መረጃ‼️
ከተያዘው ሰኔ እስከ መስከረም ባሉት ወራት በአፍሪካ ቀንድ ከመደበኛው ያነሰ ዝናብ ይኖራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያ ማዕከል አስታወቀ።
ማዕከሉ፣ በተለይ በማዕከላዊ፣ በሰሜን ምስራቅና ሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ደቡባዊ ሱዳን፣ ሰሜናዊ ኡጋንዳ፣ ከመደበኛው ያነሰ ዝናብ ይጥላል የሚል ከፍ ያለ ትንበያ መኖሩን ጠቅሷል።
በተጠቀሱት የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሰኔ እና ሐምሌ የአዝመራ መዝሪያ ወቅቶች ናቸው።
ባንጻሩ፣ ደቡባዊ ምስራቅ ኢትዮጵያን ጨምሮ አንዳንድ የቀጠናው አካባቢዎች ከፍ ያለ ዝናብ ሊያገኙ እንደሚችሉ ማዕከሉ ተንብዩዋል።
በመደበኛው ጊዜ ወይም ቀድመው ዝናብ ያገኛሉ ከተባሉት የቀጠናው አካባቢዎች መካከል ደሞ፣ የሰሜናዊ መካከለኛው ኢትዮጵያ አካባቢዎች ይገኙበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከተያዘው ሰኔ እስከ መስከረም ባሉት ወራት በአፍሪካ ቀንድ ከመደበኛው ያነሰ ዝናብ ይኖራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያ ማዕከል አስታወቀ።
ማዕከሉ፣ በተለይ በማዕከላዊ፣ በሰሜን ምስራቅና ሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ደቡባዊ ሱዳን፣ ሰሜናዊ ኡጋንዳ፣ ከመደበኛው ያነሰ ዝናብ ይጥላል የሚል ከፍ ያለ ትንበያ መኖሩን ጠቅሷል።
በተጠቀሱት የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሰኔ እና ሐምሌ የአዝመራ መዝሪያ ወቅቶች ናቸው።
ባንጻሩ፣ ደቡባዊ ምስራቅ ኢትዮጵያን ጨምሮ አንዳንድ የቀጠናው አካባቢዎች ከፍ ያለ ዝናብ ሊያገኙ እንደሚችሉ ማዕከሉ ተንብዩዋል።
በመደበኛው ጊዜ ወይም ቀድመው ዝናብ ያገኛሉ ከተባሉት የቀጠናው አካባቢዎች መካከል ደሞ፣ የሰሜናዊ መካከለኛው ኢትዮጵያ አካባቢዎች ይገኙበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16🙏7👍2
“ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ ሌሎች ተከሳሾች ለችሎት እንዲቀርቡ የጋዜጣ ጥሪ እንዲወጣ ታዘዘ።”
ፖሊስ የሙስና ወንጀል ተከሰው በፖሊስ የፍለጋ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱትን ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ አራት ግለሰቦችን ፖሊስ ለፍርድ ቤት ማቅረብ አልቻለም።
ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ሲሆን፣ በ13 ተከሳሾች ላይ የተመሰረተውን ክስ መርምሯል።
በዚህ መዝገብ ውስጥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከፍተኛ ኃላፊዎችም ተካተዋል።
አቃቤ ህግ ተከሳሾቹ ስልጣናቸውን ከህግ ውጭ በመጠቀምና የመንግስት ሥራን ተገቢ ባልሆነ መንገድ በመምራት ጉዳት አድርሰዋል በሚል ክስ አቅርቧል።
ለዛሬ ተይዞ በነበረው ችሎት ከ6ኛ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር የተመዘገቡ ተከሳሾች ባለመገኘታቸው ሂደቱ ተራዝሟል። ፍርድ ቤቱም እነዚህ ግለሰቦች በጋዜጣ ጥሪ እንዲጠሩ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በተለይ ወ/ሮ በረከት ወርቁ ከሀገር ውጭ መገኘታቸው በማህበራዊ ሚዲያ በሚታዩ መረጃዎች መጠቆሙን ተከትሎ፣ ጥሪው በአዲስ ዘመን እና በኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጦች እንዲታተም ተወስኗል።
ችሎቱ አቃቤ ህግ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ በማዘዝ፣ የጉዳዩን ቀጣይ ሂደት ለመከታተል ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል።
Via ሸገር ኤፍኤም
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ፖሊስ የሙስና ወንጀል ተከሰው በፖሊስ የፍለጋ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱትን ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ አራት ግለሰቦችን ፖሊስ ለፍርድ ቤት ማቅረብ አልቻለም።
ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ሲሆን፣ በ13 ተከሳሾች ላይ የተመሰረተውን ክስ መርምሯል።
በዚህ መዝገብ ውስጥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከፍተኛ ኃላፊዎችም ተካተዋል።
አቃቤ ህግ ተከሳሾቹ ስልጣናቸውን ከህግ ውጭ በመጠቀምና የመንግስት ሥራን ተገቢ ባልሆነ መንገድ በመምራት ጉዳት አድርሰዋል በሚል ክስ አቅርቧል።
ለዛሬ ተይዞ በነበረው ችሎት ከ6ኛ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር የተመዘገቡ ተከሳሾች ባለመገኘታቸው ሂደቱ ተራዝሟል። ፍርድ ቤቱም እነዚህ ግለሰቦች በጋዜጣ ጥሪ እንዲጠሩ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በተለይ ወ/ሮ በረከት ወርቁ ከሀገር ውጭ መገኘታቸው በማህበራዊ ሚዲያ በሚታዩ መረጃዎች መጠቆሙን ተከትሎ፣ ጥሪው በአዲስ ዘመን እና በኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጦች እንዲታተም ተወስኗል።
ችሎቱ አቃቤ ህግ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ በማዘዝ፣ የጉዳዩን ቀጣይ ሂደት ለመከታተል ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል።
Via ሸገር ኤፍኤም
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19🤪14😁5👍4👏1🤯1🤣1
በፓስተሩ ያልተገባ ድርጊት ህይወቱ ያለፈዉ ወጣት‼️
ዋቅጅራ ገነት ይባላል፡ በምዕራብ ወለጋ የቂልሹ ካራ ተወላጅ ነው። በዩናይትድ ስቴትስ ይኖር የነበረ ለሰርግ ወደ ኢትዮጵያ በመጣበት ሰአት በህክምና የልብ ድካም እንዳለበት እና ቀዶ ጥገና ማድረግ እንዳለበት ተወሰነ።
የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የሆነችዉ ፍቅረኛው ህክምናውን ትቶ ፓስተር መሰረት ታዬ የሚባል ግለሰብ ጋር እንዲሄድ ምክር ትሰጠዋለችሽ። ግለሰቡም ወደ ፓስተሩ ሔዶ መጀመሪያ የተገጠመለትን የኦክስጅን ገመድ ፓስትሩ አስወገደለት።
"አዲስ ልብ ሰጥቼሃለሁ ተፈውሰሃል" ብሎም ላከው። ዋቅጂራ የሕክምና ባለሙያዎችን ንግግር ችላ ብሎ የነቢዩን ምክር ተቀበለ። በሚያሳዝን ሁኔታም ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የመጣዉ ተስፈኛዉ ወጣት ወደ ቤቱ ለማረፍ እንደገባ እስከወዲያኛዉ አሸለበ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዋቅጅራ ገነት ይባላል፡ በምዕራብ ወለጋ የቂልሹ ካራ ተወላጅ ነው። በዩናይትድ ስቴትስ ይኖር የነበረ ለሰርግ ወደ ኢትዮጵያ በመጣበት ሰአት በህክምና የልብ ድካም እንዳለበት እና ቀዶ ጥገና ማድረግ እንዳለበት ተወሰነ።
የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የሆነችዉ ፍቅረኛው ህክምናውን ትቶ ፓስተር መሰረት ታዬ የሚባል ግለሰብ ጋር እንዲሄድ ምክር ትሰጠዋለችሽ። ግለሰቡም ወደ ፓስተሩ ሔዶ መጀመሪያ የተገጠመለትን የኦክስጅን ገመድ ፓስትሩ አስወገደለት።
"አዲስ ልብ ሰጥቼሃለሁ ተፈውሰሃል" ብሎም ላከው። ዋቅጂራ የሕክምና ባለሙያዎችን ንግግር ችላ ብሎ የነቢዩን ምክር ተቀበለ። በሚያሳዝን ሁኔታም ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የመጣዉ ተስፈኛዉ ወጣት ወደ ቤቱ ለማረፍ እንደገባ እስከወዲያኛዉ አሸለበ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😁48🙈28💔14👀13❤8😢8🤔5🤯3🙊3👍2🆒1
በአለም ዋንጫ ታሪክ የመጀመሪያው ሶማሊያዊ ዳኛ ለመሆን የታጨው ዑመር አርታን ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ተከለከለ
በአለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) እውቅና ያገኘውና በ2026ቱ የአለም ዋንጫ ላይ እንዲዳኝ ተመርጦ የነበረው ዑመር አርታን፣ ወደ አሜሪካ ለመግባት ያደረገው የቪዛ ጥያቄ ውድቅ ተደርጎበታል።
ይህ ውሳኔ በሶማሊያ ስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።
የቪዛው መከልከል ግልፅ ምክንያት ባይቀመጥም፣ ውሳኔው ዳኛው በታሪካዊው መድረክ ላይ የመሳተፍ ህልሙን አደጋ ላይ ጥሎታል።
ፊፋ እና የሶማሊያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጉዳዩን ለማስቀየር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፣ ጥብቅ የሆነው የአሜሪካ የቪዛ ፖሊሲ ትልቅ ማነቆ ሆኗል።
በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ድንቅ ብቃቱን ያሳየው አርታን፣ ይህ እገዳ ካልተነሳለት ታላቁን የስፖርት መድረክ ያጣዋል።
ቢቢሲ ስፖርት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) እውቅና ያገኘውና በ2026ቱ የአለም ዋንጫ ላይ እንዲዳኝ ተመርጦ የነበረው ዑመር አርታን፣ ወደ አሜሪካ ለመግባት ያደረገው የቪዛ ጥያቄ ውድቅ ተደርጎበታል።
ይህ ውሳኔ በሶማሊያ ስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።
የቪዛው መከልከል ግልፅ ምክንያት ባይቀመጥም፣ ውሳኔው ዳኛው በታሪካዊው መድረክ ላይ የመሳተፍ ህልሙን አደጋ ላይ ጥሎታል።
ፊፋ እና የሶማሊያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጉዳዩን ለማስቀየር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፣ ጥብቅ የሆነው የአሜሪካ የቪዛ ፖሊሲ ትልቅ ማነቆ ሆኗል።
በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ድንቅ ብቃቱን ያሳየው አርታን፣ ይህ እገዳ ካልተነሳለት ታላቁን የስፖርት መድረክ ያጣዋል።
ቢቢሲ ስፖርት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16🤣12💔9👍2🤔2
በቤት ጣራ ላይ ሶላር ፓኔል እንዲገጠም የሚያስገድድ መመሪያ ተዘጋጀ‼
ለጊዜው የሚተገበረው አዲስ በሚገነቡ ቤቶች ላይ ነው ተብሏል።
አዲስ የመኖሪያ ቤቶችና ሕንፃዎችን በሚገነቡበት ወቅት በጣሪያቸው ላይ የሶላር ፓኔል ቴክኖሎጂን እንዲገጥሙ የሚያደርግ አዲስ ብሔራዊ መመሪያ መዘጋጀቱን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ከመጪው ሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይህ መመሪያ፣ በሀገሪቱ ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት በታዳሽ ኃይል ለመተካት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ሕጉ ለጊዜው አስገዳጅ ባይሆንም የመጀመሪያ ምዕራፍ ትግበራው በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚጀመር ተገልጿል።
የሶላር ቴክኖሎጂዎች ዋጋ ከፍተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞም፣ የመግዛት አቅም ለሌላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ልዩ ልዩ ማበረታቻዎች እንደሚዘጋጁ ሚኒስቴሩ አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ለጊዜው የሚተገበረው አዲስ በሚገነቡ ቤቶች ላይ ነው ተብሏል።
አዲስ የመኖሪያ ቤቶችና ሕንፃዎችን በሚገነቡበት ወቅት በጣሪያቸው ላይ የሶላር ፓኔል ቴክኖሎጂን እንዲገጥሙ የሚያደርግ አዲስ ብሔራዊ መመሪያ መዘጋጀቱን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ከመጪው ሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይህ መመሪያ፣ በሀገሪቱ ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት በታዳሽ ኃይል ለመተካት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ሕጉ ለጊዜው አስገዳጅ ባይሆንም የመጀመሪያ ምዕራፍ ትግበራው በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚጀመር ተገልጿል።
የሶላር ቴክኖሎጂዎች ዋጋ ከፍተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞም፣ የመግዛት አቅም ለሌላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ልዩ ልዩ ማበረታቻዎች እንደሚዘጋጁ ሚኒስቴሩ አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣30❤21👍5👏1😡1
በመጪው ክረምት የተሻለ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ እንደሚኖሩ ተገለፀ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመጪው ክረምት ወቅት ሊኖር የሚችለውን የኃይል መቆራረጥ ችግር አስቀድሞ ለመከላከል ሰፋፊ ፕሮጀክቶችን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል ።
በአገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ገበየሁ ሊካሳ የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እየተሰሩ ባሉ ስራዎች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በዕቅድ የሚቋረጥ የኃይል ማስተካከያ እንደሚኖር መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል ።
በአዲስ አበባ ከተማ 4ኛው ምዕራፍ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክትን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ሲባል ከመጋቢት ወር ጀምሮ የኃይል መቆራረጥን ከፍ ማለታቸዉን የገለፀው አገልግሎቱ ይህም አስተማማኝና ጥራት ያለዉ የሀይል አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ የሚከናወን መሆኑን ገልጿል ።
አብዛኛዉ የዲስትሪቢዩሽን መስመር ረጅም ጊዜ ያገለገለ በመሆኑ ለመልሶ ግንባታው ትልቅ የፋይናንስ አቅምና ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ በዕቅድ የሚቋረጥ የኃይል ድግግሞሽ መብዛቱን አገልግሎቱ ተናግሯል።
በመጪው የክረምት ወቅት የተሻለ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በዕቅድ የሚቋረጡ የፕሮጀክት ስራዎችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጨምሮ አስታውቋል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመጪው ክረምት ወቅት ሊኖር የሚችለውን የኃይል መቆራረጥ ችግር አስቀድሞ ለመከላከል ሰፋፊ ፕሮጀክቶችን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል ።
በአገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ገበየሁ ሊካሳ የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እየተሰሩ ባሉ ስራዎች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በዕቅድ የሚቋረጥ የኃይል ማስተካከያ እንደሚኖር መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል ።
በአዲስ አበባ ከተማ 4ኛው ምዕራፍ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክትን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ሲባል ከመጋቢት ወር ጀምሮ የኃይል መቆራረጥን ከፍ ማለታቸዉን የገለፀው አገልግሎቱ ይህም አስተማማኝና ጥራት ያለዉ የሀይል አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ የሚከናወን መሆኑን ገልጿል ።
አብዛኛዉ የዲስትሪቢዩሽን መስመር ረጅም ጊዜ ያገለገለ በመሆኑ ለመልሶ ግንባታው ትልቅ የፋይናንስ አቅምና ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ በዕቅድ የሚቋረጥ የኃይል ድግግሞሽ መብዛቱን አገልግሎቱ ተናግሯል።
በመጪው የክረምት ወቅት የተሻለ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በዕቅድ የሚቋረጡ የፕሮጀክት ስራዎችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጨምሮ አስታውቋል ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12👍3🤔2🤪2😢1
አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Photo
“ብቻሽን ልትቀሪ ትችያለሽ!” 👉 ዶናልድ ትራምፕ
ትራምፕ ለእስራኤል ማስጠንቀቂያ መስጠታቸው ተሰማ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ መለገሳቸውን ይፋ አድርገዋል። እስራኤል ከኢራን ጋር የምታደርገውን ጦርነት በድጋሚ የምትቀሰቅስ ከሆነ አሜሪካ እንደማትደግፋትና ብቻዋን ልትቀር እንደምትችል ትራምፕ ያስጠነቀቁ ሲሆን ለአክሲዮስ የዜና ወኪል በሰጡት መግለጫም “ቢቢ፤ ጥንቃቄ ብታደርግ ይሻላል፤ ካልሆነ ግን በቅርቡ ብቻህን ልትቀር ትችላለህ” ሲሉ በስልክ ጥሪያቸው ወቅት በግልጽ መናገራቸውን አረጋግጠዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ይህንን ማስጠንቀቂያ የሰጡት ቀጥተኛ ትዕዛዝ ለማስተላለፍ ሳይሆን የኔታንያሁን ውሳኔ ለመገደብ መሆኑን ገልጸው እኔ ያልኩት ነገር ቢኖር አዕምሯችንን መጠቀም አለብን የሚል ብቻ ነው ካሉ በኋላ በአሁኑ ወቅት ከኢራን ጋር በጣም ጠንካራ እና ጥሩ ስምምነት ለመፈረም መቃረባቸውን ጠቁመዋል። በተጨማሪም እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከመፈጸሟ ጥቂት ቀደም ብሎ ለአሜሪካ መንግስት አጭር መረጃ መስጠቷን ትራምፕ ገልጸው ይሁን እንጂ የጦር አውሮፕላኖቹ ቀድሞውኑ ወደ ስምሪት አቅንተው በነበረበት በዚያ አጣዳፊ ሰዓት ጭምር ጣልቃ በመግባት ጥቃቱ ውስን እና የተገደበ እንዲሆን ማድረጋቸውን ይፋ አድርገዋል።
ይህ በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ይፋ የሆነው አሜሪካ ከኢራን ጋር ዲፕሎማሲያዊ ስምምነት ላይ ለመድረስ ከፍተኛ ግፊት እያደረገች ባለችበት ወቅት ሲሆን በአንጻሩ ኔታንያሁ ኢራን በድጋሚ ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ ጠንካራ ወታደራዊ ርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን በገለጹበት ወቅት በመሆኑ በሁለቱ መሪዎች መካከል ያለው ስትራቴጂካዊ ልዩነት ከቀን ወደ ቀን እየሰፋ መምጣቱን ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ትራምፕ ለእስራኤል ማስጠንቀቂያ መስጠታቸው ተሰማ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ መለገሳቸውን ይፋ አድርገዋል። እስራኤል ከኢራን ጋር የምታደርገውን ጦርነት በድጋሚ የምትቀሰቅስ ከሆነ አሜሪካ እንደማትደግፋትና ብቻዋን ልትቀር እንደምትችል ትራምፕ ያስጠነቀቁ ሲሆን ለአክሲዮስ የዜና ወኪል በሰጡት መግለጫም “ቢቢ፤ ጥንቃቄ ብታደርግ ይሻላል፤ ካልሆነ ግን በቅርቡ ብቻህን ልትቀር ትችላለህ” ሲሉ በስልክ ጥሪያቸው ወቅት በግልጽ መናገራቸውን አረጋግጠዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ይህንን ማስጠንቀቂያ የሰጡት ቀጥተኛ ትዕዛዝ ለማስተላለፍ ሳይሆን የኔታንያሁን ውሳኔ ለመገደብ መሆኑን ገልጸው እኔ ያልኩት ነገር ቢኖር አዕምሯችንን መጠቀም አለብን የሚል ብቻ ነው ካሉ በኋላ በአሁኑ ወቅት ከኢራን ጋር በጣም ጠንካራ እና ጥሩ ስምምነት ለመፈረም መቃረባቸውን ጠቁመዋል። በተጨማሪም እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከመፈጸሟ ጥቂት ቀደም ብሎ ለአሜሪካ መንግስት አጭር መረጃ መስጠቷን ትራምፕ ገልጸው ይሁን እንጂ የጦር አውሮፕላኖቹ ቀድሞውኑ ወደ ስምሪት አቅንተው በነበረበት በዚያ አጣዳፊ ሰዓት ጭምር ጣልቃ በመግባት ጥቃቱ ውስን እና የተገደበ እንዲሆን ማድረጋቸውን ይፋ አድርገዋል።
ይህ በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ይፋ የሆነው አሜሪካ ከኢራን ጋር ዲፕሎማሲያዊ ስምምነት ላይ ለመድረስ ከፍተኛ ግፊት እያደረገች ባለችበት ወቅት ሲሆን በአንጻሩ ኔታንያሁ ኢራን በድጋሚ ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ ጠንካራ ወታደራዊ ርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን በገለጹበት ወቅት በመሆኑ በሁለቱ መሪዎች መካከል ያለው ስትራቴጂካዊ ልዩነት ከቀን ወደ ቀን እየሰፋ መምጣቱን ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17🤣15👍6💯2🤪1
ወደ እንግሊዝ ሲያቀኑ የነበሩ 300 ስደተኞች ታግተው ኩላሊታቸዉ እንደሚወጣ እንደተዛተባቸዉ ተሰማ
ባለፈው ክረምት ወደ እንግሊዝ ሲያቀኑ የነበሩ ከ300 በላይ ስደተኞች አፈና፣ድብደባ እና በግዳጅ የአካል ክፍሎችን እንደሚነጠቁ ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው ተሰምቷል።ወጣቶቹ ከኢራቅ ኩርዲስታን የመጡ ሲሆን ሁሉም በሊቢያ በሚኙ ሚሊሻዎች ከእያንዳንዳቸው ቤተሰቦቻቸው 5,000 ዶላር ለማስለቀቅ የተጠየቁ ሲሆን ገንዘቡን በፍጥነት ካልከፈሉ ኩላሊቶቻቸዉን እንደሚያጡ ተዝቶባቸዉ ነበር፡፡
ከእስር የተፈቱትን አንዳንድ ታጋቾች የግዳጅ ስራዎች መፈጸማቸውንም የሚያሳዩ የፎቶ ማስረጃዎችን አጋርተዋል፡፡የቀድሞዎቹ ምርኮኞች የደረሰባቸዉን የስቃይ ማስረጃ አሳይተዋል፡፡ ወደ 180 የሚጠጉ ሰዎች በአንድ ክፍል ውስጥ በጠባብ ሁኔታ ውስጥ እንደቆዩ ተናግረዋል፡፡ቢያንስ አንድ ታጋች የተገደለ ሲሆን ምን ያህሉ በምርኮ እንደሚቀሩ የታወቀ ነገር የለም።
ሚሊሻዎቹ በሊቢያ በኩል ወደ ሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ድረስ ፍልሰተኞቹ እየመራቸው ነበር ተብሏል። ሆኖም የስደተኞቹን ጉዞ ካደራጀው ከኢራቅ የኩርድ ህዝብ-ህገ-ወጥ አዘዋዋሪ ኖህ አሮን ጋር በክፍያ ላይ አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር።አሮን አሁን በፈረንሳይ በተለያዩ የገንዘብ ማጭበርበር እና የኮንትሮባንድ ወንጀሎች የ10 አመት እስራት ተፈርዶበታል።
Via_dagu
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ባለፈው ክረምት ወደ እንግሊዝ ሲያቀኑ የነበሩ ከ300 በላይ ስደተኞች አፈና፣ድብደባ እና በግዳጅ የአካል ክፍሎችን እንደሚነጠቁ ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው ተሰምቷል።ወጣቶቹ ከኢራቅ ኩርዲስታን የመጡ ሲሆን ሁሉም በሊቢያ በሚኙ ሚሊሻዎች ከእያንዳንዳቸው ቤተሰቦቻቸው 5,000 ዶላር ለማስለቀቅ የተጠየቁ ሲሆን ገንዘቡን በፍጥነት ካልከፈሉ ኩላሊቶቻቸዉን እንደሚያጡ ተዝቶባቸዉ ነበር፡፡
ከእስር የተፈቱትን አንዳንድ ታጋቾች የግዳጅ ስራዎች መፈጸማቸውንም የሚያሳዩ የፎቶ ማስረጃዎችን አጋርተዋል፡፡የቀድሞዎቹ ምርኮኞች የደረሰባቸዉን የስቃይ ማስረጃ አሳይተዋል፡፡ ወደ 180 የሚጠጉ ሰዎች በአንድ ክፍል ውስጥ በጠባብ ሁኔታ ውስጥ እንደቆዩ ተናግረዋል፡፡ቢያንስ አንድ ታጋች የተገደለ ሲሆን ምን ያህሉ በምርኮ እንደሚቀሩ የታወቀ ነገር የለም።
ሚሊሻዎቹ በሊቢያ በኩል ወደ ሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ድረስ ፍልሰተኞቹ እየመራቸው ነበር ተብሏል። ሆኖም የስደተኞቹን ጉዞ ካደራጀው ከኢራቅ የኩርድ ህዝብ-ህገ-ወጥ አዘዋዋሪ ኖህ አሮን ጋር በክፍያ ላይ አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር።አሮን አሁን በፈረንሳይ በተለያዩ የገንዘብ ማጭበርበር እና የኮንትሮባንድ ወንጀሎች የ10 አመት እስራት ተፈርዶበታል።
Via_dagu
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16😢5👍3
ሿሿ ሲሰሩ የተያዙት ሴቶች‼️
የሿሿ ወንጀል የፈጸሙ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ሳሪስ አቦ የትራፊክ መብራት አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 A 02122 ኦሮ በሆነ ሚኒባስ ተሽከርካሪ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪና ተጠቃሚ በመምሰል አዲሱ መኮንንና ኢሳያስ ደገፋ የተባሉ የግል ተበዳዮችን በመጫን ጥቂት እንደተጓዙ ኪሳቸው ውስጥ የነበረውን የሞባይል ስልክ እና ገንዘብ ለመውሰድ ሲሞክሩ የግል ተበዳዮች ወንጀሉን ለመከላከል በሚሞክሩበት ወቅት ገፍትረዋቸው በፍጥነት በመጓዝ ላይ ሳሉ ከሌላ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨት ቆመዋል።
በወቅቱ ድርጊቱን በተመለከተው የአካባቢው ህብረተሰብና በትራፊክ ፖሊስ አማካኝነት በተሽከርካሪው ውስጥ የነበሩ ትዕግስት ጌታቸው፣ ገነት ደሳለኝ፣ ሜላት ጌታቸው፣ እየሩሳሌም ጌታነህና መአዛ ማሞ የተባሉ ተጠርጣሪዎችን ከ6 የተለያዩ ስማርት ሞባይል ስልኮችና 11 ሚሞሪ ካርዶች ጋር ሊያዙ መቻላቸውን በወንጀል ምርመራ ም/ዋና ጠቅላይ መምሪያ የልዩ ልዩ እና የተደራጁ ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በተያዙ ተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢው ምርመራ የማስፋት ተግባር እየተከናወነ ሲሆን ሌሎች ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋልም ከፍተኛ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።
ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች እየተንቀሳቀሱ ወንጀሉን የሚፈፅሙ በመሆናቸው በእነዚህ ተጠርጣሪዎች ወንጀል የተፈጸመባቸው አዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በመቅረብ ስልኮቻቸውን መረከብ እንደሚችሉ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሿሿ ወንጀል የፈጸሙ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ሳሪስ አቦ የትራፊክ መብራት አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 A 02122 ኦሮ በሆነ ሚኒባስ ተሽከርካሪ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪና ተጠቃሚ በመምሰል አዲሱ መኮንንና ኢሳያስ ደገፋ የተባሉ የግል ተበዳዮችን በመጫን ጥቂት እንደተጓዙ ኪሳቸው ውስጥ የነበረውን የሞባይል ስልክ እና ገንዘብ ለመውሰድ ሲሞክሩ የግል ተበዳዮች ወንጀሉን ለመከላከል በሚሞክሩበት ወቅት ገፍትረዋቸው በፍጥነት በመጓዝ ላይ ሳሉ ከሌላ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨት ቆመዋል።
በወቅቱ ድርጊቱን በተመለከተው የአካባቢው ህብረተሰብና በትራፊክ ፖሊስ አማካኝነት በተሽከርካሪው ውስጥ የነበሩ ትዕግስት ጌታቸው፣ ገነት ደሳለኝ፣ ሜላት ጌታቸው፣ እየሩሳሌም ጌታነህና መአዛ ማሞ የተባሉ ተጠርጣሪዎችን ከ6 የተለያዩ ስማርት ሞባይል ስልኮችና 11 ሚሞሪ ካርዶች ጋር ሊያዙ መቻላቸውን በወንጀል ምርመራ ም/ዋና ጠቅላይ መምሪያ የልዩ ልዩ እና የተደራጁ ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በተያዙ ተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢው ምርመራ የማስፋት ተግባር እየተከናወነ ሲሆን ሌሎች ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋልም ከፍተኛ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።
ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች እየተንቀሳቀሱ ወንጀሉን የሚፈፅሙ በመሆናቸው በእነዚህ ተጠርጣሪዎች ወንጀል የተፈጸመባቸው አዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በመቅረብ ስልኮቻቸውን መረከብ እንደሚችሉ ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤24👍8🤣7🙉6
ዘመናዊ ሄሊኮፕተር በኢራን ተመቷል-ትራምፕ‼️
Apache የተሰኘ የአሜሪካ ዘመኒዊ እና ቅንጡ ሄሊኮፍተር በትናትናው ዕለት በሆርሙዝ ፓትሮል እያደረገ ባለበት ሰዓት በኢራን ተመቶ መውደቁን ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ገፃቸው አስፍረዋል።
በሄሊኮፕተሩ ውስጥ የነበሩ ሁለቱም አብራሪዎች ከሞት ተርፈዋል ብለዋል።
ኢራን ለፈፀመችው ጥቃት ምላሽ እንሰጣለን ብለዋል። የዚህ ሄሊኮፕተር ዋጋ 67 ሚሊዮን ዶላር አካባቢ ይገመታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
Apache የተሰኘ የአሜሪካ ዘመኒዊ እና ቅንጡ ሄሊኮፍተር በትናትናው ዕለት በሆርሙዝ ፓትሮል እያደረገ ባለበት ሰዓት በኢራን ተመቶ መውደቁን ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ገፃቸው አስፍረዋል።
በሄሊኮፕተሩ ውስጥ የነበሩ ሁለቱም አብራሪዎች ከሞት ተርፈዋል ብለዋል።
ኢራን ለፈፀመችው ጥቃት ምላሽ እንሰጣለን ብለዋል። የዚህ ሄሊኮፕተር ዋጋ 67 ሚሊዮን ዶላር አካባቢ ይገመታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍8😱4😁3🥰1👏1😢1
ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የትግራይ ተዋጊ ኃይል የበላይ አዛዥ ሆኑ!
ጊዜያዊ መንግስቱን በማፍረስ የራሱን አስተዳደር ያነበረው የሕወሓት ቡድን በትናንትናው ዕለት በክልሉ የሚተገበር አፋኝ ረቂቅ አዋጅ ማጽደቁ ይታወሳል። እንደ ሻብያ ሁሉ ወታደራዊ ግዳጅን ግዴታ የሚያደርገው ይህ አዋጅ ታድያ አንድ ልብ ያልተባለ ስልጣንን ለደብረጽዮን ገብረሚካኤል ሰጥቷል።
አንዳፍታ ሚዲያ በተመለከተው በዚህ አዋጅ ላይ የክልሉ ፕሬዝዳንት የክልሉ ተዋጊ ኃይሎች የበላይ አዛዥ እንዲሆኑ ደንግጓል። በዚህም መሰረት አዋጁ ደብረጽዮንን ከፕሬዝዳንትነታቸው ባለፈ የክልሉ ተዋጊ ኃይል የበላይ አዛዥ አድርጓቸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ጊዜያዊ መንግስቱን በማፍረስ የራሱን አስተዳደር ያነበረው የሕወሓት ቡድን በትናንትናው ዕለት በክልሉ የሚተገበር አፋኝ ረቂቅ አዋጅ ማጽደቁ ይታወሳል። እንደ ሻብያ ሁሉ ወታደራዊ ግዳጅን ግዴታ የሚያደርገው ይህ አዋጅ ታድያ አንድ ልብ ያልተባለ ስልጣንን ለደብረጽዮን ገብረሚካኤል ሰጥቷል።
አንዳፍታ ሚዲያ በተመለከተው በዚህ አዋጅ ላይ የክልሉ ፕሬዝዳንት የክልሉ ተዋጊ ኃይሎች የበላይ አዛዥ እንዲሆኑ ደንግጓል። በዚህም መሰረት አዋጁ ደብረጽዮንን ከፕሬዝዳንትነታቸው ባለፈ የክልሉ ተዋጊ ኃይል የበላይ አዛዥ አድርጓቸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😁14👍9❤8🤔5🤪4😢3🥰1🤯1🙈1🙊1
ኮንትሮባንድ የጫኑ ተሽከርካሪዎች እንዲወረሱ ተወሰነ
መፍትሔ ወይስ ተጨማሪ ስጋት?
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኮንትሮባንድ ማጓጓዣዎችን እስከ መውረስ የሚያደርስ የጉምሩክ ማሻሻያ አዋጅ በሁለት ተቃውሞና በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።
ቀደም ሲል የነበረው የ100 ሺህ ብር ቅጣት ማነስ ሕገ-ወጥ ንግዱን ሊያስቆም ባለመቻሉ ማሻሻያው ማስፈለጉ ተገልጿል።
አዲሱ አዋጅ ዕቃ ለመደበቅ የተለወጡ ወይም ሙሉ በሙሉ ኮንትሮባንድ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ያለዋጋ ግምታቸው ተወርሰው ቀጥታ ለመንግሥት ገቢ እንዲሆኑ በግልፅ ደንግጓል።
የአስመጪዎችን የመከራከር መብት ለማስከበርም፣ ይግባኝ ለመጠየቅ ሙሉ ታክስ መክፈል የነበረበት አሰራር ተቀይሮ አከራካሪውን 50% ብቻ በማስያዝ እንዲከራከሩ ተፈቅዷል።
ግዴታቸውን ባልተወጡ አጓጓዦችና መጋዘኖች ላይ ጠንከር ያለ አስተዳደራዊ ቅጣት የተጣለ ሲሆን፣ የጥንቃቄ ጉድለት ላሳዩ ባለቤቶችም የገንዘብ መቀጮ ተደንግጓል።
ተንታኞች ግን አዋጁ የይግባኝ ቅድመ-ሁኔታን ማቃለሉ ለነጋዴው መብት መከበር ትልቅ እመርታ ቢሆንም፣ ተሽከርካሪን ሙሉ በሙሉ መውረስ ግን ንብረታቸው በሾፌሮች ወይም በባለገንዘቦች ለሕገ-ወጥ ተግባር ለሚበዘበዝባቸው ባለቤቶች ላይ መራራና ያልተመጣጠነ ኪሳራ ሊያስከትል ይችላል ሲሉ ስጋታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
መፍትሔ ወይስ ተጨማሪ ስጋት?
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኮንትሮባንድ ማጓጓዣዎችን እስከ መውረስ የሚያደርስ የጉምሩክ ማሻሻያ አዋጅ በሁለት ተቃውሞና በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።
ቀደም ሲል የነበረው የ100 ሺህ ብር ቅጣት ማነስ ሕገ-ወጥ ንግዱን ሊያስቆም ባለመቻሉ ማሻሻያው ማስፈለጉ ተገልጿል።
አዲሱ አዋጅ ዕቃ ለመደበቅ የተለወጡ ወይም ሙሉ በሙሉ ኮንትሮባንድ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ያለዋጋ ግምታቸው ተወርሰው ቀጥታ ለመንግሥት ገቢ እንዲሆኑ በግልፅ ደንግጓል።
የአስመጪዎችን የመከራከር መብት ለማስከበርም፣ ይግባኝ ለመጠየቅ ሙሉ ታክስ መክፈል የነበረበት አሰራር ተቀይሮ አከራካሪውን 50% ብቻ በማስያዝ እንዲከራከሩ ተፈቅዷል።
ግዴታቸውን ባልተወጡ አጓጓዦችና መጋዘኖች ላይ ጠንከር ያለ አስተዳደራዊ ቅጣት የተጣለ ሲሆን፣ የጥንቃቄ ጉድለት ላሳዩ ባለቤቶችም የገንዘብ መቀጮ ተደንግጓል።
ተንታኞች ግን አዋጁ የይግባኝ ቅድመ-ሁኔታን ማቃለሉ ለነጋዴው መብት መከበር ትልቅ እመርታ ቢሆንም፣ ተሽከርካሪን ሙሉ በሙሉ መውረስ ግን ንብረታቸው በሾፌሮች ወይም በባለገንዘቦች ለሕገ-ወጥ ተግባር ለሚበዘበዝባቸው ባለቤቶች ላይ መራራና ያልተመጣጠነ ኪሳራ ሊያስከትል ይችላል ሲሉ ስጋታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤21🤪7👍6👀3👏1
መረጃ‼️
የሚንስትሮች ምክር ቤት ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከ2 ትሪሊዮን 339 ቢሊዮን በላይ በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቀረበ።
ረቂቅ በጀቱ፣ ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግሥታት ድጋፍ እና ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ የሚውል መኾኑን ምክር ቤቱ አስታውቋል።
ረቂቅ በጀቱ የተዘጋጀው፣ የ2019 የፌዴራል መንግሥት በጀት የ10 ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የኾነው የ2019-2021 የልማትና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችንና የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚና የፊሲካል ማዕቀፍን መሠረት በማድረግ መኾኑን ተገልጧል።
ለተያዘው በጀት ዓመት የተመደበው 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ትሪሊዮኑ ለመደበኛ ወጪ እና 415 ነጥብ 2 ቢሊዮኑ ለካፒታል ወጪ የተመደበ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሚንስትሮች ምክር ቤት ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከ2 ትሪሊዮን 339 ቢሊዮን በላይ በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቀረበ።
ረቂቅ በጀቱ፣ ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግሥታት ድጋፍ እና ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ የሚውል መኾኑን ምክር ቤቱ አስታውቋል።
ረቂቅ በጀቱ የተዘጋጀው፣ የ2019 የፌዴራል መንግሥት በጀት የ10 ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የኾነው የ2019-2021 የልማትና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችንና የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚና የፊሲካል ማዕቀፍን መሠረት በማድረግ መኾኑን ተገልጧል።
ለተያዘው በጀት ዓመት የተመደበው 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ትሪሊዮኑ ለመደበኛ ወጪ እና 415 ነጥብ 2 ቢሊዮኑ ለካፒታል ወጪ የተመደበ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15🤔14🤪9🙏2👍1👏1👀1
ሂውማን ራይትስ ዎች፣ የአሜሪካ መንግሥት ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተወሠኑ የአፍሪካ አገራት ጋር የተፈራረማቸው የጤና ስምምነቶች የሕይወት አድን ድጋፎችን ቁልፍ የጤና መረጃዎችን ለመድኃኒት አምራች ኩባንያዎች አሳልፎ ከመስጠት ጋር የሚያስተሳስሩ ናቸው በማለት ወቀሠ።
ተቋሙ፣ አሜሪካ በቅርቡ ከኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሞዛምቢክ፣ ናይጄሪይል፣ ሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሩዋንዳ እና ኡጋንዳ ጋር የተፈራረመቻቸውን ስምምነቶች መመርመሩን ገልጧል።
ተቋሙ፣ መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶችን አደጋ ላይ የሚጥሉ የጤና ስምምነቶችን እንዲቀበሉ አሜሪካ እያስገደደች መኾኗን ገልጧል።
የጤና ስምምነቶቹ በግለሰቦች የጤና መረጃዎች ሚስጢራዊነት ላይ ስጋት ሊደቅኑ የሚችሉ ናቸው ያለው ተቋሙ፣ የአሜሪካ መንግሥት ከኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሞዛምቢክ፣ ናይጄሪያ እና ኡጋንዳ ጋር የተፈራረማቸውን ስምምነቶች በድረገጹ ላይ ይፋ ካደረገ በኋላ መልሶ አንስቷቸዋል ብሏል።
አሜሪካ፣ ከስምምነቶቹ ጋር በተያያዘ ከአገራቱ ጋር በማዕድን ዙሪያ እያካሄደቻቸው ያሉትን ድርድሮች ይፋ እንድታደርግም ተቋሙ ጠይቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ተቋሙ፣ አሜሪካ በቅርቡ ከኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሞዛምቢክ፣ ናይጄሪይል፣ ሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሩዋንዳ እና ኡጋንዳ ጋር የተፈራረመቻቸውን ስምምነቶች መመርመሩን ገልጧል።
ተቋሙ፣ መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶችን አደጋ ላይ የሚጥሉ የጤና ስምምነቶችን እንዲቀበሉ አሜሪካ እያስገደደች መኾኗን ገልጧል።
የጤና ስምምነቶቹ በግለሰቦች የጤና መረጃዎች ሚስጢራዊነት ላይ ስጋት ሊደቅኑ የሚችሉ ናቸው ያለው ተቋሙ፣ የአሜሪካ መንግሥት ከኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሞዛምቢክ፣ ናይጄሪያ እና ኡጋንዳ ጋር የተፈራረማቸውን ስምምነቶች በድረገጹ ላይ ይፋ ካደረገ በኋላ መልሶ አንስቷቸዋል ብሏል።
አሜሪካ፣ ከስምምነቶቹ ጋር በተያያዘ ከአገራቱ ጋር በማዕድን ዙሪያ እያካሄደቻቸው ያሉትን ድርድሮች ይፋ እንድታደርግም ተቋሙ ጠይቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤8👍5👏1🤔1😢1🙊1
አሜሪካ ቪዛ በፍጥነት ለማግኘት ለሚፈልጉ መንገደኞች የ750 ዶላር ተጨማሪ ክፍያ የሚጠይቅ አዲስ የሙከራ አሰራር ይፋ አደረገች
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰኔ 24 ቀን እስከ ታኅሣሥ 22 ቀን 2019 ዓ.ም የሚቆይ አዲስ የቪዛ አገልግሎት መጀመሩን አስታውቋል።
ይህ አሰራር አመልካቾች ከመደበኛው 185 ዶላር በተጨማሪ 750 ዶላር በመክፈል በ10 ቀናት ውስጥ የቃለ መጠይቅ ቀጠሮ እንዲያገኙ ያስችላል።
አላማውም በትራምፕ አስተዳደር ጥብቅ የቪዛ ቁጥጥር (የማህበራዊ ሚዲያ ፍተሻ እና እስከ 15,000 ዶላር ዋስትና ማስያዝን ጨምሮ) የመጣውን ከፍተኛ የቀጠሮ መዘግየት መቀነስ ነው።
ነገር ግን ይህንን ፕሪሚየም ክፍያ መክፈል የቪዛ መፈቀድን በፍጹም አያረጋግጥም ተብሏል።
አገልግሎቱ የሚሰጥባቸው የተመረጡ ኤምባሲዎች ዝርዝር በቅርቡ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰኔ 24 ቀን እስከ ታኅሣሥ 22 ቀን 2019 ዓ.ም የሚቆይ አዲስ የቪዛ አገልግሎት መጀመሩን አስታውቋል።
ይህ አሰራር አመልካቾች ከመደበኛው 185 ዶላር በተጨማሪ 750 ዶላር በመክፈል በ10 ቀናት ውስጥ የቃለ መጠይቅ ቀጠሮ እንዲያገኙ ያስችላል።
አላማውም በትራምፕ አስተዳደር ጥብቅ የቪዛ ቁጥጥር (የማህበራዊ ሚዲያ ፍተሻ እና እስከ 15,000 ዶላር ዋስትና ማስያዝን ጨምሮ) የመጣውን ከፍተኛ የቀጠሮ መዘግየት መቀነስ ነው።
ነገር ግን ይህንን ፕሪሚየም ክፍያ መክፈል የቪዛ መፈቀድን በፍጹም አያረጋግጥም ተብሏል።
አገልግሎቱ የሚሰጥባቸው የተመረጡ ኤምባሲዎች ዝርዝር በቅርቡ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7👍4😁3😢2😱1👀1🙉1🙊1
አሜሪካ ኢራንን ደበደበች‼️
የአሜሪካ ጦር ዛሬ ለሊቱን ኢራንን በመደብደብ 20 የተመረጡ ዒላማዎችን አውድሟል።
ይህም ኢራን ትላንት በሰው አልባ አጥፍቶ ጠፊ በመጠቀም የአሜሪካንን ሄሊኮፍተር ከጣለች በኋላ የተሰጠ ምላሽ ነው ብለዋል።
ኢራን በበኩሏ ዮርዳኖስንና ሌሎች የዓረብ አገሮችን ደብድባለች።
አሜሪካ ይህንን ጥቃት የፈፀመችው በሶስት ዙር ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአሜሪካ ጦር ዛሬ ለሊቱን ኢራንን በመደብደብ 20 የተመረጡ ዒላማዎችን አውድሟል።
ይህም ኢራን ትላንት በሰው አልባ አጥፍቶ ጠፊ በመጠቀም የአሜሪካንን ሄሊኮፍተር ከጣለች በኋላ የተሰጠ ምላሽ ነው ብለዋል።
ኢራን በበኩሏ ዮርዳኖስንና ሌሎች የዓረብ አገሮችን ደብድባለች።
አሜሪካ ይህንን ጥቃት የፈፀመችው በሶስት ዙር ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10😡8👍5👏1🕊1
ወጣቶች እየሸሹ ነው‼️
በትግራይ ክልል በደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የክልሉ አመራር አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላን የሚፈቅድና ማዕከላዊ ኮማንድ ፖስት የሚያቋቁም ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ።
ረቂቅ አዋጅ፤ ዕድሜው የደረሠ ማንኛውም የክልሉ ነዋሪ የክተት ጥሪውን ተቀብሎ በወታደራዊ ግዳጅ እንዲሳተፍ ግዴታ የሚጥል ሲሆን፤ ጥሪውን የማይቀበል ከ10 ሺሕ እስከ 50 ሺሕ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እንደሚጣልበት ደንግጓል።
የክተት ጥሪውን መሸሽ ለሚፈልጉ ግለሰቦች ሀሰተኛ የሕክምና ማስረጃ የሚሠጡ የጤና ባለሙያዎችም እስከ 50 ሺሕ ብር ቅጣት እንደሚጠብቃቸው በረቂቁ ላይ ሠፍሯል። ማዕከላዊ ኮማንድ ፖስቱን በበላይነት የሚመራው የክልሉ ፕሬዝዳንት፣ የተዋጊ ኃይሎች የበላይ አዛዥ እንደሚኾን ተጠቅሷል።
በጦር ግንባር የተከፈለውን መስዋዕትነትና የሕዝቡን ትግል የሚያሳንስ ወይም የሚያጠለሽ ጽሑፍ፣ ንግግር ወይም ምስል ማሰራጨት እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚያስቀጣም ተደንግጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በትግራይ ክልል በደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የክልሉ አመራር አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላን የሚፈቅድና ማዕከላዊ ኮማንድ ፖስት የሚያቋቁም ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ።
👉ይህን ተከተሎ በርካታ ወጣቶች እየሸሹ ነው።
ረቂቅ አዋጅ፤ ዕድሜው የደረሠ ማንኛውም የክልሉ ነዋሪ የክተት ጥሪውን ተቀብሎ በወታደራዊ ግዳጅ እንዲሳተፍ ግዴታ የሚጥል ሲሆን፤ ጥሪውን የማይቀበል ከ10 ሺሕ እስከ 50 ሺሕ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እንደሚጣልበት ደንግጓል።
የክተት ጥሪውን መሸሽ ለሚፈልጉ ግለሰቦች ሀሰተኛ የሕክምና ማስረጃ የሚሠጡ የጤና ባለሙያዎችም እስከ 50 ሺሕ ብር ቅጣት እንደሚጠብቃቸው በረቂቁ ላይ ሠፍሯል። ማዕከላዊ ኮማንድ ፖስቱን በበላይነት የሚመራው የክልሉ ፕሬዝዳንት፣ የተዋጊ ኃይሎች የበላይ አዛዥ እንደሚኾን ተጠቅሷል።
በጦር ግንባር የተከፈለውን መስዋዕትነትና የሕዝቡን ትግል የሚያሳንስ ወይም የሚያጠለሽ ጽሑፍ፣ ንግግር ወይም ምስል ማሰራጨት እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚያስቀጣም ተደንግጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13💔11👍3😢3😈3🕊2✍1💋1
አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Photo
ከ3 ጊዜ በላይ ጥቆማ የሚቀርብባቸውና ከታሪፍ በላይ የሚጭኑ አሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ።
ከነዳጅ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ አጠቃላይ ሁኔታውን ታሳቢ ያደረገ የታሪፍ ማሻሻያ ቢደረግም፣ በርካታ አሽከርካሪዎች ከተቀመጠው ታሪፍ ውጪ እያስከፈሉ መሆኑ በጥናት መረጋገጡን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ለመናኸሪያ ሬዲዮ በሰጠው ገለፃ አስታውቋል።
በመዲናዋ የሚገኙ የሚኒባስ አሽከርካሪዎች ከታሪፍ ውጪ ከማስከፈልም ባለፈ፣ ከተሰጣቸው ስምሪት ውጪ እንደሚያሽከረክሩ የተናገሩት የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው፤ ይህንን ችግር ለመፍታት ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ችግሩን ለመፍታት ካሁን ቀደም በኪሎ ሜትር ይገለጽ የነበረው የጉዞ ታሪፍ ተሳፋሪውን ያወዛግብ እንደነበር አስታውሰው፤ በተያዘው ሰኔ ወር በመነሻና መዳረሻ ላይ ያለውን የጉዞ ታሪፍ የሚገልጽ ዝርዝር እንደሚለጠፍ አስታውቀዋል።
ቢሮው ከታሪፍ በላይ በሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎች ላይ የሚሰራውን የቁጥጥር ስራ በይበልጥ ማሻሻሉን ገልጸው፤ ከ3 ጊዜ በላይ ጥቆማ የሚቀርብባቸውና ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ እንደሚደረግም ተናግረዋል።
ባለፈው የግንቦት ወር ብቻ ከታሪፍ በላይ በማስከፈልና የተቀመጠውን የታሪፍ ዝርዝር ባለመስቀላቸው ከ3 ሺህ 300 በላይ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ያመለከቱት ምክትል ኃላፊው፤ የቁጥጥር ስራውን በይበልጥ ለማጠናከር በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ባለፉት ጊዜያት በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 9417 አጭር የስልክ መስመር አሁን ላይ በርካታ ጥቆማዎችን እየተቀበለበት መሆኑን አቶ ዳኛቸው ገልጸዋል።
በተጠናቀቀው ግንቦት ወር ብቻ ወደ 400 የሚጠጉ ጥቆማዎችን ማስተናገድ መቻሉንና በ300ዎቹ ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው አብራርተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከነዳጅ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ አጠቃላይ ሁኔታውን ታሳቢ ያደረገ የታሪፍ ማሻሻያ ቢደረግም፣ በርካታ አሽከርካሪዎች ከተቀመጠው ታሪፍ ውጪ እያስከፈሉ መሆኑ በጥናት መረጋገጡን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ለመናኸሪያ ሬዲዮ በሰጠው ገለፃ አስታውቋል።
በመዲናዋ የሚገኙ የሚኒባስ አሽከርካሪዎች ከታሪፍ ውጪ ከማስከፈልም ባለፈ፣ ከተሰጣቸው ስምሪት ውጪ እንደሚያሽከረክሩ የተናገሩት የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው፤ ይህንን ችግር ለመፍታት ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ችግሩን ለመፍታት ካሁን ቀደም በኪሎ ሜትር ይገለጽ የነበረው የጉዞ ታሪፍ ተሳፋሪውን ያወዛግብ እንደነበር አስታውሰው፤ በተያዘው ሰኔ ወር በመነሻና መዳረሻ ላይ ያለውን የጉዞ ታሪፍ የሚገልጽ ዝርዝር እንደሚለጠፍ አስታውቀዋል።
ቢሮው ከታሪፍ በላይ በሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎች ላይ የሚሰራውን የቁጥጥር ስራ በይበልጥ ማሻሻሉን ገልጸው፤ ከ3 ጊዜ በላይ ጥቆማ የሚቀርብባቸውና ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ እንደሚደረግም ተናግረዋል።
ባለፈው የግንቦት ወር ብቻ ከታሪፍ በላይ በማስከፈልና የተቀመጠውን የታሪፍ ዝርዝር ባለመስቀላቸው ከ3 ሺህ 300 በላይ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ያመለከቱት ምክትል ኃላፊው፤ የቁጥጥር ስራውን በይበልጥ ለማጠናከር በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ባለፉት ጊዜያት በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 9417 አጭር የስልክ መስመር አሁን ላይ በርካታ ጥቆማዎችን እየተቀበለበት መሆኑን አቶ ዳኛቸው ገልጸዋል።
በተጠናቀቀው ግንቦት ወር ብቻ ወደ 400 የሚጠጉ ጥቆማዎችን ማስተናገድ መቻሉንና በ300ዎቹ ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው አብራርተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12👍10👏4👌1🤪1
በኦሮሚያ ክልል ፤ አርሲ ውስጥ በጥቃት አድራሾች የተቃጠለው ቤተክርስቲያን ሊሠራ ነው ተባለ!
«በአርሲ የተቃጠለውን ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን መልሰን እንሠራለን።» -የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከአንድ ሳምንት በፊት ስለተፈጸመው የኦርቶዶክሳውያን ግድያና የቤተ ክርስቲያን መቃጠል ኃዘናቸውን በመግለጥ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ፈቃደኛ መሆናቸውን ማሳወቃቸው ተዘግቧል ።
በኦሮሚያ ክልል፤ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርጫ ቀን እና በዋዜማው ግንቦት 23 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በተፈጸመው ጥቃት ንጹሐን ምእመናን መገደላቸው ተዘግቧል ። ከተፈጸመው ግድያ በተጨማሪ ከመቶ ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እንደተቃጠለ ይታወሳል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
«በአርሲ የተቃጠለውን ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን መልሰን እንሠራለን።» -የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከአንድ ሳምንት በፊት ስለተፈጸመው የኦርቶዶክሳውያን ግድያና የቤተ ክርስቲያን መቃጠል ኃዘናቸውን በመግለጥ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ፈቃደኛ መሆናቸውን ማሳወቃቸው ተዘግቧል ።
በኦሮሚያ ክልል፤ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርጫ ቀን እና በዋዜማው ግንቦት 23 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በተፈጸመው ጥቃት ንጹሐን ምእመናን መገደላቸው ተዘግቧል ። ከተፈጸመው ግድያ በተጨማሪ ከመቶ ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እንደተቃጠለ ይታወሳል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤25👍9🤪7🥰3🤔3🙏2👏1😍1