📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
❤2👍2
የጀነራል ጻድቃን ጥብቅ ወታደራዊ መረጃ!
ህወሓት ወደ መኸል ሀገር ሰብሮ ለመግባት ከውጭ ወደ ውስጥ በሱዳን በኩል በተለያዩ ግንባሮች ጥቃት ለመክፈት ሰፊ ወታደራዊ ስትራቴጂ መንደፉን ጀነራል ጻድቃን ገ/ተንሳኤ አጋልጠዋል፡፡
በወልቃይት ሲጠበቅ የነበረው የህወሓት ጥቃት፣ ባልተጠበቀበት ግንባር ሊፈነዳ እንደሚችል ጀነራሉ ተናግረዋል፡፡ ጀነራሉ በህወሓት ወታደራዊ ዝግጅት ላይ በሰጡት ማብራሪያ በአፋር እና አማራ አዋሳኝ አካባቢዎች ተደጋጋሚ ትንኮሳዎች የፈጸመው ህወሓት የትኩረት አቅጣጫውን ቀይሯል ብለዋል፡፡
በምራብ ኢትዮጵያ በኩል ጥቃት ከፍቶ ወደ ማኸል ሀገር ለመገስገስ አስቦ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ጀነራሉ ጠቁመዋል፡፡ ጀነራሉ በምራዕብ ኢትዮጵያ በኩል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በኩል ማለታቸው ነው፡፡
የህወሓት ጀነራሎች በአሁኑ ወቅት ሰፊ ወታደራዊ ስትራቴጂ ነድፈው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የገለጹት ጀነራሉ፣ በተለይ ከውጭ ወደ ውስጥ ለማጥቃት ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ ለዚህም ሱዳንን እንደ ዋና ወታደራዊ መንቀሳቀሻ እየተጠቀሙ መሆኑን ተጨባጫ መረጃዎችና እንቅስቃሴዎች መነራቸው ተናግረዋል፡፡
ሱዳን ውስጥ ለዓመታት የተደራጀው አርሚ 70 እንደ ቀጠናዊ ሚዛን ማስጠበቂያ ለመጠቀም እና ከውጭ ወደ ውስጥ ለማጥቃት ተጨማሪ ኃይል እያስገቡ ነው ብለዋል፡፡ በቅርቡ አርሚ 13 ወደ ሱዳን መሻገሩን ያረጋገጡት ጀነራሉ፣ ሌሎች ተጨማሪ አርሚዎችም ሊጨመሩ እንደሚችሉ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡
አርሚ 13 ወደ ሱዳን ለመሻገር ሲንቀሳቀስ መንገድ ላይ ሁለት ጊዜ በድሮን ጥቃት ቢመታም፣ የተረፈው አርሚ 70ን ተቀላቅሏል ብለዋል፡፡ ሽራሮ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት በህወሓት ማረጋጫ የተሰጠበት ቢሆንም፣ ሱዳን ከገባ በኋላ ሸረሪና ላይ ተጨማሪ ደብደባ መፈጸሙን ጀነራሉ ገልጸዋል፡፡
Andafta
@Addis_Reporter
ህወሓት ወደ መኸል ሀገር ሰብሮ ለመግባት ከውጭ ወደ ውስጥ በሱዳን በኩል በተለያዩ ግንባሮች ጥቃት ለመክፈት ሰፊ ወታደራዊ ስትራቴጂ መንደፉን ጀነራል ጻድቃን ገ/ተንሳኤ አጋልጠዋል፡፡
በወልቃይት ሲጠበቅ የነበረው የህወሓት ጥቃት፣ ባልተጠበቀበት ግንባር ሊፈነዳ እንደሚችል ጀነራሉ ተናግረዋል፡፡ ጀነራሉ በህወሓት ወታደራዊ ዝግጅት ላይ በሰጡት ማብራሪያ በአፋር እና አማራ አዋሳኝ አካባቢዎች ተደጋጋሚ ትንኮሳዎች የፈጸመው ህወሓት የትኩረት አቅጣጫውን ቀይሯል ብለዋል፡፡
በምራብ ኢትዮጵያ በኩል ጥቃት ከፍቶ ወደ ማኸል ሀገር ለመገስገስ አስቦ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ጀነራሉ ጠቁመዋል፡፡ ጀነራሉ በምራዕብ ኢትዮጵያ በኩል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በኩል ማለታቸው ነው፡፡
የህወሓት ጀነራሎች በአሁኑ ወቅት ሰፊ ወታደራዊ ስትራቴጂ ነድፈው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የገለጹት ጀነራሉ፣ በተለይ ከውጭ ወደ ውስጥ ለማጥቃት ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ ለዚህም ሱዳንን እንደ ዋና ወታደራዊ መንቀሳቀሻ እየተጠቀሙ መሆኑን ተጨባጫ መረጃዎችና እንቅስቃሴዎች መነራቸው ተናግረዋል፡፡
ሱዳን ውስጥ ለዓመታት የተደራጀው አርሚ 70 እንደ ቀጠናዊ ሚዛን ማስጠበቂያ ለመጠቀም እና ከውጭ ወደ ውስጥ ለማጥቃት ተጨማሪ ኃይል እያስገቡ ነው ብለዋል፡፡ በቅርቡ አርሚ 13 ወደ ሱዳን መሻገሩን ያረጋገጡት ጀነራሉ፣ ሌሎች ተጨማሪ አርሚዎችም ሊጨመሩ እንደሚችሉ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡
አርሚ 13 ወደ ሱዳን ለመሻገር ሲንቀሳቀስ መንገድ ላይ ሁለት ጊዜ በድሮን ጥቃት ቢመታም፣ የተረፈው አርሚ 70ን ተቀላቅሏል ብለዋል፡፡ ሽራሮ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት በህወሓት ማረጋጫ የተሰጠበት ቢሆንም፣ ሱዳን ከገባ በኋላ ሸረሪና ላይ ተጨማሪ ደብደባ መፈጸሙን ጀነራሉ ገልጸዋል፡፡
Andafta
@Addis_Reporter
👍4❤3🤣3🤔2😢1🤪1
በቬንዙዌላ በተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ የነፍስ አድን ስራው መዘግየት በነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ቁጣን ቀሰቀሰ
በቬንዙዌላ የተከሰተውን አስከፊ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ የመንግስት ምላሽ መዘግየትና ቸልተኝነት ህዝቡን ለከፍተኛ ቁጣና ቅሬታ ዳርጓል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
እስካሁን በደረሰው አደጋ ቢያንስ 1ሺህ7መቶ ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን ባለስልጣናት የገለጹ ሲሆን፤ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ ክስተቱን በሀገሪቱ ታሪክ ‹‹እጅግ አስከፊው የተፈጥሮ አደጋ››ሲሉ ጠርተውታል።
ሆኖም በፈራረሱ የሪል ስቴት እና የመኖሪያ ህንፃዎች ፍርስራሽ ስር የተረፉ ሰዎችን ለመታደግ የሚደረገው ጥረት እጅግ አዝጋሚ መሆን ነዋሪዎችን እያስቆጣ ይገኛል።
የመንግስት እርዳታ እና የማዳኛ ማሽነሪዎች በፍጥነት አለመድረሳቸውን ተከትሎ በቤሎ ሆሪዞንቴ እና መሰል መንደሮች የሚገኙ ነዋሪዎች የራሳቸውን ደህንነት ለአደጋ አጋልጠው በባዶ እጃቸውና በዶማ ፍርስራሹን እየቆፈሩ ሰዎችን ለማዳን ተገድደዋል።
ምንም እንኳን ከኮሎምቢያ፣ ኤል ሳልቫዶር እና አሜሪካ የመጡ የነፍስ አድን ቡድኖች ድጋፍ እያደረጉ ቢሆንም በአንዳንድ አካባቢዎች የፍለጋ ስራው በይፋ መቋረጡ ተገልጿል።
በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም በፍርስራሹ ስር ተቀብረው በመቅረታቸው የአደጋው እውነተኛ የጉዳት መጠን ምን ያህል እንደሆነ ለማወቅ አስቸጋሪ ሆኗል ሲል ቢቢሲ በዘገባው አክሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በቬንዙዌላ የተከሰተውን አስከፊ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ የመንግስት ምላሽ መዘግየትና ቸልተኝነት ህዝቡን ለከፍተኛ ቁጣና ቅሬታ ዳርጓል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
እስካሁን በደረሰው አደጋ ቢያንስ 1ሺህ7መቶ ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን ባለስልጣናት የገለጹ ሲሆን፤ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ ክስተቱን በሀገሪቱ ታሪክ ‹‹እጅግ አስከፊው የተፈጥሮ አደጋ››ሲሉ ጠርተውታል።
ሆኖም በፈራረሱ የሪል ስቴት እና የመኖሪያ ህንፃዎች ፍርስራሽ ስር የተረፉ ሰዎችን ለመታደግ የሚደረገው ጥረት እጅግ አዝጋሚ መሆን ነዋሪዎችን እያስቆጣ ይገኛል።
የመንግስት እርዳታ እና የማዳኛ ማሽነሪዎች በፍጥነት አለመድረሳቸውን ተከትሎ በቤሎ ሆሪዞንቴ እና መሰል መንደሮች የሚገኙ ነዋሪዎች የራሳቸውን ደህንነት ለአደጋ አጋልጠው በባዶ እጃቸውና በዶማ ፍርስራሹን እየቆፈሩ ሰዎችን ለማዳን ተገድደዋል።
ምንም እንኳን ከኮሎምቢያ፣ ኤል ሳልቫዶር እና አሜሪካ የመጡ የነፍስ አድን ቡድኖች ድጋፍ እያደረጉ ቢሆንም በአንዳንድ አካባቢዎች የፍለጋ ስራው በይፋ መቋረጡ ተገልጿል።
በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም በፍርስራሹ ስር ተቀብረው በመቅረታቸው የአደጋው እውነተኛ የጉዳት መጠን ምን ያህል እንደሆነ ለማወቅ አስቸጋሪ ሆኗል ሲል ቢቢሲ በዘገባው አክሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9😢3👍2💔1
#NationalExam
በትግራይ ክልል 29,755 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የብሔራዊ ፈተና መውሰድ ጀምረዋል።
በ247 ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ለቀጣዮቹ 14 ቀናት የብሔራዊ ፈተና ይወስዳሉ።
ፈተናው በክልሉ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በ8 የፈተና ማዕከላት ነው እየተሰጠ ያለው።
የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ እንደገለጸው፣ ፈተናው ከፌደራል እና ከክልሉ ከተወጣጡ የጥበቃና የፈተና ባለሙያዎች ጋር ትብብር መጀመሩን ገልጿል።
ቢሮው ፈተናው በተሳካ ሁኔታ እንዲጀመር አስተዋጽኦ ላደረጉ ፦
- ደመወዝ ሳይከፈላቸው ላስተማሩ መምህራን፣
- ለአገር አቀፍ ትምህር ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፣
- ለዩኒቨርሲቲዎች፣
- ለትምህርት ባለሙያዎች፣
- ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣
- ለኢትዮ ቴሌኮም፣
- ለፌደራልና ለትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን፣ እንዲሁም ከተለያዩ ክልሎች ለመጡ ሱፐርቫይዘሮች ምስጋና አቅርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በትግራይ ክልል 29,755 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የብሔራዊ ፈተና መውሰድ ጀምረዋል።
በ247 ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ለቀጣዮቹ 14 ቀናት የብሔራዊ ፈተና ይወስዳሉ።
ፈተናው በክልሉ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በ8 የፈተና ማዕከላት ነው እየተሰጠ ያለው።
የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ እንደገለጸው፣ ፈተናው ከፌደራል እና ከክልሉ ከተወጣጡ የጥበቃና የፈተና ባለሙያዎች ጋር ትብብር መጀመሩን ገልጿል።
ቢሮው ፈተናው በተሳካ ሁኔታ እንዲጀመር አስተዋጽኦ ላደረጉ ፦
- ደመወዝ ሳይከፈላቸው ላስተማሩ መምህራን፣
- ለአገር አቀፍ ትምህር ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፣
- ለዩኒቨርሲቲዎች፣
- ለትምህርት ባለሙያዎች፣
- ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣
- ለኢትዮ ቴሌኮም፣
- ለፌደራልና ለትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን፣ እንዲሁም ከተለያዩ ክልሎች ለመጡ ሱፐርቫይዘሮች ምስጋና አቅርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍7❤6🥰2🍾1
በጋምቤላ ክልል ህፃናትን መጠጥ ቤት እንዲገቡ ማድረግ 5 ሺህ ብር ያስቀጣል ተባለ
ለአቅመ አዳም ያልደረሱና ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ወደ መጠጥ ቤቶች እንዳይገቡ ለመጠጥ ቤት ባለቤቶች ጥብቅ መመሪያ መስጠቱን በጋምቤላ ክልል አኙዋ ብሔረሰብ ዞን የአቦቦ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት አስታውቋል። የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ አዊሊ ኡጁሉ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት መመሪያውን ተላልፈው በሚገኙ የመጠጥ ቤት ባለቤቶች ላይ የ5 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተላልፋል ።
በተጨማሪም ወላጆች ህፃናትን ጫትና የአልኮል መጠጦችን ለመግዛት ወደ ተለያዩ የንግድ ቦታዎች እንዳይልኩ ጥብቅ መመሪያ መተላለፉን ኃላፊዋ ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል። ህፃናት ለጤናቸው ሲባል የትኛውንም አይነት የአልኮል መጠጥ ሙሉ ለሙሉ ማስወገድ እንዳለባቸው ተነግሯል ።
አልኮል የሚጠጣ ሰው ጤና አደጋ ላይ የሚወድቀው ከእያንዳንዱ መጠጥ የመጀመሪያ ጠብታ ጀምሮ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ ።የአልኮል መጠጥ የጉበት ካንሰርን ጨምሮ ጉበት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ፣የልብና የደም ሥር ችግሮች ፣የደም ግፊት ፣የልብ ህመም እንዲሁም የካንሰር ተጋላጭነትን እንደሚጨምር ጥናቶች ይጠቁማሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ለአቅመ አዳም ያልደረሱና ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ወደ መጠጥ ቤቶች እንዳይገቡ ለመጠጥ ቤት ባለቤቶች ጥብቅ መመሪያ መስጠቱን በጋምቤላ ክልል አኙዋ ብሔረሰብ ዞን የአቦቦ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት አስታውቋል። የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ አዊሊ ኡጁሉ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት መመሪያውን ተላልፈው በሚገኙ የመጠጥ ቤት ባለቤቶች ላይ የ5 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተላልፋል ።
በተጨማሪም ወላጆች ህፃናትን ጫትና የአልኮል መጠጦችን ለመግዛት ወደ ተለያዩ የንግድ ቦታዎች እንዳይልኩ ጥብቅ መመሪያ መተላለፉን ኃላፊዋ ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል። ህፃናት ለጤናቸው ሲባል የትኛውንም አይነት የአልኮል መጠጥ ሙሉ ለሙሉ ማስወገድ እንዳለባቸው ተነግሯል ።
አልኮል የሚጠጣ ሰው ጤና አደጋ ላይ የሚወድቀው ከእያንዳንዱ መጠጥ የመጀመሪያ ጠብታ ጀምሮ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ ።የአልኮል መጠጥ የጉበት ካንሰርን ጨምሮ ጉበት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ፣የልብና የደም ሥር ችግሮች ፣የደም ግፊት ፣የልብ ህመም እንዲሁም የካንሰር ተጋላጭነትን እንደሚጨምር ጥናቶች ይጠቁማሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍5🥱1
ኢትዮጵያ በጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የባህር ትራንስፖርት መስመሮች ጀመረች
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በበጀት ዓመቱ ወደ ጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የጉዞ መስመሮችን በመክፈት የንግድ ትስስሩን እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል።
የተቋሙ የኮርፖሬት ማርኬቲንግ መምሪያ ኃላፊና የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ተወካይ አቶ ደምሰው በንቲ፣ በኢንዶኔዥያና በጃፓን መስመሮች ላይ ከባድ ማሽነሪዎችን፣ ተሽከርካሪዎችንና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎችን የማጓጓዝ ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ለጋዜጣ ፕላስ ገልጸዋል።
ኃላፊው አክለውም፣ ወደፊትም የደንበኞችንና የሀገሪቱን ጥቅም ማዕከል ያደረጉ አዳዲስ መዳረሻዎችን የማስፋፋት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
እነዚህ አዳዲስ የባህር መስመር ጉዞዎች መጀመራቸው የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ያሻሽላል ያሉት አቶ ደምሰው፣ የወደብ ጭነቶች በአጭር ጊዜ ወደተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ በማስቻል ጊዜንና ወጪን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቆጥብ አስገንዝበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በበጀት ዓመቱ ወደ ጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የጉዞ መስመሮችን በመክፈት የንግድ ትስስሩን እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል።
የተቋሙ የኮርፖሬት ማርኬቲንግ መምሪያ ኃላፊና የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ተወካይ አቶ ደምሰው በንቲ፣ በኢንዶኔዥያና በጃፓን መስመሮች ላይ ከባድ ማሽነሪዎችን፣ ተሽከርካሪዎችንና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎችን የማጓጓዝ ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ለጋዜጣ ፕላስ ገልጸዋል።
ኃላፊው አክለውም፣ ወደፊትም የደንበኞችንና የሀገሪቱን ጥቅም ማዕከል ያደረጉ አዳዲስ መዳረሻዎችን የማስፋፋት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
እነዚህ አዳዲስ የባህር መስመር ጉዞዎች መጀመራቸው የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ያሻሽላል ያሉት አቶ ደምሰው፣ የወደብ ጭነቶች በአጭር ጊዜ ወደተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ በማስቻል ጊዜንና ወጪን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቆጥብ አስገንዝበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12👍2🤣2😎1
በ #ሱዳን በተፈጸሙ አስከፊ ወንጀሎች ውስጥ እጃቸው አለበት የተባሉ ከፍተኛ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣የ #ኢትዮጵያ እና የቀጠናው ባለሥልጣናት ላይ በዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ምርመራ እንዲደረግ ተጠየቀ‼️
ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች እና የሕግ ድርጅቶች ጥምረት፤ በሱዳን ዳርፉር ክልል በተቀሰቀሰው ግጭት ለተፈጸሙ አስከፊ ወንጀሎች ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ረገድ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ፣ የኢትዮጵያን ጨምሮ የቻድ፣የሶማሊያ፣ የሊቢያ እና የኬኒያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ላይ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ምርመራ እንዲያደርግ ጠየቀ።
ሚድል ኢስት አይ ባወጣው ዘገባ መሠረት፤ ይህ ጥሪ ሰኞ ዕለት የቀረበው፤ ራውል ዋለንበርግ የሰብአዊ መብቶች ማዕከል (RWCHR) ከተለያዩ የሕግ፣ የምርመራ እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጥምረት ጋር በመሆን የቀረበ ነው። አቤቱታው የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ዓቃቢያነ ሕግ የውጭ አገር ባለሥልጣናትና አሸማጋዮች በሱዳን ተፋላሚ ወገኖች የተፈጸሙ ወንጀሎችን ሆን ብለው በማገዝ ወይም በማበረታታት ረገድ የተሳተፉ መሆኑን እንዲመረምሩ ይጠይቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች እና የሕግ ድርጅቶች ጥምረት፤ በሱዳን ዳርፉር ክልል በተቀሰቀሰው ግጭት ለተፈጸሙ አስከፊ ወንጀሎች ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ረገድ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ፣ የኢትዮጵያን ጨምሮ የቻድ፣የሶማሊያ፣ የሊቢያ እና የኬኒያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ላይ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ምርመራ እንዲያደርግ ጠየቀ።
ሚድል ኢስት አይ ባወጣው ዘገባ መሠረት፤ ይህ ጥሪ ሰኞ ዕለት የቀረበው፤ ራውል ዋለንበርግ የሰብአዊ መብቶች ማዕከል (RWCHR) ከተለያዩ የሕግ፣ የምርመራ እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጥምረት ጋር በመሆን የቀረበ ነው። አቤቱታው የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ዓቃቢያነ ሕግ የውጭ አገር ባለሥልጣናትና አሸማጋዮች በሱዳን ተፋላሚ ወገኖች የተፈጸሙ ወንጀሎችን ሆን ብለው በማገዝ ወይም በማበረታታት ረገድ የተሳተፉ መሆኑን እንዲመረምሩ ይጠይቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍9❤5🤯2🕊2🤣1🙊1
ለ200 ዜጎች ነጻ የልብ ሕክምና ሊሰጥ ነው
ኸርት አታክ ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከሌሎች የመንግስት እና የግል አጋር አካላት ጋር በመተባበር ከ200 ለሚልቁ ዜጎች በነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑን አስታውቋል።
ሕክምናው ከተለያዩ 6 ሀገራት በተወጣጡ 55 በጎፈቃደኛ ሀኪሞች ከእሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ድረስ እንደሚሰጥም ማህበሩ ገልጿል።
ማህበሩ ከዚህ በፊት 4 ግዜ ነፃ የልብ ህክምና መስጠቱን አስታውሶ 481 ለሚሆኑ ታማሚዎች አገልግሎት መስጠቱን ገልጿል።
ህክምናው በተለያዩ 4 የመንግስት እና የግል ሆስፒታሎች ውስጥ ወረፋ ሲጠባበቁ ለቆዩ አቅም ለሌላቸው ዜጎች እንደሚሰጥ ተገልጿል።
የልብ ህክምና ባለሙያዎችን አቅም ማጠናከር የማህበሩ አንዱ ሥራ ሲሆን፤ 6 ሲፔሻሊስት የልብ ሀኪሞች ወደ ህንድ ተልከው ሰልጥነው እንዲመጡ ለማድረግ መታቀዱ ተሰምቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኸርት አታክ ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከሌሎች የመንግስት እና የግል አጋር አካላት ጋር በመተባበር ከ200 ለሚልቁ ዜጎች በነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑን አስታውቋል።
ሕክምናው ከተለያዩ 6 ሀገራት በተወጣጡ 55 በጎፈቃደኛ ሀኪሞች ከእሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ድረስ እንደሚሰጥም ማህበሩ ገልጿል።
ማህበሩ ከዚህ በፊት 4 ግዜ ነፃ የልብ ህክምና መስጠቱን አስታውሶ 481 ለሚሆኑ ታማሚዎች አገልግሎት መስጠቱን ገልጿል።
ህክምናው በተለያዩ 4 የመንግስት እና የግል ሆስፒታሎች ውስጥ ወረፋ ሲጠባበቁ ለቆዩ አቅም ለሌላቸው ዜጎች እንደሚሰጥ ተገልጿል።
የልብ ህክምና ባለሙያዎችን አቅም ማጠናከር የማህበሩ አንዱ ሥራ ሲሆን፤ 6 ሲፔሻሊስት የልብ ሀኪሞች ወደ ህንድ ተልከው ሰልጥነው እንዲመጡ ለማድረግ መታቀዱ ተሰምቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤31👍4🙏1👌1
#ሀሰተኛ - ይህ ከላይ በምስሉ የሚታየው " ፂም ያለው እና ሽማግሌ የሚመስል ሕጻን በጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ ተወለደ " እየተባለ የሚነገረው ሀሰት ነው።
በርካቶች መረጃውን ሳያረጋግጡ በችኮላና አንዳንዶች ደግሞ ሆን ብለው የሰዎችን እይታ ለማግኘት ሲሉ ብቻ " በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጋሞ ዞን፣ ቦረዳ ወረዳ ጭላሼ ቀበሌ ልዩ ስሙ ወቆ በተባለ ሥፍራ፣ ሙሉ ፂም ያለውና መልኩ ሽማግሌ የሚመስል ሕፃን ተወለደ " ሲሉ ሀሰተኛ መረጃ አሰራጭተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በርካቶች መረጃውን ሳያረጋግጡ በችኮላና አንዳንዶች ደግሞ ሆን ብለው የሰዎችን እይታ ለማግኘት ሲሉ ብቻ " በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጋሞ ዞን፣ ቦረዳ ወረዳ ጭላሼ ቀበሌ ልዩ ስሙ ወቆ በተባለ ሥፍራ፣ ሙሉ ፂም ያለውና መልኩ ሽማግሌ የሚመስል ሕፃን ተወለደ " ሲሉ ሀሰተኛ መረጃ አሰራጭተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣22❤6🤔5👍4👀2🙈2🥰1🤪1
ፀደቀ‼️
የታክስ ቅሬታ አጣሪው ተቀየረ፤ የታክስ ቅጣትም በግማሽ ተቀነሰ‼️
*ሰኔ 23/2018 ዓ/ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ላይ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን አድርጎ በዛሬው ዕለት አጽድቋል። ማሻሻያው በተለይም ለታክስ ከፋይ ተቋማት የፍትህ አድማሱን የሚያሰፋና የቅጣት ጫናን የሚቀንስ ነው።
በአዋጁ የተካተቱት ዋና ዋና ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፦
ከዚህ ቀደም በታክስ ባለሥልጣኑ በራሱ ይሰየም የነበረው የታክስ "አስማሚ" (Mediator)፣ ከአሁን በኋላ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚሰየም ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን ይተካል፡፡ ይህም የታክስ ክርክሮች ፍትሃዊ እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲታዩ ያስችላል።
ታክስ ከፋዮች በታክስ አወሳሰን ወቅት ያልቀረቡ ነገር ግን በኋላ ላይ የዕዳ መጠን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ማስረጃዎችን ሲያቀርቡ ይጠብቃቸው የነበረው 20 በመቶ ቅጣት፣ በግማሽ ተቀንሶ ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
የታክስ ህግን በመተላለፍ ወንጀል የሚፈጽሙ ድርጅቶች ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ድንጋጌ ተካቷል። በዚህም መሰረት ወንጀሉ በተፈጸመበት ወቅት በስልጣን ላይ የነበሩ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጆች ወይም የፋይናንስ ኃላፊዎች ለወንጀሉ በግል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ህጉ በግልጽ አስቀምጧል።
ይህ ማሻሻያ የታክስ አስተዳደርን ይበልጥ ግልጽ፣ ፍትሃዊ እና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የታክስ ቅሬታ አጣሪው ተቀየረ፤ የታክስ ቅጣትም በግማሽ ተቀነሰ‼️
*ሰኔ 23/2018 ዓ/ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ላይ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን አድርጎ በዛሬው ዕለት አጽድቋል። ማሻሻያው በተለይም ለታክስ ከፋይ ተቋማት የፍትህ አድማሱን የሚያሰፋና የቅጣት ጫናን የሚቀንስ ነው።
በአዋጁ የተካተቱት ዋና ዋና ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፦
ከዚህ ቀደም በታክስ ባለሥልጣኑ በራሱ ይሰየም የነበረው የታክስ "አስማሚ" (Mediator)፣ ከአሁን በኋላ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚሰየም ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን ይተካል፡፡ ይህም የታክስ ክርክሮች ፍትሃዊ እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲታዩ ያስችላል።
ታክስ ከፋዮች በታክስ አወሳሰን ወቅት ያልቀረቡ ነገር ግን በኋላ ላይ የዕዳ መጠን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ማስረጃዎችን ሲያቀርቡ ይጠብቃቸው የነበረው 20 በመቶ ቅጣት፣ በግማሽ ተቀንሶ ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
የታክስ ህግን በመተላለፍ ወንጀል የሚፈጽሙ ድርጅቶች ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ድንጋጌ ተካቷል። በዚህም መሰረት ወንጀሉ በተፈጸመበት ወቅት በስልጣን ላይ የነበሩ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጆች ወይም የፋይናንስ ኃላፊዎች ለወንጀሉ በግል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ህጉ በግልጽ አስቀምጧል።
ይህ ማሻሻያ የታክስ አስተዳደርን ይበልጥ ግልጽ፣ ፍትሃዊ እና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19🤪5👍3
ኢትዮጵያ በቀጣናው ከፍተኛ የገቢ ግብር በመጣል 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች
በአፍሪካ ቀንድ እየተካሄደ ያለውን መጠነ-ሰፊ የፋይናንስ እና የግብር ማሻሻያ ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት መካከል በተቀጣሪ ሰራተኞች ደመወዝ ላይ ከፍተኛ ግብር በመጣል ሶስተኛዋ ሀገር መሆንዋ ታውቋል።
የቀጣናውን የቅጥር ገቢ ግብር (PAYE) ተመን ያነጻጸረው አዲስ ጥናት እንደሚያሳየው፣ የገቢዎች ሚኒስቴር ከፍተኛውን የግብር ተመን 35 በመቶ አድርሶ እየተገበረ ይገኛል። ይህም ግልጽ የሆነ ከፍተኛ የግብር ጫና ካለባትና 40 በመቶ ከምትከፍለው ኡጋንዳ፣ እንዲሁም 35 በመቶ የመጨረሻ የግብር ተመን ካላትና ተጨማሪ ልዩ ልዩ ታክሶችን ከምትጥለው ኬንያ ቀጥሎ ኢትዮጵያን በሶስተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል።
ይህ ደረጃ የመጣው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በሐምሌ 2025 ያከናወነችውን አጠቃላይ የግብር ማሻሻያ ተከትሎ ነው። መንግስት ቀደም ሲል በሀገር ቁጥጥር ስር የነበረውን የኢኮኖሚ ሞዴል ወደ ነፃ ገበያ ለመቀየር በሚያደርገው ሽግግር፣ የመሠረተ ልማት ጉድለቶችን ለመሙላትና የኢትዮጵያን ብር ለማረጋጋት መደበኛ ተቀጣሪዎችን ዋነኛ የገቢ ምንጭ አድርጓል።
ይህ የደረጃ ምደባ የወጣው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በሐምሌ 2025 ሰፊ የፊስካል እና የግብር ማሻሻያ ማድረጓን ተከትሎ ነው። መንግስት የኢኮኖሚ ሞዴሉን ከመንግስት ቁጥጥር ወደ ነፃ ገበያ መርህ ለመቀየር በሚያደርገው ጉዞ፣ የመሰረተ ልማት ጉድለቶችን ለመሙላት እና የኢትዮጵያን ብር የመግዛት አቅም ለማረጋጋት በመደበኛው የስራ ዘርፍ ላይ በሚጣል የገቢ ግብር ላይ በእጅጉ ተደግፏል። ይሁን እንጂ የግብር እርከኑ የተቀረጸበት መንገድ መካከለኛ ደረጃ ላይ ያሉ ስራ አስኪያጆች እና ባለሙያዎች በፍጥነት ወደ ከፍተኛው 35 በመቶ የግብር ጣሪያ ውስጥ እንዲገቡ የሚያስገድድ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይናገራሉ።
በአንጻሩ ጎረቤቶቹ ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ከፍተኛውን የገቢ ግብር ተመናቸውን በ30 በመቶ የወሰኑ ሲሆን፣ ደቡብ ሱዳን ደግሞ በ15 በመቶ ዝቅተኛ ታክስ በቀጣናው የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
ይህ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የግብር ፖሊሲ ልዩነት በቀጣናው የሰለጠነ የሰው ኃይል ዝውውር ላይ ጫና እየፈጠረ ይገኛል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአፍሪካ ቀንድ እየተካሄደ ያለውን መጠነ-ሰፊ የፋይናንስ እና የግብር ማሻሻያ ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት መካከል በተቀጣሪ ሰራተኞች ደመወዝ ላይ ከፍተኛ ግብር በመጣል ሶስተኛዋ ሀገር መሆንዋ ታውቋል።
የቀጣናውን የቅጥር ገቢ ግብር (PAYE) ተመን ያነጻጸረው አዲስ ጥናት እንደሚያሳየው፣ የገቢዎች ሚኒስቴር ከፍተኛውን የግብር ተመን 35 በመቶ አድርሶ እየተገበረ ይገኛል። ይህም ግልጽ የሆነ ከፍተኛ የግብር ጫና ካለባትና 40 በመቶ ከምትከፍለው ኡጋንዳ፣ እንዲሁም 35 በመቶ የመጨረሻ የግብር ተመን ካላትና ተጨማሪ ልዩ ልዩ ታክሶችን ከምትጥለው ኬንያ ቀጥሎ ኢትዮጵያን በሶስተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል።
ይህ ደረጃ የመጣው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በሐምሌ 2025 ያከናወነችውን አጠቃላይ የግብር ማሻሻያ ተከትሎ ነው። መንግስት ቀደም ሲል በሀገር ቁጥጥር ስር የነበረውን የኢኮኖሚ ሞዴል ወደ ነፃ ገበያ ለመቀየር በሚያደርገው ሽግግር፣ የመሠረተ ልማት ጉድለቶችን ለመሙላትና የኢትዮጵያን ብር ለማረጋጋት መደበኛ ተቀጣሪዎችን ዋነኛ የገቢ ምንጭ አድርጓል።
ይህ የደረጃ ምደባ የወጣው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በሐምሌ 2025 ሰፊ የፊስካል እና የግብር ማሻሻያ ማድረጓን ተከትሎ ነው። መንግስት የኢኮኖሚ ሞዴሉን ከመንግስት ቁጥጥር ወደ ነፃ ገበያ መርህ ለመቀየር በሚያደርገው ጉዞ፣ የመሰረተ ልማት ጉድለቶችን ለመሙላት እና የኢትዮጵያን ብር የመግዛት አቅም ለማረጋጋት በመደበኛው የስራ ዘርፍ ላይ በሚጣል የገቢ ግብር ላይ በእጅጉ ተደግፏል። ይሁን እንጂ የግብር እርከኑ የተቀረጸበት መንገድ መካከለኛ ደረጃ ላይ ያሉ ስራ አስኪያጆች እና ባለሙያዎች በፍጥነት ወደ ከፍተኛው 35 በመቶ የግብር ጣሪያ ውስጥ እንዲገቡ የሚያስገድድ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይናገራሉ።
በአንጻሩ ጎረቤቶቹ ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ከፍተኛውን የገቢ ግብር ተመናቸውን በ30 በመቶ የወሰኑ ሲሆን፣ ደቡብ ሱዳን ደግሞ በ15 በመቶ ዝቅተኛ ታክስ በቀጣናው የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
ይህ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የግብር ፖሊሲ ልዩነት በቀጣናው የሰለጠነ የሰው ኃይል ዝውውር ላይ ጫና እየፈጠረ ይገኛል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣11❤10🤔5👍1🙊1
"የሕወሃት አመራር ወደ አዲስ አበባም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ የመጓዝ ፍላጎት የለውም!" -ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር
የፌዴራል መንግሥቱ በአሁኑ ወቅት ወታደሮቹን ከምዕራብ ትግራይ ወደ ምስራቅ ትግራይ እያሠማራ መሆኑን የሕወሃት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር በዛሬው ማምሻ ጋዜጣዊ መግለጫቸው አስታውቀዋል። በትግራይ ቴሌቪዥን በተላለፈው በዚህ መግለጫ ላይ ኃላፊዋ አሜሪካ በ"አክራሪ" የሕወሃት አመራሮችና አባላት ላይ የጣለችውን የቪዛ እገዳ አስመልክተው የተናገሩ ሲሆን፥ እገዳው በግለሰቦች ላይ ሳይሆን በሕወሃት "መርሆች" ላይ ያነጣጠረ ነው ብለዋል። ይሁን እንጂ ሕወሃት በመሠረታዊ መርሆዎቹ ላይ ፈጽሞ እንደማይደራደር አጽንዖት ሰጥተዋል።
ፈትለወርቅ አክለውም፥ የሕወሃት አመራር ወደ አዲስ አበባም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ የመጓዝ ፍላጎት እንደሌለው ለአሜሪካ ማሳወቃቸውን ገልጸዋል። የትግራይ ሕዝብና የድርጅቱ ጥያቄ ራስን በራስ የማስተዳደርና የራስን ዕጣ ፈንታ በራስ የመወሰን መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊዋ፥ የአሜሪካ ጥቅም ሊረጋገጥ የሚችለው ሕወሃትን በማስፈራራት ሳይሆን አብሮ በመስራት ብቻ እንደሆነ አስገንዝበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የፌዴራል መንግሥቱ በአሁኑ ወቅት ወታደሮቹን ከምዕራብ ትግራይ ወደ ምስራቅ ትግራይ እያሠማራ መሆኑን የሕወሃት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር በዛሬው ማምሻ ጋዜጣዊ መግለጫቸው አስታውቀዋል። በትግራይ ቴሌቪዥን በተላለፈው በዚህ መግለጫ ላይ ኃላፊዋ አሜሪካ በ"አክራሪ" የሕወሃት አመራሮችና አባላት ላይ የጣለችውን የቪዛ እገዳ አስመልክተው የተናገሩ ሲሆን፥ እገዳው በግለሰቦች ላይ ሳይሆን በሕወሃት "መርሆች" ላይ ያነጣጠረ ነው ብለዋል። ይሁን እንጂ ሕወሃት በመሠረታዊ መርሆዎቹ ላይ ፈጽሞ እንደማይደራደር አጽንዖት ሰጥተዋል።
ፈትለወርቅ አክለውም፥ የሕወሃት አመራር ወደ አዲስ አበባም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ የመጓዝ ፍላጎት እንደሌለው ለአሜሪካ ማሳወቃቸውን ገልጸዋል። የትግራይ ሕዝብና የድርጅቱ ጥያቄ ራስን በራስ የማስተዳደርና የራስን ዕጣ ፈንታ በራስ የመወሰን መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊዋ፥ የአሜሪካ ጥቅም ሊረጋገጥ የሚችለው ሕወሃትን በማስፈራራት ሳይሆን አብሮ በመስራት ብቻ እንደሆነ አስገንዝበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤18🤔8🤣7👍2
ጣሊያን ለኢትዮጵያ የ70 ሚሊየን ዩሮ የረጅም ጊዜ ብድር ፈቀደች
የኢትዮጵያ መንግስት ሀገሪቱ የጀመረችውን ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም እና የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለማስፈጸም የሚውል የ70 ሚሊየን ዩሮ የረጅም ጊዜ ቀላል የብድር ስምምነት ከጣሊያን ጋር ተፈራረመ።
የብድር ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ እና በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ በዛሬው ዕለት ተፈራርመውታል። ይህ ድጋፍ ጣሊያን ለኢትዮጵያ ለመስጠት ካቀደችው አጠቃላይ የ150 ሚሊየን ዩሮ የበጀት ድጋፍ ማዕቀፍ ውስጥ የመጀመሪያው ምዕራፍ መሆኑ ተገልጿል።
በስምምነቱ ወቅት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ እንደገለጹት፤ ይህ የብድር ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ አጋርነትና የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር ነው።
ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ዓመታት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ ሁለተኛውን ምዕራፍ በስኬት ማጠናቀቋን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ ይህ የገንዘብ ድጋፍም ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ትልቅ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ ከጣሊያን መንግስት ጋር በኢነርጂ፣ በቡና እና በከተማ ልማት ዘርፎች ጠንካራ ትብብር እንዳላት ያወሱት አቶ አሕመድ፣ ይህ አዲስ ስምምነትም አጋር ሀገራት በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ሂደት ውጤታማነት ላይ ያላቸውን ከፍተኛ እምነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም፣ ኢትዮጵያ ለሶስተኛው የበጀት ድጋፍ ምዕራፍ ትግበራ ከዓለም ባንክ ጋር የአንድ ቢሊየን 450 ሚሊየን ዶላር ስምምነት መፈራረሟን በአብነት ጠቅሰዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ መንግስት ሀገሪቱ የጀመረችውን ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም እና የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለማስፈጸም የሚውል የ70 ሚሊየን ዩሮ የረጅም ጊዜ ቀላል የብድር ስምምነት ከጣሊያን ጋር ተፈራረመ።
የብድር ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ እና በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ በዛሬው ዕለት ተፈራርመውታል። ይህ ድጋፍ ጣሊያን ለኢትዮጵያ ለመስጠት ካቀደችው አጠቃላይ የ150 ሚሊየን ዩሮ የበጀት ድጋፍ ማዕቀፍ ውስጥ የመጀመሪያው ምዕራፍ መሆኑ ተገልጿል።
በስምምነቱ ወቅት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ እንደገለጹት፤ ይህ የብድር ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ አጋርነትና የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር ነው።
ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ዓመታት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ ሁለተኛውን ምዕራፍ በስኬት ማጠናቀቋን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ ይህ የገንዘብ ድጋፍም ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ትልቅ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ ከጣሊያን መንግስት ጋር በኢነርጂ፣ በቡና እና በከተማ ልማት ዘርፎች ጠንካራ ትብብር እንዳላት ያወሱት አቶ አሕመድ፣ ይህ አዲስ ስምምነትም አጋር ሀገራት በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ሂደት ውጤታማነት ላይ ያላቸውን ከፍተኛ እምነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም፣ ኢትዮጵያ ለሶስተኛው የበጀት ድጋፍ ምዕራፍ ትግበራ ከዓለም ባንክ ጋር የአንድ ቢሊየን 450 ሚሊየን ዶላር ስምምነት መፈራረሟን በአብነት ጠቅሰዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢15❤11👍2
የ29 አመቷ የአዲስ አበባ ልጅ ሜላት ኪሮስ የአሜሪካ ህግ አውጪ ምክርቤት Congress በመሆን ተመርጣለች። የመጀመሪያዋ ትውልደ ኢትዮጵያ የኮንግሬስ ተመራጭ ናት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍65❤34🥱8🥰2🏆2🎉1👌1🤪1
📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
❤4👍2🤔1
የሊቢያው ኦላ ኢነርጂ የቶታልኤነርጂስን የኢትዮጵያ ንብረቶች በሙሉ ጠቀለለ
የሊቢያው ኦላ ኢነርጂ ግሩፕ በኢትዮጵያ የሚገኙትን የፈረንሳዩ ቶታልኤነርጂስ ንብረቶች በሙሉ ለመጠቅለል የሚያስችለውን የግዢ ስምምነት በፓሪስ ተፈራረመ።
ይህ ስምምነት ኦላ ኢነርጂ በኢትዮጵያ የነዳጅ ማከፋፈል ገበያ ውስጥ ትልቁ የውጭ ኩባንያ ያደርገዋል።
ይህ ግዙፍ የአክሲዮን ግዢ በኢትዮጵያ የሚገኙ ወደ 120 የሚጠጉ የነዳጅ ማደያዎችን፣ የ13 ሺህ ሜትር ኩብ አቅም ያለውን የነዳጅ ማከማቻ ተርሚናል እና ተያያዥ የንግድ እንቅስቃሴዎችን ያጠቃልላል።
በስምምነቱ ላይ የሊቢያ ዘይትና ጋዝ ሚኒስትር ከሊፋ አብዱልሳዲቅ እና የቶታልኤነርጂስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፓትሪክ ፑያን ጨምሮ የሁለቱም ወገኖች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ግዢው ሊቢያ በአፍሪካ አህጉር ያላትን የኢኮኖሚ ተፅዕኖ እና የውጭ ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት የምታደርገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሊቢያው ኦላ ኢነርጂ ግሩፕ በኢትዮጵያ የሚገኙትን የፈረንሳዩ ቶታልኤነርጂስ ንብረቶች በሙሉ ለመጠቅለል የሚያስችለውን የግዢ ስምምነት በፓሪስ ተፈራረመ።
ይህ ስምምነት ኦላ ኢነርጂ በኢትዮጵያ የነዳጅ ማከፋፈል ገበያ ውስጥ ትልቁ የውጭ ኩባንያ ያደርገዋል።
ይህ ግዙፍ የአክሲዮን ግዢ በኢትዮጵያ የሚገኙ ወደ 120 የሚጠጉ የነዳጅ ማደያዎችን፣ የ13 ሺህ ሜትር ኩብ አቅም ያለውን የነዳጅ ማከማቻ ተርሚናል እና ተያያዥ የንግድ እንቅስቃሴዎችን ያጠቃልላል።
በስምምነቱ ላይ የሊቢያ ዘይትና ጋዝ ሚኒስትር ከሊፋ አብዱልሳዲቅ እና የቶታልኤነርጂስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፓትሪክ ፑያን ጨምሮ የሁለቱም ወገኖች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ግዢው ሊቢያ በአፍሪካ አህጉር ያላትን የኢኮኖሚ ተፅዕኖ እና የውጭ ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት የምታደርገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍6
አሳዛኝ ዜና
በሠሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ሰዶማ ወይም ድሬ ሮቃ አካባቢ በቁጥር 23 ቀበሌ ቀስማ ጎጥ ላይ ምክኒያቱ በውል ባልታወቀ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ከ50 ያላነሱ የአርሶ አደራችን መኖሪያ ቤቶች በትላንትናው እለት ተቃጥለዋል።
የዚህ አከባቢ ህዝብ ጀግና እና አስተዋይ ህዝቦች ሲሆኑ ሀገር በፈለጋቸው ወቅትም ክንዳዘው ሳይዝል ከትላንት እስከ ዛሬ ፀንተው የቆሙ ህዝቦች ናቸው።
በመሆኑም ሁላችነም በጋራ ሆነን ወገኖቻችን አንገታቸውን መድፋት ስለሌለባቸው እንድናቋቁማቸው ጥሪየን አቀርባለሁ።
ዘመን ተሻጋሪው
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሠሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ሰዶማ ወይም ድሬ ሮቃ አካባቢ በቁጥር 23 ቀበሌ ቀስማ ጎጥ ላይ ምክኒያቱ በውል ባልታወቀ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ከ50 ያላነሱ የአርሶ አደራችን መኖሪያ ቤቶች በትላንትናው እለት ተቃጥለዋል።
የዚህ አከባቢ ህዝብ ጀግና እና አስተዋይ ህዝቦች ሲሆኑ ሀገር በፈለጋቸው ወቅትም ክንዳዘው ሳይዝል ከትላንት እስከ ዛሬ ፀንተው የቆሙ ህዝቦች ናቸው።
በመሆኑም ሁላችነም በጋራ ሆነን ወገኖቻችን አንገታቸውን መድፋት ስለሌለባቸው እንድናቋቁማቸው ጥሪየን አቀርባለሁ።
ዘመን ተሻጋሪው
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤24😢18💔9👍2
አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት‼️
በእጅ ስልካችን ረቂቅ እና ያልተፈቀዱ ግብይቶችን የሚፈፅሙ እና በስፋት እየተሰራጩ የሚገኙ ጎጂ መተግበሪያዎችን ስለማሳወቅ‼️
ጥቃት አድራሾች የጥቃት ዘዴያቸውን በመቀያየርና ጎጂ መተግበሪያዎችን በማበለፀግ ወይም በመጠቀም ከሞባይል ላይ የግል መረጃ ስርቆትን ጨምሮ ያልተፈቀዱ የገንዘብ ዝውውሮችን ይፈፅማሉ።
የሚከተሉት እጅግ ውስብስብ፣ ረቂቅ እና አደገኛ የሆኑ ጎጂ መተግበሪያዎችም በስፋት እየተሰራጩ እንደሚገኙ ለማወቅ ችለናል።
1. ትረስት መተግበሪያ (Trust.Apk)
ትረስት የተሰኘው ጎጂ መተግበሪያ https://trust--application በሚል ማስፈንጠሪያ (ሊንክ) እየተሰራጨ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህን ጎጂ መተግበሪያ ተጠቂዎች ስልካቸው ላይ በሚጭኑበት ወቅት የሞባይል ስክሪናቸውን ማየት/ማንበብ እንዲሁም ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ስልካቸውን በመቆጣጠር እንደ ይለፍ ቃል/ፒን የመሳሰሉ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በመመንተፍ ከሞባይሉ ባለቤት እውቅና ውጪ የሞባይል መተግበሪያም ይሁን የአጭር ኮድ (*889*) አገልግሎቶችን በመጠቀም ያልተፈቀደ ግብይቶችን መፈፅም የሚችል አደገኛ መተግበሪያ ነው።
2. ጎግል ቲቪ (Google TV)
ጎግል ቲቪ (Google TV) የተሰኘውን ጎጂ መተግበሪያ በሊንክ አማካኝነት ወደ ጎግል ክሮም (Google Chrome) በመግባት ተጠቂው በሚጭንበት ጊዜ እንደ ይለፍ ቃል/ፒን ያሉ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በመመንተፍ፣ ከተጠቂው እውቅና ውጪ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያን በመጠቀም ገንዘብ ማስተላለፍም ሆነ በርቀት መቆጣጠር (Remote Access) ችሎታን በመጠቀም ጥቃት መሰንዘር የሚችል ነው።
3. ኖውን (Known)
ሶስተኛው ጎጂ መተግበሪያ በማህበራዊ ትስስር ድረ-ገፆች ላይ እየተዘዋወረ ሲገኝ ከላይ እንደ ጠቀስናቸው መተግበሪያዎች ከጎግል ክሮም (Google Chrome) እየወረዱ ይገኛሉ። ይህን መተግበሪያ ከሌሎቹ ለየት የሚያደርገው አንዴ ስልካችን ላይ ከተጫነና እንደ ተደራሽነት (Accessibility)፣ የመሳሪያ ፍቃድ አስተዳደር (Device Administrator Rights) ያሉ ፍቃዶችን ከተቸረው ሙሉ በሙሉ ስልካችንን በመቆጣጠር “Installing system update...” የሚል መልዕክት ብቻ ጥቁር ስክሪን ላይ የሚያሳይ ሲሆን ተጠቃሚው ይህንን መተግበሪያ ለማጥፋት ግዴታ ሴፍ ሞድ (Safe Mode) በኩል መግባት ይኖርበታል። ሌላው ይሄን መተግበሪያ ለየት የሚያደርገው ከፍተኛ የሆነ የኔትዎርክ አጠቃቀም ሲኖረው፣እምነት ለመገንባትና ተጠቂዎችን ለማታለል Google Play Store የሚመስል ሀሰተኛ ገፅ በመፍጠር ተጠቃሚዎች የማሳመን ስራን ይሰራል። በዋነኝነት ደግሞ ከተጠቂው እውቅና ውጪ ገንዘብ ያስተላልፋል።
በመሆኑም፣ ይህንን የጥንቃቄ መልዕክት በአግባቡ በመገንዘብ ራሳችሁን፣ ቤተሰባችሁን እና በዙሪያችሁ ያሉ ሰዎችን ለደርሱ ከሚችሉ ጥቃቶች እንድትጠብቁ ጥሪያችንን እያቀረብን ከታች የተቀመጡትን የጥንቃቄ መልዕክቶች በአግባቡ እንድተገብሩ እናሳስባለን።
ደንበኞች ከዚህ መሰል ጥቃት እንዴት እራሳቸውን መከላከል ይችላሉ?
👉 ካልታመኑ ምንጮች (ጎግል ክሮም የመሳሰሉ ብሮውዘሮች ፣ቴሌግራም፣ ዋትስአፕ) ላይ መተግበሪያዎችን ከማውረድ ይቆጠቡ።
👉 እንደ ጎግል ፕሌይ፣ አማዞን አፕስቶር ወይም ሳምሰንግ ጋላክሲ ስቶር ጥብቅ የደህንነት ፍተሻዎችን የሚያደርጉ ይፋዊ የመተግበሪያ ማከማቻዎችን ይጠቀሙ።
👉 ለሁሉም የባንኩ መተግበሪያዎች እንደ አሻራ ያሉ ባለ ሁለት ደረጃ ማረጋገጫ ይጠቀሙ።
👉 በሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎ ላይ የአሻራ (Biometrics) እና PIN ማረጋገጫን ባንድ ላይ ይጠቀሙ።
ይህን ለማድረግ፡
👉 መተግበሪያዎችን ተአማኒ ካልሆኑ ድረ-ገፆች ላይ አውርዳችሁ ለመጫን ስትሞክሩ ስልካችሁ የሚልክላችሁን እንደ ‘File May be Harmful’ የመሳሰሉ የጥንቃቄ መልዕክቶችን ችላ አይበሉ።
👉 ከአጠራጣሪ ኢ-ሜይሎች የሚላኩ ማስፈንጠሪያም (suspicious links) ሆነ ፋይል (Attachment) ሳያረጋግጡ ከመክፈት ይቆጠቡ።
👉 ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል ፍቃዶችን (Permission) የሚጠይቁ መተግበሪያዎች ላይ አስፈላጊ ነው ወይንስ አያስፈልግም ሚለውን የራስዎን ጥናት በማድረግ ፍቃዱን ይገድቡ።
#CBE
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በእጅ ስልካችን ረቂቅ እና ያልተፈቀዱ ግብይቶችን የሚፈፅሙ እና በስፋት እየተሰራጩ የሚገኙ ጎጂ መተግበሪያዎችን ስለማሳወቅ‼️
ጥቃት አድራሾች የጥቃት ዘዴያቸውን በመቀያየርና ጎጂ መተግበሪያዎችን በማበለፀግ ወይም በመጠቀም ከሞባይል ላይ የግል መረጃ ስርቆትን ጨምሮ ያልተፈቀዱ የገንዘብ ዝውውሮችን ይፈፅማሉ።
የሚከተሉት እጅግ ውስብስብ፣ ረቂቅ እና አደገኛ የሆኑ ጎጂ መተግበሪያዎችም በስፋት እየተሰራጩ እንደሚገኙ ለማወቅ ችለናል።
1. ትረስት መተግበሪያ (Trust.Apk)
ትረስት የተሰኘው ጎጂ መተግበሪያ https://trust--application በሚል ማስፈንጠሪያ (ሊንክ) እየተሰራጨ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህን ጎጂ መተግበሪያ ተጠቂዎች ስልካቸው ላይ በሚጭኑበት ወቅት የሞባይል ስክሪናቸውን ማየት/ማንበብ እንዲሁም ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ስልካቸውን በመቆጣጠር እንደ ይለፍ ቃል/ፒን የመሳሰሉ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በመመንተፍ ከሞባይሉ ባለቤት እውቅና ውጪ የሞባይል መተግበሪያም ይሁን የአጭር ኮድ (*889*) አገልግሎቶችን በመጠቀም ያልተፈቀደ ግብይቶችን መፈፅም የሚችል አደገኛ መተግበሪያ ነው።
2. ጎግል ቲቪ (Google TV)
ጎግል ቲቪ (Google TV) የተሰኘውን ጎጂ መተግበሪያ በሊንክ አማካኝነት ወደ ጎግል ክሮም (Google Chrome) በመግባት ተጠቂው በሚጭንበት ጊዜ እንደ ይለፍ ቃል/ፒን ያሉ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በመመንተፍ፣ ከተጠቂው እውቅና ውጪ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያን በመጠቀም ገንዘብ ማስተላለፍም ሆነ በርቀት መቆጣጠር (Remote Access) ችሎታን በመጠቀም ጥቃት መሰንዘር የሚችል ነው።
3. ኖውን (Known)
ሶስተኛው ጎጂ መተግበሪያ በማህበራዊ ትስስር ድረ-ገፆች ላይ እየተዘዋወረ ሲገኝ ከላይ እንደ ጠቀስናቸው መተግበሪያዎች ከጎግል ክሮም (Google Chrome) እየወረዱ ይገኛሉ። ይህን መተግበሪያ ከሌሎቹ ለየት የሚያደርገው አንዴ ስልካችን ላይ ከተጫነና እንደ ተደራሽነት (Accessibility)፣ የመሳሪያ ፍቃድ አስተዳደር (Device Administrator Rights) ያሉ ፍቃዶችን ከተቸረው ሙሉ በሙሉ ስልካችንን በመቆጣጠር “Installing system update...” የሚል መልዕክት ብቻ ጥቁር ስክሪን ላይ የሚያሳይ ሲሆን ተጠቃሚው ይህንን መተግበሪያ ለማጥፋት ግዴታ ሴፍ ሞድ (Safe Mode) በኩል መግባት ይኖርበታል። ሌላው ይሄን መተግበሪያ ለየት የሚያደርገው ከፍተኛ የሆነ የኔትዎርክ አጠቃቀም ሲኖረው፣እምነት ለመገንባትና ተጠቂዎችን ለማታለል Google Play Store የሚመስል ሀሰተኛ ገፅ በመፍጠር ተጠቃሚዎች የማሳመን ስራን ይሰራል። በዋነኝነት ደግሞ ከተጠቂው እውቅና ውጪ ገንዘብ ያስተላልፋል።
በመሆኑም፣ ይህንን የጥንቃቄ መልዕክት በአግባቡ በመገንዘብ ራሳችሁን፣ ቤተሰባችሁን እና በዙሪያችሁ ያሉ ሰዎችን ለደርሱ ከሚችሉ ጥቃቶች እንድትጠብቁ ጥሪያችንን እያቀረብን ከታች የተቀመጡትን የጥንቃቄ መልዕክቶች በአግባቡ እንድተገብሩ እናሳስባለን።
ደንበኞች ከዚህ መሰል ጥቃት እንዴት እራሳቸውን መከላከል ይችላሉ?
👉 ካልታመኑ ምንጮች (ጎግል ክሮም የመሳሰሉ ብሮውዘሮች ፣ቴሌግራም፣ ዋትስአፕ) ላይ መተግበሪያዎችን ከማውረድ ይቆጠቡ።
👉 እንደ ጎግል ፕሌይ፣ አማዞን አፕስቶር ወይም ሳምሰንግ ጋላክሲ ስቶር ጥብቅ የደህንነት ፍተሻዎችን የሚያደርጉ ይፋዊ የመተግበሪያ ማከማቻዎችን ይጠቀሙ።
👉 ለሁሉም የባንኩ መተግበሪያዎች እንደ አሻራ ያሉ ባለ ሁለት ደረጃ ማረጋገጫ ይጠቀሙ።
👉 በሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎ ላይ የአሻራ (Biometrics) እና PIN ማረጋገጫን ባንድ ላይ ይጠቀሙ።
ይህን ለማድረግ፡
👉 መተግበሪያዎችን ተአማኒ ካልሆኑ ድረ-ገፆች ላይ አውርዳችሁ ለመጫን ስትሞክሩ ስልካችሁ የሚልክላችሁን እንደ ‘File May be Harmful’ የመሳሰሉ የጥንቃቄ መልዕክቶችን ችላ አይበሉ።
👉 ከአጠራጣሪ ኢ-ሜይሎች የሚላኩ ማስፈንጠሪያም (suspicious links) ሆነ ፋይል (Attachment) ሳያረጋግጡ ከመክፈት ይቆጠቡ።
👉 ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል ፍቃዶችን (Permission) የሚጠይቁ መተግበሪያዎች ላይ አስፈላጊ ነው ወይንስ አያስፈልግም ሚለውን የራስዎን ጥናት በማድረግ ፍቃዱን ይገድቡ።
#CBE
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤40👍10🙏2🥰1🤯1👌1
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከፌደራል መንግስት ጋር የሚደራደር ከሆነ በአዲስ አበባ ከተማ ሳይሆን “በሌላ ሶስተኛ ሀገር” እንደሚሆን ለአሜሪካ ማሳወቁን የፓርቲው ጽህፈት ቤት ኃላፊ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ተናገሩ።
የአሜሪካ መንግስት “ቪዛ መከልከል ይቅር እና ሌላ ቢያደርግም”፤ “የትግራይ ህዝብ ህልውናን ለማረጋገጥ” ህወሓት “እስከ መጨረሻ እንደሚታገል” ኃላፊዋ ገልጸዋል።
“ሞንጆሪኖ” በሚለው የቅጽል ስማቸው ይበልጡኑ የሚታወቁት ፈትለወርቅ ይህንን የገለጹት፤ ትላንት ማክሰኞ ሰኔ 23፤ 2018 በመቐለ ከተማ በሚገኘው የህወሓት ጽህፈት ቤት ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ነው።
በትላንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል የፕሪቶሪያ ስምምነት ሁኔታ፣ የጦርነት ስጋት፣ የወጣቶች አፈሳ፣ የአሜሪካ ቪዛ እገዳ እንዲሁም ትግራይን በተመለከተ አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት ያወጧቸው መግለጫዎች ይገኙበታል።
የፕሪቶሪያ ስምምነት “መፍረሱን” በተደጋጋሚ በሚያወጣቸው መግለጫዎች ያሳወቀው ህወሓት፤ ለዚህም ዋነኛው ተጠያቂ የፌደራል መንግስት መሆኑን ሲገልጽ ቆይቷል።
የህወሓት ጽህፈት ቤት ኃላፊ በትላንቱ መግለጫቸው፤ የፕሪቶሪያ ስምምነትን “የፌደራል መንግስት እንደ መሳርያ ነው የተጠቀመበት” ሲሉ ተመሳሳይ አቋም አንጸባርቀዋል።
“የፕሪቶሪያ ውል እንዲፈጸም ህወሓት ጥረት አድርጓል። ውሉን የሚጥሱ በርካታ ነገሮች ቢሰሩም፤ ‘የፕሪቶርያ ስምምነት ፈርሷል’ ሳይል በትእግስት ቆይቷል። በዚህ ጉዳይ ህወሓት እንደ ፓርቲ ትልቅ ትልቅ መስዋእትነት ከፍሏል” ሲሉም ፈትለወርቅ ለፓርቲው ልሳናት እና ለክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኞች ተናግረዋል።
Via Ethiopia Insider
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአሜሪካ መንግስት “ቪዛ መከልከል ይቅር እና ሌላ ቢያደርግም”፤ “የትግራይ ህዝብ ህልውናን ለማረጋገጥ” ህወሓት “እስከ መጨረሻ እንደሚታገል” ኃላፊዋ ገልጸዋል።
“ሞንጆሪኖ” በሚለው የቅጽል ስማቸው ይበልጡኑ የሚታወቁት ፈትለወርቅ ይህንን የገለጹት፤ ትላንት ማክሰኞ ሰኔ 23፤ 2018 በመቐለ ከተማ በሚገኘው የህወሓት ጽህፈት ቤት ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ነው።
በትላንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል የፕሪቶሪያ ስምምነት ሁኔታ፣ የጦርነት ስጋት፣ የወጣቶች አፈሳ፣ የአሜሪካ ቪዛ እገዳ እንዲሁም ትግራይን በተመለከተ አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት ያወጧቸው መግለጫዎች ይገኙበታል።
የፕሪቶሪያ ስምምነት “መፍረሱን” በተደጋጋሚ በሚያወጣቸው መግለጫዎች ያሳወቀው ህወሓት፤ ለዚህም ዋነኛው ተጠያቂ የፌደራል መንግስት መሆኑን ሲገልጽ ቆይቷል።
የህወሓት ጽህፈት ቤት ኃላፊ በትላንቱ መግለጫቸው፤ የፕሪቶሪያ ስምምነትን “የፌደራል መንግስት እንደ መሳርያ ነው የተጠቀመበት” ሲሉ ተመሳሳይ አቋም አንጸባርቀዋል።
“የፕሪቶሪያ ውል እንዲፈጸም ህወሓት ጥረት አድርጓል። ውሉን የሚጥሱ በርካታ ነገሮች ቢሰሩም፤ ‘የፕሪቶርያ ስምምነት ፈርሷል’ ሳይል በትእግስት ቆይቷል። በዚህ ጉዳይ ህወሓት እንደ ፓርቲ ትልቅ ትልቅ መስዋእትነት ከፍሏል” ሲሉም ፈትለወርቅ ለፓርቲው ልሳናት እና ለክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኞች ተናግረዋል።
Via Ethiopia Insider
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9🤣6👍5💯1🤪1