📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
❤3👍2
የማስተርስ ትምህርት አራት አመት‼️
"የማስተርስ ትምህርት ወደ 4 ዓመት ሊያድግ ይገባል " ተባለ‼️
የአሰራር ለውጥ ካልተደረገ ወደፊት ለሚመረቁ ተማሪዎች እውቅና ለመስጠት ትልቅ ተግዳሮት ይፈጥራል ብሏል የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን
በኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚሰጠው የሁለተኛ ዲግሪ (የማስተርስ) ትምህርት ፕሮግራም ከሁለት ዓመት ወደ አራት ዓመት ሊያድግ እንደሚገባ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ ይህንን ያስታወቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት የ11 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሰጠው ሙያዊ ማብራሪያ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ በሁለት ዓመት መደበኛ መርሃ ግብር እየተሰጠ ያለው የማስተርስ ትምህርት፣ አዲስ ከጸደቀው የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ደንብና ከአለም አቀፍ በተለይም ከአውሮፓ ስታንዳርድ ጋር የማይገናኝ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ክፍተት በአስቸኳይ የማይስተካከል ከሆነ፣ ወደፊት ለሚመረቁ ተማሪዎች የትምህርት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ወይም እውቅና (Authentication) ለመስጠት ትልቅ ተግዳሮት እንደሚሆን ባለስልጣኑ አስገንዝቧል።
ከእነዚህም መካከል በሀገራችን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ሳያመጡ ወደ ውጭ ሀገር ሄደው ከተማሩ በኋላ፣ ወደ ሀገር ቤት ሲመለሱ የሚጠይቁት የብቃት ማረጋገጫ ጉዳይ ትልቅ አነጋጋሪ አጀንዳ ሆኗል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ2017 ዓ.ም ያጸደቀው የኢትዮጵያ የትምህርትና ስልጠና የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ደንብ፣ እውቅና ካላቸው የውጭ ሀገር የትምህርት ተቋማት የተገኙ የብቃት ማረጋገጫዎች በሀገሪቱ መመዘኛ መሰረት ተመዝነው እውቅና እንዲሰጣቸው ቢደነግግም፣ አሁን ያለው አሰራር ግን ይህንን ለመተግበር አስቸጋሪ አድርጎታል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እንዳመለከተው፣ ለአማራጭ የትምህርት ክሬዲት ስርአት (ECTS) በአውሮፓ (ከፍተኛ) የሆነው መስፈርት፣ በኢትዮጵያ ደንብ ውስጥ ' (ዝቅተኛ) ሆኖ ተቀምጧል። ይህንን ወደ ዓመት ሲተረጎም የማስተርስ ፕሮግራም ደንቡ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ የ4 ዓመት ፕሮግራም መሆን እንዳለበት ያስገድዳል።
ጉዳዩን በተመለከተ ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት እንዲሁም ለትምህርት ሚኒስቴር በደብዳቤ ቢገለጽም እስካሁን ምንም ምላሽ አልተገኘም ተብሏል፡፡
ኢትዮ ኤፍ ኤም
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
"የማስተርስ ትምህርት ወደ 4 ዓመት ሊያድግ ይገባል " ተባለ‼️
የአሰራር ለውጥ ካልተደረገ ወደፊት ለሚመረቁ ተማሪዎች እውቅና ለመስጠት ትልቅ ተግዳሮት ይፈጥራል ብሏል የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን
በኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚሰጠው የሁለተኛ ዲግሪ (የማስተርስ) ትምህርት ፕሮግራም ከሁለት ዓመት ወደ አራት ዓመት ሊያድግ እንደሚገባ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ ይህንን ያስታወቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት የ11 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሰጠው ሙያዊ ማብራሪያ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ በሁለት ዓመት መደበኛ መርሃ ግብር እየተሰጠ ያለው የማስተርስ ትምህርት፣ አዲስ ከጸደቀው የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ደንብና ከአለም አቀፍ በተለይም ከአውሮፓ ስታንዳርድ ጋር የማይገናኝ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ክፍተት በአስቸኳይ የማይስተካከል ከሆነ፣ ወደፊት ለሚመረቁ ተማሪዎች የትምህርት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ወይም እውቅና (Authentication) ለመስጠት ትልቅ ተግዳሮት እንደሚሆን ባለስልጣኑ አስገንዝቧል።
ከእነዚህም መካከል በሀገራችን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ሳያመጡ ወደ ውጭ ሀገር ሄደው ከተማሩ በኋላ፣ ወደ ሀገር ቤት ሲመለሱ የሚጠይቁት የብቃት ማረጋገጫ ጉዳይ ትልቅ አነጋጋሪ አጀንዳ ሆኗል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ2017 ዓ.ም ያጸደቀው የኢትዮጵያ የትምህርትና ስልጠና የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ደንብ፣ እውቅና ካላቸው የውጭ ሀገር የትምህርት ተቋማት የተገኙ የብቃት ማረጋገጫዎች በሀገሪቱ መመዘኛ መሰረት ተመዝነው እውቅና እንዲሰጣቸው ቢደነግግም፣ አሁን ያለው አሰራር ግን ይህንን ለመተግበር አስቸጋሪ አድርጎታል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እንዳመለከተው፣ ለአማራጭ የትምህርት ክሬዲት ስርአት (ECTS) በአውሮፓ (ከፍተኛ) የሆነው መስፈርት፣ በኢትዮጵያ ደንብ ውስጥ ' (ዝቅተኛ) ሆኖ ተቀምጧል። ይህንን ወደ ዓመት ሲተረጎም የማስተርስ ፕሮግራም ደንቡ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ የ4 ዓመት ፕሮግራም መሆን እንዳለበት ያስገድዳል።
ጉዳዩን በተመለከተ ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት እንዲሁም ለትምህርት ሚኒስቴር በደብዳቤ ቢገለጽም እስካሁን ምንም ምላሽ አልተገኘም ተብሏል፡፡
ኢትዮ ኤፍ ኤም
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡20❤14🥱3👍2👀2😢1
ጄኔራል ባጫ ደበሌ የአፍሪካ ህብረት የህወሓትን እርምጃ እንዲያወግዝ ጠየቁ
በቅርቡ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ ወደ ፕሬዝዳንትነት የተመለሱት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ አሳሳቢ የተባለ አዋጅ በመላ ክልሉ ማወጃቸው ይታወሳል። ይህንኑ አዋጅ መመልከታቸውን የገለጹት በናይሮቢ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጄኔራል ባጫ ደበሌ፤ “የክተት አዋጅ እና የግዳጅ ምልመላ” በሚል ርዕስ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ የአዋጁ ዋነኛ ዓላማ ሕዝቡን ለጠቅላላ ጦርነት መቀስቀስ እንደሆነ አመልክተዋል።
ከዚህ ጦርነት ቀስቃሽ እንቅስቃሴ በስተጀርባ የራስን ጦር እንደገና ማጠናከር እና ታጣቂዎችን እንደ "ቅጥረኛ ተዋጊ" ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን ግጭት መላክ የሚሉ ግቦች እንዳሉ የገለጹት ጄኔራል ባጫ፤ የአፍሪካ ህብረት ይህን የህወሓት ድርጊት በአደባባይ እንዲያወግዝ ጠይቀዋል።
በተጨማሪም ህብረቱ ይህ አዋጅ በአስቸኳይ እንዲሰረዝ፣ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመለስና የፖለቲካ ሂደቶች እንዲቀጥሉ ግፊት እንዲያደርግ አምባሳደሩ አሳስበዋል። ሊፈጠር የሚችለውን አላስፈላጊ ቀውስ ለመከላከልም የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በቅርቡ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ ወደ ፕሬዝዳንትነት የተመለሱት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ አሳሳቢ የተባለ አዋጅ በመላ ክልሉ ማወጃቸው ይታወሳል። ይህንኑ አዋጅ መመልከታቸውን የገለጹት በናይሮቢ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጄኔራል ባጫ ደበሌ፤ “የክተት አዋጅ እና የግዳጅ ምልመላ” በሚል ርዕስ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ የአዋጁ ዋነኛ ዓላማ ሕዝቡን ለጠቅላላ ጦርነት መቀስቀስ እንደሆነ አመልክተዋል።
ከዚህ ጦርነት ቀስቃሽ እንቅስቃሴ በስተጀርባ የራስን ጦር እንደገና ማጠናከር እና ታጣቂዎችን እንደ "ቅጥረኛ ተዋጊ" ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን ግጭት መላክ የሚሉ ግቦች እንዳሉ የገለጹት ጄኔራል ባጫ፤ የአፍሪካ ህብረት ይህን የህወሓት ድርጊት በአደባባይ እንዲያወግዝ ጠይቀዋል።
በተጨማሪም ህብረቱ ይህ አዋጅ በአስቸኳይ እንዲሰረዝ፣ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመለስና የፖለቲካ ሂደቶች እንዲቀጥሉ ግፊት እንዲያደርግ አምባሳደሩ አሳስበዋል። ሊፈጠር የሚችለውን አላስፈላጊ ቀውስ ለመከላከልም የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪20❤15🤣3👍2😎1
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እናት ወ/ሮ አዳነሽ በርሄ በ97 ዓመታቸው ማረፋቸውን የአገሪቱ ማስታወቂያ ሚኒስቴር አስታወቀ። ከኤርትራ ነጻነት አንስቶ ከ35 ዓመታት በላይ በብቸኝነት ኤርትራን እየመሩ ያሉት የ80 ዓመቱ አዛውንት ፕሬዝዳንት ኢሳያስ እናት ያረፉት ሰኞ ዕለት ነበር።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20😢11😱8🤣8👍3
በታዋቂው ፖለቲከኛ ጃዋር መሐመድ እና በሚዲያ ባለሙያው ግሩም ጫላ መካከል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ የሰላ የቃላት ምልልስ ተካሂዷል።
ይህ ውጥረት የጀመረው ግሩም ጫላ በፌስቡክ ገጹ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ለማድመቅ ያደረገውን ጥረት አድንቆ፣ ሆኖም በህንጻዎች ላይ የተተከሉት መብራቶች እየጠፉ ከተማዋ ወደ ጨለማ እየተመለሰች መሆኗን በመተቸት ባወጣው ጽሁፍ ነው። ግሩም በጽሁፉ ይህ ስራ ጊዜያዊ ሳይሆን ቋሚ እንዲሆን ክትትል ሊደረግበት እንደሚገባ አሳስቦ ነበር።
ይህንን የፌስቡክ ጽሁፍ ተከትሎ ጃዋር መሐመድ በኤክስ ገጹ ላይ የግሩምን ጽሁፍ በማያያዝ "ብልጭልጩ እየጨለመ ነው ይለናል ይህ ሞዴል ባለ ጊዜ" የሚል ፌዝ ያዘለ አስተያየት አስፍሯል።
ይህ የጃዋር አስተያየት ግሩምን ማስቆጣቱ አልቀረም። በግል የጽሁፍ መልዕክት ግሩም ለጃዋር "አንተ ለመላው የኦሮሞ ማህበረሰብ ውርደት ነህ... በሁሉም መንፈስ የተሸጥክ ነህ" የሚል ከባድ ስድብ እንደላከለት፣ ጃዋር ያጋራው የስክሪን ሾት ማስረጃ ያሳያል።
ለዚህ የግሩም መልዕክት ጃዋር መሐመድ በይፋዊ የኤክስ ገጹ ላይ ጠንካራ ምላሽ ሰጥቷል። ጃዋር በመልዕክቱ "ግሩም ጫላ፣ የኦሮሞን አርሶ አደሮች የሚያፈናቅሉ፣ መሬታቸውን የሚሰርቁ እና ያገኙትን ገንዘብ በቅንጦት መኪናዎች ላይ የሚያባክኑና በዚህም የሚመጻደቁ እንዳንተ ያሉ ሌቦችን ማጋለጤ 'የተሸጥክ' የሚያስብለኝ ከሆነ፣ ያንን ስያሜ በክብር እለብሰዋለሁ" ሲል አስታውቋል።
ይህ በሁለቱ ግለሰቦች መካከል የተፈጠረው መካረር በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ይህ ውጥረት የጀመረው ግሩም ጫላ በፌስቡክ ገጹ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ለማድመቅ ያደረገውን ጥረት አድንቆ፣ ሆኖም በህንጻዎች ላይ የተተከሉት መብራቶች እየጠፉ ከተማዋ ወደ ጨለማ እየተመለሰች መሆኗን በመተቸት ባወጣው ጽሁፍ ነው። ግሩም በጽሁፉ ይህ ስራ ጊዜያዊ ሳይሆን ቋሚ እንዲሆን ክትትል ሊደረግበት እንደሚገባ አሳስቦ ነበር።
ይህንን የፌስቡክ ጽሁፍ ተከትሎ ጃዋር መሐመድ በኤክስ ገጹ ላይ የግሩምን ጽሁፍ በማያያዝ "ብልጭልጩ እየጨለመ ነው ይለናል ይህ ሞዴል ባለ ጊዜ" የሚል ፌዝ ያዘለ አስተያየት አስፍሯል።
ይህ የጃዋር አስተያየት ግሩምን ማስቆጣቱ አልቀረም። በግል የጽሁፍ መልዕክት ግሩም ለጃዋር "አንተ ለመላው የኦሮሞ ማህበረሰብ ውርደት ነህ... በሁሉም መንፈስ የተሸጥክ ነህ" የሚል ከባድ ስድብ እንደላከለት፣ ጃዋር ያጋራው የስክሪን ሾት ማስረጃ ያሳያል።
ለዚህ የግሩም መልዕክት ጃዋር መሐመድ በይፋዊ የኤክስ ገጹ ላይ ጠንካራ ምላሽ ሰጥቷል። ጃዋር በመልዕክቱ "ግሩም ጫላ፣ የኦሮሞን አርሶ አደሮች የሚያፈናቅሉ፣ መሬታቸውን የሚሰርቁ እና ያገኙትን ገንዘብ በቅንጦት መኪናዎች ላይ የሚያባክኑና በዚህም የሚመጻደቁ እንዳንተ ያሉ ሌቦችን ማጋለጤ 'የተሸጥክ' የሚያስብለኝ ከሆነ፣ ያንን ስያሜ በክብር እለብሰዋለሁ" ሲል አስታውቋል።
ይህ በሁለቱ ግለሰቦች መካከል የተፈጠረው መካረር በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤25👍13🤣4👌3🕊2🤪2✍1🥱1🙊1
ከጅቡቲ የጫነውን ነዳጅ አፋር ላይ ሲቀሽብ የነበረው አሽከርካሪ እጅ ከፍንጅ ተያዘ
ከጅቡቲ የተጫነ ነዳጅን በሕ-ገወጥ መንገድ በመቀሸብ ላይ የነበረ የነዳጅ ጫኝ ተሸከርካሪ በአፋር ክልል የፀጥታ ሃይሎችና በንግድ ቢሮ በተደረገ ክትትል እጅ ከፍንጅ መያዙን የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል ።ወደ ተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ነዳጅን ለማሠራጨት የተጣለበትን ሃላፊነት ወደ ጎን በመተውና የግል ጥቅምን በማስቀደም ጅቡቲ የጫነውን ነዳጅ በሕ-ገወጥ መንገድ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ሲል የቀሸበው ግለሰብ መያዙን ባለስልጣኑ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ይፋ አድርጓል ።
ሃላፊነት በጎደላቸው ግለሰቦች የሚፈጸሙ መሠል ተግባራት በነዳጅ ስርጭት ላይ ከሚያደርሱት መስተጓጎል በተጨማሪ የቀሸቡትን ነዳጅ በሕገ-ወጦች በኩል በውድ ዋጋ በመሸጥ በህብረተሰቡ ላይ ጫናን ይፈጥራሉ።በመሆኑም ግለሰቦቹ ለነዳጅ ብክነትና ለአደጋ ተጋላጭነት የሚዳርግ ተግባርን በቸልተኝነት እየፈፀሙ መሆኑ ተነግራል፡፡
ይህን ጥፋት በሚፈፅሙ አካላት ላይ የሚደረገው ክትትልና የእርምት እርምጃ በፀጥታ አካላት፣በክልል ንግድ ቢሮዎችና በባለስልጣን መስሪያቤቱ በኩል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተቋሙ አሳስቧል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከጅቡቲ የተጫነ ነዳጅን በሕ-ገወጥ መንገድ በመቀሸብ ላይ የነበረ የነዳጅ ጫኝ ተሸከርካሪ በአፋር ክልል የፀጥታ ሃይሎችና በንግድ ቢሮ በተደረገ ክትትል እጅ ከፍንጅ መያዙን የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል ።ወደ ተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ነዳጅን ለማሠራጨት የተጣለበትን ሃላፊነት ወደ ጎን በመተውና የግል ጥቅምን በማስቀደም ጅቡቲ የጫነውን ነዳጅ በሕ-ገወጥ መንገድ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ሲል የቀሸበው ግለሰብ መያዙን ባለስልጣኑ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ይፋ አድርጓል ።
ሃላፊነት በጎደላቸው ግለሰቦች የሚፈጸሙ መሠል ተግባራት በነዳጅ ስርጭት ላይ ከሚያደርሱት መስተጓጎል በተጨማሪ የቀሸቡትን ነዳጅ በሕገ-ወጦች በኩል በውድ ዋጋ በመሸጥ በህብረተሰቡ ላይ ጫናን ይፈጥራሉ።በመሆኑም ግለሰቦቹ ለነዳጅ ብክነትና ለአደጋ ተጋላጭነት የሚዳርግ ተግባርን በቸልተኝነት እየፈፀሙ መሆኑ ተነግራል፡፡
ይህን ጥፋት በሚፈፅሙ አካላት ላይ የሚደረገው ክትትልና የእርምት እርምጃ በፀጥታ አካላት፣በክልል ንግድ ቢሮዎችና በባለስልጣን መስሪያቤቱ በኩል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተቋሙ አሳስቧል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤18👍8👌1
እስከ አምስት ዓመት እስራት የሚያስቀጡ ጥፋቶች የተካተቱበት አዲሱ የመረጃ ነጻነት አዋጅ በፓርላማ ጸደቀ
ለ15 ዓመታት በስራ ላይ ከቆየው “የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት አዋጅ” የመገናኛ ብዙኃንን የሚመለከተው ክፍል ተለይቶ ሌላ ራሱን የቻለ ህግ እንዲወጣለት የተደረገው በ2013 ዓ.ም ነበር።
የመረጃ ነጻነትን የሚመለከተው ቀሪው ክፍል በተመሳሳይ መልኩ አዋጅ ቢዘጋጅለትም፤ ለፓርላማ የሚቀርብበት ሂደት ተጓትቶ ቆይቷል።
ከዓመታት ጥበቃ በኋላ የመረጃ ነጻነትን ለመደንገግ የተዘጋጀው የአዋጅ ረቂቅ፤ ከሁለት ወራት በፊት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲቀርብ ተደርጓል።
ምክር ቤቱ መጋቢት 29፤ 2018 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የቀረበለትን ይህን የአዋጅ ረቂቅ፤ በዝርዝር እንዲታይ ለፓርላማው የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶት ነበር።
ቋሚ ኮሚቴው የአዋጅ ረቂቁን ለፓርላማ ለተወካዮች ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም እንዲሁም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር አምስት የሚደርሱ ውይይቶችን ካደረገ በኋላ የውሳኔ ሃሳብ አዘጋጅቷል።
በረቂቅ አዋጁ ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎችን እና አዳዲስ ድንጋጌዎችን ያካተተው የውሳኔ ሃሳብ፤ ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 18፤ 2018 በተካሄደ የፓርላማ ስብሰባ ላይ ከቀረበ በኋላ አዋጁ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል።
በረቂቅ አዋጁ ላይ የተደረጉት ማሻሻያዎች፤ በመግቢያው ላይ ከተቀመጠው የአዋጁን ዓላማዎች ከሚያብራራው ክፍል ጀምሮ “ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች” እስከተዘረዘሩበት ድረስ ያሉትን የሸፈኑ ናቸው።
ከእነዚህ ማሻሻያዎች መካከል ከመረጃ አሰጣጥ ጋር የተያያዙ እስከ አምስት እስራት የሚያስቀጡ የጥፋት አይነቶች ይገኙበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ለ15 ዓመታት በስራ ላይ ከቆየው “የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት አዋጅ” የመገናኛ ብዙኃንን የሚመለከተው ክፍል ተለይቶ ሌላ ራሱን የቻለ ህግ እንዲወጣለት የተደረገው በ2013 ዓ.ም ነበር።
የመረጃ ነጻነትን የሚመለከተው ቀሪው ክፍል በተመሳሳይ መልኩ አዋጅ ቢዘጋጅለትም፤ ለፓርላማ የሚቀርብበት ሂደት ተጓትቶ ቆይቷል።
ከዓመታት ጥበቃ በኋላ የመረጃ ነጻነትን ለመደንገግ የተዘጋጀው የአዋጅ ረቂቅ፤ ከሁለት ወራት በፊት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲቀርብ ተደርጓል።
ምክር ቤቱ መጋቢት 29፤ 2018 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የቀረበለትን ይህን የአዋጅ ረቂቅ፤ በዝርዝር እንዲታይ ለፓርላማው የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶት ነበር።
ቋሚ ኮሚቴው የአዋጅ ረቂቁን ለፓርላማ ለተወካዮች ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም እንዲሁም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር አምስት የሚደርሱ ውይይቶችን ካደረገ በኋላ የውሳኔ ሃሳብ አዘጋጅቷል።
በረቂቅ አዋጁ ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎችን እና አዳዲስ ድንጋጌዎችን ያካተተው የውሳኔ ሃሳብ፤ ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 18፤ 2018 በተካሄደ የፓርላማ ስብሰባ ላይ ከቀረበ በኋላ አዋጁ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል።
በረቂቅ አዋጁ ላይ የተደረጉት ማሻሻያዎች፤ በመግቢያው ላይ ከተቀመጠው የአዋጁን ዓላማዎች ከሚያብራራው ክፍል ጀምሮ “ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች” እስከተዘረዘሩበት ድረስ ያሉትን የሸፈኑ ናቸው።
ከእነዚህ ማሻሻያዎች መካከል ከመረጃ አሰጣጥ ጋር የተያያዙ እስከ አምስት እስራት የሚያስቀጡ የጥፋት አይነቶች ይገኙበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍3🤣2😡2🤪1
የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በበጀት ዓመቱ ካቀደው የገቢ እቅድ ማሳካት የቻለው 37 በመቶውን ብቻ መሆኑ ተገለፀ
የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሊገባደድ በተቃረበው በጀት ዓመት ለመሰብሰብ ካቀደው 45 ቢሊየን ብር ውስጥ ማሳካት የቻለው 16.6 ቢሊየን ብር ወይም 37 በመቶውን ብቻ መሆኑን አስታወቀ፡፡
ቢሮው በከፍተኛ አመራሮቹ ባካሄደው የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ እንደገለጸው፣ በበጀት ዓመቱ የገቢ አሰባሰብን ጨምሮ ዝቅተኛ አፈፃፀም የተመዘገበባቸውን ተግባራት ለማካካስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል፡፡
በዚህም መሠረት የቀሩትን ተግባራት ለማከናወንና የተቀመጠውን የገቢ ግብ ለማሳካት የሚያስችል የዘጠና ቀን እቅድ ተነድፎ ወደ ተግባር ተገብቷል፡፡
ይህ የዘጠና ቀናት የማካካሻ እቅድ እስከ ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን፣ ከመሬት ሊዝ ጨረታ፣ ከአገልግሎት ለውጥ፣ ከመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት፣ እንዲሁም በምደባ ከሚተላለፉ ቦታዎች የሚገኝ የሊዝ ቅድመ ክፍያን ጨምሮ ከ17.34 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሊገባደድ በተቃረበው በጀት ዓመት ለመሰብሰብ ካቀደው 45 ቢሊየን ብር ውስጥ ማሳካት የቻለው 16.6 ቢሊየን ብር ወይም 37 በመቶውን ብቻ መሆኑን አስታወቀ፡፡
ቢሮው በከፍተኛ አመራሮቹ ባካሄደው የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ እንደገለጸው፣ በበጀት ዓመቱ የገቢ አሰባሰብን ጨምሮ ዝቅተኛ አፈፃፀም የተመዘገበባቸውን ተግባራት ለማካካስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል፡፡
በዚህም መሠረት የቀሩትን ተግባራት ለማከናወንና የተቀመጠውን የገቢ ግብ ለማሳካት የሚያስችል የዘጠና ቀን እቅድ ተነድፎ ወደ ተግባር ተገብቷል፡፡
ይህ የዘጠና ቀናት የማካካሻ እቅድ እስከ ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን፣ ከመሬት ሊዝ ጨረታ፣ ከአገልግሎት ለውጥ፣ ከመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት፣ እንዲሁም በምደባ ከሚተላለፉ ቦታዎች የሚገኝ የሊዝ ቅድመ ክፍያን ጨምሮ ከ17.34 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍2🤪2🤣1
ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ቀን ሰራተኞች‼️
በኮንስትራክሽን ዘርፍ ለቀን ሠራተኞች የብቃት ማረጋገጫ አስገዳጅ ሊሆን ነው
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በኮንስትራክሽን ዘርፍ እየታየ ያለውን የጥራትና የደህንነት ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል አዲስ መመሪያ በማዘጋጀት ላይ መሆኑን አስታውቋል።
ይህ አዲስ መመሪያ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ባለሙያዎችን ብቻ ሳይሆን፣ ዕለት ተዕለት የሚሰሩ የቀን ሠራተኞችንም የብቃት ደረጃ ማረጋገጥን ግዴታ የሚያደርግ ነው። ሚኒስቴሩ በዘርፉ የተሻለ ጥራትና ደህንነትን ለማስፈን እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጿል።
እንደ አዲሱ መመሪያ ዝርዝር ሁኔታ፡-
📌በየትኛውም የግንባታ ቦታ ላይ ለመስራት የሚፈልጉ ባለሙያዎች እና የቀን ሠራተኞች የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት መያዝ ግዴታ ይሆናል።
📌ሕጋዊ የሰርተፊኬሽን ሥርዓት ያላሟላ እና ብቃቱ ያልተረጋገጠ ማንኛውም ባለሙያ ወይም ሠራተኛ በኮንስትራክሽን ሥራ ላይ እንዳይሳተፍ ሙሉ በሙሉ ይከለከላል።
📌መመሪያው ሙሉ በሙሉ ሕግ ሆኖ ወደ መሬት ወርዶ ተግባራዊ እስኪሆን ድረስ የተወሰኑ ዓመታት ሊወስድ ይችላል።
📌 በአሁኑ ወቅት ግን የዚህ አሠራር የቅድመ ዝግጅት እና የሙከራ እንቅስቃሴዎች በይፋ መጀመራቸው ተገልጿል።
የዚህ አሠራር ዋና ዓላማ የግንባታ ሥራዎችን ጥራትና የሥራ ደህንነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ማሻሻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በኮንስትራክሽን ዘርፍ ለቀን ሠራተኞች የብቃት ማረጋገጫ አስገዳጅ ሊሆን ነው
👉ይህ መመሪያ በሰራተኛች ብቃት ማነስ ምክንያት በንብረት እና በግንባት ጥራት ላይ የሚደርስን ችግር ለመቀነስ ነው ተብሏል።
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በኮንስትራክሽን ዘርፍ እየታየ ያለውን የጥራትና የደህንነት ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል አዲስ መመሪያ በማዘጋጀት ላይ መሆኑን አስታውቋል።
ይህ አዲስ መመሪያ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ባለሙያዎችን ብቻ ሳይሆን፣ ዕለት ተዕለት የሚሰሩ የቀን ሠራተኞችንም የብቃት ደረጃ ማረጋገጥን ግዴታ የሚያደርግ ነው። ሚኒስቴሩ በዘርፉ የተሻለ ጥራትና ደህንነትን ለማስፈን እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጿል።
እንደ አዲሱ መመሪያ ዝርዝር ሁኔታ፡-
📌በየትኛውም የግንባታ ቦታ ላይ ለመስራት የሚፈልጉ ባለሙያዎች እና የቀን ሠራተኞች የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት መያዝ ግዴታ ይሆናል።
📌ሕጋዊ የሰርተፊኬሽን ሥርዓት ያላሟላ እና ብቃቱ ያልተረጋገጠ ማንኛውም ባለሙያ ወይም ሠራተኛ በኮንስትራክሽን ሥራ ላይ እንዳይሳተፍ ሙሉ በሙሉ ይከለከላል።
📌መመሪያው ሙሉ በሙሉ ሕግ ሆኖ ወደ መሬት ወርዶ ተግባራዊ እስኪሆን ድረስ የተወሰኑ ዓመታት ሊወስድ ይችላል።
📌 በአሁኑ ወቅት ግን የዚህ አሠራር የቅድመ ዝግጅት እና የሙከራ እንቅስቃሴዎች በይፋ መጀመራቸው ተገልጿል።
የዚህ አሠራር ዋና ዓላማ የግንባታ ሥራዎችን ጥራትና የሥራ ደህንነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ማሻሻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12🙊9👍3👌1
‹‹በ4 አቅጣጫ የከበበንን ጠላት ብቻውን አስቀርተንዋል›› ጀነራል ጆን መዲድ
የሕወሓት ጀነራሎች እና ወታደራዊ መኮንኖች የሚያሰሙት ዛቻ እና ፉክራ ቀጥሏል፡፡ የትግራይ ሕዝብ ለጦርነት ድቤ ድለቃቸው ጆሮውን ቢነፍጋቸውም በግድ በጦር ሜዳ ሊማግዱት በየአደባባዩ የ‹እናሸንፋለን› ፉከራ እያሰሙ ነው፡፡
ከትግራይ ጦር አዛዦች መሀል አንዱ የሆኑት ጀነራል ዩሀንስ ወልደጊዮርጊስ (ጆን መዲድ) በዎይን ሚዲያ በኩል የተለመደ ክስ እና የእናሸንፋለን ፉከራ አሰምቷል፡፡ ጀነራሉ፣ ‹‹በአራት አቅጣጫ የከበበንን ጠላት አሰላለፍ በጣጥሰን፣ ብልጽግናን ብቻውን አስቀርተንዋል›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ትናንት ተባብረው የዘመቱብንን ኃይሎችን በታትንን፣ በቀጠናው አዲስ አሰላለፍ ፈጥረናል የሚሉት የጦር አዛዡ፤ አልተቋጨም ያሉትን ህልውና ለማረጋገጥ እየተዘጋጀን ነው ብለዋል፡፡“ጠላቶቻችን ብዙ ነገር እያሰቡ ነው፤ ብዙ ነገር ደግሞ ይፈርስባቸዋል” ሲሉም አክለዋል፡፡
ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ አዲስ የኃይል አሰላለፍ እንዲፈጠር አድርገናል የሚሉት ጀነራሉ፤ ‹‹በ2013 ከጎረቤት ሀገራት እሰከ ሀገር ውስጥ ኃይሎች አስተባብሮ የዘመተብንን ጠላት ብቻውን አስቀርተን፣ የራሳችን አሰላለፍ ፈጥረናል›› ብለዋል፡፡ “በዚያን ጊዜ ተፈጥሮ የነበረውን እኛን የማጥፋት አሰላለፍ በትነን፣ ከሀገር ውስጥ እና በምስራቅ አፍሪካ አዳዲስ የአሰላለፍ ለውጦች መፍጠር ችለናል›› ነው ያሉት። ጆን መዲድ አዲስ አሰላለፍ ፈጥረናል የሚሉት ጽምዶን ነው፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሕወሓት ጀነራሎች እና ወታደራዊ መኮንኖች የሚያሰሙት ዛቻ እና ፉክራ ቀጥሏል፡፡ የትግራይ ሕዝብ ለጦርነት ድቤ ድለቃቸው ጆሮውን ቢነፍጋቸውም በግድ በጦር ሜዳ ሊማግዱት በየአደባባዩ የ‹እናሸንፋለን› ፉከራ እያሰሙ ነው፡፡
ከትግራይ ጦር አዛዦች መሀል አንዱ የሆኑት ጀነራል ዩሀንስ ወልደጊዮርጊስ (ጆን መዲድ) በዎይን ሚዲያ በኩል የተለመደ ክስ እና የእናሸንፋለን ፉከራ አሰምቷል፡፡ ጀነራሉ፣ ‹‹በአራት አቅጣጫ የከበበንን ጠላት አሰላለፍ በጣጥሰን፣ ብልጽግናን ብቻውን አስቀርተንዋል›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ትናንት ተባብረው የዘመቱብንን ኃይሎችን በታትንን፣ በቀጠናው አዲስ አሰላለፍ ፈጥረናል የሚሉት የጦር አዛዡ፤ አልተቋጨም ያሉትን ህልውና ለማረጋገጥ እየተዘጋጀን ነው ብለዋል፡፡“ጠላቶቻችን ብዙ ነገር እያሰቡ ነው፤ ብዙ ነገር ደግሞ ይፈርስባቸዋል” ሲሉም አክለዋል፡፡
ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ አዲስ የኃይል አሰላለፍ እንዲፈጠር አድርገናል የሚሉት ጀነራሉ፤ ‹‹በ2013 ከጎረቤት ሀገራት እሰከ ሀገር ውስጥ ኃይሎች አስተባብሮ የዘመተብንን ጠላት ብቻውን አስቀርተን፣ የራሳችን አሰላለፍ ፈጥረናል›› ብለዋል፡፡ “በዚያን ጊዜ ተፈጥሮ የነበረውን እኛን የማጥፋት አሰላለፍ በትነን፣ ከሀገር ውስጥ እና በምስራቅ አፍሪካ አዳዲስ የአሰላለፍ ለውጦች መፍጠር ችለናል›› ነው ያሉት። ጆን መዲድ አዲስ አሰላለፍ ፈጥረናል የሚሉት ጽምዶን ነው፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19🤣6👍2🤔2😎2🤯1😢1
የማስታወቂያ ግብዣ
የተከበራችሁ ቤተሰቦች ከ36,000 በላይ ተከታይ ባለው እና በደቂቃዎች ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝ ባለው በዚህ የቴሌግራም ቻናል ላይ ምርትና አገልግሎታችሁን ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንድታስተዋውቁ በአክብሮት ተጋብዛችኋል‼
✔Youtube ቻናል …
✔የትምህርት ተቋማት…...
✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…...
✔የትራንስፖርት አገልግሎት…....
✔ኤጀንሲዎች……
✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች......
✔ሌሎችም የምትሰጧቸውን አገልግሎቶች.....ማስተዋወቅ የምትፈልጉ በዚህ በኩል ኑ 👇
መልዕክት መቀበያ:—@Addis_reporter_bot
የተከበራችሁ ቤተሰቦች ከ36,000 በላይ ተከታይ ባለው እና በደቂቃዎች ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝ ባለው በዚህ የቴሌግራም ቻናል ላይ ምርትና አገልግሎታችሁን ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንድታስተዋውቁ በአክብሮት ተጋብዛችኋል‼
✔Youtube ቻናል …
✔የትምህርት ተቋማት…...
✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…...
✔የትራንስፖርት አገልግሎት…....
✔ኤጀንሲዎች……
✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች......
✔ሌሎችም የምትሰጧቸውን አገልግሎቶች.....ማስተዋወቅ የምትፈልጉ በዚህ በኩል ኑ 👇
መልዕክት መቀበያ:—@Addis_reporter_bot
❤4👍2
ጋናዊዉ ጠንቋይ ፖርቱጋል የዘንድሮዉን የአለምዋንጫ ታሸንፋለች አለ
ጋናዊዉ ጠንቋይ ናና ክዋኩ ቦንሳም ፖርቱጋል የዘንድሮዉን የአለምዋንጫ እንደምታሸንፍ ተናግሯል። "ይህ የአለምዋንጫ የፖርቱጋል እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ ነዉ። ያሸንፋሉ" ሲል ተንብዮአል።
ይህ ጠንቋይ ከሰሞኑ ሀገሩ ጋና ከእንግሊዝ ጋር በነበራት ጨዋታ ሃሪ ኬን ጋና ላይ ግብ እንዳያስቆጥር እረግሜዋለሁ ብሎ ፤ እንግሊዛዊዉ አጥቂም ግብ ሳያስቆጥር ወጥቶ ነበር። ከዚህ ጨዋታ በኋላ ጋናዊዉ ጠንቋይ የአለማቀፍ ሚዲያዎችን ትኩረት ስቦ ቆይቷል።
ይህ ጠንቋይ በፈረንጆቹ 2014 ክርስቲያኖ ሮናልዶን እረግሞት ነበር። በወቅቱ በነበረዉ የአለምዋንጫ ወቅትም ሮናልዶ በጉዳት ነበር የተጫወተው ይባላል። ጠንቋዩም በእኔ እርግማን ነዉ ተጨዋቹ የተጎዳዉ ብሎ ነበር።
አሁን ደግሞ የዘንድሮዉን የአለምዋንጫ ፖርቱጋል ታሸንፋለች ብሏል። ይህ ጠንቋይ በአካን ቋንቋ የስሙ ትርጓሜ "የእሮቡ ሠይጣን" እንደማለት ነዉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ጋናዊዉ ጠንቋይ ናና ክዋኩ ቦንሳም ፖርቱጋል የዘንድሮዉን የአለምዋንጫ እንደምታሸንፍ ተናግሯል። "ይህ የአለምዋንጫ የፖርቱጋል እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ ነዉ። ያሸንፋሉ" ሲል ተንብዮአል።
ይህ ጠንቋይ ከሰሞኑ ሀገሩ ጋና ከእንግሊዝ ጋር በነበራት ጨዋታ ሃሪ ኬን ጋና ላይ ግብ እንዳያስቆጥር እረግሜዋለሁ ብሎ ፤ እንግሊዛዊዉ አጥቂም ግብ ሳያስቆጥር ወጥቶ ነበር። ከዚህ ጨዋታ በኋላ ጋናዊዉ ጠንቋይ የአለማቀፍ ሚዲያዎችን ትኩረት ስቦ ቆይቷል።
ይህ ጠንቋይ በፈረንጆቹ 2014 ክርስቲያኖ ሮናልዶን እረግሞት ነበር። በወቅቱ በነበረዉ የአለምዋንጫ ወቅትም ሮናልዶ በጉዳት ነበር የተጫወተው ይባላል። ጠንቋዩም በእኔ እርግማን ነዉ ተጨዋቹ የተጎዳዉ ብሎ ነበር።
አሁን ደግሞ የዘንድሮዉን የአለምዋንጫ ፖርቱጋል ታሸንፋለች ብሏል። ይህ ጠንቋይ በአካን ቋንቋ የስሙ ትርጓሜ "የእሮቡ ሠይጣን" እንደማለት ነዉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣45❤20👍4👌1😎1
ጋዜጠኛ ሣህለገብርኤል ይትባረክ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
ሰኔ 19/2018 ዓ.ም
ከጋዜጠኝነት ሙያው በተጨማሪ በማረሚያ ፖሊስ አባልነት እስከ ረዳት ኢንስፔክተርነት ማዕረግ የደረሰው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል፣ ሕይወቱ እስካለፈበት ዕለት ድረስ በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ክፍል የሚዲያ ማስተባበሪያ ኃላፊ በመሆን እያገለገለ ነበር።
በ18 ዓመቱ የማረሚያ ፖሊስን የተቀላቀለው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል ይትባረክ፣ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበር።
በጋዜጠኛ ሣህለገብርኤል ይትባረክ ሕልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለፅን፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹ እና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛል።
የአብሥራ ተፈራ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ሰኔ 19/2018 ዓ.ም
ከጋዜጠኝነት ሙያው በተጨማሪ በማረሚያ ፖሊስ አባልነት እስከ ረዳት ኢንስፔክተርነት ማዕረግ የደረሰው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል፣ ሕይወቱ እስካለፈበት ዕለት ድረስ በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ክፍል የሚዲያ ማስተባበሪያ ኃላፊ በመሆን እያገለገለ ነበር።
በ18 ዓመቱ የማረሚያ ፖሊስን የተቀላቀለው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል ይትባረክ፣ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበር።
በጋዜጠኛ ሣህለገብርኤል ይትባረክ ሕልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለፅን፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹ እና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛል።
የአብሥራ ተፈራ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢24❤10👍6💔5
📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
👍2
በሳውዲ አረቢያ በ12 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ፍርድ ተፈጸመ ፤ ሌሎች 63 ዜጎችም በሞት ስጋት ላይ ይገኛሉ።
በሳውዲ አረቢያ በያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት 2026 የመጀመሪያዎቹ ወራት ብቻ 12 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ፍርድ መፈጸሙ ተገለጸ። እንደ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ገለጻ፣ በደቡብ ምዕራብ ሳውዲ አረቢያ በሚገኘው ከሚስ ሙሻይት ማቆያ ማዕከል ውስጥ በአንድ ክፍል ብቻ የታሰሩ 63 ኢትዮጵያውያን ከዕፅ ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ብቻ በማንኛውም ሰዓት የሞት ፍርድ ሊፈጸምባቸው እንደሚችል በከፍተኛ ስጋት ገልጿል።
ሳውዲ አረቢያ በዘንድሮው ዓመት ብቻ የሞት ፍርድ የፈጸመችባቸው ሰዎች ቁጥር 100 መድረሳቸው የተረጋገጠ ሲሆን በሳውዲ ባለሥልጣናት የሞት ፍርድ ከተፈጸመባቸው 100 ሰዎች መካከል 12ቱ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 48 ሳውዲውያን፣ 7 ፓኪስታናውያን፣ 6 ሱዳናውያን፣ 4 የመናውያን እና 4 ሶርያውያን መሆናቸውን የፈረንሳይ የዜና አገልግሎት ከመንግሥት መግለጫዎች በመነሳት ዘግቧል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ፣ በሳውዲ አረቢያ የሞት ቅጣት አፈጻጸም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን "አስፈሪ ምዕራፍ" ሲል የገለጸው ሲሆን፣ በተለይም የውጭ ሀገር ዜጎች ያልተገባ የፍርድ ሂደት ሰለባ እየሆኑ መሆናቸውን አጋልጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሳውዲ አረቢያ በያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት 2026 የመጀመሪያዎቹ ወራት ብቻ 12 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ፍርድ መፈጸሙ ተገለጸ። እንደ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ገለጻ፣ በደቡብ ምዕራብ ሳውዲ አረቢያ በሚገኘው ከሚስ ሙሻይት ማቆያ ማዕከል ውስጥ በአንድ ክፍል ብቻ የታሰሩ 63 ኢትዮጵያውያን ከዕፅ ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ብቻ በማንኛውም ሰዓት የሞት ፍርድ ሊፈጸምባቸው እንደሚችል በከፍተኛ ስጋት ገልጿል።
ሳውዲ አረቢያ በዘንድሮው ዓመት ብቻ የሞት ፍርድ የፈጸመችባቸው ሰዎች ቁጥር 100 መድረሳቸው የተረጋገጠ ሲሆን በሳውዲ ባለሥልጣናት የሞት ፍርድ ከተፈጸመባቸው 100 ሰዎች መካከል 12ቱ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 48 ሳውዲውያን፣ 7 ፓኪስታናውያን፣ 6 ሱዳናውያን፣ 4 የመናውያን እና 4 ሶርያውያን መሆናቸውን የፈረንሳይ የዜና አገልግሎት ከመንግሥት መግለጫዎች በመነሳት ዘግቧል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ፣ በሳውዲ አረቢያ የሞት ቅጣት አፈጻጸም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን "አስፈሪ ምዕራፍ" ሲል የገለጸው ሲሆን፣ በተለይም የውጭ ሀገር ዜጎች ያልተገባ የፍርድ ሂደት ሰለባ እየሆኑ መሆናቸውን አጋልጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
💔20❤11👍4😢3
ብሪክስ ሀገራት ያቋቋሙት የልማት ባንክን፤ ኢትዮጵያ በአባልነት እንድትቀላቀል የሚያስችላት የማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመራ።
ረቂቅ አዋጁ በፓርላማ ጸድቆ ለባንኩ የገዢዎች ቦርድ ሲገባ፤ ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ እና አልጄሪያ በመቀጠል አራተኛዋ አፍሪካዊት የልማት ባንኩ አባል አገር ትሆናለች።ዋና መስሪያ ቤቱን በቻይና ሻንጋይ ከተማ ያደረገው የብሪክስ የልማት ባንክ፤ “ኒው ዴቬሎፕመንት ባንክ” በሚል ስያሜ የሚጠራ ነው።
ይህንን ባንክ ኢትዮጵያ በአባልነት መቀላቀሏ “ለሀገራዊ የልማት ፋይናንስ፣ ለመሰረተ ልማት ድጋፍ እና ለማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት አማራጭ የገንዘብ ምንጮችን ለማግኘት” ያስችላታል ተብሎ እንደታመነበት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።በቀድሞዋ የብራዚል ፕሬዝዳንት ዲልማ ሮዜፍ የሚመራው “ኒው ዴቬሎፕመንት ባንክ” ባንክ፤ “ታዳጊ ሀገራት ለሚያከናውኗቸው የመሰረተ ልማት እና የዘላቂ ልማት ዕቅዶች” የሚውል ገንዘብ ለማሰባሰብ የተቋቋመ ነው።
በ100 ቢሊዮን ዶላር የተፈቀደ እና በ52.7 ቢሊዮን ዶላር የተከፈለ ካፒታል የተቋቋመው ይኸው ባንክ፤ ከሻንጋይ በተጨማሪ በብራዚሏ ሳኦ ፖሎ እና በህንድ ጉጅራት ከተሞች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች አሉት።
ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የባንኩ መስራች አባላት ሲሆኑ፤ ባንግላዴሽ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ ግብጽ፣ አልጄሪያ እና ኡዝቤኪስታን ባለፉት አምስት ዓመታት ባንኩን በአባልነት ተቀላቅለዋል።የ“ኒው ዴቬሎፕመንት ባንክ” የገዢዎች ቦርድ ኢትዮጵያን በዕጩ አባልነት የተቀበለው በጥቅምት 2015 ዓ.ም. ነበር።
Via Ethiopia Insider
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ረቂቅ አዋጁ በፓርላማ ጸድቆ ለባንኩ የገዢዎች ቦርድ ሲገባ፤ ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ እና አልጄሪያ በመቀጠል አራተኛዋ አፍሪካዊት የልማት ባንኩ አባል አገር ትሆናለች።ዋና መስሪያ ቤቱን በቻይና ሻንጋይ ከተማ ያደረገው የብሪክስ የልማት ባንክ፤ “ኒው ዴቬሎፕመንት ባንክ” በሚል ስያሜ የሚጠራ ነው።
ይህንን ባንክ ኢትዮጵያ በአባልነት መቀላቀሏ “ለሀገራዊ የልማት ፋይናንስ፣ ለመሰረተ ልማት ድጋፍ እና ለማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት አማራጭ የገንዘብ ምንጮችን ለማግኘት” ያስችላታል ተብሎ እንደታመነበት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።በቀድሞዋ የብራዚል ፕሬዝዳንት ዲልማ ሮዜፍ የሚመራው “ኒው ዴቬሎፕመንት ባንክ” ባንክ፤ “ታዳጊ ሀገራት ለሚያከናውኗቸው የመሰረተ ልማት እና የዘላቂ ልማት ዕቅዶች” የሚውል ገንዘብ ለማሰባሰብ የተቋቋመ ነው።
በ100 ቢሊዮን ዶላር የተፈቀደ እና በ52.7 ቢሊዮን ዶላር የተከፈለ ካፒታል የተቋቋመው ይኸው ባንክ፤ ከሻንጋይ በተጨማሪ በብራዚሏ ሳኦ ፖሎ እና በህንድ ጉጅራት ከተሞች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች አሉት።
ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የባንኩ መስራች አባላት ሲሆኑ፤ ባንግላዴሽ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ ግብጽ፣ አልጄሪያ እና ኡዝቤኪስታን ባለፉት አምስት ዓመታት ባንኩን በአባልነት ተቀላቅለዋል።የ“ኒው ዴቬሎፕመንት ባንክ” የገዢዎች ቦርድ ኢትዮጵያን በዕጩ አባልነት የተቀበለው በጥቅምት 2015 ዓ.ም. ነበር።
Via Ethiopia Insider
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤6👍4
የቤት ኪራይ በተመን ሊወሰን ነው‼️
ከ2019 ጀምሮ የቤት ኪራይ ዋጋ በአዲስ መተመኛ ሊወሰን ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን ፍትሃዊ፣ ሳይንሳዊና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ለመወሰን የተዘጋጀ የዋጋ መተመኛ ጥናት ዛሬ ቀርቦ በባለድርሻ አካላት ፊት ውይይት ተካሂዷል።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደ ጊዮርጊስ እንደገለጹት፣ ከተማ አስተዳደሩ የኑሮ ጫናን ለመቀነስ እና በቤት ኪራይ ገበያ ውስጥ የተስፋፉ ሕገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን ለመግታት በተከታታይ እየሰራ ነው።
እንደ ኃላፊዋ ገለጻ፣ በ2016 ዓ.ም. የተከናወነው ሰፊ የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባ በዘርፉ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፣ አሁን የቀረበው የኪራይ ዋጋ መተመኛ ጥናትም የውል ማደስ ሂደትን ፍትሃዊና ግልጽ ለማድረግ ያግዛል።
ጥናቱ የአከራዮችን ተገቢ ገቢ ከወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ጋር በማጣጣም የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ተከራዮችም ከገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ እንዲከፍሉ እና የተረጋጋ የኢኮኖሚ ኑሮ እንዲመሩ እንደሚያስችል ተገልጿል።
እንዲሁም ጥናቱ የቤት ኪራይ ገበያውን ጤናማና ሊተነበይ በሚችል መልኩ በማደራጀት፣ በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን የእምነት ክፍተት ለመቀነስ እንዲሁም የሕገ-ወጥ ደላሎችን ጣልቃ ገብነት ለመግታት እንደሚረዳ ተጠቁሟል።
ጥናቱ በአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፣ በ2019 በጀት ዓመት በተግባር እንደሚውል ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከ2019 ጀምሮ የቤት ኪራይ ዋጋ በአዲስ መተመኛ ሊወሰን ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን ፍትሃዊ፣ ሳይንሳዊና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ለመወሰን የተዘጋጀ የዋጋ መተመኛ ጥናት ዛሬ ቀርቦ በባለድርሻ አካላት ፊት ውይይት ተካሂዷል።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደ ጊዮርጊስ እንደገለጹት፣ ከተማ አስተዳደሩ የኑሮ ጫናን ለመቀነስ እና በቤት ኪራይ ገበያ ውስጥ የተስፋፉ ሕገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን ለመግታት በተከታታይ እየሰራ ነው።
እንደ ኃላፊዋ ገለጻ፣ በ2016 ዓ.ም. የተከናወነው ሰፊ የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባ በዘርፉ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፣ አሁን የቀረበው የኪራይ ዋጋ መተመኛ ጥናትም የውል ማደስ ሂደትን ፍትሃዊና ግልጽ ለማድረግ ያግዛል።
ጥናቱ የአከራዮችን ተገቢ ገቢ ከወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ጋር በማጣጣም የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ተከራዮችም ከገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ እንዲከፍሉ እና የተረጋጋ የኢኮኖሚ ኑሮ እንዲመሩ እንደሚያስችል ተገልጿል።
እንዲሁም ጥናቱ የቤት ኪራይ ገበያውን ጤናማና ሊተነበይ በሚችል መልኩ በማደራጀት፣ በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን የእምነት ክፍተት ለመቀነስ እንዲሁም የሕገ-ወጥ ደላሎችን ጣልቃ ገብነት ለመግታት እንደሚረዳ ተጠቁሟል።
ጥናቱ በአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፣ በ2019 በጀት ዓመት በተግባር እንደሚውል ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤39👍6
‹‹TDF እየሸሸ ነው፤ አልዋጋም ብሏል›› ጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ‼️
‹‹ቲዲኤፍ የሚባለው ጦር እየሸሸ ቤቱ ተቀምጧል፤ አልዋጋም ብሏል፤ ትግራይ ያሉ መሪዎች ከሻብያ የሚሰጣቸውን ተልዕኮ ተቀብለው የጦርነት ፍላጎታቸውን አልተዉም፤ ነገር ግን አቅማቸው ስለተመናመነ እየወላወሉ ነው፡፡ በፊት ማስተዳደር በቻሉበት አቅም ማስተዳደር ስላልቻሉ አፋኝ ሕግ አውጥተው ማስተዳደር ነው የሚፈልጉት፤ ቀደም ሲል የሰሩት ወንጀል ለመሸፈን ሌላ ወንጀል እየሰሩ እንዳለ ይሰማኛል፡፡
ጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ በዛሬው ዕለት የተናገሩት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
‹‹ቲዲኤፍ የሚባለው ጦር እየሸሸ ቤቱ ተቀምጧል፤ አልዋጋም ብሏል፤ ትግራይ ያሉ መሪዎች ከሻብያ የሚሰጣቸውን ተልዕኮ ተቀብለው የጦርነት ፍላጎታቸውን አልተዉም፤ ነገር ግን አቅማቸው ስለተመናመነ እየወላወሉ ነው፡፡ በፊት ማስተዳደር በቻሉበት አቅም ማስተዳደር ስላልቻሉ አፋኝ ሕግ አውጥተው ማስተዳደር ነው የሚፈልጉት፤ ቀደም ሲል የሰሩት ወንጀል ለመሸፈን ሌላ ወንጀል እየሰሩ እንዳለ ይሰማኛል፡፡
ጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ በዛሬው ዕለት የተናገሩት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍20❤8🤣6🤪4🙉2👌1
ታሞ ሊጠይቁት አስራ ሰባት ፍቅረኛሞቹ ሆስፒታል የመጡበት የቻይናዊው አስገራሚ ታሪክ
በፈረንጆቹ 2015 ሚስተር ዩዋን የተባለ ቻይናዊ ሰው በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ሆስፒታል ይገባል።
ይሁንና አደጋው በአካባቢው የዜና ማሰራጫዎች ላይ መተላለፉን ተከትሎ፣ ያላሰበው አስገራሚ ትዕይንት በሆስፒታሉ ውስጥ ተፈጠረ።
ሊጠይቁት የመጡ 17 ፍቅረኛሞቹ በአንድ ጊዜ አልጋው አጠገብ ተገኙ!
ሁሉም ሴቶች እርስ በርሳቸው በፍጹም አይተዋወቁም የነበረ ሲሆን፥ አንዳንዶቹ ከዩዋን ጋር ለዓመታት የዘለቀ የፍቅር ግንኙነት እንደነበራቸው ታውቋል።
ይህ ሚስጥር በአንድ አደጋ ምክንያት በአደባባይ በመጋለጡ፣ በሆስፒታሉ የነበሩ ታካሚዎችና ነርሶች በሁኔታው በእጅጉ ተገርመዋል።
ፍቅረኛሞቹም ጉዳዩን ሲረዱ በከፍተኛ ድንጋጤ እና ቁጣ ውስጥ ወድቀው ነበር።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በፈረንጆቹ 2015 ሚስተር ዩዋን የተባለ ቻይናዊ ሰው በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ሆስፒታል ይገባል።
ይሁንና አደጋው በአካባቢው የዜና ማሰራጫዎች ላይ መተላለፉን ተከትሎ፣ ያላሰበው አስገራሚ ትዕይንት በሆስፒታሉ ውስጥ ተፈጠረ።
ሊጠይቁት የመጡ 17 ፍቅረኛሞቹ በአንድ ጊዜ አልጋው አጠገብ ተገኙ!
ሁሉም ሴቶች እርስ በርሳቸው በፍጹም አይተዋወቁም የነበረ ሲሆን፥ አንዳንዶቹ ከዩዋን ጋር ለዓመታት የዘለቀ የፍቅር ግንኙነት እንደነበራቸው ታውቋል።
ይህ ሚስጥር በአንድ አደጋ ምክንያት በአደባባይ በመጋለጡ፣ በሆስፒታሉ የነበሩ ታካሚዎችና ነርሶች በሁኔታው በእጅጉ ተገርመዋል።
ፍቅረኛሞቹም ጉዳዩን ሲረዱ በከፍተኛ ድንጋጤ እና ቁጣ ውስጥ ወድቀው ነበር።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣36❤15👍4🤪3😈2🤔1👀1
⁉️ የምስራቁ ጦርነት የኑሮአችንን ዋጋ እንዴት እያናጋው ነው? 💥
🚨የኃያላን መንግስታት ፍጥጫ እና የድንበር ጦርነቶች ከሩቅ የሚታዩ የዜና አርዕስቶች ብቻ አይደሉም፤ የኢትዮጵያን ገበያ እና የኪሳችንን አቅም በቀጥታ የሚፈትኑ ማዕበሎች እንጂ።
የሀገር ውስጥ ወቅታዊ ፈተናዎችን እና አጠቃላይ የአህጉራችንን እና የዓለምን ዜናዎች አቀናጅቶ የሚያቀርብላችሁን ስፑትኒክን አሁኑኑ ይከተሉ 👇
🔗 https://t.me/+r3LZG4PCAKI3NmMy
📣 @sputnik_ethiopia
🚨የኃያላን መንግስታት ፍጥጫ እና የድንበር ጦርነቶች ከሩቅ የሚታዩ የዜና አርዕስቶች ብቻ አይደሉም፤ የኢትዮጵያን ገበያ እና የኪሳችንን አቅም በቀጥታ የሚፈትኑ ማዕበሎች እንጂ።
የሀገር ውስጥ ወቅታዊ ፈተናዎችን እና አጠቃላይ የአህጉራችንን እና የዓለምን ዜናዎች አቀናጅቶ የሚያቀርብላችሁን ስፑትኒክን አሁኑኑ ይከተሉ 👇
🔗 https://t.me/+r3LZG4PCAKI3NmMy
📣 @sputnik_ethiopia
❤2👍2
ጥይት ወደውጪ መላክ ተጀመረ‼️
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ጥይት በመሸጥ የውጪ ምንዛሬ እየተገኘ መሆኑ ተዘገበ።
ከወራት በፊት በአገር ውስጥ ጥይት ማምረት መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ገልፀው ነበር፡፡
መከላከያ ሰራዊት ትናንት ባጋራው መረጃ በአገር ውስጥ የሚመረተው ጥይት የውጪ ምንዛሬ እያስገኘ መሆኑን ገልጧል፡፡
‹‹ኢትዮጵያ በያዘችው የለውጥ ጉዞ የጸጥታ መዋቅሯን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት እና ወታደራዊ ቁሶችን በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ለመገንባት የሚያስችል ታሪካዊ እርምጃ ወስዳለች›› የሚለው ሰራዊቱ፤ ይህ አካሄድ ሀገሪቱ በወታደራዊ አቅም ረገድ የነበራትን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ የራሷን የጸጥታ ፍላጎት በራሷ አቅም የምትፈታበትን አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል ብሏል።
በዚህ ረገድ መንግሥት ድሮን ቴክኖሎጂን በሀገር ውስጥ የማልማት እና የመገጣጠም ሥራን በስፋት እየተገበረ ይገኛል።
የድሮን ማዕከላት መቋቋም እና በሥራ ላይ መዋል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የአየር ክልሉን በአስተማማኝ ሁኔታ በመቆጣጠር እና የጸጥታ ስጋቶችን በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በታገዘ መንገድ ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ አስችሎታል ብሏል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪዎች ለቀላል እና ለከባድ የጦር መሣሪያዎች የሚያስፈልጉ ጥይቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመራቸው ሌላው ትልቅ ስኬት ነው ያለም ሲሆን፤ ‹‹ይህም በድንገተኛ የጸጥታ ተግዳሮቶች ጊዜ የጦር መሣሪያ እና ጥይት አቅርቦት እጥረት እንዳያጋጥም ዋስትና ከመስጠቱም በላይ፣ ለውጭ ግዥ ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ለማዳን አግዟል፤ ከዚያም አልፎ ሀገር ውስጥ የተመረተውን ጥይት ወደ ጎረቤት ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬ ማስገኘት ተጀምሯል›› በማለት አብራርቷል፡፡
Via : አንዳፍታ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ጥይት በመሸጥ የውጪ ምንዛሬ እየተገኘ መሆኑ ተዘገበ።
ከወራት በፊት በአገር ውስጥ ጥይት ማምረት መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ገልፀው ነበር፡፡
መከላከያ ሰራዊት ትናንት ባጋራው መረጃ በአገር ውስጥ የሚመረተው ጥይት የውጪ ምንዛሬ እያስገኘ መሆኑን ገልጧል፡፡
‹‹ኢትዮጵያ በያዘችው የለውጥ ጉዞ የጸጥታ መዋቅሯን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት እና ወታደራዊ ቁሶችን በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ለመገንባት የሚያስችል ታሪካዊ እርምጃ ወስዳለች›› የሚለው ሰራዊቱ፤ ይህ አካሄድ ሀገሪቱ በወታደራዊ አቅም ረገድ የነበራትን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ የራሷን የጸጥታ ፍላጎት በራሷ አቅም የምትፈታበትን አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል ብሏል።
በዚህ ረገድ መንግሥት ድሮን ቴክኖሎጂን በሀገር ውስጥ የማልማት እና የመገጣጠም ሥራን በስፋት እየተገበረ ይገኛል።
የድሮን ማዕከላት መቋቋም እና በሥራ ላይ መዋል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የአየር ክልሉን በአስተማማኝ ሁኔታ በመቆጣጠር እና የጸጥታ ስጋቶችን በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በታገዘ መንገድ ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ አስችሎታል ብሏል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪዎች ለቀላል እና ለከባድ የጦር መሣሪያዎች የሚያስፈልጉ ጥይቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመራቸው ሌላው ትልቅ ስኬት ነው ያለም ሲሆን፤ ‹‹ይህም በድንገተኛ የጸጥታ ተግዳሮቶች ጊዜ የጦር መሣሪያ እና ጥይት አቅርቦት እጥረት እንዳያጋጥም ዋስትና ከመስጠቱም በላይ፣ ለውጭ ግዥ ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ለማዳን አግዟል፤ ከዚያም አልፎ ሀገር ውስጥ የተመረተውን ጥይት ወደ ጎረቤት ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬ ማስገኘት ተጀምሯል›› በማለት አብራርቷል፡፡
Via : አንዳፍታ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣45❤19🌚6👍5🤪2👌1👀1