አዲስ ሪፖርተር - NEWS
36.2K subscribers
17K photos
415 videos
21 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
ለኢራን 300 ቢሊዮን ዶላር የስምምነቱ አካል ነው‼️
የአሜሪካ እና ኢራን ስምምነት የሚከተሉትን ያጠቃልላል።
▪️ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ወታደራዊ ጥቃት ያበቃል። ይህ የስምምነት አካል እስራኤል በሊባኖስ ያለውን ጥቃት ታቆማለች ወይ የሚለው ጉዳይ አጣበቂኝ ውስጥ ከቶታል።
▪️አሜሪካ እና ኢራን የተጣሉ እገዳዎችን በፍጥነት ማንሳት ይጀምራሉ።
▪️ ለኢራን መልሶ ግንባታ 300 ቢሊዮን ዶላር እቅድ ተይዟል።
▪️አሜሪካ ሁሉንም አይነት የኢራን ማዕቀቦች 'በጊዜ ሰሌዳው መሰረት' ታነሳለች።
▪️አሜሪካ የታገዱ ሁሉንም የኢራን ንብረቶችን ትለቃለች።
ስምምነቱ 'በአጭር ጊዜ' ሊፈረም ነው ሲሉ ትራምፕ በ G7 ስብሰባ ላይ ተናግረዋል። እስራኤል ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ባደረጉት ስምምነት መናደዷን በይፋ ገልፃለች።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
20👍9🙏2🤪2👌1
የትግራይ ክልል መምህራን ማኅበር፣ በክልሉ የመምህራን ደመወዝ ለበርካታ ወራት ባለመክፈሉ መምህራን ከነቤተሰቦቻቸው በርሃብ ምክንያት እየታመሙ፣ እየተሠቃዩ እና አልፎ አልፎም ለሞት እየተዳረጉ ይገኛሉ ሲል ዛሬ ለኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር በጻፈው ደብዳቤ ገለጸ።

ማኅበሩ፣ በፖለቲከኞች መካከል በተፈጠረ የሃሳብ ልዩነት ምክንያት የመምህራን ደመወዝ መከልከል ''የግፍ ግፍ" እና "በታሪክ የሚያስወቅስ" ተግባር ነው በማለት ኮንኗል።

የክልሉ መምህራን ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው ከዚህ ቀደም በደብዳቤና በሠማላዊ ሠልፍ ጭምር በተደጋጋሚ መጠየቁን የጠቀሠው ማኅበሩ፣ ኾኖም ለችግሩ ምላሽ የሚሠጥ አካል አልተገኘም ብሏል።

የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ከፌዴራሉ መንግሥትና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ለችግሩ መፍትሔ እንዲያፈላልግም ማኅበሩ ጠይቋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
18👍2
ግብጽ በሱዳናዊያን ማዕድን አውጭዎች ላይ የአየር ጥቃት ፈጸመች።

በግብፅ እና በሱዳን መካከል ለረጅም ዘመናት አወዛጋቢ ሆኖ በቆየው "የሀላይብ ትሪያንግል" (Halaib Triangle) ግዛት ውስጥ የግብፅ ወታደራዊ አውሮፕላኖች በፈጸሙት ድንገተኛ የአየር ጥቃት ቢያንስ የሰባት ሱዳናዊያን ወርቅ አውጪዎች ሕይወት ማለፉ ተዘገበ።
ጥቃቱ የተፈጸመው በዚሁ አወዛጋቢ ቀጠና ውስጥ በሚገኘው "ጀበል አል ኡቃያት" በተሰኘው የወርቅ ማውጫ ስፍራ ላይ ነው። እንደ የአይን እማኞች እና የአካባቢው መረጃዎች ከሆነ፣ በጥቃቱ ወቅት የግብፅ የጦር ሄሊኮፕተሮች በስፋት የታዩ ሲሆን ከሰባቱ ሟቾች በተጨማሪ በአስር የሚቆጠሩ ዜጎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።

በአሁኑ ሰዓት ሱዳን በከፋ የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኝ ሲሆን፣ የግብፅ መንግስት ደግሞ የጄነራል አብዱልፈታህ አል-ቡርሃን የሚመራውን የሱዳን ጦር (SAF) በግልጽ በመደገፍ የቅርብ ወዳጅ ሆና እየሰራች ነው። ግብፅ ለሱዳን ወታደራዊ መንግስት ዲፕሎማሲያዊ እና ወታደራዊ ድጋፍ በምትሰጥበት በዚህ ወቅት ግን በድንበር አካባቢ የሚገኙ

ሱዳናዊያንን ኢላማ ያደረገ ጥቃት መፈጸሟ በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ላይ ጥያቄን ጭሯል። የሱዳን ወታደራዊ መንግስት ዜጎቹ በግብፅ ጦር መገደላቸው እየታወቀ እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት ይፋዊ መግለጫ አለመስጠቱ እና ዝምታን ጉዳዩን አስገራሚ አድርጎታል። ይህ ዝምታ በሱዳን ህዝብ ዘንድ "መንግስት ለወታደራዊ ድጋፍ ሲል የዜጎቹን ደህንነት ችላ ብሏል" የሚል ቅሬታን እየቀሰቀሰ ይገኛል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
23👍7
"ሮናልዶ የድሮዉ ሮናልዶ አይደለም። እድሜዉ ጨምሯል።እሱን መከላከል ከባድ አልነበረም" ይህንን ያለዉ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎዉ ተከላካይ ሙካዉ ነዉ።

በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በአለምዋንጫ አፍሪካን ወክላ የተካፈለችዉ ኮንጎ ትናንት ምሽት ፖርቱጋልን በአለምዋንጫዉ ከብርቱ ተገዳዳሪነት በኋላ ነጥብ አስጥላ ወጥታለች።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
16🤣3👍2
"ተመልሰን ቦምብ ልናዘንብ እንችላለን" - የትራምፕ ዛቻ

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በስምምነቱ መሰረት ካልተጓዘች አዲስ ጥቃት አመራለሁ ሲሉ ዛቱ፡፡

በቡድን ሰባት ጉባዔ ፈረንሳይ የሚገኙት ትራምፕ ከኢራን ጋር የተደረሰው ስምምነት “ገና እንዳልተገባደደ” ጠቅሰው በመግባቢያ ሰነዱ አተገባበር ደስተኛ ካልሆኑ ቴህራን ላይ ጥቃት መፈጸም እንደሚቀጥሉ አስጠንቅቀዋል፡፡

ኢራን ከእስራኤልና አሜሪካ ጋር ስምምነት ላይ ከደረሰች በኋላ በሰጡት የመጀመሪያ አስተያየት "ጥቃቱ በዚሁ ከቀጠለ ጠንካራ ምላሽ የምንሰጥ ይሆናል" ሲሉ ትራምፕ ተደምጠዋል።

ፕሬዝዳንቱ "ተመልሰን ቦምብ ልናዘንብ እንችላለን" ሲሉም ዝተዋል።

"የመግባቢያ ስምምነቱ አልተጠናቀቀም" ያሉት ትራምፕ "ካልወደድኩት ወታደራዊ እርምጃ እንወስዳለን" ሲሉም የመፍረስ አደጋ እንዳለው ጠቁመዋል።

"ስምምነቱ በብዙ ምክንያት አስፈላጊ ነው" ካሉ በኋላ "99.9% የተስማማንበት ኢራን የኑክሌር መሳሪያ እንደማይኖራት ነው" ብለዋል።

ኢራን ለመልሶ ግንባታ የሚሆን 300 ዶላር ካሳ ይከፈላታል መባሉን "ውሸት ነው፣ ሳንቲም አናወጣም" ሲሉ አስተባብለዋል።   #thetimesofisrael

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
11🤔5🥱4👍3😡2
የፋርማሲ ተማሪዎች ቅሬታ‼️
የፋርማሲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ተፈታኞች ፈተናው አስቀድሞ ተሰርቋል በማለት ቅሬታ አቀረቡ፤ የሚመለከተው አካል ማብራሪያ እንዲሰጥም ጠይቀዋል።

ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት ክፍል ብሔራዊ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) አስቀድሞ ተሰርቆ ለተወሰኑ ተማሪዎች ተሰራጭቷል ሲሉ ተፈታኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ ተማሪዎች እንዳሉት፤ ለፈተናው በርካታ ልፋትና ዝግጅት ቢያደርጉም፣ ኃላፊነት በማይሰማቸው አካላት አማካኝነት ፈተናው ቀድሞ ወጥቶ መሰራጨቱን የሚያሳዩ መረጃዎች እንደደረሷቸው ገልጸዋል።

ይህ መሆኑም በከፍተኛ ጥረትና በራሳቸው ልፋት የተፈተኑ ተማሪዎችን ስነ-ልቦና በእጅጉ የጎዳና ፍትሃዊነትን ያጓደለ ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል።

ተፈታኞቹ አያይዘውም፣ ጉዳዩ በሚመለከታቸው አካላት ትምህርት ሚኒስቴርና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም በኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች ማህበር (EPA) በኩል በአስቸኳይ ታይቶ፣ አስፈላጊው ማጣሪያ እንዲደረግና ተገቢው ምላሽ እንዲሰጣቸው በትህትና ጠይቀዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
10👍6🤯1👀1🙊1
የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት 38.23 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰበሰበ

በጉምሩክ ኮሚሽን የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈሪ መኮንን

በ2018 በጀት አመት በአስራ አንድ ወራት 42.49 ቢሊዮን ብር ጥቅል ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 38.23 ቢሊዬን ብር ገቢ መሰበሰቡን አስታውቀዋል፡፡

የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ3.97 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ተጠቁሟል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
7👍6🤣21👌1
📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944

👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
 👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ

🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !

👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
👍53
15 ቢልየን ብር አልተመለሰም

በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ያለአግባብ የተፈፀመ ክፍያ መሆኑ ተረጋግጦ ለመንግስት ተመላሽ እንዲደረግ ከታዘዘው ገንዘብ ወደ 15 ቢሊዮን ብር አሁንም ተመላሽ አልሆነም ተባለ፡፡

ተጨማሪ ከ23 ሺህ ዶላር በላይም ወደ መንግስት ካዝና መመለስ ሲኖርበት መ/ቤቶቹ ተመላሽ እንዳላደረጉ የተናገረው የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ነው፡፡

የመንግስትና የህዝብ ሀብት ባክኖ እንዳይቀር በቢሊዮን የሚቆጠረው ብር ተመላሽ እንዲሆን በድጋሚ ለመስሪያ ቤቶቹ ማሳሰቢያ ሰጥቻለሁ ብሏል፡፡

በ2016 በጀት ዓመትና ከዚያ በፊት ከህግ ውጪ የተፈፀሙ ክፍያዎች መሆናቸው በሒሳብ ምርመራ ተረጋግጦ 21 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር እና ከ23 ሺህ ዶላር በላይ ወይም በአሁኑ ምንዛሪ ከ3 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ለመንግስት ተመላሽ እንዲሆን ጥፋቱን የፈፀሙ ተቋማት በደብዳቤ ተጠይቀው ነበር ተብሏል፡፡

ከመካከሉ ለመንግስት ተመላሽ የተደረገው 31 በመቶው ወይም 6 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብሩ ብቻ መሆኑን የፌዴራል ዋና ኦዲተር የ2017 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት ያሳያል፡፡

ያላግባብ ወጭ ተደርጓል፤ ለመንግስት ይመለስ የተባለው እና በውጭ ምንዛሬ 23,200 ዶላር ግን መቶ በመቶ ለመንግስት ሳይመለስ ቀርቷል ይላል ሪፖርቱ፡፡

የዋና ኦዲተር የኦዲት ግኝት ሪፖርት ዛሬ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡

ከህግ ውጭ የተከፈሉ እና ለመንግስት መመለስ አለባቸው የተባሉት በአብዛኛው በጉምሩክና ፣ የገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እንዲሁም በዩኒቨርስቲዎች የተፈፀሙ መሆናቸውን ሪፖርቱ ያሳያል፡፡

ከመካከላቸው ግን ከ32 እስከ 99 በመቶ ያላግባብ ያወጡትን ገንዘብ የመለሱ ተቋማትም አሉ፡፡

እንደማሳያ የኮምቦልቻ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ፣ የኤርፖርት ጉምሩክ 621 ሚሊዮን ፣ አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ 120.7 ሚሊዮን የቃሊቲ ጉምሩክ 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ያላግባብ አውጥተውት ከነበረው ገንዘብ ለመንግስት ተመላሽ አድርገዋል ተብሏል፡፡

የተጠቀሱት እና ሌሎችም ተቋማት ህግ ጥሰው ያላግባብ ወጭ ያደረጉትንና እስካሁን ለመንግስት ያልመለሱትን ወደ 15 ቢሊዮን ብር የተጠጋ ገንዘብ ተመላሽ እንዲያደርጉም ተጠይቀዋል፡፡

እንዲህ ያለው የሒሳብ አያያዝ መዝረክረክም ለመንግስት ገንዘብ መባከን ምክንያት እንዳይሆን አስፈላጊ እርምጃ ይወስድ ሲል የፌዴራል ዋና ኦዲተር አሳስቧል፡፡
ሸገር ራዲዮ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
7🥱5👍2🤔2🫡1
ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ቀነሰ‼️
በአሜሪካና ኢራን መካከል ለወራት የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆምና የሆርሙዝ ሰርጥን ለመክፈት ያለመ ጊዜያዊ ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ቀንሷል።

እንደ ሮይተርስ ዘገባ የተፈረመው ስምምነት በአቅርቦት ላይ የነበረውን ስጋት በማቃለሉ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በበርሜል 77.93 ዶላር ሆኗል።

በተመሳሳይ ፣ የዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዲየት (WTI) ዋጋም ወርዶ በበርሜል $74.81 ሆኖ ተመዝግቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
17👍3🙏2
በሣውላ ከተማ የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ ።

በሣውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፀ

ተማሪን ወክሎ ከመምህር ስነ ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ተሳተፈ የተባለው ከቡልቂ ከተማ ሙሉ ፩ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አብነት እንዳለን ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው።

ፈተናውን ከኩረጃና ስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ ከሰጠው ተማሪ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል።

የሣውላ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል።

በፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሠራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል።

ምንጭ ሣውላ ከተማ መንግሥት ኮሙኒኬሽን

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
13🤣6👍3😢2
#TPLF

አሜሪካ በህወሓት (TPLF) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የእገዳ ጣለች

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እንዲሁም በመላ ቀጠና ያለውን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ጥለዋል ባሏቸው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ገደብ መጣሉን አስታውቀዋል።

ውሳኔው የተላለፈው በስደተኞችና ዜግነት አዋጅ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ስልጣን መሰረት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ እገዳው በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት በሚያስተጓጉሉ " አክራሪ አቋም " ባላቸው አባላትና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ በህወሓት አመራሮችና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል እየተባባሰ የመጣው ውጥረት የሰሜን ኢትዮጵያን ሰላም ዳግም ስጋት ላይ መጣሉን ጠቅሷል።

በተለይም በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ በትግራይ የፀጥታ ኃይሎች (TSF) እና በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት (ENDF) መካከል የተከሰተው ቀጥተኛ ግጭት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የተገኘውን አንጻራዊ መረጋጋት የሚፈታተን መሆኑ አመልክቷል።

አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር የሚፈልገውን የትግራይን ጨምሮ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ መደገፏን እንደምትቀጥል የገለጸው መግለጫው፤ በክልሉ ሰላምና መረጋጋትን በሚያናጉ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ያሉትን አማራጮች ሁሉ ጥቅም ላይ እንደምታውል አስታውቃለች።

የቪዛ ማዕቀብ የተጣለባቸው የህወሓት (TPLF) አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ስም በይፋ አልተገለጸም።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
32👍9🤪4💯2👌1
ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ የተላከ 63 ኪሎ ግራም ጫት ተያዘ

የዩናይትድ ስቴትስ የጉምሩክ እና የድንበር ጥበቃ መኮንኖች ሐሙስ ጁን 4 ቀን በዋሽንግተን ዱለስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በስተርሊንግ የግብርና ስፔሻሊስቶች ወደ ሳክራሜንቶ ፣ ካሊፎርኒያ የሚጓዘውን የአየር ጭነት ከመረመሩ በኋላ ጫቱ መያዙን ባለሥልጣናቱ አስታወቁ።

የጉዞው ዋጋ ወደ 17,000 ዶላር የሚገመት ጫት መሆኑን ገልፀዋል። ጭነቱ በተለያዩ ቅመማ ቅመሞች ውስጥ የተሸሸገ ሲሆን በ102 ሣጥኖች ውስጥ የተካተተ መሆኑን ኃላፊዎቹ ተናግረዋል። ጫት በተለምዶ በምስራቅ አፍሪካ እና በአረብ ባሕረ ገብ መሬት ይበቅላ።

አንዳንድ ተጠቃሚዎች አበረታች ሻይ ለማዘጋጀት የደረቁ የጫት ቅጠሎችን ያፈላሉ። እፅዋቱ ካቲኖን እና ካቲን የተባሉ ሁለት የማዕከላዊ የነርቭ ሥርዓት አነቃቂዎች እንደያዘ አሜሪካ ማስታወቋን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል።

የፌደራል ባለስልጣናት እንዳሉት ጫት መነቃቃት ይፈጥራል፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ የመተንፈስ ችግር፣ የደም ግፊት መጨመር እና የልብ ምት መጨመር ያስከትላል። የዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ወደብ ዳይሬክተር የሆኑት ክሪስቲን ዋው "ጫት ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ተከልክሏል ያሉ ሲሆን ምክንያቱም በውስጡ ያሉት የኬሚካል ንጥረነገሮች ቁጥጥር የሚደረግባቸው ንጥረ ነገሮች ናቸው" ብለዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
14😡5👍2🤔2🥰1👀1🙊1
አሜሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ40 አገራት ለሰብዓዊ ዕርዳታና ለአደጋ ምላሽ የሚውል 1 ቢሊዮን ዶላር ለተመድ ሕጻናት ድርጅት (ዩኒሴፍ) እና ለዓለም ምግብ ፕሮግራም ለመስጠት ወሠነች።

ከገንዘብ ድጋፉ 800 ሚሊዮን ዶላሩ ለዓለም የምግብ ፕሮግራም የሚሠጥ ሲሆን፣ 218 ሚሊዮን ዶላር ደሞ ለዩኒሴፍ እንደሚሠጥ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ገልጧል።

ገንዘቡ ለሁለቱ ድርጅቶች የተፈቀደው፣ የእርዳታ አሠጣጣቸው ሊለካ የሚችል ውጤት የሚያስመዘግብና ተጠያቂነትን የሚያሠፍን በመኾኑ እንደኾነ መስሪያ ቤቱ ጠቅሷል።

ድርጅቶቹ፣ ገንዘቡን ለምግብ እርዳታ፣ ለአልሚ ምግብ አቅርቦት፣ ለጤና፣ ለሕጻናት እንክብካቤ፣ ለሎጅስቲክ እንዲሁም ለውሃና ንጽህና አጠባበቅ እንዲያውሉት ተፈቅዶላቸዋል።

ከገንዘብ ድጋፉ ተጠቃሚ ከሚኾኑት አገራት መካከል ከኢትዮጵያ በተጨማሪ፣ በርማ እና ዩክሬን ይገኙበታል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
12👍8😡3😢1🙏1
መረጃ‼️

የቀይ ባሕር አፋሮች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የዓለም መንግሥታት የኤርትራ መንግሥት ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ተቆጣጣሪ ልዩ ራፖርተር ጋር እንዲተባበርና ልዩ ራፖርተሩ ወደ ኤርትራ እንዲገቡ እንዲፈቅድ ተጽዕኖ እንዲያደርጉ ጠየቀ።

ልዩ ራፖርተሩ በኤርትራ ዙሪያ ለተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ሰሞኑን ያቀረቡትን ሪፖርት እንደሚደግፍ የገለጠው ድርጅቱ፣ ምክር ቤቱ የልዩ ራፖርተሩን ተልዕኮ እንዲያጠናክርና የልዩ ራፖርተሩን የጊዜ ቆይታ እንዲያራዝም ጠይቋል።

ድርጅቱ፣ አባል አገራት ኤርትራዊያን ስደተኞችን፣ ጋዜጠኞችንና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ከኤርትራ መንግሥት የድንበር-ዘለል "ማስፈራሪያዎች" እና "ዛቻዎች" እንዲከላከሉ ጭምር ጥሪ አድርጓል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
15👍4🤪3
"በምድር ላይ ከኖሩት ሁሉ እጅግ ኃያሉ ሰው እኔ ነኝ’" ትራምፕ

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት እኩለ ሌሊት ላይ በትሩዝ ሶሻል የማኅበራዊ ገጻቸው ባስተላለፉት ተከታታይ መልዕክቶች፣ "በዚህች ፕላኔት ላይ ከተራመዱት ሰዎች ሁሉ እጅግ ኃያሉ ሰው እኔ ነኝ" የሚል ይዘት ያለውን ጽሑፍ በማጋራት ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆነዋል።

ትራምፕ ያጋሩት ጽሑፍ "የፕሬዝዳንታዊ ታሪክ ምሁር ዴቭ ኪንግ" በተባሉ ሰው የተጻፈ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንቱን እንደ ታላቁ እስክንድር፣ ጄንጊስ ካን እና ናፖሊዮን ካሉ ታዋቂ የዓለም ታሪክ መሪዎች ጋር በማነጻጸር ከሁሉም እንደሚበልጡ ይገልጻል።

ይህ መግለጫ ይፋ የሆነው ትራምፕ ረቡዕ ዕለት ከአሜሪካ ጋር ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የኢራን ጦርነት ለማቆም የሚያስችለውን ስምምነት በፈረሙ ማግስት ነው። ምንም እንኳን ይህ የሰላም ስምምነት በብዙ ወገኖች ዘንድ ከፍተኛ ትችት ቢሰነዘርበትም፣ ትራምፕ ግን እሳቸው ይህንን ስምምነት ባያደርጉ ኖሮ ዓለም "ከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ" ውስጥ ትወድቅ እንደነበር በመግለጽ ውሳኔያቸውን ተከላክለዋል።

ጽሑፉን ያዘጋጁት የታሪክ ምሁሩ ዴቭ ኪንግ፣ ትራምፕን እንደ አቲላ ዘ ሁን (Attila the Hun) እና ዊሊያም ዘ ኮንከረር ካሉ ታሪካዊ ኃያላን መሪዎች ጋር ጭምር በማወዳደር የእሳቸው ተፅዕኖ የላቀ እንደሆነ ይሞግታሉ። ይህ የትራምፕ የሌሊት ማኅበራዊ ሚዲያ ፖስት በአሜሪካ ፖለቲካና በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘንድ አሁንም ከፍተኛ ክርክርና መነጋገሪያነቱን ቀጥሏል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣3515🤡5👍4🥱2🤷‍♂1🥰1🤔1😢1😎1
ወደ ካናዳ የሥራ ስምሪት ተጀምሯል የሚሉ ማስታወቂያዎች ሀሰተኛ  መረጃዎች ናቸው ተባለ
 
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ ካናዳ የሚደረግ የሥራ ስምሪትም ሆነ ምዝገባ እስካሁን አልተጀመረም ሲል አስታውቋል።ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ፣ ወደ ካናዳ የሥራ ስምሪት ተጀምሯል በሚል ስም የሚሰራጩ ማስታወቂያዎች ሀሰተኛ መሆናቸውን ገልጾ ዜጎች እንዳይታለሉ አሳስቧል።
 
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከሳውዲ አረቢያ፣ ከተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ ከጆርዳን፣ ከኳታር እና ከሊባኖስ ጋር ባላት የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት ብቻ ህጋዊ የሥራ ስምሪት እየተካሄደ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
 
መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ጋር ስምምነት የፈጸመው ሚኒስቴሩ ወጣቶችን በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ ተወዳዳሪ ማድረግና የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ለማመቻቸት መሆኑን ጠቅሷል።በተጨማሪም ወደ ካናዳ እንልክዎታለን በሚል ሰበብ ገንዘብ የሚጠይቁ አካላት አጭበርባሪዎች መሆናቸውን ጠቁሞ  ለማንኛውም ፕሮግራም ክፍያ እንደማይጠየቅ መግለፁን ብስራት ሬድዮ ሰምቷል ።
 
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
9👍8
የቴዲ አፍሮ የቀድሞው ማናጀር አቶ አዲስ ገሰሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የጃኖ ባንድ መስራች የነበሩት እና የሙዚቀኛ ገሰሰ ዘለቀ ወንድም የሆኑት ታዋቂው የሙዚቃ ፕሮዲዮሰርና ማኔጀር አቶ አዲስ ገሰሰ በአሜሪካን ሀገር ህይወታቸው ማለፉን የቅርብ ወዳጆቻቸው ለመዝናኛ ሚዲያ አስታወቁ።

አቶ አዲስ ዓለም አቀፍ ዝና ያተረፉትን የቦብ ማርሊ ልጆችንእና በርከት ያሉ ታዋቂ ሙዚቀኞችን የማማከርና የማስተዳደር ስራ የሰሩ ጉምቱ የሙዚቃ አስተዳደር ባለሞያ ነበሩ። አቶ አዲስ የቴዲ አፍሮ ማኔጀር በመሆንም ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል።

በትላንትናው እለት አመሻሹ ላይ በኒው ጀርሲ ግዛት ህይወታቸው ያለፈው አቶ አዲስ ገሰሰ ፣ የሞታቸው ምክንያት ለጊዜው ያልታወቀ ሲሆን አስከሬናቸውን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ እንደታሰበ የደረሰን መረጃ ያመለከታል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
19😢9👍4💔2