📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
❤2👍2
በአርባ ምንጭ ከተማ የ12 ዓመቷን የገዛ ሚስቱ እህትን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
ተከሳሽ አቶ ኃይማኖት ዮሐንስ የተባለው ግለሰብ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት ሰዓቱ በውል በማይታወቅበት በአርባ ምንጭ ከተማ ሼቻ ክፍለ ከተማ ዶይሳ ቀበሌ ልዩ ስፍራው አሻም ሆቴል ጀርባ አከባቢ የባለቤቱ እህት በሆነች ታዳጊ ልጅ ላይ የግብረ ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል መፈፀሙ ተገልጿል።
ተከሳሽ ከእሱ እና ከባለቤቱ ጋር በአንድ ቤት በሥራ አጋዥነት የምትኖረውን ዕድሜዋ 12 ዓመት የሆነችውን የግል ተበዳይን ባለቤቱ ለስራ በሄደችበት ምሽት አጋጣሚውን በመጠቀም የፖርኖግራፊ (ልቅ የወሲብ) ፊልም በቴለቪዥን በመክፈት እንድትመለከት ካደረገ በኋላ የግል ተበዳይ የለበሰችውን ልብስ አውልቆ በመራቢያ አካሏ እና በመቀመጫዋ በተደጋጋሚ ጊዜ የግብረ ስጋ ግንኙነት የፈፀመባት እና ድርጊቱን ለሰዎች እንዳትናገር ያስጠነቀቃት ቢሆንም በድርጊቱ ምክንያት በግል ተበዳይ ላይ በተከሰተ ህመም ተበዳይ ጉዳዩን ለጎረቤት በመንገሯ የወንጀል ምርመራ ሂደቱ ተጀምሮ ለውጤት በቅቷል ሲል የዓቃቤ ክስ መዝገብ ያስረዳል።
የወንጀል ድርጊቱ መፈፀም ሪፖርት የደረሰው የከተማው ፖሊስ መምሪያ የሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ልዩ መርማሪ ከዐ/ሕግ ጋር በመቀናጀት የምርመራ መዝገቡን በሰው እና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ ክስ ይመሰርታል።ጉዳዩን የተመለከተው የአርባ ምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል ብይን ሰጥቷል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ተከሳሽ አቶ ኃይማኖት ዮሐንስ የተባለው ግለሰብ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት ሰዓቱ በውል በማይታወቅበት በአርባ ምንጭ ከተማ ሼቻ ክፍለ ከተማ ዶይሳ ቀበሌ ልዩ ስፍራው አሻም ሆቴል ጀርባ አከባቢ የባለቤቱ እህት በሆነች ታዳጊ ልጅ ላይ የግብረ ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል መፈፀሙ ተገልጿል።
ተከሳሽ ከእሱ እና ከባለቤቱ ጋር በአንድ ቤት በሥራ አጋዥነት የምትኖረውን ዕድሜዋ 12 ዓመት የሆነችውን የግል ተበዳይን ባለቤቱ ለስራ በሄደችበት ምሽት አጋጣሚውን በመጠቀም የፖርኖግራፊ (ልቅ የወሲብ) ፊልም በቴለቪዥን በመክፈት እንድትመለከት ካደረገ በኋላ የግል ተበዳይ የለበሰችውን ልብስ አውልቆ በመራቢያ አካሏ እና በመቀመጫዋ በተደጋጋሚ ጊዜ የግብረ ስጋ ግንኙነት የፈፀመባት እና ድርጊቱን ለሰዎች እንዳትናገር ያስጠነቀቃት ቢሆንም በድርጊቱ ምክንያት በግል ተበዳይ ላይ በተከሰተ ህመም ተበዳይ ጉዳዩን ለጎረቤት በመንገሯ የወንጀል ምርመራ ሂደቱ ተጀምሮ ለውጤት በቅቷል ሲል የዓቃቤ ክስ መዝገብ ያስረዳል።
የወንጀል ድርጊቱ መፈፀም ሪፖርት የደረሰው የከተማው ፖሊስ መምሪያ የሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ልዩ መርማሪ ከዐ/ሕግ ጋር በመቀናጀት የምርመራ መዝገቡን በሰው እና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ ክስ ይመሰርታል።ጉዳዩን የተመለከተው የአርባ ምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል ብይን ሰጥቷል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16🤯8👍4😢4
በሰነዶች ማረጋገጫ ንብረት ገዝተው ስም ያላዛወሩ ዜጎች በአስቸኳይ ይዞታቸውን እንዲያስመዘግቡ ተጠየቀ
ቀደም ባሉ ጊዜያት ከሪል እስቴት አልሚዎችም ሆነ ከግለሰቦች ጋር የቤት ወይም የመሬት ግብይት ፈጽመው፣ በሰነዶች ማረጋገጫ ብቻ የያዙና እስካሁን የስመ-ንብረት ዝውውር ያላደረጉ አካላት በአስቸኳይ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀረበ ።
የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ መኮንን ያኢ እንደገለጹት፤ ግዢ ፈጽመው የስም ዝውውር ያላደረጉ ወገኖች ለከፍተኛ ጉዳትና ለአደጋ እየተጋለጡ ይገኛሉ።
የስመ-ንብረት ዝውውር ዋና ዓላማ አንድ ግለሰብ ያፈራውን ንብረት ለሌላ አካል የሚያስተላልፍበት ሕጋዊ ሥርዓት መሆኑንና የመጨረሻው መዳረሻም የይዞታ ማረጋገጫ (ካርታ) ማግኘት መሆኑን ኃላፊው አስረድተዋል።
በመሆኑም ባለንብረቶች መብታቸውን ለማስከበርና ንብረታቸውን ከማንኛውም ሕጋዊ ስጋት ለመጠበቅ ሲሉ፣ ሳይዘገዩ ወደ መሬት ተቋማት በመቅረብ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ቀደም ባሉ ጊዜያት ከሪል እስቴት አልሚዎችም ሆነ ከግለሰቦች ጋር የቤት ወይም የመሬት ግብይት ፈጽመው፣ በሰነዶች ማረጋገጫ ብቻ የያዙና እስካሁን የስመ-ንብረት ዝውውር ያላደረጉ አካላት በአስቸኳይ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀረበ ።
የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ መኮንን ያኢ እንደገለጹት፤ ግዢ ፈጽመው የስም ዝውውር ያላደረጉ ወገኖች ለከፍተኛ ጉዳትና ለአደጋ እየተጋለጡ ይገኛሉ።
የስመ-ንብረት ዝውውር ዋና ዓላማ አንድ ግለሰብ ያፈራውን ንብረት ለሌላ አካል የሚያስተላልፍበት ሕጋዊ ሥርዓት መሆኑንና የመጨረሻው መዳረሻም የይዞታ ማረጋገጫ (ካርታ) ማግኘት መሆኑን ኃላፊው አስረድተዋል።
በመሆኑም ባለንብረቶች መብታቸውን ለማስከበርና ንብረታቸውን ከማንኛውም ሕጋዊ ስጋት ለመጠበቅ ሲሉ፣ ሳይዘገዩ ወደ መሬት ተቋማት በመቅረብ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13👍2
አራት ልጆቻቸውን እሰከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ አስተምረው የልጅ ልጆችም ያዩት የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኝ እናት
ከላይ በምስሉ የምታያቸው ወ/ሮ አልማዝ አሻራው ይባላሉ። በጌዴኦ ዞን የገደብ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ፣ በቤተሰብ ጫና ምክንያት በ1982 ዓ.ም ከ4ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳቋረጡ ይገልጻሉ።
በ1983 ዓ.ም ትዳር የመሰረቱት ወ/ሮ አልማዝ የስምንት ልጆች እናት ናቸው። አራት ልጆቻቸውን እሰከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ አስተምረዋል፣ የልጅ ልጆችም አይተዋል።
የቀሩት አራት ልጆቻቸው ደግሞ ከ5ኛ እሰከ 12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ትምህርታቸውን ዳግም መማር ያሰቡት ትላንት ያላሳኩትን፣ ያልኖሩትን ህልማቸውን ዳግም ለመኖር እንደሆነ ወ/ሮ አልማዝ ይገልጻሉ።
እኚህ ብርቱ እናት ዘንድሮ እየተሰጠ የሚገኘውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው፣ በመጀመሪያው ዙር በበይነ መረብ ፈተናቸውን መውሰድ ጀምረዋል። ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ተምረው መመረቅ ህልማቸው እንደሆነም ይናገራሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከላይ በምስሉ የምታያቸው ወ/ሮ አልማዝ አሻራው ይባላሉ። በጌዴኦ ዞን የገደብ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ፣ በቤተሰብ ጫና ምክንያት በ1982 ዓ.ም ከ4ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳቋረጡ ይገልጻሉ።
በ1983 ዓ.ም ትዳር የመሰረቱት ወ/ሮ አልማዝ የስምንት ልጆች እናት ናቸው። አራት ልጆቻቸውን እሰከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ አስተምረዋል፣ የልጅ ልጆችም አይተዋል።
የቀሩት አራት ልጆቻቸው ደግሞ ከ5ኛ እሰከ 12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ትምህርታቸውን ዳግም መማር ያሰቡት ትላንት ያላሳኩትን፣ ያልኖሩትን ህልማቸውን ዳግም ለመኖር እንደሆነ ወ/ሮ አልማዝ ይገልጻሉ።
እኚህ ብርቱ እናት ዘንድሮ እየተሰጠ የሚገኘውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው፣ በመጀመሪያው ዙር በበይነ መረብ ፈተናቸውን መውሰድ ጀምረዋል። ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ተምረው መመረቅ ህልማቸው እንደሆነም ይናገራሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤39👍5👌1
የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በመስረቅ ያከማቸ ግለሰብ በ6 ዓመት እስራት ተቀጣ
የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመስረቅ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በ6 ዓመት ጽኑ እስራት መቀጣቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት አሰታውቋል፡፡
ግለሰቡ ከ3.8 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸውን የኤሌክትሪክ ገመዶች፣ አልሙኒየሞችና መዳቦች በመስረቅ ባሳለፍነው መጋቢት ወር መጨረሻ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ያሰታወሰው አግልግሎቱ፤ በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የካ ምድብ ችሎት ባደረገው ክርክር በግለሰቡ ላይ የ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲወሰን ማደረግ መቻሉን ለጣቢያችን የላከው መረጃ ያመላክታል፡፡
በተያያዘም በየካ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ኬብሮን መድኃኒት ቤት አካባቢ በግንባታ ላይ ከሚገኝ ህንፃ ላይ የወደቀ ህንፃ መወጣጫ ዊንች በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብልና በትራንስፎርመር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የገለጸው አገልግሎቱ፤ ተቋሙ ጉዳት የደረሰበትን የኤሌክትሪክ ኬብልና ትራንስፎርመር በመተካት ወደ አገልግሎት ለመመለስ ከ1 ሚሊየን 9 መቶ ሺሕ ብር በላይ እንዲከፍል በፍርድ ቤት ስለመወሰኑ ገልጿል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመስረቅ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በ6 ዓመት ጽኑ እስራት መቀጣቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት አሰታውቋል፡፡
ግለሰቡ ከ3.8 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸውን የኤሌክትሪክ ገመዶች፣ አልሙኒየሞችና መዳቦች በመስረቅ ባሳለፍነው መጋቢት ወር መጨረሻ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ያሰታወሰው አግልግሎቱ፤ በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የካ ምድብ ችሎት ባደረገው ክርክር በግለሰቡ ላይ የ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲወሰን ማደረግ መቻሉን ለጣቢያችን የላከው መረጃ ያመላክታል፡፡
በተያያዘም በየካ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ኬብሮን መድኃኒት ቤት አካባቢ በግንባታ ላይ ከሚገኝ ህንፃ ላይ የወደቀ ህንፃ መወጣጫ ዊንች በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብልና በትራንስፎርመር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የገለጸው አገልግሎቱ፤ ተቋሙ ጉዳት የደረሰበትን የኤሌክትሪክ ኬብልና ትራንስፎርመር በመተካት ወደ አገልግሎት ለመመለስ ከ1 ሚሊየን 9 መቶ ሺሕ ብር በላይ እንዲከፍል በፍርድ ቤት ስለመወሰኑ ገልጿል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍3
ትምህርት መስከረም 5 ይጀመራል!
የትምህርት ሚኒስቴር በመላው ሀገሪቱ ወጥነት ያለው የማስተማር ሂደት እንዲኖር ለማስቻል ያዘጋጀውን የ2019 ዓ.ም አጠቃላይ የትምህርት ዘመን ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ (ካላንደር) ለክልሎች እና ለከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች አስተላልፏል።
በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፦
- ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይከናወናል።
- መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም በይፋ ትምህርት ይጀምራል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የትምህርት ሚኒስቴር በመላው ሀገሪቱ ወጥነት ያለው የማስተማር ሂደት እንዲኖር ለማስቻል ያዘጋጀውን የ2019 ዓ.ም አጠቃላይ የትምህርት ዘመን ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ (ካላንደር) ለክልሎች እና ለከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች አስተላልፏል።
በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፦
- ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይከናወናል።
- መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም በይፋ ትምህርት ይጀምራል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12👍8🤔4👌1
በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለው አፈሳ ተጠናክሮ በመቀጠሉ ምክንያት ይህንን ድርጊት በመቃወም በዛሬው ዕለት መቀሌን ጨምሮ በአዲጉደምና በሌሎች ከተሞች ከሰዎች እንቅስቃሴ ታቃበው ውለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10👍7🤣5😢3💔3
መረጃ‼️
የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት አስተዳደር ባለሥልጣን፣ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ ያለ ሕጋዊ ፍቃድ አንዳንድ የሕክምና መሳሪያዎችን የማስተዋወቅ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ሲል ከሠሠ።
ባለሥልጣኑ ዩትዩብንና ቲክቶክን ጨምሮ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ ሕጋዊ ማረጋገጫ እና ፍቃድ ያልተሠጠባቸውን የሕክምና መሳሪያዎች ያስተዋወቁ አካላት ማስታወቂያዎቹን ባስቸኳይ እንዲያነሱ አሳስቧል።
አንዳንድ የሕክምና መሳሪያዎች ለሕዝብ በማስታወቂያ መልክ እንዳይቀርቡ በሕግ የተከለከሉ ናቸው ያለው ባለስልጣኑ፣ ማሳሰቢያውን በመጣስ ያለ ሕጋዊ ፍቃድ የሕክምና መሳሪያዎችን ማስተዋወቅ በሚቀጥሉ አካላት ላይ ሕጋዊ ርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት አስተዳደር ባለሥልጣን፣ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ ያለ ሕጋዊ ፍቃድ አንዳንድ የሕክምና መሳሪያዎችን የማስተዋወቅ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ሲል ከሠሠ።
ባለሥልጣኑ ዩትዩብንና ቲክቶክን ጨምሮ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ ሕጋዊ ማረጋገጫ እና ፍቃድ ያልተሠጠባቸውን የሕክምና መሳሪያዎች ያስተዋወቁ አካላት ማስታወቂያዎቹን ባስቸኳይ እንዲያነሱ አሳስቧል።
አንዳንድ የሕክምና መሳሪያዎች ለሕዝብ በማስታወቂያ መልክ እንዳይቀርቡ በሕግ የተከለከሉ ናቸው ያለው ባለስልጣኑ፣ ማሳሰቢያውን በመጣስ ያለ ሕጋዊ ፍቃድ የሕክምና መሳሪያዎችን ማስተዋወቅ በሚቀጥሉ አካላት ላይ ሕጋዊ ርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17👍2
አማራ ባንክ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ አስመዘገበ
ባንኩ ያስመዘገበው ትርፍ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ከ3 እጥፍ በላይ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ባንኩ ያስመዘገበው ትርፍ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ከ3 እጥፍ በላይ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍8🥰1👌1
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በአምስተኛው የኢኮኖሚ ሪፎርም ግምገማ ማጠናቀቂያ ለኢትዮጵያ የ464 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ የብድር ክፍያ ፈቀደ
ይህም አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፉን 2.647 ቢሊዮን ዶላር አድርሶታል።
ድርጅቱ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የተመዘገቡትን የወጪ ንግድ እና የታክስ ገቢ እድገቶች ያደነቀ ቢሆንም፣ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት የነዳጅ ዋጋ መናር ያሳደረውን ጫና ለመቋቋም 200 ሚሊዮን ዶላር ቀድሞ እንዲለቀቅ ማድረጉን ገልጿል።
በተጨማሪም IMF ሁለተኛ ዙር የዋጋ ንረት ከተከሰተ ብሔራዊ ባንክ ፖሊሲውን ይበልጥ ሊያጠብቅ እንደሚገባ አሳስቧል።
ባንኩ በወርቅ ግብይት ላይ ያለውን ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲያቆም፣ ድጎማዎች ሲነሱ ተጋላጭ ወገኖች እንዲጠበቁ፣ እና አዳዲስ ገለልተኛ የቦርድ አባላትን በመሾም የባንኩን ገለልተኝነት እንዲያጠናክር መክሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ይህም አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፉን 2.647 ቢሊዮን ዶላር አድርሶታል።
ድርጅቱ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የተመዘገቡትን የወጪ ንግድ እና የታክስ ገቢ እድገቶች ያደነቀ ቢሆንም፣ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት የነዳጅ ዋጋ መናር ያሳደረውን ጫና ለመቋቋም 200 ሚሊዮን ዶላር ቀድሞ እንዲለቀቅ ማድረጉን ገልጿል።
በተጨማሪም IMF ሁለተኛ ዙር የዋጋ ንረት ከተከሰተ ብሔራዊ ባንክ ፖሊሲውን ይበልጥ ሊያጠብቅ እንደሚገባ አሳስቧል።
ባንኩ በወርቅ ግብይት ላይ ያለውን ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲያቆም፣ ድጎማዎች ሲነሱ ተጋላጭ ወገኖች እንዲጠበቁ፣ እና አዳዲስ ገለልተኛ የቦርድ አባላትን በመሾም የባንኩን ገለልተኝነት እንዲያጠናክር መክሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢11❤5🤪4👍2
🚨 እስራኤል የኢራንን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የፓርላማ አፈ-ጉባኤውን ለመግደል አቅዳ ነበር" — ኒው ዮርክ ታይምስ
አሜሪካ ከኢራን ጋር እጅግ ስሱ የሆኑ ዲፕሎማሲያዊ ንግግሮችን በምታደርግበት ወቅት፣ እስራኤል የኢራኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺን እና የፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባቄር ቃሊባፍን ለመግደል አቅዳ እንደነበር የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ኒው ዮርክ ታይምስ ዘግቧል።
እንዲህ ዓይነቱ የደህንነት እርምጃ የተጀመረውን የዲፕሎማሲ ሂደት ሙሉ በሙሉ ያከሽፈዋል በሚል የሰጉት የአሜሪካ ባለስልጣናት፣ ለሁለቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጥቃት ሊሰነዘርባቸው እንደሚችል ለኢራን ሚስጥራዊ ማስጠንቀቂያ እንዲያስተላልፉ በርካታ የቀጠናውን ሀገራት ጠይቀው ነበር። በተጨማሪም ዋሽንግተን ድርድሩ በሚካሄድበት ወቅት እንዲህ ዓይነቱን ጥቃት እንዳትፈጽም እስራኤልን አጥብቃ አሳስባለች።
እስራኤል አራግቺን እና ቃሊባፍን በግድያ ኢላማ ስም ዝርዝሯ ውስጥ አስገብታቸው የነበረ ቢሆንም፣ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ውይይት ሲጀመር ግን ለጊዜው ከዝርዝሩ አንስታቸው ነበር። የአሜሪካ ባለስልጣናት እንዳሉት፣ ሁለቱ ግለሰቦች በንቁ ጦርነት ወቅት እንደ ህጋዊ ወታደራዊ ኢላማ ሊቆጠሩ የሚችሉ ቢሆንም፣ የሰላም ንግግሩ ባለፈው ሚያዝያ ከተጀመረ በኋላ ግን እነሱን መግደል ውይይቱን ሙሉ በሙሉ የሚያስቆምና ጦርነቱን በድጋሚ የሚቀሰቅስ ይሆን ነበር።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አሜሪካ ከኢራን ጋር እጅግ ስሱ የሆኑ ዲፕሎማሲያዊ ንግግሮችን በምታደርግበት ወቅት፣ እስራኤል የኢራኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺን እና የፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባቄር ቃሊባፍን ለመግደል አቅዳ እንደነበር የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ኒው ዮርክ ታይምስ ዘግቧል።
እንዲህ ዓይነቱ የደህንነት እርምጃ የተጀመረውን የዲፕሎማሲ ሂደት ሙሉ በሙሉ ያከሽፈዋል በሚል የሰጉት የአሜሪካ ባለስልጣናት፣ ለሁለቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጥቃት ሊሰነዘርባቸው እንደሚችል ለኢራን ሚስጥራዊ ማስጠንቀቂያ እንዲያስተላልፉ በርካታ የቀጠናውን ሀገራት ጠይቀው ነበር። በተጨማሪም ዋሽንግተን ድርድሩ በሚካሄድበት ወቅት እንዲህ ዓይነቱን ጥቃት እንዳትፈጽም እስራኤልን አጥብቃ አሳስባለች።
እስራኤል አራግቺን እና ቃሊባፍን በግድያ ኢላማ ስም ዝርዝሯ ውስጥ አስገብታቸው የነበረ ቢሆንም፣ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ውይይት ሲጀመር ግን ለጊዜው ከዝርዝሩ አንስታቸው ነበር። የአሜሪካ ባለስልጣናት እንዳሉት፣ ሁለቱ ግለሰቦች በንቁ ጦርነት ወቅት እንደ ህጋዊ ወታደራዊ ኢላማ ሊቆጠሩ የሚችሉ ቢሆንም፣ የሰላም ንግግሩ ባለፈው ሚያዝያ ከተጀመረ በኋላ ግን እነሱን መግደል ውይይቱን ሙሉ በሙሉ የሚያስቆምና ጦርነቱን በድጋሚ የሚቀሰቅስ ይሆን ነበር።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15🥱3👍2🥰2🤣1
📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
👍2
ኦሮሚያ ክልል የመዋቅር ለውጥ ሊያደርግ ነው‼
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዚህ ቀደም በቢሮ ደረጃ የነበሩ መዋቅሮችን በኮሚሽን፣ በኢንስቲትዩት፣ በባለሥልጣን፣ በአገልግሎት ዘርፍ እንዲሁም 5 ተቋማትን በልዩ ሁኔታ ለማደራጀት ረቂቅ ሰነድ ማዘጋጀቱ ተነግሯል።
በዚህም መሠረት:-
📌 የፐብሊክ ሰርቪስና ማረሚያ ቤቶች በኮሚሽን ደረጃ፤ የቁጥጥር፣ የኮንስትራክሽንና የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በባለሥልጣን ደረጃ እንዲዋቀሩ ተወስኗል።
📌 የመንግሥት ኮሙኒኬሽንና የሰነዶች ምዝገባን ጨምሮ 4 መሥሪያ ቤቶች በአገልግሎት ደረጃ፣ እንዲሁም የእርሻና የኦሮሞ ባህል ጥናትና ምርምርን ጨምሮ 4 መሥሪያ ቤቶች በኢንስቲትዩት ደረጃ ተደራጅተዋል።
📌የክልሉ ዩኒቨርሲቲዎች አስተዳደር፣ ኦቢኤን፣ ቡሳ ጎኖፋ፣ ፖሊስና ሉዓላዊ ፈንድ ደግሞ በልዩ ሁኔታ የተዋቀሩ ተቋማት ሆነዋል።
📌በትምህርት፣ ጤና፣ ግብርና እና ገቢዎች ቢሮዎች የሚመሩ 21 ዋና ዋና ቢሮዎች ባሉበት የሚቀጥሉ ሲሆን፣ ሌሎች በርካታ መሥሪያ ቤቶችና ኤጀንሲዎች ግን በእነዚህ ዋና ቢሮዎች ሥር ተጠቃለው እንዲተዳደሩ በረቂቁ ተመልክቷል ሰል ዋዜማ ዘግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዚህ ቀደም በቢሮ ደረጃ የነበሩ መዋቅሮችን በኮሚሽን፣ በኢንስቲትዩት፣ በባለሥልጣን፣ በአገልግሎት ዘርፍ እንዲሁም 5 ተቋማትን በልዩ ሁኔታ ለማደራጀት ረቂቅ ሰነድ ማዘጋጀቱ ተነግሯል።
በዚህም መሠረት:-
📌 የፐብሊክ ሰርቪስና ማረሚያ ቤቶች በኮሚሽን ደረጃ፤ የቁጥጥር፣ የኮንስትራክሽንና የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በባለሥልጣን ደረጃ እንዲዋቀሩ ተወስኗል።
📌 የመንግሥት ኮሙኒኬሽንና የሰነዶች ምዝገባን ጨምሮ 4 መሥሪያ ቤቶች በአገልግሎት ደረጃ፣ እንዲሁም የእርሻና የኦሮሞ ባህል ጥናትና ምርምርን ጨምሮ 4 መሥሪያ ቤቶች በኢንስቲትዩት ደረጃ ተደራጅተዋል።
📌የክልሉ ዩኒቨርሲቲዎች አስተዳደር፣ ኦቢኤን፣ ቡሳ ጎኖፋ፣ ፖሊስና ሉዓላዊ ፈንድ ደግሞ በልዩ ሁኔታ የተዋቀሩ ተቋማት ሆነዋል።
📌በትምህርት፣ ጤና፣ ግብርና እና ገቢዎች ቢሮዎች የሚመሩ 21 ዋና ዋና ቢሮዎች ባሉበት የሚቀጥሉ ሲሆን፣ ሌሎች በርካታ መሥሪያ ቤቶችና ኤጀንሲዎች ግን በእነዚህ ዋና ቢሮዎች ሥር ተጠቃለው እንዲተዳደሩ በረቂቁ ተመልክቷል ሰል ዋዜማ ዘግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11🤣7👍5🤪1
አዲስ የቡና ጥናት‼️
ቡናን በየቀኑ አብዝቶ መጠጣት ለጉበት ጤንነት ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው ተረጋገጠ።
አዩዘሀበሻ የጥናቱን ውጤት እንደሚከተለው አጠናቅሮታል።
በሎስ አንጀለስ በሚገኘው የሲናይ የሕክምና ማዕከል ከቡና ጋር በተያያዘ በተሰራው አዲስ ጥናት ቡናን አብዝቶ መጠቀም ጭምር ለጉበት ጤንነት ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው ተረጋገጠ።
ቡና የሚሰጠው ጥቅም በውስጡ ከያዘው ካፌይን ሳይሆን በያዘው ከፍተኛ አንቲ-ኦክሲዳንት ነው።
ቡና ከፍተኛ ፀረ-ኦክሳይድ(Antioxidant) ስላለው ተመራማሪዎቹ ቡናን በየቀኑ መጠቀም ዘላቂ የጉበት ጠባሳ፣ ለረጅም ጊዜ የጉበት በሽታዎች ሊከሰት ከሚችለው ጉዳት፣የሰባ የጉበት በሽታ፣ የቫይረስ ሄፓታይተስ፣ ከአልኮል ጋር የተያያዘ የጉበት በሽታ እና ሌሎችንም ጨምሮ ቡና የመከላከል አቅም እንዳለው ጥናቱ አሳይቷል።
ሲርሆሲስ የተባለው የጉበት በሽታ በዓለም ዙሪያ ከ58 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን የሚያጠቃ የጉበት በሽታ ሲሆን በየዓመቱ በዓለም ዙሪያ ወደ 1.5 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ይገድላል። ሰዎች ቡናን በቀን አምስት ወይም ከዚያ በላይ ኩባያዎች ቢጠጡም እንኳ ዕለታዊ የቡና ኩባያዎ የጉበት በሽታ ወይም የጉበት ካንሰር የመያዝ እድልዎን ሊቀንስ እንደሚችል አዲሱ ጥናት አረጋግጧል።
እነዚህ ተመራማሪዎች 354,000 ናሙናዎችን/ሰዎችን) በመጠቀም ጥናቱን ከአስር አመታት በላይ ተከታትለውታል።
በዚህም የጥናቱ ውጤት ከትናንት በስቲያ ረቡዕ ሰኔ 24/2018 ዓ.ም በክሊኒካል ጋስትሮኢንተሮሎጂ እና ሄፓቶሎጂ መጽሔት ላይ የታተመ ሲሆን ይህ ጥናት ምናልባት የቡናን ተጽእኖ በተመለከተ "ለረጅም ጊዜ ክትትል የተደረገበት ጥሩ ጥናት ነው” ሲሉ በሎስ አንጀለስ በሚገኘው የሲዳርስ-ሲናይ የሕክምና ማዕከል የሄፓቶሎጂ ንቅለ ተከላ ባለሙያ የሆኑት የመጀመሪያ የጥናቱ ደራሲ ዶ/ር ህዩንሶክ ኪም ተናግረዋል።
በጥናቱ መሠረት ሄፓቶሴሉላር ካርሲኖማ የተባለው በጣም የተለመደው የጉበት ካንሰር ሲሆን በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ 685,000 የሚጠጉ ሰዎችን የሚያጠቃ ሲሆን ከ597,000 በላይ ሰዎችን በየአመቱ ለሞት ይዳርጋል። ተመራማሪዎቹ ቡናን አብዝቶ መጠጣት የጉበትን ጤንነት ይበልጥ ይጨምራል ብለዋል።
👉በቀን ከአንድ እስከ ሁለት ኩባያ የሚጠጡ ሰዎች:-
📌ለሲርሆሲስ የመጋለጥ እድላቸው በ 20% ይቀንሳል፣
📌ለጉበት ካንሰር የመጋለጥ እድላቸው በ 24% ይቀንሳል።
📌 በጉበት ምክንያት የመሞት እድልን በ31% ይቀንሳል።
👉በቀን ከሶስት እስከ አራት ኩባያዎች የሚጠጡ ሰዎች ደግሞ በሲርሆሲስ እና የጉበት ካንሰር ተጋላጭነትን በ35% ይቀንሳል፣ ከጉበት ጋር በተያያዘ የመሞት እድልን በ41% ይቀንሳል።
👉አምስት ኩባያዎች ወይም ከዚያ በላይ የሚጠጡ ሰዎች በሲርሆሲስ የመያዝ እድላቸው በ 32% ይቀንሳል፣ በጉበት ካንሰር የመያዝ አደጋን በ47% ይቀንሳል እና ከጉበት ጋር የተያያዘ ሞትን በ 42% እንደሚቀንስ ጥናቱ አረጋግጧል። ነገር ግን ቡናው በሚጠጣበት ጊዜ የስኳር መጠን እና የሚጨመሩ ሌሎች ማጣፈጫዎች ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ጥናቱ መክሯል። ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ቡናን በየቀኑ አብዝቶ መጠጣት ለጉበት ጤንነት ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው ተረጋገጠ።
አዩዘሀበሻ የጥናቱን ውጤት እንደሚከተለው አጠናቅሮታል።
በሎስ አንጀለስ በሚገኘው የሲናይ የሕክምና ማዕከል ከቡና ጋር በተያያዘ በተሰራው አዲስ ጥናት ቡናን አብዝቶ መጠቀም ጭምር ለጉበት ጤንነት ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው ተረጋገጠ።
ቡና የሚሰጠው ጥቅም በውስጡ ከያዘው ካፌይን ሳይሆን በያዘው ከፍተኛ አንቲ-ኦክሲዳንት ነው።
ቡና ከፍተኛ ፀረ-ኦክሳይድ(Antioxidant) ስላለው ተመራማሪዎቹ ቡናን በየቀኑ መጠቀም ዘላቂ የጉበት ጠባሳ፣ ለረጅም ጊዜ የጉበት በሽታዎች ሊከሰት ከሚችለው ጉዳት፣የሰባ የጉበት በሽታ፣ የቫይረስ ሄፓታይተስ፣ ከአልኮል ጋር የተያያዘ የጉበት በሽታ እና ሌሎችንም ጨምሮ ቡና የመከላከል አቅም እንዳለው ጥናቱ አሳይቷል።
ሲርሆሲስ የተባለው የጉበት በሽታ በዓለም ዙሪያ ከ58 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን የሚያጠቃ የጉበት በሽታ ሲሆን በየዓመቱ በዓለም ዙሪያ ወደ 1.5 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ይገድላል። ሰዎች ቡናን በቀን አምስት ወይም ከዚያ በላይ ኩባያዎች ቢጠጡም እንኳ ዕለታዊ የቡና ኩባያዎ የጉበት በሽታ ወይም የጉበት ካንሰር የመያዝ እድልዎን ሊቀንስ እንደሚችል አዲሱ ጥናት አረጋግጧል።
እነዚህ ተመራማሪዎች 354,000 ናሙናዎችን/ሰዎችን) በመጠቀም ጥናቱን ከአስር አመታት በላይ ተከታትለውታል።
በዚህም የጥናቱ ውጤት ከትናንት በስቲያ ረቡዕ ሰኔ 24/2018 ዓ.ም በክሊኒካል ጋስትሮኢንተሮሎጂ እና ሄፓቶሎጂ መጽሔት ላይ የታተመ ሲሆን ይህ ጥናት ምናልባት የቡናን ተጽእኖ በተመለከተ "ለረጅም ጊዜ ክትትል የተደረገበት ጥሩ ጥናት ነው” ሲሉ በሎስ አንጀለስ በሚገኘው የሲዳርስ-ሲናይ የሕክምና ማዕከል የሄፓቶሎጂ ንቅለ ተከላ ባለሙያ የሆኑት የመጀመሪያ የጥናቱ ደራሲ ዶ/ር ህዩንሶክ ኪም ተናግረዋል።
በጥናቱ መሠረት ሄፓቶሴሉላር ካርሲኖማ የተባለው በጣም የተለመደው የጉበት ካንሰር ሲሆን በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ 685,000 የሚጠጉ ሰዎችን የሚያጠቃ ሲሆን ከ597,000 በላይ ሰዎችን በየአመቱ ለሞት ይዳርጋል። ተመራማሪዎቹ ቡናን አብዝቶ መጠጣት የጉበትን ጤንነት ይበልጥ ይጨምራል ብለዋል።
👉በቀን ከአንድ እስከ ሁለት ኩባያ የሚጠጡ ሰዎች:-
📌ለሲርሆሲስ የመጋለጥ እድላቸው በ 20% ይቀንሳል፣
📌ለጉበት ካንሰር የመጋለጥ እድላቸው በ 24% ይቀንሳል።
📌 በጉበት ምክንያት የመሞት እድልን በ31% ይቀንሳል።
👉በቀን ከሶስት እስከ አራት ኩባያዎች የሚጠጡ ሰዎች ደግሞ በሲርሆሲስ እና የጉበት ካንሰር ተጋላጭነትን በ35% ይቀንሳል፣ ከጉበት ጋር በተያያዘ የመሞት እድልን በ41% ይቀንሳል።
👉አምስት ኩባያዎች ወይም ከዚያ በላይ የሚጠጡ ሰዎች በሲርሆሲስ የመያዝ እድላቸው በ 32% ይቀንሳል፣ በጉበት ካንሰር የመያዝ አደጋን በ47% ይቀንሳል እና ከጉበት ጋር የተያያዘ ሞትን በ 42% እንደሚቀንስ ጥናቱ አረጋግጧል። ነገር ግን ቡናው በሚጠጣበት ጊዜ የስኳር መጠን እና የሚጨመሩ ሌሎች ማጣፈጫዎች ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ጥናቱ መክሯል። ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20👍3🤣3