📍አፍሪካ ህብረት አቅራቢያ መሀል ቡልጋሪያ አዲሱ ትልቁ መስጂድ ጋር ቢፈልጉ በዶላር የሚያከራዩት አልያም በመሃል ከተማ የመኖር ህልምዎን የሚያሳኩበት !
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
🔥15% ቅድሚያ | 🔥 20% ቅናሽ
☎️ 0928384058 | 0914976944
👉🛏️ባለ 1መኝታ 53 ካሬ =4.2ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
👉 🛏️ባለ 1መኝታ 69ካሬ =5.2ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ ባለ 2መኝታ 105 ካሬ =9.2 ሚሊዮን አጠቃላይ ዋጋ
👉🛏️ባለ 3መኝታ 160 =12 ሚሊየን አጠቃላይ ዋጋ
🔥ቅድመ ክፍያ 750,000 ብር !
👉በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ የንግድ ሱቆችን ከ20 ካሬ ጀምሮ ከ1-3ኛ ወለል ማግኘት ይችላሉ።
for further
☎️ 0928384058 | 0914976944
❤3👍3
የምግብ ዋጋ 14.6 በመቶ ጨመረ
የግንቦት ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ደግሞ 13.4 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 14.6 በመቶ የጨመረ ሲሆን በዋናነት አትክልት፣ ስጋ ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በመጨመራቸው የተመዘገበ ነው።
ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 11.1 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንሰፖርት (12.1 በመቶ)፣ አልኮል መጠጦችና ትምባሆ (14.6 በመቶ)፣ በኮሙዩኒኬሽን (9.1 በመቶ) ፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች (10.5 በመቶ) እንዲሁም ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች (17.9 በመቶ) ሆነው ተመዝግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የግንቦት ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ደግሞ 13.4 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 14.6 በመቶ የጨመረ ሲሆን በዋናነት አትክልት፣ ስጋ ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በመጨመራቸው የተመዘገበ ነው።
ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 11.1 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንሰፖርት (12.1 በመቶ)፣ አልኮል መጠጦችና ትምባሆ (14.6 በመቶ)፣ በኮሙዩኒኬሽን (9.1 በመቶ) ፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች (10.5 በመቶ) እንዲሁም ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች (17.9 በመቶ) ሆነው ተመዝግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢8❤7👍2😱2👀1
ጥርስን እንደገና የሚያሳድገው መድሃኒት‼️
ሳይንቲስቶች የሰው ልጆች በተፈጥሮ የጠፉ ጥርሶችን እንደገና እንዲያሳድጉ የሚያስችል መድሃኒት ፈጠሩ‼️
በህክምና ምርምር ኢንስቲትዩት ኪታኖ ሆስፒታል በዶ/ር ካትሱ ታካሃሺ የሚመራው የጃፓን ተመራማሪዎች የጥርስን ተፈጥሯዊ እድገት የሚያነቃቃ ፈር ቀዳጅ የሆነ መድሃኒት ፈጥረዋል።
መድሃኒቱ የሚሠራው የጥርስን እድገት የሚከላከለውን ዩኤስኤግ-1 የተባለውን ፕሮቲን በመግታት ነው።
ይህ መድሃኒት በአይጦች ላይ ሙከራ ተደርጎ አዲስ-ጥርሶችን በተሳካ ሁኔታ በማሳደጉ የምርምር ቡድኑ አሁን ይህን ለውጥ የሚያመጣ ህክምና በአስር አመታት ውስጥ ወደ ገበያ ለማውጣት በሰዎች ላይ ክሊኒካዊ ሙከራዎችን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ሳይንቲስቶች የሰው ልጆች በተፈጥሮ የጠፉ ጥርሶችን እንደገና እንዲያሳድጉ የሚያስችል መድሃኒት ፈጠሩ‼️
በህክምና ምርምር ኢንስቲትዩት ኪታኖ ሆስፒታል በዶ/ር ካትሱ ታካሃሺ የሚመራው የጃፓን ተመራማሪዎች የጥርስን ተፈጥሯዊ እድገት የሚያነቃቃ ፈር ቀዳጅ የሆነ መድሃኒት ፈጥረዋል።
መድሃኒቱ የሚሠራው የጥርስን እድገት የሚከላከለውን ዩኤስኤግ-1 የተባለውን ፕሮቲን በመግታት ነው።
ይህ መድሃኒት በአይጦች ላይ ሙከራ ተደርጎ አዲስ-ጥርሶችን በተሳካ ሁኔታ በማሳደጉ የምርምር ቡድኑ አሁን ይህን ለውጥ የሚያመጣ ህክምና በአስር አመታት ውስጥ ወደ ገበያ ለማውጣት በሰዎች ላይ ክሊኒካዊ ሙከራዎችን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤18👏8👍2
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ውል ላይ ደረሰ
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ሰነድ መጽደቁን በሂደቱ ላይ ቁልፍ አስታራቂ የሆኑት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም እና ወሳኙን የሆርሙዝ ወሽመጥ ድጋሚ ለመክፈት ያለመውን ይህንን ስምምነት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሰላም እንደ አሁኑ ቀርቦ አያውቅም” ብለዋል።
ሂደቱን ለማደናቀፍ የሚነዙ የሀሰት መረጃዎችን ወደ ጎን በመተው ፓኪስታን ቀጣይ እርምጃዎችን ለማጠናቀቅ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በቅርበት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጊቺም በበኩላቸው የጦርነቱ ማክተሚያ መቃረቡን አረጋግጠዋል።
ከሁለቱም ወገኖች ተስፋ ሰጪ መግለጫዎች ቢሰሙም፣ በአደባባይ ያላቸው የድርድር አቋም አሁንም የተራራቀ መሆኑ ይስተዋላል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መገናኛ ብዙኃን የተናፈሰው የስምምነቱ ይዘት ከእውነታው የራቀ ነው ያሉ ሲሆን፣ ኢራናውያንን “በቅንነት ለመደራደር የማይመቹ” ሲሉ ተችተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ሰነድ መጽደቁን በሂደቱ ላይ ቁልፍ አስታራቂ የሆኑት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም እና ወሳኙን የሆርሙዝ ወሽመጥ ድጋሚ ለመክፈት ያለመውን ይህንን ስምምነት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሰላም እንደ አሁኑ ቀርቦ አያውቅም” ብለዋል።
ሂደቱን ለማደናቀፍ የሚነዙ የሀሰት መረጃዎችን ወደ ጎን በመተው ፓኪስታን ቀጣይ እርምጃዎችን ለማጠናቀቅ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በቅርበት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጊቺም በበኩላቸው የጦርነቱ ማክተሚያ መቃረቡን አረጋግጠዋል።
ከሁለቱም ወገኖች ተስፋ ሰጪ መግለጫዎች ቢሰሙም፣ በአደባባይ ያላቸው የድርድር አቋም አሁንም የተራራቀ መሆኑ ይስተዋላል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መገናኛ ብዙኃን የተናፈሰው የስምምነቱ ይዘት ከእውነታው የራቀ ነው ያሉ ሲሆን፣ ኢራናውያንን “በቅንነት ለመደራደር የማይመቹ” ሲሉ ተችተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤25👍2🎉1
ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ላለማምረት ከአሜሪካ ጋር ከስምምነት ላይ ደረሰች!
ኢራን ከአሜሪካ ጋር በደረሰችው የረቂቅ ስምምነት መሠረት የኑክሌር መሣሪያዎችን ላለማምረትም ኾነ ላለመታጠቅ መስማማቷን አንድ ከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣን ለሮይተርስ የዜና ወኪል ገልጸዋል።
ቴህራን በረቂቅ የመግባቢያ ሰነዱ ላይ ባስቀመጠችው ስምምነት ማንኛውንም ዓይነት የኑክሌር መሣሪያ ከማምረት እና ከማግኘት ሙሉ በሙሉ ትቆጠባለች።።
ስማቸው ያልተጠቀሰ አንድ ከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣን ይኸው ከአሜሪካ ጋር የተደረገው የረቂቅ ስምምነት ሂደት መቋጫ ማግኘቱን ለሮይተርስ አረጋግጠዋል።
@Addis_reporter
@Addis_reporter
ኢራን ከአሜሪካ ጋር በደረሰችው የረቂቅ ስምምነት መሠረት የኑክሌር መሣሪያዎችን ላለማምረትም ኾነ ላለመታጠቅ መስማማቷን አንድ ከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣን ለሮይተርስ የዜና ወኪል ገልጸዋል።
ቴህራን በረቂቅ የመግባቢያ ሰነዱ ላይ ባስቀመጠችው ስምምነት ማንኛውንም ዓይነት የኑክሌር መሣሪያ ከማምረት እና ከማግኘት ሙሉ በሙሉ ትቆጠባለች።።
ስማቸው ያልተጠቀሰ አንድ ከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣን ይኸው ከአሜሪካ ጋር የተደረገው የረቂቅ ስምምነት ሂደት መቋጫ ማግኘቱን ለሮይተርስ አረጋግጠዋል።
@Addis_reporter
@Addis_reporter
😁17❤16👍6
ኢራን ለእስራኤል ምላሽ ልሰጥ ነው‼️
እስራኤል በዛሬው ዕለት በቤሩት ላይ ጥቃት መፈፀሟን ተከትሎ ኢራን ምላሽ ለመስጠት እየተዘጋጀች መሆኑን የሀገሪቱ የዜና ወኪል የሆነው ታስኒም ኒውስ ዘግቧል።
እስራኤል በቤሩት ላይ የፈፀመችው ጥቃት ትክክል አለመሆኑን ትራምፕ ገልፀዋል።
አሜሪካ እና ኢራን በሚቀጥሉት 2-3 ሰዓታት ውስጥ የስምምነት ፊርማ እንደሚያደርጉ ትራምፕ ቢገልፁም ኢራን ዛሬ የሚፈፀም ስምምነት የለም ብላለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
እስራኤል በዛሬው ዕለት በቤሩት ላይ ጥቃት መፈፀሟን ተከትሎ ኢራን ምላሽ ለመስጠት እየተዘጋጀች መሆኑን የሀገሪቱ የዜና ወኪል የሆነው ታስኒም ኒውስ ዘግቧል።
እስራኤል በቤሩት ላይ የፈፀመችው ጥቃት ትክክል አለመሆኑን ትራምፕ ገልፀዋል።
አሜሪካ እና ኢራን በሚቀጥሉት 2-3 ሰዓታት ውስጥ የስምምነት ፊርማ እንደሚያደርጉ ትራምፕ ቢገልፁም ኢራን ዛሬ የሚፈፀም ስምምነት የለም ብላለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍10😁1
የሜታ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማርክ ዙከርበርግ በቅርቡ በተከሰተው የሶፍትዌር መቋረጥ ዙሪያ የኩባንያውን ስህተት አመነ
ማርክ ዙከርበርግ ለሠራተኞቹ ባስተላለፈው ውስጣዊ መልዕክት፣ ኩባንያው በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ላይ ባደረገው ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይና የሠራተኞች መዋቅር ለውጥ ምክንያት ስህተቶች መፈጠራቸውን ገልጿል።
ሜታ ከኦፕንኤአይ እና ማይክሮሶፍት ጋር ለመወዳደር ቢሊዮን ዶላሮችን እያፈሰሰ ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ማርክ ዙከርበርግ ለሠራተኞቹ ባስተላለፈው ውስጣዊ መልዕክት፣ ኩባንያው በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ላይ ባደረገው ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይና የሠራተኞች መዋቅር ለውጥ ምክንያት ስህተቶች መፈጠራቸውን ገልጿል።
ሜታ ከኦፕንኤአይ እና ማይክሮሶፍት ጋር ለመወዳደር ቢሊዮን ዶላሮችን እያፈሰሰ ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13👍5
ሶማሊያ ለቱርክ 3 የነዳጅ እና ጋዝ ፍለጋ ቀጠናዎችን ፈቀደች፤ ተጨማሪ ለመስጠትም ዝግጁ መሆኗን ገለጸች
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ሀገራቸው ካሏት 12 የባህር ላይ የሃይድሮካርቦን (የነዳጅ እና ጋዝ) ፍለጋ ቀጠናዎች መካከል ሶስቱን ለቱርክ መስጠታቸውን አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ ይህ አጋርነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ተጨባጭ እና ቀጣይነት ያለው የደህንነትና የልማት ድጋፍ የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል።
ቀሪዎቹ ዘጠኝ ብሎኮች ለምዕራባውያን ኩባንያዎች የተሰጡ ቢሆንም፣ አንደኛው ኩባንያ የኢንቨስትመንት አቅም ማነስን በመጥቀስ ሰባቱን ብሎኮች በቅርቡ መልሶ ማስረከቡ ተገልጿል። ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በሀገሪቱ ከሚገኝ መገናኛ ብዙሃን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ቱርክ ካስፈለጋት በቀጣይም ከተሰጧት ሶስት ቀጠናዎችን በተጨማሪ ሌሎችንም ለመስጠት ሀገራቸው ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።
ከበርካታ አስርት ዓመታት ግጭት በኋላ ወደ መረጋጋት በተወሰነ ደረጃ እየተመለሰች የምትገኘው ሶማሊያ፣ የሃይድሮካርቦን ፍለጋ መርሃ ግብሯ ለኢኮኖሚ እድገቷ ስትራቴጂካዊ ፋይዳ እንዳለው አምናበታለች። የሀገሪቱ የባህር ክልል ከፍተኛ ያልተነካ የነዳጅና ጋዝ ክምችት እንዳለው ቢገመትም፣ በንግድ ደረጃ ማውጣት ግን የረጅም ጊዜ እቅድ መሆኑ ተመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ሀገራቸው ካሏት 12 የባህር ላይ የሃይድሮካርቦን (የነዳጅ እና ጋዝ) ፍለጋ ቀጠናዎች መካከል ሶስቱን ለቱርክ መስጠታቸውን አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ ይህ አጋርነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ተጨባጭ እና ቀጣይነት ያለው የደህንነትና የልማት ድጋፍ የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል።
ቀሪዎቹ ዘጠኝ ብሎኮች ለምዕራባውያን ኩባንያዎች የተሰጡ ቢሆንም፣ አንደኛው ኩባንያ የኢንቨስትመንት አቅም ማነስን በመጥቀስ ሰባቱን ብሎኮች በቅርቡ መልሶ ማስረከቡ ተገልጿል። ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በሀገሪቱ ከሚገኝ መገናኛ ብዙሃን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ቱርክ ካስፈለጋት በቀጣይም ከተሰጧት ሶስት ቀጠናዎችን በተጨማሪ ሌሎችንም ለመስጠት ሀገራቸው ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።
ከበርካታ አስርት ዓመታት ግጭት በኋላ ወደ መረጋጋት በተወሰነ ደረጃ እየተመለሰች የምትገኘው ሶማሊያ፣ የሃይድሮካርቦን ፍለጋ መርሃ ግብሯ ለኢኮኖሚ እድገቷ ስትራቴጂካዊ ፋይዳ እንዳለው አምናበታለች። የሀገሪቱ የባህር ክልል ከፍተኛ ያልተነካ የነዳጅና ጋዝ ክምችት እንዳለው ቢገመትም፣ በንግድ ደረጃ ማውጣት ግን የረጅም ጊዜ እቅድ መሆኑ ተመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10👍7
የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ከ40 ዓመታት በኋላ የነዳጅ ምርት ማጓጓዝ ጀመረ
የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት (ኢባትሎ) ሀገሪቱ ከውጭ የምታስገባውን የነዳጅ ምርት የማጓጓዝ ሥራ ከ40 ዓመታት በኋላ በድጋሚ መጀመሩን አስታወቀ። ተቋሙ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከናይጄሪያ የተገዛን የኤቪዬሽን (የአውሮፕላን) እና የናፍጣ ነዳጅ በቻርተር መርከቦች ማጓጓዝ ችሏል።
በሆርሙዝ ባህር ሰርጥ አካባቢ በተቀሰቀሰው ግጭት ምክንያት በተፈጠረው የትራንስፖርት መስተጓጎል እና በሀገር ውስጥ እየጨመረ የመጣውን የነዳጅ ፍላጎት ለማሟላት መንግሥት የነዳጅ ግዢ ምንጮቹን እያሰፋ ይገኛል።
በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያለበትን ከፍተኛ የአውሮፕላን ነዳጅ ፍላጎት ለማሟላትና አማራጭ መስመሮችን ለመጠቀም ከናይጄሪያው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ግዢ ተፈጽሟል።
ኢባትሎ እንዳስታወቀው ተቋሙ መንግሥት በፈጠረው ምቹ ሁኔታ በመጠቀም 120 ሺህ ሜትሪክ ቶን የአውሮፕላን እና የናፍጣ ነዳጅ በሦስት ተከታታይ ጉዞዎች ወደ ጅቡቲው ሆራይዘን ተርሚናል ማጓጓዝ ችሏል። ይህ ስኬት ነዳጅ የማጓጓዝ ልምድ ላልነበረውና "አቅም የለውም" ተብሎ ለሚታሰበው የሎጂስቲክስ ተቋም ትልቅ የሥራ ክንውን መሆኑን አስምሮበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት (ኢባትሎ) ሀገሪቱ ከውጭ የምታስገባውን የነዳጅ ምርት የማጓጓዝ ሥራ ከ40 ዓመታት በኋላ በድጋሚ መጀመሩን አስታወቀ። ተቋሙ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከናይጄሪያ የተገዛን የኤቪዬሽን (የአውሮፕላን) እና የናፍጣ ነዳጅ በቻርተር መርከቦች ማጓጓዝ ችሏል።
በሆርሙዝ ባህር ሰርጥ አካባቢ በተቀሰቀሰው ግጭት ምክንያት በተፈጠረው የትራንስፖርት መስተጓጎል እና በሀገር ውስጥ እየጨመረ የመጣውን የነዳጅ ፍላጎት ለማሟላት መንግሥት የነዳጅ ግዢ ምንጮቹን እያሰፋ ይገኛል።
በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያለበትን ከፍተኛ የአውሮፕላን ነዳጅ ፍላጎት ለማሟላትና አማራጭ መስመሮችን ለመጠቀም ከናይጄሪያው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ግዢ ተፈጽሟል።
ኢባትሎ እንዳስታወቀው ተቋሙ መንግሥት በፈጠረው ምቹ ሁኔታ በመጠቀም 120 ሺህ ሜትሪክ ቶን የአውሮፕላን እና የናፍጣ ነዳጅ በሦስት ተከታታይ ጉዞዎች ወደ ጅቡቲው ሆራይዘን ተርሚናል ማጓጓዝ ችሏል። ይህ ስኬት ነዳጅ የማጓጓዝ ልምድ ላልነበረውና "አቅም የለውም" ተብሎ ለሚታሰበው የሎጂስቲክስ ተቋም ትልቅ የሥራ ክንውን መሆኑን አስምሮበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍4🥱3🤪3👏2
ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ የበኩር ልጆች ወይም የመጀመሪያ ልጆች ከፍ ያለ I.Q አላቸው ከታናናሽ ወንድም እና እህቶቻቸዉ በተሻለ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤29👍6🤝4😢3👌3👏1💯1🤷1
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ።
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲሄድ በነበረ ተሽከርካሪ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል።
አደጋው የደረሰው ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ ነው።
ዛሬ ሰኔ 08/10/18ዓ.ም ማለዳ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ አውቶቡስ በተለምዶ ሐረጎ እየተባለ በሚጠራው መንገድ ላይ በደረሠበት አደጋ እስካሁን የ28 ሰው ሕይወት ሲያልፍ በርካቶች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባተቸዋል።
የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ገብቶ ነው አደጋው የደረሠው።
በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ አሁንም ርብርብ እየተደረገ መኾኑን የገለጸው ፓሊስ የአደጋውን ምክንያት በመጣራት ላይ ነው ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲሄድ በነበረ ተሽከርካሪ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል።
አደጋው የደረሰው ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ ነው።
ዛሬ ሰኔ 08/10/18ዓ.ም ማለዳ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ አውቶቡስ በተለምዶ ሐረጎ እየተባለ በሚጠራው መንገድ ላይ በደረሠበት አደጋ እስካሁን የ28 ሰው ሕይወት ሲያልፍ በርካቶች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባተቸዋል።
የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ገብቶ ነው አደጋው የደረሠው።
በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ አሁንም ርብርብ እየተደረገ መኾኑን የገለጸው ፓሊስ የአደጋውን ምክንያት በመጣራት ላይ ነው ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢32💔26❤7👍2🙏1🥱1
በመጨረሻም ተስማሙ‼️
አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም ከስምምነቱ ደረሱ።
በመጪው አርብ በስዊዘርላንድ ጀኔቫ ሊፈራረሙ ቀጠሮ ይዘዋል።
ይህን ተከትሎ ሆርሙዝ ክፈት መደረጉን፣ በኢራን ላይ የተጣለው የባህር ላይ እገዳ መነሳቱን ትራምፕ አስታውቀዋል።
ኢራንም ስምምነቱን መቀበሏን የገለፀች ሲሆን ሊባኖስን ጨምሮ ጦርነቱ ሙሉ ለሙሉ እንዲቆም ተስማምቻለሁ ብላለች። ይህ የትራምፕ ስምምነት እስራኤልን ከጨዋታው ውጪ ማድረጉ አነጋጋሪ ሆኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም ከስምምነቱ ደረሱ።
በመጪው አርብ በስዊዘርላንድ ጀኔቫ ሊፈራረሙ ቀጠሮ ይዘዋል።
ይህን ተከትሎ ሆርሙዝ ክፈት መደረጉን፣ በኢራን ላይ የተጣለው የባህር ላይ እገዳ መነሳቱን ትራምፕ አስታውቀዋል።
ኢራንም ስምምነቱን መቀበሏን የገለፀች ሲሆን ሊባኖስን ጨምሮ ጦርነቱ ሙሉ ለሙሉ እንዲቆም ተስማምቻለሁ ብላለች። ይህ የትራምፕ ስምምነት እስራኤልን ከጨዋታው ውጪ ማድረጉ አነጋጋሪ ሆኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍23🕊7🎉3❤2👏1
የተባበሩት አረብ #ኤምሬትስ የሚሰነዘሩባትን ጥቃቶች ለማስቆም #ለኢራን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር መክፈሏ ተዘገበ
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በኢራን የሚሰነዘሩባት ጥቃቶች እንዲቆሙላት ለቴህራን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር መክፈሏን ሮይተርስ ዘገበ።ኤምሬትስ እስካሁን 3 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን የከፈለች ሲሆን የስምምነቱ ጠቅላላ መጠን እስከ 10 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ ይችላል ሲሉ ሁለት የቀጠናው የመረጃ ምንጮች ገልጸዋል። ሌሎች ሁለት ምንጮች ደግሞ ለሮይተርስ እንደተናገሩት ኤምሬትስ ለኢራን የምትከፍለው ጠቅላላ ገንዘብ 20 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል።
ክስተቱ አቡ ዳቢ እጅግ አስገራሚ በሆነ መልኩ የአቋም ለውጥ ማድረጓን የሚያሳይ ሲሆን፥ ኢራንም ከጦርነቱ ይበልጥ ጠንክራ መውጣቷን የሚያመላክት ሆኗል ሲል ዘገባው አመላክቷል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በጦርነቱ ወቅት በኢራን ላይ በደርዘን የሚቆጠሩ ጥቃቶችን በመሰንዘር ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጎን ተሰልፋ የነበረች ሲሆን፥ በተጨማሪም ግጭቱን ለማስቆም ፓኪስታን የምታደርገውን የሽምግልና ጥረት እንድታቆም ሞክራ ነበር።
ሳዑዲ ዓረቢያ ለኢስላማባድ አዲስ ብድር ለመስጠት የተገደደችውም፥ ኤምሬትስ ፓኪስታን የውይይት መድረክ በማዘጋጀቷ እንደ ቅጣት በመቁጠር ያለባትን ዕዳ በአስቸኳይ እንድትከፍል መጠየቋን ተከትሎ ነው።
ባለፈው ሳምንት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሀገሪቱ ብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ እና የአቡ ዳቢ ምክትል ገዥ ከሆኑት ሼክ ታህኑን ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ለሚደረግ ስብሰባ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ አባላትን ተቀብላለች። በአሜሪካ ማዕቀብ የተጣለባቸው እነዚህ የአብዮታዊ ዘብ ባለሥልጣናት ያረፉትም በታህኑን የክብር እንግዶች ማረፊያ ቤት ውስጥ ነበር።
ብሉምበርግ በዚህ ሳምንት እንደዘገበው ከሆነ ደግሞ፥ ኤምሬትስ ውጥረቶችን ለማርገብ ከከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣናት ጋር ፊት ለፊት የሚደረጉ ውይይቶችን ለማካሄድ ዲፕሎማቶቿን ልካለች።
አንድ የባሕረ ሰላጤው ዲፕሎማት ለኤምኢኢ (MEE) እንደተናገሩት፥ መንግሥታቸው ይህ ስብሰባ የተካሄደው በቴህራን ውስጥ እንደሆነ የሚያምን ሲሆን ይህም ኤምሬትስ ጥቃት እንዳይሰነዘርባት ለማድረግ የተከናወነ ጥረት አካል ነው ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በኢራን የሚሰነዘሩባት ጥቃቶች እንዲቆሙላት ለቴህራን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር መክፈሏን ሮይተርስ ዘገበ።ኤምሬትስ እስካሁን 3 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን የከፈለች ሲሆን የስምምነቱ ጠቅላላ መጠን እስከ 10 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ ይችላል ሲሉ ሁለት የቀጠናው የመረጃ ምንጮች ገልጸዋል። ሌሎች ሁለት ምንጮች ደግሞ ለሮይተርስ እንደተናገሩት ኤምሬትስ ለኢራን የምትከፍለው ጠቅላላ ገንዘብ 20 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል።
ክስተቱ አቡ ዳቢ እጅግ አስገራሚ በሆነ መልኩ የአቋም ለውጥ ማድረጓን የሚያሳይ ሲሆን፥ ኢራንም ከጦርነቱ ይበልጥ ጠንክራ መውጣቷን የሚያመላክት ሆኗል ሲል ዘገባው አመላክቷል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በጦርነቱ ወቅት በኢራን ላይ በደርዘን የሚቆጠሩ ጥቃቶችን በመሰንዘር ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጎን ተሰልፋ የነበረች ሲሆን፥ በተጨማሪም ግጭቱን ለማስቆም ፓኪስታን የምታደርገውን የሽምግልና ጥረት እንድታቆም ሞክራ ነበር።
ሳዑዲ ዓረቢያ ለኢስላማባድ አዲስ ብድር ለመስጠት የተገደደችውም፥ ኤምሬትስ ፓኪስታን የውይይት መድረክ በማዘጋጀቷ እንደ ቅጣት በመቁጠር ያለባትን ዕዳ በአስቸኳይ እንድትከፍል መጠየቋን ተከትሎ ነው።
ባለፈው ሳምንት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሀገሪቱ ብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ እና የአቡ ዳቢ ምክትል ገዥ ከሆኑት ሼክ ታህኑን ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ለሚደረግ ስብሰባ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ አባላትን ተቀብላለች። በአሜሪካ ማዕቀብ የተጣለባቸው እነዚህ የአብዮታዊ ዘብ ባለሥልጣናት ያረፉትም በታህኑን የክብር እንግዶች ማረፊያ ቤት ውስጥ ነበር።
ብሉምበርግ በዚህ ሳምንት እንደዘገበው ከሆነ ደግሞ፥ ኤምሬትስ ውጥረቶችን ለማርገብ ከከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣናት ጋር ፊት ለፊት የሚደረጉ ውይይቶችን ለማካሄድ ዲፕሎማቶቿን ልካለች።
አንድ የባሕረ ሰላጤው ዲፕሎማት ለኤምኢኢ (MEE) እንደተናገሩት፥ መንግሥታቸው ይህ ስብሰባ የተካሄደው በቴህራን ውስጥ እንደሆነ የሚያምን ሲሆን ይህም ኤምሬትስ ጥቃት እንዳይሰነዘርባት ለማድረግ የተከናወነ ጥረት አካል ነው ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍5🙈4🤣1👀1🙊1