አዲስ ሪፖርተር - NEWS
35.8K subscribers
16.9K photos
414 videos
21 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
አሜሪካ ተማሪዎቿን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲያነቡ ልታስደርግ ነው።

የቴክሳስ ግዛት ተማሪዎችን የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን እንዲያነቡ ሊያስገድድ መሆኑ ተዘግቧል።

በአሜሪካ የቴክሳስ ግዛት የትምህርት ምክር ቤት በግዛቲቱ ያሉ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን እንዲያነቡ የሚያስገድድ አዲስ የንባብ ዕቅድ በ9 የድጋፍ በ5 የተቃውሞ ድምፅ አጽድቋል።

ከሦስት ዓመት በኋላ ተግባራዊ የሚሆነው ይህ እቅድ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን ብቻ ሳይሆን የቻርልስ ዲከንስ “Great Expectations” እና የዊሊያም ሼክስፒር “The Tragedy of Julius Caesar” የመሳሰሉ ታዋቂ የእንግሊዝ ሥነ-ጽሑፍ ሥራዎችንም ያካትታል ነው የተባለው።

ውሳኔው በአሜሪካ ውስጥ በሃይማኖትና በመንግሥት መለያየት ላይ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።

ደጋፊዎቹ የአይሁድ-ክርስትና እሴቶችና ባህሎች በአሜሪካ ታሪክና ምሥረታ ውስጥ ትልቅ ሚና እንዳላቸው በመግለጽ ተማሪዎች ሊያውቋቸው ይገባል ይላሉ።

የቴክሳስ የትምህርት ቦርድ አባል ብራንደን ሆል “መጽሐፍ ቅዱስን ከ60 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትምህርት ቤቶች እየመለስን ነው” ብለዋል።

በሌላ በኩል ተቃዋሚዎች እቅዱ የሃይማኖት ነፃነትን የሚጎዳ፣ ክርስትናን ከሌሎች ሃይማኖቶች በላይ የሚያቆም እና የአሜሪካን ባህላዊ ብዝሃነት የሚያቀል መሆኑን ይናገራሉ።

የ“Freedom Network” ዋና ዳይሬክተር ፌሊሺያ ማርቲን እቅዱ ሌሎች ሃይማኖቶችን፣ የቀደምት አሜሪካውያንን እና የተለያዩ ማህበረሰቦችን አስተዋፅኦ ችላ እንደሚል ተችታለች።

ተማሪዎች ከአዲስ ኪዳን ውስጥ ስለ ኢየሱስ የሚናገሩ ክፍሎችን እና “የጠፋው ልጅ” የሚባለውን ምሳሌ እንዲማሩ በእቅዱ ተካትቷል።

እንዲሁም የቴክሳስ መምህራን ማህበር እቅዱ በጣም ሰፊ መሆኑን እና መምህራን ለተማሪዎቻቸው ተገቢ የሆኑ መጽሐፍትን የመምረጥ ነፃነታቸውን ሊያሳንስ እንደሚችል ገልጿል።

ይህ ውሳኔ በቴክሳስ ውስጥ ክርስቲያናዊ እሴቶችን በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ ለማጠናከር ከተወሰዱ ተከታታይ እርምጃዎች አንዱ ሲሆን፤ ባለፈው ዓመትም በትምህርት ክፍሎች ውስጥ የአሥርቱ ትዕዛዛት እንዲሰቀሉ የሚያስገድድ ሕግ ተላልፎ ነበር፤ ይህም በፌዴራል ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ድጋፍ አግኝቷል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ውሳኔውን በመደገፍ በአሜሪካ ውስጥ የሃይማኖት እሴቶችን ለማጠናከር የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ገልጸው፣ “ሃይማኖት ከቀድሞው የበለጠ ጠንካራ ሆኖ ወደ አገራችን ተመልሷል” ብለዋል።

በአጠቃላይ ውሳኔው በአሜሪካ የትምህርት፣ የሃይማኖት ነፃነት እና የመንግሥት-ሃይማኖት ግንኙነት ላይ ሰፊ ውይይት እንዲቀጥል አድርጓል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
56👍8🤪6😡5🤔1🎉1👌1💯1
የ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይሆናል

የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ሰኔ 22 ቀን ከሰዓት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ነጥቡ ላይ ውይይት ካደረጉ በኃላ ይፋ ይደረጋል ሲል ቢሮው ማስታወቁን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።

የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ ያስችላል። የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 11 እና 12 /2018 ዓ.ም  በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለ56,737 ተማሪዎች መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
13👍5
"የቡና የውጭ ምንዛሬ ገቢ ወደ 6 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ይሰራል" ግብርና ሚኒስቴር

የኢትዮጵያ ቡና የውጭ ምንዛሬ ገቢን በቀጣይ አምስት ዓመት ወደ 6 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ እንደሚሰራ የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ አዲሱ አረጋ ተናገሩ፡፡

ለቀጣይ አምስት ዓመታት በሚተገበረው ሃገራዊ የቡና ልማት ፓኬጅ መተግበሪያ ሰነድ ይፋ ሆኗል።
አሁን ላይ የኢትዮጵያ ቡና የውጭ ምንዛሬ ወደ 3 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተጠቁሟል።

በቀጣይ አምስተ ዓመታት ይህንን ገቢ ወደ 6 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ይሰራል ሲሉ አቶ አቶ አዲሱ ገልፀዋል፡፡

እንደ ጋዜጣ ፕላስ ዘገበሰ አርሶ አደሩ አሁንም በባህላዊ እውቀት እያመረተ እንደሚገኝ ጠቅሰው በሄክታር 8 ኩንታል ምርታማነትን በቀጣይ አምስት ዓመታት ወደ 21 ኩንታል ማድረስ ይጠበቃል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
9👍2🤔2
📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944

👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
 👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ

🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !

👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
2👍2
በአዲስ አበባ ከተማ የሲጋራ ቁራጭ መንገድ ላይ መጣል 2 ሺህ ብር ያስቀጣል ተባለ

የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን የሲጋራ ቁራጭ በመንገድ፣ በአደባባይ ወይም በማንኛውም የህዝብ መገልገያ ቦታ ላይ የሚጥል ግለሰብ በ2 ሺህ ብር እንደሚቀጣ ገልጿል።ይህ እርምጃ የከተማዋን ንፅህና፣ የህዝብን ጤና ለመጠበቅ እና የትምባሆ ተጠቃሚነትን ለመቀነስ የሚደረገው የቁጥጥር አካል መሆኑ ተገልጿል።

የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ሙሉእመቤት ታደሰ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ቅጣቱ የሚተገበረው በከተማ አስተዳደሩ ደንብ ቁጥር 167/2016 መሠረት ነው።ደንቡ የትምባሆ ምርቶችን አጠቃቀም ለመቆጣጠርና ከጭስ ነፃ የሆነ የከተማ አካባቢን ለመፍጠር የወጣ መሆኑን ጠቁመዋል።

ባለሥልጣኑ በአዲስ አበባ ከተማ 79 በመቶ የሚሆኑት የህዝብ መገልገያ ተቋማት ከጭስ ነፃ መሆናቸውን ገልጿል።በከተማዋ የአጫሾች መጠን ከ5.3 በመቶ ወደ 4.6 በመቶ መቀነሱን በመግለጽ እየተወሰዱ ያሉ የቁጥጥርና የግንዛቤ ማስጨበጫ እርምጃዎች ውጤት እያሳዩ መሆናቸውን አመልክቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
19👍7🤣4🤯1😢1🙏1👌1💯1👀1
የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ለመወያየት አዲስ አበባ ገቡ፤ ጉብኝቱ በስድስት ወራት ውስጥ ለ4ኛ ጊዜ የተደረገ ነው!

የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ለመወያየት ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል።ይህ ጉብኝት በሁለቱ አገራት መካከል በፍጥነት እያደገ የመጣውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ተከትሎ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው አራተኛው ውይይት ሆኖ ተመዝግቧል።

ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት የወጣው መግለጫ እንደሚያመለክተው፤ ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ እና አብሯቸው የተጓዘው ልዑክ በኢትዮጵያ ዋና ከተማ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።ጉብኝቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን እና ስትራቴጂካዊ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ሲሆን፤ ውይይቱም በዋናነት በቀጠናዊ ደኅንነት፣ መረጋጋት እና በሶማሊያና በኢትዮጵያ የጋራ ጥቅሞች ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
5👍4😢2
የአሜሪካው ግዙፍ የፈርኒቸር ኩባንያ ‘አሽሊ ፈርኒቸር’ በኢትዮጵያ ሁለተኛ ቅርንጫፉን ከፈተ

በአሜሪካ የተመሰረተውና ለ80 ዓመታት ዓለም አቀፍ የፈርኒቸር ብራንድ ሆኖ የቆየው አሽሊ ፈርኒቸር  ለዩስራ ሆም በሰጠው የብቸኛ ወኪልነትና አቅራቢነት ፈቃድ መሠረት በኢትዮጵያ ሁለተኛ ቅርንጫፉን በይፋ ከፍቷል።

በእለቱ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ፣ የዩስራ ሆም መሥራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ዩስራ ኑርሁሴንን ጨምሮ የሁለቱ ድርጅቶች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶችና የንግድ ማኅበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።

የአሽሊ ፈርኒቸር ወደ ኢትዮጵያ መግባት ሆቴሎችና አልሚዎች ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የፈርኒቸር ምርቶች ለማግኘት ወደ ውጭ ሀገር በመጓዝ ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬና የትራንስፖርት ወጪ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቀንስ ተጠቁሟል።

ከ155  ሀገራት  በላይ የሚገኘው አሽሊ ፈርኒቸር  የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የንግድ ትስስር በማጠናከርና የሀገሪቱን ገፅታ በመልካም ጎን በማሳየት ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
11🥰4👍2
ህወሃት ምላሽ ሰጠ‼️
‹‹በትግራይ ዙሪያ የድሮን ክትትሉ ቀጥሏል›› ሕወሓት‼️

ሕወሓት ወታደራዊ ግዳጅ እየፈጸመ መሆኑን ካደ፡፡ ቡድኑ የአውሮፓ ህብረት ያወጣውን ማሳሰቢያ ተከትሎ ባወጣው መግለጫ፣ መሬት ላይ ያሉ እውታዎችን በመካድ፤ የፌዴራል መንግስቱ ላይ ተጨማሪ ክሶችን አቅርቧል፡፡

ህወሓት በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ በትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያወጣውን መግለጫና የሰነዘረውን ወቀሳ ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ ጠንከር ያለ ይፋዊ ምላሽ ሰጥቷል። የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ ህወሓት "ትይዩ ክልላዊ ምክር ቤት አቋቁሟል" እና "የግዳጅ ውትድርና ምልመላ እያካሄደ ነው" በማለት የሰነዘረውን ወቀሳ ያጣጣለው ድርጅቱ፣ ሕብረቱ መሬት ላይ ያለውን ነባራዊ እውነታ ወደ ጎን በመተው በተሳሳተ መረጃ ላይ የተመሠረተ መግለጫ አውጥቷል ሲል ኮንኗል።

ህወሓት በትግራይ ውስጥ "ትይዩ ክልላዊ ምክር ቤት" አቋቁሟል የሚለው ወቀሳ ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ ነው ብሏል። በትግራይ ሕዝብ ስም የተቋቋመ ሌላ አዲስ ምክር ቤት እንደሌለ የገለጸው ድርጅቱ፣ ቀደም ሲል በሕግ የተመረጠው ብቸኛው የትግራይ ክልላዊ ምክር ቤት ከከተሞች እስከ ገጠር ማኅበረሰብ ሰፊ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ወደ መደበኛ ሥራው መመለሱንና ይህም በታችኛው መዋቅር በኩል ጭምር ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን አስታውቋል።
ድርጅቱ አስገዳጅ ምልመላ እያካሄደ ነው መባሉ ግልጽ ያልሆነና በማስረጃ ያልተደገፈ ክስ ነው ሲል አጣጥሎታል። ይሁን እንጂ በትግራይ ዙሪያ ከፍተኛ የወታደራዊ ኃይል ስምሪት፣ ቀጣይነት ያለው የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃቶችና የአየር ላይ ክትትሎች ባሉበት ነባራዊ ሁኔታ፣ የክልሉ ባለሥልጣናት ሕዝቡን ከዳግም ጭፍጨፋና ከህልውና አደጋ የመጠበቅና ራሱን የመከላከል ሞራላዊና ሕጋዊ ኃላፊነት እንዳለባቸው አስገንዝቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
18🤣4👍3🤔1
⁉️ የምስራቁ ጦርነት የኑሮአችንን ዋጋ እንዴት እያናጋው ነው? 💥

🚨የኃያላን መንግስታት ፍጥጫ እና የድንበር ጦርነቶች ከሩቅ የሚታዩ የዜና አርዕስቶች ብቻ አይደሉም፤ የኢትዮጵያን ገበያ እና የኪሳችንን አቅም በቀጥታ የሚፈትኑ ማዕበሎች እንጂ።

የሀገር ውስጥ ወቅታዊ ፈተናዎችን እና አጠቃላይ የአህጉራችንን እና የዓለምን ዜናዎች አቀናጅቶ የሚያቀርብላችሁን ስፑትኒክን አሁኑኑ ይከተሉ 👇
🔗 https://t.me/+r3LZG4PCAKI3NmMy
📣 @sputnik_ethiopia
4👍2
አፈሳው በጭምብል ሆኗል‼️
በትግራይ ክልል በሁሉም ቦታዎች አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ቀጥሏል።
ከላይ የሚታየው ምስል በዛሬው ዕለት ሰኔ 22/2018 ዓ.ም ከሺላናት የተያዙ ወጣቶች ወደ አዲ ጉዶም ፖሊስ ጣቢያ ሲወሰዱ የሚያሳይ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አፈሳውን የሚፈፅሙት ታጣቂዎች ጭምብል የለበሱ ናቸው። ህወሃት ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስገዳጅ ወታደራዊ አፈሳ እያደረግሁ አይደለም ብሏል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
💔54🤷‍♂2👍2😢1
ተማሪዎች ውጤታቸው መመልከት ይችላሉ።

በ2018 የትምህርት ዘመን በ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና 95.85% ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

ተማሪዎች ውጤታቸውን ይህንን ማስፈንጠሪያ https://aa.ministry.et/#/result በመጫን መመልከት ይችላሉ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
9👍4
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ (ሰኔ 23) ይጀምራል‼️

የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገራችን በ607 የፈተና ማዕከላት በስድስት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል::

ለፈተናው በድምሩ 563 ሺህ 501 ተፈታኞች የተመዘገቡ ሲሆን፣ 306 ሺህ 456 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 257 ሺህ 45 የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው::

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
7👍3🎉3
ኢትዮጵያ ያለባትን የ1 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ለመክፈል ከአበዳሪዎቿ ጋር ስምምነት ላይ ደረሰች!

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የግል አበዳሪዎች ተበድራው የነበረውን 1 ቢሊዮን ዶላር (ዩሮቦንድ) በወቅቱ መክፈል አቅቷት የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ዕዳውን የምታቀልበት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ኢትዮጵያ ከነበረባት 1 ቢሊዮን ዶላር ላይ የ12% ቅናሽ የተደረገላት ሲሆን በዚህ መሰረት የምትከፍለው ዕዳ ወደ 880 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ብሏል።

ይህንን 880 ሚሊዮን ዶላር እስከ 2029 ድረስ በ6.15% ወለድ በየደረጃው እንድትከፍል ጊዜ የተሰጣት ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ሳትከፍል ያሳለፈችውን 99.4 ሚሊዮን ዶላር የወለድ ዕዳ ትከፍላለች።

ስምምነቱ ወደፊት ኢትዮጵያ ብድር ባስፈለጋት ጊዜ እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ድረስ በድጋሚ የመበደር መብት ወይም ዕድልን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ዋናዎቹ አበዳሪ ሀገራት (ቻይና እና ፈረንሳይ) ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ገፅታ የሚያሻሽልና ተጨማሪ የውጭ ብድርና 1እርዳታ በቀላሉ እንድታገኝ በር የሚከፍት በመሆኑ .በገበያው ላይ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
21🤪19👍7🥱4🥰1👌1🤣1
ዱባይ ለኢትዮጵያውያን ማስጠንቀቂያ‼️
የዱባይ ፖሊስ በኢትዮጵያውያን ላይ የመጨረሻ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጠ‼️

​ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዲጂታል መድረኮች በሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች ላይ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። ይህ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው በትውልድ ኢትዮጵያውያን መካከል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተደረጉ ያሉ አንዳንድ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ነው።

​የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በጋራ ባዘጋጁት መድረክ እንደተገለጸው፣ በአረብ ኤምሬቶች የሳይበር ወንጀል ህግ መሰረት የሚከተሉት ድርጊቶች ከፍተኛ ቅጣት እንደሚያስከትሉ ተገልጿል፦

📌 ​የጥላቻ ንግግር: በማህበረሰቡ መካከል መከፋፈልን፣ ጥላቻን እና ንቀትን የሚያንጸባርቁ የብሄር ፖለቲካ ቅስቀሳዎችን ሶሻል ሚዲያ ላይ መለጠፍ።

📌 ​ስድብ እና ስም ማጥፋት: ግለሰቦችን ወይም ተቋማትን በቪዲዮ፣ በጽሁፍ ወይም በኮሜንት መዝለፍ እና ስም ማጥፋት ህግ የተከለከለ ነው።

📌 ​ያለ ፈቃድ መረጃ ማውጣት: የግለሰቦችን ግላዊነት የሚነኩ ምስሎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም መረጃዎችን ያለ ፈቃድ ማሰራጨት በህግ የሚያስቀጣ ነው።

📌 ​የገንዘብ ማሰባሰብ: ያለ መንግስት ፈቃድ በማህበራዊ ሚዲያ በኩል በስምምነት ገንዘብ ማሰባሰብ በኢምሬትስ ህግ የተከለከለ ነው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍109🤔1
እራሴን ችዬ እዋጋለሁ-እስራኤል‼️
የእስራኤል  መከላከያ ሚኒስትር ከኢራን ጋር ዳግም ወደ ጦርነት በቀናት ውስጥ ልንገባ እንችላለን አሉ።

አይ ዲ ኤፍ ዝግጅት እንዲያደርግም ትዕዛዝ ተሰጥቶታል ብለዋል ሚኒስትሩ እስራኤል ካትዝ።

ኢራን ምንም ዓይነት ሚሳኤል ወደ እስራኤል ካስወነጨፈች አፀፋው የማያወላዳ ይሆናል ያሉት ካትዝ በቀናት ውስጥ “ምናልባትም ነገ”ወደ ጦርነቱ ልንመለስ እንችላለን በሚል አሳስበዋል።

ከአሜሪካ ጋር እየተደራደረች ወደ እስራኤል ጥቃት የማድረስ ፍላጎት ኢራን አላት ብለዋል እስራኤል ካትዝ።

"ኢራን ጥቃት ካደረሰች፤ሶስተኛው የኢራን ጦርነት ይሆናል፤ነገሩ እጅግ ግልፅም ነው”በሚል አፅንዖት ሰጥተዋል።

እስራኤል ሚሳዔል ሲወነጨፍባት አደገኛ ምላሽ ሳትሰጥ አታልፈውም የሚል መረጃም ሚኒስትሩ አጋርተዋል።

በኢራን ላይ ያለማንም ደጋፊ  ፣ራሳችንን ችለን ጥቃት ለማድረስ እንዲሁም ሰማያዊ እና ነጭ ዘመቻ(ብሉ ኤንድ ዋይት) ኢራን ውስጥ ለማድረግ ጦሩ እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ ሰጥቻለሁ ብለዋል።

ብሉ ኤንድ ዋይት ዘመቻ በእስራኤል ጦርና ፖለቲከኞች ራስን ችሎ ማጥቃት የሚል ትርጓሜ ይሰጠዋል መባሉን ፎክስ ኒውስን ጠቅሰው ኤን ቢሲ ዘግቧል ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
17🥱9👍3🤔1🙏1🤣1😎1
ደረቅ ቼክ ምንድን ነዉሼርር
**
ቼክ ማለት ገንዘብን ተክቶ የሚያገለግል ተላላፊ የገንዘብ ሰነድ ነው፡፡ ቼክ ሊፈርም የሚችለው በአንድ ባንክ ውስጥ ተንቀሳቃሽ ሂሳብ ያለው ሰው ነው፡፡ድርጅት ከሆነ ደግሞ ፈራሚው በድርጅቱ ቼክ ላይ የመፈረም ስልጣን የተሰጠው መሆን አለበት፡፡

ቼክ ከመቀበላችሁ በፊት በቼኩ ላይ -የሚከፈለው የገንዘብ መጠን በአሀዝና በፊደል መፃፉን - የሚከፈለው ሰው ስም እና የባንኩ ቅርንጫፍ መፃፉን -ቼኩን የሰጠው ሰው ፊርማ መኖሩን -ቼኩ የተፃፈበት ቀን እና ቦታ መኖሩ ማረጋገጥ የግድ አስፈላጊ መሆኑን የንግድ ህግ አንቀፅ 827 ይደነግጋል።

ቼኩ ለማን እንደሚከፈል ስም ካልተጠቀሰበት ማንኛውም ቼኩን ይዞ የቀረበ ሰው ይከፈለዋል። ቼኩ በስሙ የተፃፈለት ሰው ወይም በትዕዛዝ የሚል ካለበት ደግሞ በቀላሉ ከጀርባው በመፈረም ለሌላ ሰው ሊያስተላልፈው ይችላል ።ያም ሰው በጀርባው ፈርሞ ለሌላ ሰው ማስተላለፍ ይችላል፡፡ -የገንዘብ መጠኑ ያልተጠቀሰበትን ቼክ ፈርሞ መስጠት አደገኛ ነው ፡፡ ቼኩ የተፃፈለት ወይም የተላለፈለት ሰው የፈለገውን ገንዘብ ሊሞላበት ይችላል፡፡

ቼኩ የሚከፈለው ለባንኩ ለክፍያ በቀረበ ቀን ነው። - ሆኖም ቼኩ በን/ሕ/ቁ 857 መሠረት የወጣበት ቀን ከግምት ሳይስገባ ቼኩ ላይ ከተፃፈው ቀን ጀምሮ በ6 ወር ውስጥ ለባንኩ ለክፍያ መቅረብ አለበት፡፡ -ቼኩን የሚፈርመው ሰው የክፍያውን ቀን ቼኩን ከፃፈበት ወይም ቼኩን ካወጣበት ቀን ወደፊት ወይም ወደ ኋላ ሊያደርገው ይችላል። ለምሳሌ ዛሬ ቼኩን ሲፅፍ የተፃፈበት ቀን ወደኃላ 7 ወር አድርጎ ቀኑን ቢፅፈው ለክፍያ መቅረብ ያለበት 6 ወር ጊዜ ስላለፈ ባንኩ መክፈልም ሆነ ያልከፈለበትን ምክንያት ለመግለፅ ሳይገደድ ቼኩ ለክፍያ መቅረብ ባለበት ጊዜ ባለመቅረቡ ብቻ ይመልሰዋል፡፡

ዛሬ የሚሰጥ ቼክ ወደፊት የዛሬ 4 ወር አድርጎ ቀኑ ከተፃፈበት ለክፍያ መቅረብ የሚችለው ከአራት ወራት በኃላ ካለው ቀን ጀምሮ ባለው 6 ወራት ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ ቼክ ተቀባዬች የሚሰጣቸውን ቼክ ገንዘቡን መቀበል ከሚችሉበት ቀን አንፃር በጥንቃቄ የተፃፈበት ቀን ማየት ያስፈልጋል ::

-ቼክ የሰጠው ሰው ቼኩ ለባንኩ ለክፍያ ከመቅረቡ በፊት ባንኩን እንዳትከፍል ብሎ መከልከል ይችላል። ባንኩም የክፍያ መከልከያ ትእዛዝ ከደረሰው መክፈል የለበትም። 

ቼኩን ለባንክ አቅርበህ በቼኩ ላይ የተጠቀሰውን ያህል በቂ ገንዘብ ከሌለ በሂሳቡ ውስጥ ያለውን ያህል መቀበል ይቻላል። ለቀረው ገንዘብ ደግሞ ባንኩ ‘‘በቂ ስንቅ ለውም’’ የሚል የፅሁፍ ማስረጃ ቼኩን ይዞ ለቀረበው ሰው ይሰጠዋል። -በተለምዶ ‘‘ደረቅ ቼክ’’ የሚባለው ለክፍያ ሲቀርብ በሂሳቡ ውስጥ በቂ ገንዘብ ከሌለው ሲሆን ባንኩ በሚሰጠው ማስረጃ መሰረት ቼክ ሰጪውን ወይም አውጭውን በወንጀል ያስጠይቃል። ሆን ተብሎ ከተፈፀመ ቼክ አውጪው በወንጀል ህግ አቀፅ 693 መሰረት በቀላል እስራት ወይም ነገሩ ከባድ ከሆነ ደግሞ ከአስር አመት በማይበልጥ ፅኑ እስርና በመቀጮ ይቀጣል።

ደረቅ ቼኩ የተሰጠው በቸልተኝነት ከሆነ ደግሞ ሰጭው በመቀጮ ወይም ከአንድ አመት በማይበልጥ ቀላል እስር ይቀጣል ፡፡ -ሳይከፈል የቀረውን የቼኩን ገንዘብ ና ወጭውን ቼኩ የተፃፈለት ወይም ተፈርሞ የተላለፈለት ሰው በፍትሀ ብሔር ከሶ ገንዘቡን ማስመለስ ይችላል፡፡ -በብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት ደረቅ ቼክ የሚሰጡ ሰዎች በጥፋታቸው በጥቁር መዝገብ ውስጥ የሚገቡ ሲሆን ከገንዘብ መቀጮ አንስቶ በቼክ ሂሳብ የማንቀሳቀስ መብታቸውን እስከማሳጣት ቅጣት ይጣልባቸዋል፡፡

ለግብይት ቅልጥፍና እንዲሁም ለገንዘብ እንቅስቃሴ አመቺነት በቼክ መጠቀሙ ከጥሬ ገንዘብ የተሻለ ዘመናዊ አሰራር በመሆኑ ቼክ አስፈላጊና ልንጠቀምበት የሚገባ የገንዘብ ሰነድ ነው። ለማንኛውም ቼክ ስንሰጥም ሆነ ስንቀበል ከላይ የተነሱትን ነጥቦች ልብ ልንል ይገባል።
Via- መላኩ ፍቃዱ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
12👍4🎉1
📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944

👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
 👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ

🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !

👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
2👍2
የጀነራል ጻድቃን ጥብቅ ወታደራዊ መረጃ!

ህወሓት ወደ መኸል ሀገር ሰብሮ ለመግባት ከውጭ ወደ ውስጥ በሱዳን በኩል በተለያዩ ግንባሮች ጥቃት ለመክፈት ሰፊ ወታደራዊ ስትራቴጂ መንደፉን ጀነራል ጻድቃን ገ/ተንሳኤ አጋልጠዋል፡፡

በወልቃይት ሲጠበቅ የነበረው የህወሓት ጥቃት፣ ባልተጠበቀበት ግንባር ሊፈነዳ እንደሚችል ጀነራሉ ተናግረዋል፡፡ ጀነራሉ በህወሓት ወታደራዊ ዝግጅት ላይ በሰጡት ማብራሪያ በአፋር እና አማራ አዋሳኝ አካባቢዎች ተደጋጋሚ ትንኮሳዎች የፈጸመው ህወሓት የትኩረት አቅጣጫውን ቀይሯል ብለዋል፡፡

በምራብ ኢትዮጵያ በኩል ጥቃት ከፍቶ ወደ ማኸል ሀገር ለመገስገስ አስቦ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ጀነራሉ ጠቁመዋል፡፡ ጀነራሉ በምራዕብ ኢትዮጵያ በኩል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በኩል ማለታቸው ነው፡፡

የህወሓት ጀነራሎች በአሁኑ ወቅት ሰፊ ወታደራዊ ስትራቴጂ ነድፈው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የገለጹት ጀነራሉ፣ በተለይ ከውጭ ወደ ውስጥ ለማጥቃት ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ ለዚህም ሱዳንን እንደ ዋና ወታደራዊ መንቀሳቀሻ እየተጠቀሙ መሆኑን ተጨባጫ መረጃዎችና እንቅስቃሴዎች መነራቸው ተናግረዋል፡፡

ሱዳን ውስጥ ለዓመታት የተደራጀው አርሚ 70 እንደ ቀጠናዊ ሚዛን ማስጠበቂያ ለመጠቀም እና ከውጭ ወደ ውስጥ ለማጥቃት ተጨማሪ ኃይል እያስገቡ ነው ብለዋል፡፡ በቅርቡ አርሚ 13 ወደ ሱዳን መሻገሩን ያረጋገጡት ጀነራሉ፣ ሌሎች ተጨማሪ አርሚዎችም ሊጨመሩ እንደሚችሉ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

አርሚ 13 ወደ ሱዳን ለመሻገር ሲንቀሳቀስ መንገድ ላይ ሁለት ጊዜ በድሮን ጥቃት ቢመታም፣ የተረፈው አርሚ 70ን ተቀላቅሏል ብለዋል፡፡ ሽራሮ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት በህወሓት ማረጋጫ የተሰጠበት ቢሆንም፣ ሱዳን ከገባ በኋላ ሸረሪና ላይ ተጨማሪ ደብደባ መፈጸሙን ጀነራሉ ገልጸዋል፡፡
Andafta

@Addis_Reporter
👍43🤣3🤔2😢1🤪1