በዓለም ላይ ቀዳሚዎቹ የወርቅ አምራቾች ቻይና፣ አውስትራሊያ፣ ሩሲያ፣ ካናዳ እና አሜሪካ ናቸው።
በኩባንያ ደረጃ ደግሞ ከፍተኛውን ምርት የሚያቀርቡት እንደ ኒውሞንት (Newmont Corporation) እና ባሪክ ጎልድ (Barrick Gold) ያሉ ግዙፍ ዓለም አቀፍ የኮርፖሬት ማዕድን ኩባንያዎች ናቸው።
ከፍተኛ ወርቅ አምራች የሆኑት ቻይና፣አውስትራሊያ፣ሩሲያ፣ ካናዳ እና አሜሪካ ሲሆኑ
* ቻይና፦ በዓመት ከ370 ሜትሪክ ቶን በላይ በማምረት የዓለማችን ቀዳሚዋ ወርቅ አምራች አገር ናት።
* አውስትራሊያ፦ በየዓመቱ ከ300 ሜትሪክ ቶን በላይ ወጥ የሆነ ምርት በማውጣት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
* ሩሲያ፦ በዓመት በግምት ከ300 እስከ 330 ሜትሪክ ቶን በማምረት በዓለም አቀፍ ደረጃ ሦስተኛውን ደረጃ ይዛለች።
* ካናዳ፦ በሰሜን አሜሪካ ዋነኛ አምራች ስትሆን፣ በዓመት ከ170 እስከ 200 ሜትሪክ ቶን ታመርታለች።
* አሜሪካ፦ በዋነኝነት በኔቫዳ ግዛት ከሚገኙ ማዕድናት የሚወጣ ሲሆን፣ በየዓመቱ በግምት ከ170 እስከ 200 ሜትሪክ ቶን ታመርታለች።
የኩባንያዎች ምርት በአብዛኛው በግል ባለሀብቶች እና በመንግሥት በሚተዳደሩ ግዙፍ ተቋማት የሚመራ ነው፦
* ኒውሞንት ኮርፖሬሽን (Newmont Corporation)፦ በአሜሪካ የሚገኘው ይህ ዓለም አቀፍ ኩባንያ በጠቅላላ የምርት መጠን የዓለማችን ትልቁ የወርቅ ማዕድን ኩባንያ ነው።
* ባሪክ ጎልድ (Barrick Gold)፦ በኔቫዳ የሚገኘውን ካርሊን ትሬንድ (Carlin Trend) ጨምሮ በርካታ የዓለማችን ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ማዕድናት የሚያስተዳድር ግዙፍ የካናዳ ኩባንያ ነው።
* አግኒኮ ኢግል ማይንስ (Agnico Eagle Mines)፦ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በከፍተኛ ዕድገት እና በተረጋጋ የሥራ እንቅስቃሴ የሚታወቅ ሌላኛው የካናዳ ኩባንያ ነው።
* ፖሊየስ (Polyus)፦ በሳይቤሪያ የወርቅ ክምችት ላይ ሰፊ ይዞታ ያለው የሩሲያ ትልቁ ወርቅ አምራች ነው።
* ዚጂን ማይኒንግ (Zijin Mining)፦ በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርቱን በፍጥነት እያሳደገ የመጣ የቻይና ሁለገብ ኩባንያ ነው።
* ናቮይ ማይኒንግ (NMMC)፦ በኡዝቤኪስታን ውስጥ ግዙፍ የማዕድን ሥራዎችን የሚያከናውን ትልቅ የመንግሥት የኢንዱስትሪ ተቋም ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በኩባንያ ደረጃ ደግሞ ከፍተኛውን ምርት የሚያቀርቡት እንደ ኒውሞንት (Newmont Corporation) እና ባሪክ ጎልድ (Barrick Gold) ያሉ ግዙፍ ዓለም አቀፍ የኮርፖሬት ማዕድን ኩባንያዎች ናቸው።
ከፍተኛ ወርቅ አምራች የሆኑት ቻይና፣አውስትራሊያ፣ሩሲያ፣ ካናዳ እና አሜሪካ ሲሆኑ
* ቻይና፦ በዓመት ከ370 ሜትሪክ ቶን በላይ በማምረት የዓለማችን ቀዳሚዋ ወርቅ አምራች አገር ናት።
* አውስትራሊያ፦ በየዓመቱ ከ300 ሜትሪክ ቶን በላይ ወጥ የሆነ ምርት በማውጣት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
* ሩሲያ፦ በዓመት በግምት ከ300 እስከ 330 ሜትሪክ ቶን በማምረት በዓለም አቀፍ ደረጃ ሦስተኛውን ደረጃ ይዛለች።
* ካናዳ፦ በሰሜን አሜሪካ ዋነኛ አምራች ስትሆን፣ በዓመት ከ170 እስከ 200 ሜትሪክ ቶን ታመርታለች።
* አሜሪካ፦ በዋነኝነት በኔቫዳ ግዛት ከሚገኙ ማዕድናት የሚወጣ ሲሆን፣ በየዓመቱ በግምት ከ170 እስከ 200 ሜትሪክ ቶን ታመርታለች።
የኩባንያዎች ምርት በአብዛኛው በግል ባለሀብቶች እና በመንግሥት በሚተዳደሩ ግዙፍ ተቋማት የሚመራ ነው፦
* ኒውሞንት ኮርፖሬሽን (Newmont Corporation)፦ በአሜሪካ የሚገኘው ይህ ዓለም አቀፍ ኩባንያ በጠቅላላ የምርት መጠን የዓለማችን ትልቁ የወርቅ ማዕድን ኩባንያ ነው።
* ባሪክ ጎልድ (Barrick Gold)፦ በኔቫዳ የሚገኘውን ካርሊን ትሬንድ (Carlin Trend) ጨምሮ በርካታ የዓለማችን ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ማዕድናት የሚያስተዳድር ግዙፍ የካናዳ ኩባንያ ነው።
* አግኒኮ ኢግል ማይንስ (Agnico Eagle Mines)፦ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በከፍተኛ ዕድገት እና በተረጋጋ የሥራ እንቅስቃሴ የሚታወቅ ሌላኛው የካናዳ ኩባንያ ነው።
* ፖሊየስ (Polyus)፦ በሳይቤሪያ የወርቅ ክምችት ላይ ሰፊ ይዞታ ያለው የሩሲያ ትልቁ ወርቅ አምራች ነው።
* ዚጂን ማይኒንግ (Zijin Mining)፦ በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርቱን በፍጥነት እያሳደገ የመጣ የቻይና ሁለገብ ኩባንያ ነው።
* ናቮይ ማይኒንግ (NMMC)፦ በኡዝቤኪስታን ውስጥ ግዙፍ የማዕድን ሥራዎችን የሚያከናውን ትልቅ የመንግሥት የኢንዱስትሪ ተቋም ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍3🤩1
በአርሲ ግጭት 8 ሚሊሻ እና ፖሊሶችን ጨምሮ በአጠቃላይ 11 ሰዎች ናቸው የተገደሉት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ‼️
ለግጭቱ ሐይማኖታዊ መልክ ለመሰጠት የተደረገው ሙከራ ተገቢ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ተናግረዋል።
ሽፍቶች በአካባቢው ያለውን ሰላም ለማደብዘዝ ሙከራ እንዳደርጉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ 22 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ እና ከተፈናቃዮች ውስጥ 90 በመቶ በላይ የሚሆኑት መመለሳቸውን አንስተዋል፡፡
የአርሲ ሀገረ ስብከት 13 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን ገልፆ ነበር።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ለግጭቱ ሐይማኖታዊ መልክ ለመሰጠት የተደረገው ሙከራ ተገቢ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ተናግረዋል።
ሽፍቶች በአካባቢው ያለውን ሰላም ለማደብዘዝ ሙከራ እንዳደርጉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ 22 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ እና ከተፈናቃዮች ውስጥ 90 በመቶ በላይ የሚሆኑት መመለሳቸውን አንስተዋል፡፡
የአርሲ ሀገረ ስብከት 13 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን ገልፆ ነበር።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡57❤9👍3
📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
❤2👍2
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የደርግ ዘመንን ጥምረት በማንሳት ሱዳን፣ ሕወሓት እና ኤርትራ በጋራ እየሠሩ መሆኑን ገለጹ!
- ስማቸው ያልተጠቀሱ ሌሎች የውጭ ተዋናዮች ተሳትፎ መኖሩንም ጠቆሙ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት በፓርላማ ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ፥ ሱዳን፣ ሕወሓት እና ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ በጋራ እየሠሩ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን፤ ድርጊቱን የደርግን ሥርዓት ለመጣል ከነበረው ጥምረት ጋር በሚመሳሰል መልኩ፣ ስማቸው ያልተጠቀሱ የውጭ ኃይሎች ከጀርባ እየተሳተፉ መሆኑን ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት ማብራሪያ፤ ይህ ጥምረት በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ የሚደቅነው ምንም ዓይነት ሥጋት እንደሌለ አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለምክር ቤቱ ሲናገሩ «ሻዕቢያ፣ ወያኔ እና ሱዳን ይቅርና ሌሎችም ቢጨመሩ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ቅንጣት ታህል ሥጋት የላቸውም» ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
- ስማቸው ያልተጠቀሱ ሌሎች የውጭ ተዋናዮች ተሳትፎ መኖሩንም ጠቆሙ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት በፓርላማ ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ፥ ሱዳን፣ ሕወሓት እና ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ በጋራ እየሠሩ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን፤ ድርጊቱን የደርግን ሥርዓት ለመጣል ከነበረው ጥምረት ጋር በሚመሳሰል መልኩ፣ ስማቸው ያልተጠቀሱ የውጭ ኃይሎች ከጀርባ እየተሳተፉ መሆኑን ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት ማብራሪያ፤ ይህ ጥምረት በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ የሚደቅነው ምንም ዓይነት ሥጋት እንደሌለ አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለምክር ቤቱ ሲናገሩ «ሻዕቢያ፣ ወያኔ እና ሱዳን ይቅርና ሌሎችም ቢጨመሩ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ቅንጣት ታህል ሥጋት የላቸውም» ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍14❤12🤣10🤪1
ያልታከመ የማህፀን ኢንፌክሽን መካንነትን ሊያስከትል ይችላል ተባለ
በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይንም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል እንደሚችል ከብስራት ሬዲዮ ጋር ቆይታ ያደረጉት የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ታዘባቸዉ ዉዴ ገልፀዋል።
የማህፀን ወይንም ብልት አካባቢ የሚከሰት ኢንፌክሽን በርካታ ሰዎችን ከሚያጠቁ የኢንፌክሽን አይነቶች መካከል ዋነኛዉ መሆኑ ተገልጿል ።ለማህፀን ኢንፌክሽን አጋላጭ የሚሆኑ በርካታ ምክንያቶች መኖራቸዉን የሚገልፁት ዶክተር ታዘባቸዉ በግብረ ስጋ ግንኙነት የሚተላለፉ እንደ ክላሚዲያ እና ጎኖሪያ ያሉ ባክቴሪያዎች ዋነኞቹ መሆናቸዉን አስገንዝበዋል ።
በአብዛኛዉ መካንነትን ሊያስከትሉ የሚችሉትም በባክቴሪያ አማካኝነት የሚከሰቱ ኢንፌክሽኖች ናቸዉ። የማህፀን ኢንፌክሽን ከመከሰቱ አስቀድሞ መከላከል ዋነኛዉ መፍትሄ መሆኑን ዶክተር ታዘባቸዉ ገልፀው ብልት አካባቢ የማሳከክ ፣የመቁሰል ፣የሆድ ህመም እና ሽንት በሚሸናበት ወቅት የማቃጠል ስሜት ሲኖር ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ምርመራ ማድረግ እና ህክምና ማግኘት ተገቢ ነዉ ብለዋል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይንም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል እንደሚችል ከብስራት ሬዲዮ ጋር ቆይታ ያደረጉት የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ታዘባቸዉ ዉዴ ገልፀዋል።
የማህፀን ወይንም ብልት አካባቢ የሚከሰት ኢንፌክሽን በርካታ ሰዎችን ከሚያጠቁ የኢንፌክሽን አይነቶች መካከል ዋነኛዉ መሆኑ ተገልጿል ።ለማህፀን ኢንፌክሽን አጋላጭ የሚሆኑ በርካታ ምክንያቶች መኖራቸዉን የሚገልፁት ዶክተር ታዘባቸዉ በግብረ ስጋ ግንኙነት የሚተላለፉ እንደ ክላሚዲያ እና ጎኖሪያ ያሉ ባክቴሪያዎች ዋነኞቹ መሆናቸዉን አስገንዝበዋል ።
በአብዛኛዉ መካንነትን ሊያስከትሉ የሚችሉትም በባክቴሪያ አማካኝነት የሚከሰቱ ኢንፌክሽኖች ናቸዉ። የማህፀን ኢንፌክሽን ከመከሰቱ አስቀድሞ መከላከል ዋነኛዉ መፍትሄ መሆኑን ዶክተር ታዘባቸዉ ገልፀው ብልት አካባቢ የማሳከክ ፣የመቁሰል ፣የሆድ ህመም እና ሽንት በሚሸናበት ወቅት የማቃጠል ስሜት ሲኖር ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ምርመራ ማድረግ እና ህክምና ማግኘት ተገቢ ነዉ ብለዋል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤4👍4
ኢትዮጵያን ከሶማሊላንድ ሪፐብሊክ በርበራ ወደብ የሚያገናኝ እጅግ ዘመናዊና ፈጣን የኤሌክትሪክ ባቡር ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል ተባለ። የግንባታው አጠቃላይ ወጪ $3.47 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን ወጪው በኢትዮጵያ እና በኢሜሬትስ የሚሸፈን ይሆናል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍19❤12🤣8🤝2🤔1👌1🤪1
የፌደራል መንግስት የ2019 በጀት 2 ነጥብ 34 ትሪሊየን ብር ሆኖ ጸድቋል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡
የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2019 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት በጀት ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አቅርቧል፡፡
በዚህም መሰረት 2 ነጥብ 34 ትሪሊየን ብር ሆኖ የቀረበውን የፌደራል መንግስት የ2019 በጀት ምክር ቤቱ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል፡፡
የፀደቀው ጠቅላላ በጀት ከ2018 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ411 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ወይም 21 ነጥብ 3 በመቶ እድገት እንዳለው ተመላክቷል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡
የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2019 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት በጀት ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አቅርቧል፡፡
በዚህም መሰረት 2 ነጥብ 34 ትሪሊየን ብር ሆኖ የቀረበውን የፌደራል መንግስት የ2019 በጀት ምክር ቤቱ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል፡፡
የፀደቀው ጠቅላላ በጀት ከ2018 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ411 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ወይም 21 ነጥብ 3 በመቶ እድገት እንዳለው ተመላክቷል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17👍4😡2
የገቢዎች ሚኒስቴር ለኤሌክትሮኒክስ ደረሰኝ ሶፍትዌር አቅራቢዎች እስከ 250 ሺህ ዶላር የዋስትና ገደብ ጣለ‼️
የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ለመሰማራት በሚፈልጉ የኤሌክትሮኒክስ ደረሰኝ ሶፍትዌር አቅራቢዎች ላይ እንደየደረጃቸው እስከ 250,000 የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የፋይናንስ ዋስትና የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ አውጥቷል።
በዚህ ወር አጋማሽ ላይ የወጣው መመሪያ በሀገሪቱ የታክስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ውስጥ የገበያ መግቢያ አዲስና ፈታኝ መስፈርት እንደሚሆን ይጠበቃል።
የዋስትናው መጠንም በአቅራቢው የአገልግሎት ዓይነትና በሚያገለግሉት ግብር ከፋዮች ልኬት ላይ ተመስርቶ በ10 ደረጃዎች የተከፋፈለ ነው።
በዚህም መሰረት የሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት አቅራቢዎች 30,000 ዶላር፣ የሶፍትዌር-አስ-አ-ሰርቪስ አቅራቢዎች 50,000 ዶላር፣ የኢ-ኮሜርስና ዲጂታል ገበያ አንቀሳቃሾች 25,000 ዶላር፣ እንዲሁም የራሳቸውን የውስጥ ደረሰኝ ሥርዓት የሚጠቀሙ ግብር ከፋዮች 15,000 ዶላር የባንክ ወይም የኢንሹራንስ ዋስትና ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
የዋስትናው መጠንም አቅራቢዎች የሚያገለግሏቸው ደንበኞች ቁጥር ወይም የሽያጭ ልውውጣቸው እያደገ ሲሄድ በየሁለት ዓመቱ የሚታደስ ሲሆን፣ ከ40 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮችን ለሚያገለግሉ ወይም ከ1 ትሪሊዮን ብር በላይ ዓመታዊ ሽያጭ ላላቸው ድርጅቶች ከፍተኛው የዋስትና ጣሪያ 250,000 ዶላር ይደርሳል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ለመሰማራት በሚፈልጉ የኤሌክትሮኒክስ ደረሰኝ ሶፍትዌር አቅራቢዎች ላይ እንደየደረጃቸው እስከ 250,000 የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የፋይናንስ ዋስትና የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ አውጥቷል።
በዚህ ወር አጋማሽ ላይ የወጣው መመሪያ በሀገሪቱ የታክስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ውስጥ የገበያ መግቢያ አዲስና ፈታኝ መስፈርት እንደሚሆን ይጠበቃል።
የዋስትናው መጠንም በአቅራቢው የአገልግሎት ዓይነትና በሚያገለግሉት ግብር ከፋዮች ልኬት ላይ ተመስርቶ በ10 ደረጃዎች የተከፋፈለ ነው።
በዚህም መሰረት የሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት አቅራቢዎች 30,000 ዶላር፣ የሶፍትዌር-አስ-አ-ሰርቪስ አቅራቢዎች 50,000 ዶላር፣ የኢ-ኮሜርስና ዲጂታል ገበያ አንቀሳቃሾች 25,000 ዶላር፣ እንዲሁም የራሳቸውን የውስጥ ደረሰኝ ሥርዓት የሚጠቀሙ ግብር ከፋዮች 15,000 ዶላር የባንክ ወይም የኢንሹራንስ ዋስትና ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
የዋስትናው መጠንም አቅራቢዎች የሚያገለግሏቸው ደንበኞች ቁጥር ወይም የሽያጭ ልውውጣቸው እያደገ ሲሄድ በየሁለት ዓመቱ የሚታደስ ሲሆን፣ ከ40 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮችን ለሚያገለግሉ ወይም ከ1 ትሪሊዮን ብር በላይ ዓመታዊ ሽያጭ ላላቸው ድርጅቶች ከፍተኛው የዋስትና ጣሪያ 250,000 ዶላር ይደርሳል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7👍3
በወላይታ ሶዶ ከተማ የ14 ሰዎችን ኤቲኤም ካርድ የሰረቀው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
በወላይታ ሶዶ ከተማ የኤቲኤም (ATM) ካርድ በመቀየር የማጭበርበር ወንጀል ለመፈጸም የሞከረው ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል ።የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነትና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት በወላይታ ሶዶ ከተማ አንድ የባንክ ደንበኛ ከኤቲኤም ማሽን ገንዘብ ለማውጣት ሲሞክር ማሽኑ ችግር አጋጥሞት ነበር።
በወቅቱ በአቅራቢያው የነበረው ተጠርጣሪ ዳንኤል ደሳለኝ “ካርዱን ስጠኝ፣ በፀጉሬ ጠርጌ እሰጥሃለሁ” በሚል የማታለያ ዘዴ ካርዱን ተቀብሎ ወስዷል።በሰዓቱም የሚስጥር ቁጥሩን (PIN) ሲያስገባ በመመልከት ካርዱን ጠርጎ የመለሰ በማስመሰል ሌላ የተቀየረ የኤቲኤም ካርድ ሰጥቶ ዋናውን ካርድ ይዞ ለማምለጥ ሞክሯል።የደረሰውን ጥቆማ ተከትሎ ፖሊስ ባደረገው ፈጣን ክትትል ተጠርጣሪውን እጅ ከፍንጅ በመያዝ ቁጥጥር ስር አውሏል።
ፖሊስ ምርመራውን በማስፋት በፍርድ ቤት በተሰጠ የብርበራ ትዕዛዝ በተጠርጣሪው የተጎጂውን ካርድ ጨምሮ 14 የተለያዩ ሰዎች የኤቲኤም ካርዶችን ይዞ መገኘቱ ተገልጿል።ፖሊስ ህብረተሰቡ ከኤቲኤም ማሽኖች ገንዘብ በሚያወጣበት ጊዜ የሚስጥር ቁጥሩን ለሌላ አካል እንዳያሳይ በማሽኑ አጠቃቀም ላይ ችግር ካጋጠመውም ከማያውቀው ሰው እርዳታ ከመጠየቅ ይልቅ የባንኩን ባለሙያዎች ወይም የጥበቃ አካላትን ብቻ እንዲያነጋግር አሳስቧል።(Dagu)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በወላይታ ሶዶ ከተማ የኤቲኤም (ATM) ካርድ በመቀየር የማጭበርበር ወንጀል ለመፈጸም የሞከረው ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል ።የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነትና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት በወላይታ ሶዶ ከተማ አንድ የባንክ ደንበኛ ከኤቲኤም ማሽን ገንዘብ ለማውጣት ሲሞክር ማሽኑ ችግር አጋጥሞት ነበር።
በወቅቱ በአቅራቢያው የነበረው ተጠርጣሪ ዳንኤል ደሳለኝ “ካርዱን ስጠኝ፣ በፀጉሬ ጠርጌ እሰጥሃለሁ” በሚል የማታለያ ዘዴ ካርዱን ተቀብሎ ወስዷል።በሰዓቱም የሚስጥር ቁጥሩን (PIN) ሲያስገባ በመመልከት ካርዱን ጠርጎ የመለሰ በማስመሰል ሌላ የተቀየረ የኤቲኤም ካርድ ሰጥቶ ዋናውን ካርድ ይዞ ለማምለጥ ሞክሯል።የደረሰውን ጥቆማ ተከትሎ ፖሊስ ባደረገው ፈጣን ክትትል ተጠርጣሪውን እጅ ከፍንጅ በመያዝ ቁጥጥር ስር አውሏል።
ፖሊስ ምርመራውን በማስፋት በፍርድ ቤት በተሰጠ የብርበራ ትዕዛዝ በተጠርጣሪው የተጎጂውን ካርድ ጨምሮ 14 የተለያዩ ሰዎች የኤቲኤም ካርዶችን ይዞ መገኘቱ ተገልጿል።ፖሊስ ህብረተሰቡ ከኤቲኤም ማሽኖች ገንዘብ በሚያወጣበት ጊዜ የሚስጥር ቁጥሩን ለሌላ አካል እንዳያሳይ በማሽኑ አጠቃቀም ላይ ችግር ካጋጠመውም ከማያውቀው ሰው እርዳታ ከመጠየቅ ይልቅ የባንኩን ባለሙያዎች ወይም የጥበቃ አካላትን ብቻ እንዲያነጋግር አሳስቧል።(Dagu)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12🤣11👍7👀1🙉1
በቀጣይ 5 ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶች ይገነባሉ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጹ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በቀጣይ አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለመገንባት መታቀዱን ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ማብራሪያ ባለፉት ሰባት ዓመታት 1.2 ሚሊዮን ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰው በቀጣዩ አምስት ዓመታት ተጨማሪ 1.5 ሚሊዮን ቤቶች እንደሚገነቡ ተናግረዋል።
እንደ ገለጻቸው የቤቶቹ ግንባታ በመንግሥት፣ በግል ዘርፍ ተሳትፎ እና በሌሎች የአጋርነት መንገዶች የሚከናወን ሲሆን ለዚህም የሚያግዝ ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በካቢኔ መፅደቁን አስታውቀዋል።
በተጨማሪም የኮንስትራክሽን ግብዓት የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ምርት መጀመራቸውን፣ዘርፉን የሚደግፉ የሰው ኃይል ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆናቸውን እና በከተማና በገጠር የቤት ግንባታ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ገልጸዋል።
የቤት ፋይናንስ ተደራሽነትን ለማሳደግ የሞርጌጅ ስርዓት እየተዘጋጀ መሆኑንም ጠቁመው፣ ዜጎች ቤት በቀጥታ መግዛት ባይችሉም በረጅም ጊዜ ክፍያ ከገቢያቸው ጋር በሚጣጣም መንገድ ባለቤት እንዲሆኑ መንግሥት በተለያዩ አማራጮች ላይ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በቀጣይ አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለመገንባት መታቀዱን ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ማብራሪያ ባለፉት ሰባት ዓመታት 1.2 ሚሊዮን ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰው በቀጣዩ አምስት ዓመታት ተጨማሪ 1.5 ሚሊዮን ቤቶች እንደሚገነቡ ተናግረዋል።
እንደ ገለጻቸው የቤቶቹ ግንባታ በመንግሥት፣ በግል ዘርፍ ተሳትፎ እና በሌሎች የአጋርነት መንገዶች የሚከናወን ሲሆን ለዚህም የሚያግዝ ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በካቢኔ መፅደቁን አስታውቀዋል።
በተጨማሪም የኮንስትራክሽን ግብዓት የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ምርት መጀመራቸውን፣ዘርፉን የሚደግፉ የሰው ኃይል ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆናቸውን እና በከተማና በገጠር የቤት ግንባታ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ገልጸዋል።
የቤት ፋይናንስ ተደራሽነትን ለማሳደግ የሞርጌጅ ስርዓት እየተዘጋጀ መሆኑንም ጠቁመው፣ ዜጎች ቤት በቀጥታ መግዛት ባይችሉም በረጅም ጊዜ ክፍያ ከገቢያቸው ጋር በሚጣጣም መንገድ ባለቤት እንዲሆኑ መንግሥት በተለያዩ አማራጮች ላይ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣26❤21👍6🤪1
መረጃ‼️
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት፣ በኤርትራ የተመድ የሰብዓዊ መብት ተቆጣጣሪ ልዩ ራፖርተርን የጊዜ ቆይታ በ23 የድጋፍ ድምጽ በድጋሚ ላንድ ዓመት አራዘመ።
የምክር ቤቱ አባል የኾነችው ኢትዮጵያ፣ የልዩ ራፖርተሩን የጊዜ ቆይታ ለማራዘም የቀረበውን ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ ደግፋ ድምጽ ሠጥታለች።
ኬንያንና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ 17 አገራት ድምጸ ተዓቅቦ ሲያደርጉ፣ ግብጽ፣ ቻይና፣ ቡሩንዲ፣ ፓኪስታን እና ሕንድ የውሳኔ ሀሳቡን ተቃውመዋል።
ረቂቅ የውሳኔ ሀሳቡን ያቀረቡት የአውሮፓ አገራት ነበሩ።
ኤርትራ፣ ከእንግዲህ በልዩ ራፖርተሩ ዙሪያ ከአጋር አገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደማታደርግ በቅርቡ ማሳወቋ አይዘነጋም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት፣ በኤርትራ የተመድ የሰብዓዊ መብት ተቆጣጣሪ ልዩ ራፖርተርን የጊዜ ቆይታ በ23 የድጋፍ ድምጽ በድጋሚ ላንድ ዓመት አራዘመ።
የምክር ቤቱ አባል የኾነችው ኢትዮጵያ፣ የልዩ ራፖርተሩን የጊዜ ቆይታ ለማራዘም የቀረበውን ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ ደግፋ ድምጽ ሠጥታለች።
ኬንያንና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ 17 አገራት ድምጸ ተዓቅቦ ሲያደርጉ፣ ግብጽ፣ ቻይና፣ ቡሩንዲ፣ ፓኪስታን እና ሕንድ የውሳኔ ሀሳቡን ተቃውመዋል።
ረቂቅ የውሳኔ ሀሳቡን ያቀረቡት የአውሮፓ አገራት ነበሩ።
ኤርትራ፣ ከእንግዲህ በልዩ ራፖርተሩ ዙሪያ ከአጋር አገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደማታደርግ በቅርቡ ማሳወቋ አይዘነጋም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አሜሪካ እና ኢራን የተኩስ ልውውጥ‼️
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ፤ " ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ ሶስት የንግድ እና የነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ የድሮን ጥቃት ፈጽማለች " በማለት እንደ በስትራቴጂካዊ የኢራን ቦታዎች ላይ ከባድ የአየር ድብደባ ፈጽሟል።
የመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት ዳግም በእጅጉ አገርሽቷል።
ኢራን፣ ዋሽንግተን ኦማን አቅራቢያ አዳዲስ የባህር መስመሮችን ለመክፈት ጥረት እያደረገች እንደሆነና ይህም የተደረሰውን የመግባቢያ ስምምነት (MoU) የሚጥስ እንደሆነ ትገልጻለች። ይህ እየተባለ ባለበት ሰዓትና ኢራንም መረከቦች በዛ እንዳያልፉ ባስጠነቀቀችበት ሰዓት ነው ኦማን አቅራቢያ 3 መርከቦች የተመቱ።
አሜሪካም ፣ ለተፈጸመው ጥቃት መላሽ ለመስጠት ወሳኝ ስትራቴጂካዊ የሚባሉ የኢራን ወደብ ቦታዎች ደብድባለች። ከዚህ ወታደራዊ እርምጃ ትንሽ ቀደም ብሎ፣ የአሜሪካው ግምጃ ቤት ለኢራን ተሰጥቶ የነበረውን ጊዜያዊ የነዳጅ ማዕቀብ ማቃለያ በይፋ የሰረዘ ሲሆን ይህም ቴህራን በሕጋዊ መንገድ ነዳጅ ወደ ውጭ የመላክ አቅሟን ያግደዋል።
ኢራን፣ አሜሪካ " የተደረሰውን ስምምነት ጥሳለች " የሚል ክስ እያቀረበችባት ነው።
አሁን ላይ የተፈጠረው ሁኔታ ዓለም አቀፍ ነዳጅ ዋጋ እንዲጨምር አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ፤ " ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ ሶስት የንግድ እና የነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ የድሮን ጥቃት ፈጽማለች " በማለት እንደ በስትራቴጂካዊ የኢራን ቦታዎች ላይ ከባድ የአየር ድብደባ ፈጽሟል።
የመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት ዳግም በእጅጉ አገርሽቷል።
ኢራን፣ ዋሽንግተን ኦማን አቅራቢያ አዳዲስ የባህር መስመሮችን ለመክፈት ጥረት እያደረገች እንደሆነና ይህም የተደረሰውን የመግባቢያ ስምምነት (MoU) የሚጥስ እንደሆነ ትገልጻለች። ይህ እየተባለ ባለበት ሰዓትና ኢራንም መረከቦች በዛ እንዳያልፉ ባስጠነቀቀችበት ሰዓት ነው ኦማን አቅራቢያ 3 መርከቦች የተመቱ።
አሜሪካም ፣ ለተፈጸመው ጥቃት መላሽ ለመስጠት ወሳኝ ስትራቴጂካዊ የሚባሉ የኢራን ወደብ ቦታዎች ደብድባለች። ከዚህ ወታደራዊ እርምጃ ትንሽ ቀደም ብሎ፣ የአሜሪካው ግምጃ ቤት ለኢራን ተሰጥቶ የነበረውን ጊዜያዊ የነዳጅ ማዕቀብ ማቃለያ በይፋ የሰረዘ ሲሆን ይህም ቴህራን በሕጋዊ መንገድ ነዳጅ ወደ ውጭ የመላክ አቅሟን ያግደዋል።
ኢራን፣ አሜሪካ " የተደረሰውን ስምምነት ጥሳለች " የሚል ክስ እያቀረበችባት ነው።
አሁን ላይ የተፈጠረው ሁኔታ ዓለም አቀፍ ነዳጅ ዋጋ እንዲጨምር አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍7😢1
የቤት ኪራይ ጭማሪ ይፋ ሆነ
በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ውል ምዝገባ ተጀመረ፤ የጭማሪው ጣሪያ 11.5% ሆነ
በአዲስ አበባ ከተማ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል ምዝገባ ዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች በይፋ ተጀምሯል።
ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ፍትሐዊ የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መጽደቁን የከተማዋ የቤቶች አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል።
ይህ አሰራር በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን ለመግታትና የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ ያለመ ነው።
ውሳኔው የነዋሪዎችን የመክፈል አቅም ያገናዘበ ሳይንሳዊ ጥናት ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ አከራዮች ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ፣ ተከራዮች ደግሞ ከስነ-ልቦና ስጋትና መፈናቀል ድነው እንዲረጋጉ ይረዳል ተብሏል።
ይሁን እንጂ አዲሱ የዋጋ ተመን ከመጣሉ በፊት በርካታ አከራዮች በተከራዮቻቸው ላይ አስቀድመው ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ማድረጋቸው በነዋሪዎች ዘንድ ቅሬታ እየቀሰቀሰ ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ውል ምዝገባ ተጀመረ፤ የጭማሪው ጣሪያ 11.5% ሆነ
በአዲስ አበባ ከተማ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል ምዝገባ ዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች በይፋ ተጀምሯል።
ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ፍትሐዊ የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መጽደቁን የከተማዋ የቤቶች አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል።
ይህ አሰራር በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን ለመግታትና የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ ያለመ ነው።
ውሳኔው የነዋሪዎችን የመክፈል አቅም ያገናዘበ ሳይንሳዊ ጥናት ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ አከራዮች ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ፣ ተከራዮች ደግሞ ከስነ-ልቦና ስጋትና መፈናቀል ድነው እንዲረጋጉ ይረዳል ተብሏል።
ይሁን እንጂ አዲሱ የዋጋ ተመን ከመጣሉ በፊት በርካታ አከራዮች በተከራዮቻቸው ላይ አስቀድመው ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ማድረጋቸው በነዋሪዎች ዘንድ ቅሬታ እየቀሰቀሰ ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14🤔4👍2
የኤርትራ መንግስት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ በፓርላማ ቀርበው ለሰጡት ማብራሪያ እና በተለይ ከኤርትራ (ሻዕቢያ)፣ ከሕወሓት እና ከሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ላነሷቸው ነጥቦች በማስታወቂያ ሚኒስቴሩ በኩል ፈጣንና ጠንከር ያለ ምላሽ ሰጥቷል።
ሁለቱ ወገኖች በቀጠናው ሰላምና በጎረቤት ሀገራት ጣልቃ ገብነት ዙሪያ እርስ በርሳቸው ተቃራኒ የሆኑ ክሶችን ሰንዝረዋል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በፓርላማ ንግግራቸው በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ወጣቶችን በጉልበት እያፈሱ ለሱዳን ጦርነት "እየሸጡ" መሆኑን ገልጸዋል።
"የትግራይ ወጣቶች በማያውቁት ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ህይወታቸውን እያጡ ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ድርጊት የህዝቡን መከራ የሚያባብስ ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
በተቃራኒው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ ለሱዳን ግጭት መባባስ ተጠያቂው የኢትዮጵያ መንግስት ራሱ ነው ሲል ገልጿል።
ኢትዮጵያ ለሱዳኑ ፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (RSF) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሚስጥራዊ የጦር ሰፈርና ማሰልጠኛ በመስጠት በቀጥታ በጦርነቱ ውስጥ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑንና ለዚህም "ግልጽ ማስረጃዎች አሉ" ሲል አጸፋዊ ክስ ሰንዝሯል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም አይነት "ትንኮሳ" ለመመከት መንግስታቸው ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኤርትራ መንግስት በበኩሉ፣ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ህግጋትንና የቀጠናውን ሀገራት ሉዓላዊነት እየጣሰች ያለችው "የባህር በር ባለቤትነት" በሚል በምታሳየው የግዛት ማስፋፋት ፍላጎት ነው ብሏል።
የኢትዮጵያ መንግስት በአንድ በኩል "ጥቃት አድራሽ" በሌላ በኩል ደግሞ "ተጠቂ" ሆኖ የመቅረብ ድራማ እየሰራ ነው ስትልም ወርፋለች።
@Addis_Reporter
ሁለቱ ወገኖች በቀጠናው ሰላምና በጎረቤት ሀገራት ጣልቃ ገብነት ዙሪያ እርስ በርሳቸው ተቃራኒ የሆኑ ክሶችን ሰንዝረዋል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በፓርላማ ንግግራቸው በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ወጣቶችን በጉልበት እያፈሱ ለሱዳን ጦርነት "እየሸጡ" መሆኑን ገልጸዋል።
"የትግራይ ወጣቶች በማያውቁት ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ህይወታቸውን እያጡ ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ድርጊት የህዝቡን መከራ የሚያባብስ ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
በተቃራኒው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ ለሱዳን ግጭት መባባስ ተጠያቂው የኢትዮጵያ መንግስት ራሱ ነው ሲል ገልጿል።
ኢትዮጵያ ለሱዳኑ ፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (RSF) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሚስጥራዊ የጦር ሰፈርና ማሰልጠኛ በመስጠት በቀጥታ በጦርነቱ ውስጥ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑንና ለዚህም "ግልጽ ማስረጃዎች አሉ" ሲል አጸፋዊ ክስ ሰንዝሯል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም አይነት "ትንኮሳ" ለመመከት መንግስታቸው ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኤርትራ መንግስት በበኩሉ፣ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ህግጋትንና የቀጠናውን ሀገራት ሉዓላዊነት እየጣሰች ያለችው "የባህር በር ባለቤትነት" በሚል በምታሳየው የግዛት ማስፋፋት ፍላጎት ነው ብሏል።
የኢትዮጵያ መንግስት በአንድ በኩል "ጥቃት አድራሽ" በሌላ በኩል ደግሞ "ተጠቂ" ሆኖ የመቅረብ ድራማ እየሰራ ነው ስትልም ወርፋለች።
@Addis_Reporter
👍8❤5🤔1😢1🤣1
📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
👍4❤2
ኢራናውያን በሽተኞች ናቸው-ትራምፕ‼️
የኢራን ሰዎች በሽተኞች ናቸው፣ ከእነሱ ጋር ስምምነት አላደርግም ሲሉ ዶናልድ ትራምፕ ተናግረዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢራን ሰዎች በሽተኞች ናቸው፣ ከእነሱ ጋር ስምምነት አላደርግም ሲሉ ዶናልድ ትራምፕ ተናግረዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣11❤3👍2💯2🤡1
የመቅጃ ማሽኖች ልኬት ችግር በታየባቸው ማደያዎች ላይ ተገቢው የህግ እርምጃ ተወስዷል ተባለ
በአዲስ አበባ ከተማ በነዳጅ ማደያዎች ላይ በተከናወነው የመቅጃ ልኬት ምርመራ፣ የመቅጃ ማሽኖች ልኬት ችግር በታየባቸው ማደያዎች ላይ ተገቢው የህግ እርምጃ ተወስዷል ሲል የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አሳወቀ ፡፡
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ወ/ሮ ሃላፊ ሀቢባ ሲራጅ እንደገለጹት፣ በሁለት ነዳጅ ማደያዎች የመቅጃ ማሽን የልኬት ችግር በመገኘቱ ከነዳጅ አቅርቦት ለሁለት ወራት እንዲታገዱ ተደርጓል። እርምጃ የተወሰደባቸው የነዳጅ ማደያዎች በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጋርመንት አካባቢ የሚገኘው ኖክ ነዳጅ ማደያ እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው አልፋ ነዳጅ ማደያ ናቸው ብለዋል።
እንዲሁም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ተባረክ ነዳጅ ማደያ ከነዳጅ አቅርቦት ለአንድ ወር እንዲታገድ ተደርጓል የተባለ ሲሆን፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቱሉ ዲምቱ የሚገኘው የተባበሩት ነዳጅ ማደያ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካዛንቺስ ሱፐር ማርኬት አካባቢ የሚገኘው ኦላ ነዳጅ ማደያ የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ አክለውም፣ ቢሮው በከተማው ውስጥ ልኬትን በማዛባት ፍትሃዊ የንግድ ውድድርን የሚያደናቅፉ ድርጊቶችን በሚፈጽሙ ነዳጅ ማደያዎች ላይ የጀመረውን የክትትልና የሕግ ማስከበር እርምጃ ይበልጥ በማጠናከር እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአዲስ አበባ ከተማ በነዳጅ ማደያዎች ላይ በተከናወነው የመቅጃ ልኬት ምርመራ፣ የመቅጃ ማሽኖች ልኬት ችግር በታየባቸው ማደያዎች ላይ ተገቢው የህግ እርምጃ ተወስዷል ሲል የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አሳወቀ ፡፡
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ወ/ሮ ሃላፊ ሀቢባ ሲራጅ እንደገለጹት፣ በሁለት ነዳጅ ማደያዎች የመቅጃ ማሽን የልኬት ችግር በመገኘቱ ከነዳጅ አቅርቦት ለሁለት ወራት እንዲታገዱ ተደርጓል። እርምጃ የተወሰደባቸው የነዳጅ ማደያዎች በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጋርመንት አካባቢ የሚገኘው ኖክ ነዳጅ ማደያ እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው አልፋ ነዳጅ ማደያ ናቸው ብለዋል።
እንዲሁም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ተባረክ ነዳጅ ማደያ ከነዳጅ አቅርቦት ለአንድ ወር እንዲታገድ ተደርጓል የተባለ ሲሆን፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቱሉ ዲምቱ የሚገኘው የተባበሩት ነዳጅ ማደያ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካዛንቺስ ሱፐር ማርኬት አካባቢ የሚገኘው ኦላ ነዳጅ ማደያ የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ አክለውም፣ ቢሮው በከተማው ውስጥ ልኬትን በማዛባት ፍትሃዊ የንግድ ውድድርን የሚያደናቅፉ ድርጊቶችን በሚፈጽሙ ነዳጅ ማደያዎች ላይ የጀመረውን የክትትልና የሕግ ማስከበር እርምጃ ይበልጥ በማጠናከር እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20👍3🥱1
ኢትዮጵያ በኤርትራ ላይ የቀረበውን የሰብዓዊ መብት ውሳኔ ደገፈች‼️
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በኤርትራ ላይ የሾመውን የልዩ ራፖርተር የሥራ ዘመን አራዘመ።
ኢትዮጵያ የውሳኔ ሃሳቡን ደግፋ ድምፅ ሰጥታለች
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በኤርትራ ያለውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ የሚከታተሉትን የልዩ ራፖርተር ዶ/ር መሐመድ አብደልሰላምን የሥራ ዘመን ለአንድ ተጨማሪ ዓመት ማራዘሙ ታውቋል።
ምክር ቤቱ የልዩ ራፖርተሩን የሥራ ዘመን ለማራዘም የቀረበውን ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ ያሳለፈው በአብላጫ ድምፅ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ መንግስት የውሳኔ ሃሳቡን በመደገፍ ድምፅ መስጠቱ ተረጋግጧል።
በምክር ቤቱ አባላት መካከል በተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ላይ የቀረበውን ረቂቅ ውሳኔ ኢትዮጵያን ጨምሮ 23 ሀገራት የደገፉት ሲሆን፣ 6 ሀገራት ደግሞ ተቃውመውታል።
ቀሪዎቹ 17 ሀገራት ደግሞ ድምፅ ከመስጠት መታቀባቸው ታውቋል።
ኢትዮጵያ ለውሳኔ ሃሳቡ ድጋፏን የቸረች ሲሆን፣ የኤርትራ መንግስት የዜጎቹን የሰብዓዊ መብት እንዲያከብርና ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርግ የበኩሏን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች።
ይህ የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ አቋም በቀጣናዊ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ውሳኔው በሁለቱ ጎረቤት ሀገራት የወደፊት ግንኙነት እና በአጠቃላይ በምስራቅ አፍሪካ ፖለቲካዊ ምህዳር ላይ የራሱ የሆነ ከፍተኛ አንድምታ ይኖረዋል ተብሎ ይገመታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በኤርትራ ላይ የሾመውን የልዩ ራፖርተር የሥራ ዘመን አራዘመ።
ኢትዮጵያ የውሳኔ ሃሳቡን ደግፋ ድምፅ ሰጥታለች
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በኤርትራ ያለውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ የሚከታተሉትን የልዩ ራፖርተር ዶ/ር መሐመድ አብደልሰላምን የሥራ ዘመን ለአንድ ተጨማሪ ዓመት ማራዘሙ ታውቋል።
ምክር ቤቱ የልዩ ራፖርተሩን የሥራ ዘመን ለማራዘም የቀረበውን ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ ያሳለፈው በአብላጫ ድምፅ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ መንግስት የውሳኔ ሃሳቡን በመደገፍ ድምፅ መስጠቱ ተረጋግጧል።
በምክር ቤቱ አባላት መካከል በተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ላይ የቀረበውን ረቂቅ ውሳኔ ኢትዮጵያን ጨምሮ 23 ሀገራት የደገፉት ሲሆን፣ 6 ሀገራት ደግሞ ተቃውመውታል።
ቀሪዎቹ 17 ሀገራት ደግሞ ድምፅ ከመስጠት መታቀባቸው ታውቋል።
ኢትዮጵያ ለውሳኔ ሃሳቡ ድጋፏን የቸረች ሲሆን፣ የኤርትራ መንግስት የዜጎቹን የሰብዓዊ መብት እንዲያከብርና ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርግ የበኩሏን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች።
ይህ የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ አቋም በቀጣናዊ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ውሳኔው በሁለቱ ጎረቤት ሀገራት የወደፊት ግንኙነት እና በአጠቃላይ በምስራቅ አፍሪካ ፖለቲካዊ ምህዳር ላይ የራሱ የሆነ ከፍተኛ አንድምታ ይኖረዋል ተብሎ ይገመታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤8🤣7👍3
ልዩ መረጃ‼️
ዩክሬን ለራሺያ ሲዋጉ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ስም ዝርዝር ይፋ አደረገች‼️
የዩክሬይን የስለላ ተቋም በሩሲያ ጦርነት ‹‹ተሰልፈዋል›› ያላቸውን 34 ኢትዮጵያዊያን ስም ዝርዝር ይፋ አደረገ፡፡
በዩክሬይን መንግስት የስለላ ተቋም ስር የሚንቀሳቀሰው ‹‹አይ ወንት ቱ ሊቭ›› የተሰኘው ፕሮጀክት ዛሬ በሩሲያ ጦርነት ውስጥ እየተሳተፉ ነው ያላቸውን 34 ኢትዮጵያዊያን ስም ይፋ አድርጓል፡፡ ፕሮጀክቱ ይህንን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ‹‹የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጄ ላቭሮቭ ወደኢትዮጵያ የገቡት በአፍሪካ የሚያደርጉት ጉብኝት አንዱ አካል አድርገው ነው፡፡ ይህ ጉብኝታቸው ደግሞ ሩሲያ በዩክሬይን ላይ በምታደርገው ጦርነት የአፍሪካ ዜጎችን ማሰለፏ ከፍተኛ ተቃውሞ መቀስቀሱን ተከትሎ ነው›› ብሏል፡፡
ሚኒስትሩ አዲስ አበባ መግባታቸውን ምክንያት በማድረግም ለሩሲያ ተሰልፈው የሚዋጉ 34 ኢትዮጵያዊያንን ስም ይፋ ለማድረግ መወሰኑን የጠቀሰው ፕሮጀክቱ ከእነዚህ መካከል ቢያንስ 3ቱ መሞታቸውን አስታውቋል፡፡ ፕሮጀክቱ እንደገለፀው እነዚህ ኢትዮጵያዊያን ለሩሲያ ጦር ሀይል የፈረሙት በተለያየ ጊዜ ነው፡፡ እ.ኤ.አ ዲሴምበር 24 ቀን 2024 አ.ም 8ቱ ኮንትራት መፈረማቸውን ጠቅሶ፣ ሴፕቴምበር 1 ቀን 2025 ደግሞ 10ሩ እንዲሁም ኦክቶበር 30 ቀን 2025 በተመሳሳይ 9 ሰዎች ኮንትራት መፈፀማቸውን አስረድቷል፡፡ እነዚህ ኢትዮጵያዊያን ኮንትራቱን የፈረሙት በቀጥታ ከሩሲያ ጦር ሀይል ጋር ሳይሆን በህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች አማካኝነት እንደሆነ አስታውቋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዩክሬን ለራሺያ ሲዋጉ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ስም ዝርዝር ይፋ አደረገች‼️
የዩክሬይን የስለላ ተቋም በሩሲያ ጦርነት ‹‹ተሰልፈዋል›› ያላቸውን 34 ኢትዮጵያዊያን ስም ዝርዝር ይፋ አደረገ፡፡
በዩክሬይን መንግስት የስለላ ተቋም ስር የሚንቀሳቀሰው ‹‹አይ ወንት ቱ ሊቭ›› የተሰኘው ፕሮጀክት ዛሬ በሩሲያ ጦርነት ውስጥ እየተሳተፉ ነው ያላቸውን 34 ኢትዮጵያዊያን ስም ይፋ አድርጓል፡፡ ፕሮጀክቱ ይህንን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ‹‹የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጄ ላቭሮቭ ወደኢትዮጵያ የገቡት በአፍሪካ የሚያደርጉት ጉብኝት አንዱ አካል አድርገው ነው፡፡ ይህ ጉብኝታቸው ደግሞ ሩሲያ በዩክሬይን ላይ በምታደርገው ጦርነት የአፍሪካ ዜጎችን ማሰለፏ ከፍተኛ ተቃውሞ መቀስቀሱን ተከትሎ ነው›› ብሏል፡፡
ሚኒስትሩ አዲስ አበባ መግባታቸውን ምክንያት በማድረግም ለሩሲያ ተሰልፈው የሚዋጉ 34 ኢትዮጵያዊያንን ስም ይፋ ለማድረግ መወሰኑን የጠቀሰው ፕሮጀክቱ ከእነዚህ መካከል ቢያንስ 3ቱ መሞታቸውን አስታውቋል፡፡ ፕሮጀክቱ እንደገለፀው እነዚህ ኢትዮጵያዊያን ለሩሲያ ጦር ሀይል የፈረሙት በተለያየ ጊዜ ነው፡፡ እ.ኤ.አ ዲሴምበር 24 ቀን 2024 አ.ም 8ቱ ኮንትራት መፈረማቸውን ጠቅሶ፣ ሴፕቴምበር 1 ቀን 2025 ደግሞ 10ሩ እንዲሁም ኦክቶበር 30 ቀን 2025 በተመሳሳይ 9 ሰዎች ኮንትራት መፈፀማቸውን አስረድቷል፡፡ እነዚህ ኢትዮጵያዊያን ኮንትራቱን የፈረሙት በቀጥታ ከሩሲያ ጦር ሀይል ጋር ሳይሆን በህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች አማካኝነት እንደሆነ አስታውቋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13👍3🤔2😢2🥰1