።
በተነሳው የ"ቸልተኝነት እና የዝምታ" ክስ ላይ ምላሽ የሰጡን የፖሊስ ኃላፊዎች፣ ተቋሙ በምንም መልኩ ዝምታን እንዳልመረጠ አስታውቀዋል። ኃላፊው ለቀረበባቸው ወቀሳ በሰጡት ምላሽ፣ ፖሊስ ወንጀለኞች በስፋት ይንቀሳቀሱባቸዋል የተባሉትን ሰሚት፣ ገርጂ እና 'ጥላሁን' የተባሉ አካባቢዎችን ለይቶ ሰፊ የጸጥታ ማስከበር አሰሳ እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ወንጀለኞች የሚሰባሰቡባቸውን ህገ-ወጥ የሺሻ ቤቶችን የማፍረስ ስራ እየተሰራ ሲሆን፣ በአንድ ቀን በተደረገ ኦፕሬሽን ብቻ 80 ያህል የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ማስመለስ መቻሉን ፖሊስ በምላሹ አስረድቷል። ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት ድረስ የዘለቀ ጥብቅ አሰሳ በየቀኑ እየተካሄደ መሆኑንም አክለዋል።
ከዚህ ቀደም የነበሩ አመራሮች የጸጥታ ስራዎችን ለሚዲያ ፍጆታ ይጠቀሙበት እንደነበር የወቀሱት ኃላፊው፣ "አሁን ያለው የጸጥታ መዋቅር ማወናበድ ሳይሆን በተጨባጭ ወንጀልን ከስረ-መሰረቱ ለማጥፋት ትልቅ ኦፕሬሽን እየሰራ ስለሆነ ነው እንጂ የተኛንበት ጊዜ የለም" ሲሉ ተከራክረዋል።
በፖሊስ ኃላፊው ምላሽ ውስጥ ጎልቶ የወጣው ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ በነዚህ አካባቢዎች ያለው የውጭ ዜጎች ወንጀል ተሳትፎ ነው። ከዩጋንዳ፣ ናይጄሪያ እና ሌሎችም ሀገራት የመጡ፣ እንዲሁም ህጋዊ የጉዞ ሰነድ የሌላቸው በርካታ ስደተኞች በአካባቢው ተሰባስበው ይገኛሉ። እነዚህ የውጭ ዜጎች በስርቆት፣ በዝሙት አዳሪነት እና በተለያዩ ወንጀሎች ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውንና ፖሊስም ህጋዊ እርምጃ እየወሰደባቸው መሆኑ ተጠቁሟል።
የህዝቡን የዕለት ተዕለት ስቃይ እና የፖሊስን ሪፖርት ጎን ለጎን ስንመዝነው፣ አንድ ትልቅ የአሰራር እና የትኩረት ክፍተት ይታያል። በአንድ በኩል ህዝቡ እና አረጋውያን እናቶች ጥቃት እየደረሰባቸው ያለው በማለዳው (ጠዋት) የጨለማ ሰዓት መሆኑን እያማረሩ ነው። በሌላ በኩል ግን ፖሊስ ትልቅ እርምጃ እየወሰድኩ ነው ብሎ ያቀረበው ማስረጃ "ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት" የሚያደርገውን አሰሳ ነው። ይህ የሚያሳየው ወንጀለኞቹ የፖሊስን የጥበቃ ሰዓት ክፍተት አጥንተው የዘረፋ ሰዓታቸውን ወደ ጠዋት ማለዳ ሲያሸጋግሩ፣ ፖሊስ ግን አሁንም ትኩረቱን ምሽት ላይ ብቻ ማድረጉን ነው።
ፖሊስ "ለሚዲያ ፍጆታ ሳይሆን በተግባር እየሰራሁ ነው" ማለቱ የሚበረታታ ቢሆንም ስኬቱ ሊለካ የሚገባው በተያዙ ስልኮች ብዛት ብቻ ሳይሆን በማለዳ ወደ ቤተክርስቲያን እና ወደ ስራ የሚወጣው ነዋሪ በሚያገኘው የደህንነት ዋስትና ነው። በመሆኑም የጸጥታ አካላት የኦፕሬሽን ስልታቸውን እና የሰዓት ስምሪታቸውን ነዋሪው እየተጠቃበት ካለው የማለዳ ሰዓት ጋር ሊያስተካክሉ ይገባል። ፖሊስ አደረግኩት የሚለው ኦፕሬሽን በተግባር የህዝቡን ስጋት እስካላቀለለ ድረስ፣ "ቸልተኝነት አለ" የሚለው የህዝብ ቅሬታ መቀጠሉ አይቀርም።
#ዘሐበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በመዲናዋ አዲስ አበባ በተለይም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ ሰሚት፣ ገርጂ እና አካባቢው ከመቼውም ጊዜ በላይ የተበራከተው የማጅራት መምታት እና የንጥቂያ ወንጀል የነዋሪውን ደህንነት ክፉኛ እየፈተነ ይገኛል። የወንጀሉ ገጽታ እና የጸጥታ አካላት እየወሰዱት ያለው እርምጃ ነዋሪዎችን እና የፖሊስ ኃላፊዎችን እያወዛገበ ሲሆን፣ የህዝቡን ስጋት እና የፖሊስን ምላሽ እንደሚከተለው አጠናቅረነዋል።
እንደ ነዋሪዎች እና ስማቸው እንዳይጠቀስ ከፈለጉ የውስጥ ፖሊስ አባላት ዘ-ሐበሻ ባገኘው መረጃ፣ የዘረፋው ወንጀል መልኩን ቀይሮ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ለወትሮው በምሽት ይፈጸም የነበረው ማጅራት መምታት፣ አሁን የክረምቱን መግባት እና የጠዋቱን ጨለማ እንደ ሽፋን በመጠቀም ወደ ማለዳ ተሸጋግሯል።
የዚህ አዲስ የማለዳ ላይ ጥቃት ዋነኛ ሰለባ እየሆኑ ያሉት ደግሞ፣ ጠዋት በጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን የሚያመሩ አረጋውያን እናቶች ናቸው። ይህ በየዕለቱ እየተፈጸመ ያለ አስነዋሪ ድርጊት ቢሆንም፣ የፖሊስ የበላይ ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት ከማሰብ ይልቅ ጉዳዩን አድበስብሶ ማለፍን መርጠዋል የሚል ጠንካራ ወቀሳ ከውስጥ ምንጮች ቀርቧል። "የህዝቡ ስቃይ ዝም ተብሎ ስለታለፈ እና ኃላፊዎች እርምጃ ባለመውሰዳቸው መረጃውን ለሚዲያ አድርሰናል" ያሉት የውስጥ ምንጮች፣ ተቋማዊ ቸልተኝነት መኖሩን በጽኑ ተችተዋል።
በተነሳው የ"ቸልተኝነት እና የዝምታ" ክስ ላይ ምላሽ የሰጡን የፖሊስ ኃላፊዎች፣ ተቋሙ በምንም መልኩ ዝምታን እንዳልመረጠ አስታውቀዋል። ኃላፊው ለቀረበባቸው ወቀሳ በሰጡት ምላሽ፣ ፖሊስ ወንጀለኞች በስፋት ይንቀሳቀሱባቸዋል የተባሉትን ሰሚት፣ ገርጂ እና 'ጥላሁን' የተባሉ አካባቢዎችን ለይቶ ሰፊ የጸጥታ ማስከበር አሰሳ እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ወንጀለኞች የሚሰባሰቡባቸውን ህገ-ወጥ የሺሻ ቤቶችን የማፍረስ ስራ እየተሰራ ሲሆን፣ በአንድ ቀን በተደረገ ኦፕሬሽን ብቻ 80 ያህል የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ማስመለስ መቻሉን ፖሊስ በምላሹ አስረድቷል። ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት ድረስ የዘለቀ ጥብቅ አሰሳ በየቀኑ እየተካሄደ መሆኑንም አክለዋል።
ከዚህ ቀደም የነበሩ አመራሮች የጸጥታ ስራዎችን ለሚዲያ ፍጆታ ይጠቀሙበት እንደነበር የወቀሱት ኃላፊው፣ "አሁን ያለው የጸጥታ መዋቅር ማወናበድ ሳይሆን በተጨባጭ ወንጀልን ከስረ-መሰረቱ ለማጥፋት ትልቅ ኦፕሬሽን እየሰራ ስለሆነ ነው እንጂ የተኛንበት ጊዜ የለም" ሲሉ ተከራክረዋል።
በፖሊስ ኃላፊው ምላሽ ውስጥ ጎልቶ የወጣው ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ በነዚህ አካባቢዎች ያለው የውጭ ዜጎች ወንጀል ተሳትፎ ነው። ከዩጋንዳ፣ ናይጄሪያ እና ሌሎችም ሀገራት የመጡ፣ እንዲሁም ህጋዊ የጉዞ ሰነድ የሌላቸው በርካታ ስደተኞች በአካባቢው ተሰባስበው ይገኛሉ። እነዚህ የውጭ ዜጎች በስርቆት፣ በዝሙት አዳሪነት እና በተለያዩ ወንጀሎች ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውንና ፖሊስም ህጋዊ እርምጃ እየወሰደባቸው መሆኑ ተጠቁሟል።
የህዝቡን የዕለት ተዕለት ስቃይ እና የፖሊስን ሪፖርት ጎን ለጎን ስንመዝነው፣ አንድ ትልቅ የአሰራር እና የትኩረት ክፍተት ይታያል። በአንድ በኩል ህዝቡ እና አረጋውያን እናቶች ጥቃት እየደረሰባቸው ያለው በማለዳው (ጠዋት) የጨለማ ሰዓት መሆኑን እያማረሩ ነው። በሌላ በኩል ግን ፖሊስ ትልቅ እርምጃ እየወሰድኩ ነው ብሎ ያቀረበው ማስረጃ "ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት" የሚያደርገውን አሰሳ ነው። ይህ የሚያሳየው ወንጀለኞቹ የፖሊስን የጥበቃ ሰዓት ክፍተት አጥንተው የዘረፋ ሰዓታቸውን ወደ ጠዋት ማለዳ ሲያሸጋግሩ፣ ፖሊስ ግን አሁንም ትኩረቱን ምሽት ላይ ብቻ ማድረጉን ነው።
ፖሊስ "ለሚዲያ ፍጆታ ሳይሆን በተግባር እየሰራሁ ነው" ማለቱ የሚበረታታ ቢሆንም ስኬቱ ሊለካ የሚገባው በተያዙ ስልኮች ብዛት ብቻ ሳይሆን በማለዳ ወደ ቤተክርስቲያን እና ወደ ስራ የሚወጣው ነዋሪ በሚያገኘው የደህንነት ዋስትና ነው። በመሆኑም የጸጥታ አካላት የኦፕሬሽን ስልታቸውን እና የሰዓት ስምሪታቸውን ነዋሪው እየተጠቃበት ካለው የማለዳ ሰዓት ጋር ሊያስተካክሉ ይገባል። ፖሊስ አደረግኩት የሚለው ኦፕሬሽን በተግባር የህዝቡን ስጋት እስካላቀለለ ድረስ፣ "ቸልተኝነት አለ" የሚለው የህዝብ ቅሬታ መቀጠሉ አይቀርም።
#ዘሐበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17👍5
ህወሓት ዳግም ያቋቋመው የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ሀገራዊ የምክክር መድረኩን ውድቅ በማድረግ በሂደቱ ላይ እንደማይሳተፍ አስታወቀ
በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሃት) ዳግም የተቋቋመው የትግራይ ክልላዊ መንግሥት እየተካሄደ ያለውን ሀገራዊ የምክክር ሂደት ውድቅ ማድረጉን ያስታወቀ ሲሆን፥ «ተቀባይነት የሌለው» ሲል በገለጸው የውይይት መድረክ ላይ የክልሉ መንግሥትም ሆነ የትግራይ ሕዝብ አልተወከሉም ብሏል።
የትግራይ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ትናንት ባወጣው መግለጫ፥ መድረኩ የትግራይ ሕዝብ የሚጋፈጣቸውን መሠረታዊ ጥያቄዎች መመለስ አልቻለም በሚል አስተዳደሩ በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ላይ እንደማይሳተፍ አስታውቋል። ቢሮው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የፌዴራል መንግሥት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ቁልፍ ድንጋጌዎችን ተግባራዊ አላደረገም ሲል የከሰሰ ሲሆን፥ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ቢፈረምም ትግራይ አሁንም ከባድ ሰብአዊ፣ ፖለቲካዊ እና የደኅንነት ተግዳሮቶች እየገጠሟት ይገኛል ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሃት) ዳግም የተቋቋመው የትግራይ ክልላዊ መንግሥት እየተካሄደ ያለውን ሀገራዊ የምክክር ሂደት ውድቅ ማድረጉን ያስታወቀ ሲሆን፥ «ተቀባይነት የሌለው» ሲል በገለጸው የውይይት መድረክ ላይ የክልሉ መንግሥትም ሆነ የትግራይ ሕዝብ አልተወከሉም ብሏል።
የትግራይ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ትናንት ባወጣው መግለጫ፥ መድረኩ የትግራይ ሕዝብ የሚጋፈጣቸውን መሠረታዊ ጥያቄዎች መመለስ አልቻለም በሚል አስተዳደሩ በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ላይ እንደማይሳተፍ አስታውቋል። ቢሮው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የፌዴራል መንግሥት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ቁልፍ ድንጋጌዎችን ተግባራዊ አላደረገም ሲል የከሰሰ ሲሆን፥ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ቢፈረምም ትግራይ አሁንም ከባድ ሰብአዊ፣ ፖለቲካዊ እና የደኅንነት ተግዳሮቶች እየገጠሟት ይገኛል ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15🤪7👍5🤣3🤯2
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አጋሮች የቀነሰባቸውን 2.8 በመቶ ድርሻ መልሰው የመግዛት መብት እንዳላቸው ተገለጸ
ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚንቀሳቀሰው ቅርንጫፍ ኩባንያው ያደረገውን ተጨማሪ የካፒታል ኢንቨስትመንት ተከትሎ፣ ሌሎች አብረውት ኢንቨስት ያደረጉ አጋሮቹ ያጡትን የ2.78 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ መልሰው የመግዛት መብታቸው የተጠበቀ መሆኑን አስታወቀ።
የቴሌኮም ኩባንያው እና ደቡብ አፍሪካዊው የእናት ኩባንያው ቮዳኮም ግሩፕ ‘ቮዳፋሚሊ ኢትዮጵያ ሆልዲንግ’ በተሰኘው የኢንቨስትመንት ተቋማቸው አማካኝነት፣ እስከ እኤአ መጋቢት 2026 በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 21.3 ቢሊዮን የኬንያ ሺሊንግ የሚያወጣ የካፒታል ማሰባሰቢያ ጥሪ ላይ ብቻቸውን ተሳትፈዋል።
ይህንን የካፒታል ማሳደግ ጥሪ ሳፋሪኮም እና ቮዳኮም ብቻቸውን በመሸፈናቸው በኢትዮጵያው ኩባንያ ውስጥ የነበራቸውን ጥምር ድርሻ ከ57.41 በመቶ ወደ 60.19 በመቶ ከፍ ማድረግ ችለዋል። ይህ እርምጃ እንደ ሱሚቶሞ ኮርፖሬሽን ፣ ብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ያሉትን ሌሎች አጋር ኩባንያዎች የነበራቸውን የባለቤትነት ድርሻ እንዲቀንስ አድርጎት ነበር።
ይሁን እንጂ ሳፋሪኮም አጋሮቹ የተዳከመውን ድርሻቸውን ወደነበረበት ለመመለስና ያጡትን የ2.78 በመቶ ድርሻ መልሰው መግዛት የሚችሉበት ሕጋዊ መብት እንዳላቸው በይፋ አረጋግጧል።
ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን የኔትወርክ ተደራሽነት ለማስፋፋት እና የንግድ እንቅስቃሴውን ለማጠናከር ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እያፈሰሰ የሚገኝ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እስከ መጋቢት 2027 ዓ.ም ድረስ ወጪና ገቢውን አጣጥሞ ሙሉ በሙሉ ትርፋማ መሆን እንደሚጀምር ግምቱን አስቀምጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚንቀሳቀሰው ቅርንጫፍ ኩባንያው ያደረገውን ተጨማሪ የካፒታል ኢንቨስትመንት ተከትሎ፣ ሌሎች አብረውት ኢንቨስት ያደረጉ አጋሮቹ ያጡትን የ2.78 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ መልሰው የመግዛት መብታቸው የተጠበቀ መሆኑን አስታወቀ።
የቴሌኮም ኩባንያው እና ደቡብ አፍሪካዊው የእናት ኩባንያው ቮዳኮም ግሩፕ ‘ቮዳፋሚሊ ኢትዮጵያ ሆልዲንግ’ በተሰኘው የኢንቨስትመንት ተቋማቸው አማካኝነት፣ እስከ እኤአ መጋቢት 2026 በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 21.3 ቢሊዮን የኬንያ ሺሊንግ የሚያወጣ የካፒታል ማሰባሰቢያ ጥሪ ላይ ብቻቸውን ተሳትፈዋል።
ይህንን የካፒታል ማሳደግ ጥሪ ሳፋሪኮም እና ቮዳኮም ብቻቸውን በመሸፈናቸው በኢትዮጵያው ኩባንያ ውስጥ የነበራቸውን ጥምር ድርሻ ከ57.41 በመቶ ወደ 60.19 በመቶ ከፍ ማድረግ ችለዋል። ይህ እርምጃ እንደ ሱሚቶሞ ኮርፖሬሽን ፣ ብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ያሉትን ሌሎች አጋር ኩባንያዎች የነበራቸውን የባለቤትነት ድርሻ እንዲቀንስ አድርጎት ነበር።
ይሁን እንጂ ሳፋሪኮም አጋሮቹ የተዳከመውን ድርሻቸውን ወደነበረበት ለመመለስና ያጡትን የ2.78 በመቶ ድርሻ መልሰው መግዛት የሚችሉበት ሕጋዊ መብት እንዳላቸው በይፋ አረጋግጧል።
ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን የኔትወርክ ተደራሽነት ለማስፋፋት እና የንግድ እንቅስቃሴውን ለማጠናከር ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እያፈሰሰ የሚገኝ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እስከ መጋቢት 2027 ዓ.ም ድረስ ወጪና ገቢውን አጣጥሞ ሙሉ በሙሉ ትርፋማ መሆን እንደሚጀምር ግምቱን አስቀምጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12👍7
የአዲስ አበባ ታክሲዎች ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት ክፍያ እንዲሰበስቡ ተወሰነ
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከተወሰነው ታሪፍ በላይ እንዲሚያስከፍሉ ከማኅበረሰቡ የሚነሳውን ቅሬታ ለመፍታት ክፍያው ከመነሻው እንዲሰበሰብ የሚያስገድድ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስታውቋል።
አሽከርካሪዎች በታሪፍ መመሪያው መሠረት ብቻ ከመነሻው የትራንስፖርት ክፍያ እንዲሰበስቡ ለማስቻል ተቆጣጣሪዎች በመነሻ መጫኛ ቦታዎች ላይ ተመድበው ሥራ መጀመራቸውን የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ተናግረዋል።
ይህ አሠራር በጉዞ ወቅት "ሒሳብ ጨምሩ" በሚል ከአሽከርካሪዎች የሚነሳውን አግባብነት የሌለው ጥያቄ ለመግታት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል።
ይሁን እንጂ አዲሱ አሠራር ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ አንዳንድ ተግዳሮቶች መፈጠራቸውን የቢሮው ኃላፊዎች ጠቁመዋል።
በከተማዋ በሚገኙ መነሻዎች ላይ ክፍያውን አስቀድሞ በመሰብሰብ ሂደት የተወሰነ ጊዜ እየወሰደ መሆኑ በማኅበረሰቡ በኩል ቅሬታ መፍጠሩ ተገልጿል።
በተመሳሳይ አንዳንድ አሽከርካሪዎች መንገድ ከጀመሩ በኋላ ታሪፍ የመጨመር አዝማሚያዎችን እያሳዩ መሆናቸውን ቢሮው አስታውቋል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ ማኅበረሰቡ የጉዳዩን ፋይዳ በመገንዘብ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግና ህገ-ወጥ አሽከርካሪዎችን በተመለከተ ጥቆማዎችን በመስጠት የዜግነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አቶ ዳኛቸው አሳስበዋል።
በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም ያለ ረዳት በሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ሲገለጽ መቆየቱ የሚታወስ ቢሆንም፤ ቢሮው በአሁኑ ወቅት ትኩረቱን አዲሱ የአሠራር ሥርዓት ላይ ማድረጉን አመልክቷል።
ይሁን እንጂ የረዳት አጠቃቀምን በተመለከተ ግልጽና ወጥ የሆነ የአሠራር ሥርዓት እንደሚያስፈልግ አቶ ዳኛቸው ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከተወሰነው ታሪፍ በላይ እንዲሚያስከፍሉ ከማኅበረሰቡ የሚነሳውን ቅሬታ ለመፍታት ክፍያው ከመነሻው እንዲሰበሰብ የሚያስገድድ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስታውቋል።
አሽከርካሪዎች በታሪፍ መመሪያው መሠረት ብቻ ከመነሻው የትራንስፖርት ክፍያ እንዲሰበስቡ ለማስቻል ተቆጣጣሪዎች በመነሻ መጫኛ ቦታዎች ላይ ተመድበው ሥራ መጀመራቸውን የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ተናግረዋል።
ይህ አሠራር በጉዞ ወቅት "ሒሳብ ጨምሩ" በሚል ከአሽከርካሪዎች የሚነሳውን አግባብነት የሌለው ጥያቄ ለመግታት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል።
ይሁን እንጂ አዲሱ አሠራር ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ አንዳንድ ተግዳሮቶች መፈጠራቸውን የቢሮው ኃላፊዎች ጠቁመዋል።
በከተማዋ በሚገኙ መነሻዎች ላይ ክፍያውን አስቀድሞ በመሰብሰብ ሂደት የተወሰነ ጊዜ እየወሰደ መሆኑ በማኅበረሰቡ በኩል ቅሬታ መፍጠሩ ተገልጿል።
በተመሳሳይ አንዳንድ አሽከርካሪዎች መንገድ ከጀመሩ በኋላ ታሪፍ የመጨመር አዝማሚያዎችን እያሳዩ መሆናቸውን ቢሮው አስታውቋል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ ማኅበረሰቡ የጉዳዩን ፋይዳ በመገንዘብ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግና ህገ-ወጥ አሽከርካሪዎችን በተመለከተ ጥቆማዎችን በመስጠት የዜግነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አቶ ዳኛቸው አሳስበዋል።
በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም ያለ ረዳት በሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ሲገለጽ መቆየቱ የሚታወስ ቢሆንም፤ ቢሮው በአሁኑ ወቅት ትኩረቱን አዲሱ የአሠራር ሥርዓት ላይ ማድረጉን አመልክቷል።
ይሁን እንጂ የረዳት አጠቃቀምን በተመለከተ ግልጽና ወጥ የሆነ የአሠራር ሥርዓት እንደሚያስፈልግ አቶ ዳኛቸው ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤35👍9🤔1