ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ለውጭ ተቋም የሚሰጠውን የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ ለናይጄሪያው የፋይናንስ ግዙፍ ተቋም ‘ዩናይትድ ካፒታል ግሩፕ’ መስጠቱን በይፋ አስታወቀ።
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የተሰጠው ይህ ፈቃድ፤ ባለሥልጣኑ፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና ሌሎች የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ለወራት ያደረጉትን ጥብቅ የሕግና የሰነድ ምርመራ ተከትሎ የተሰጠ መሆኑን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክር ሀና ተኸልኩ በተለይ ለካፒታል ጋዜጣ ተናግረዋል።
ዩናይትድ ካፒታል ‘ዩናይትድ ካፒታል ፋይናንሻል ሰርቪስስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር’ የተሰኘ ሙሉ በሙሉ የራሱ የሆነ የአካባቢው ቅርንጫፍ በመክፈት ከስድስት አስርት ዓመታት በላይ ያካበተውን የአፍሪካ አቀፍ ልምድ ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ገብቷል።
ባለስልጣኑ እንደገለፀው ፤ ይህ ሙሉ በሙሉ በውጭ ተቋም ባለቤትነት የተያዘ ፈቃድ መሰጠቱ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሊበራላይዜሽን ማሻሻያ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ማረጋገጫ ነው። ተቋሙ በሕግ ከተቀመጠው የ25 ሚሊዮን ብር አነስተኛ ካፒታል በላይ፣ ከ1.5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ በቀጥታ ወደ ሀገር ውስጥ አስገብቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ለውጭ ተቋም የሚሰጠውን የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ ለናይጄሪያው የፋይናንስ ግዙፍ ተቋም ‘ዩናይትድ ካፒታል ግሩፕ’ መስጠቱን በይፋ አስታወቀ።
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የተሰጠው ይህ ፈቃድ፤ ባለሥልጣኑ፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና ሌሎች የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ለወራት ያደረጉትን ጥብቅ የሕግና የሰነድ ምርመራ ተከትሎ የተሰጠ መሆኑን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክር ሀና ተኸልኩ በተለይ ለካፒታል ጋዜጣ ተናግረዋል።
ዩናይትድ ካፒታል ‘ዩናይትድ ካፒታል ፋይናንሻል ሰርቪስስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር’ የተሰኘ ሙሉ በሙሉ የራሱ የሆነ የአካባቢው ቅርንጫፍ በመክፈት ከስድስት አስርት ዓመታት በላይ ያካበተውን የአፍሪካ አቀፍ ልምድ ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ገብቷል።
ባለስልጣኑ እንደገለፀው ፤ ይህ ሙሉ በሙሉ በውጭ ተቋም ባለቤትነት የተያዘ ፈቃድ መሰጠቱ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሊበራላይዜሽን ማሻሻያ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ማረጋገጫ ነው። ተቋሙ በሕግ ከተቀመጠው የ25 ሚሊዮን ብር አነስተኛ ካፒታል በላይ፣ ከ1.5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ በቀጥታ ወደ ሀገር ውስጥ አስገብቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍3😡2🎉1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የትግራይ ተወላጆች በሱዳን ጦርነት‼️
ከላይ የሚታየው ቪዲዮ የህወሃት አርሚ 70 ተብለው የሚጠሩ ታጣቂዎች የአርቡርሃን ጦርን በመደገፍ በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ እየተሳተፉ የሚገኙ ናቸው።
በትናንትናው ዕለት በሽራሮ አካባቢ ገመሃሎ በህወሓት ታጣቂዎች ላይ የኢትዮጵያ አየር ሃይል የፈፀመው ድንገተኛ የድሮን ጥቃት ታጣቂዎቹ ወደ ሱዳን ለመሄድ እየተንቀሳቀሱ ስለነበር ነው ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከላይ የሚታየው ቪዲዮ የህወሃት አርሚ 70 ተብለው የሚጠሩ ታጣቂዎች የአርቡርሃን ጦርን በመደገፍ በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ እየተሳተፉ የሚገኙ ናቸው።
በትናንትናው ዕለት በሽራሮ አካባቢ ገመሃሎ በህወሓት ታጣቂዎች ላይ የኢትዮጵያ አየር ሃይል የፈፀመው ድንገተኛ የድሮን ጥቃት ታጣቂዎቹ ወደ ሱዳን ለመሄድ እየተንቀሳቀሱ ስለነበር ነው ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪13👍9❤5💔3🤡2👏1😱1🕊1
የውጭ ባለሀብቶች እና ተቋማት ነዳጅ እንዲያስገቡ ተፈቀደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሃገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ስርዓት ላይ እየደረሰ ያለውን ጫና ለማቃለል በማለም፤ ኤምባሲዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና በዉጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ ነዳጅ እንዲያስገቡ የሚፈቅድ አዲስ መመሪያ ተግባራዊ አድርጓል።
ባለፈዉ ሳምንት ይፋ የሆነዉ ይህ መመሪያ፤ እውቅና የተሰጣቸው ተቋማት የተጣራ የነዳጅ ምርቶችን በፍራንኮ ቫሉታ ስርዓት እንዲያስገቡ የሚፈቅድ ሲሆን፣ ይህም ከሀገር ውስጥ የባንክ ስርዓት ምንም ዓይነት የውጭ ምንዛሬ ሳይጠይቁ የራሳቸውን ፍላጎት እንዲሸፍኑ የሚያስችል ነው።
ይሁን እንጂ አዲሱ አሰራር አጠቃላይ የነዳጅ ገበያውን ለግል ነጋዴዎች ክፍት የሚያደርግ ባለመሆኑ፣ በዚህ መንገድ የገባ ነዳጅ ለሕዝብ ሊሸጥ፣ ለሶስተኛ ወገን ሊተላለፍ ወይም በተለመደው የሀገር ውስጥ የንግድ ነዳጅ አቅርቦት ላይ ሊቀላቀል እንደማይችል በጥብቅ መከልከሉን የዘገበው ካፒታል ጋዜጣ ነዉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሃገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ስርዓት ላይ እየደረሰ ያለውን ጫና ለማቃለል በማለም፤ ኤምባሲዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና በዉጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ ነዳጅ እንዲያስገቡ የሚፈቅድ አዲስ መመሪያ ተግባራዊ አድርጓል።
ባለፈዉ ሳምንት ይፋ የሆነዉ ይህ መመሪያ፤ እውቅና የተሰጣቸው ተቋማት የተጣራ የነዳጅ ምርቶችን በፍራንኮ ቫሉታ ስርዓት እንዲያስገቡ የሚፈቅድ ሲሆን፣ ይህም ከሀገር ውስጥ የባንክ ስርዓት ምንም ዓይነት የውጭ ምንዛሬ ሳይጠይቁ የራሳቸውን ፍላጎት እንዲሸፍኑ የሚያስችል ነው።
ይሁን እንጂ አዲሱ አሰራር አጠቃላይ የነዳጅ ገበያውን ለግል ነጋዴዎች ክፍት የሚያደርግ ባለመሆኑ፣ በዚህ መንገድ የገባ ነዳጅ ለሕዝብ ሊሸጥ፣ ለሶስተኛ ወገን ሊተላለፍ ወይም በተለመደው የሀገር ውስጥ የንግድ ነዳጅ አቅርቦት ላይ ሊቀላቀል እንደማይችል በጥብቅ መከልከሉን የዘገበው ካፒታል ጋዜጣ ነዉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍6🤪5👏2👌1
ኢሰመኮ ሶስት ሰዎች ናቸው የሞቱት አለ❗❗
" ሁለት የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ እንዲሁም አንድ የእስልምና እምነት ተከታይ በአጠቃላይ የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት አልፏል " - ኢሰመኮ
• የአርሲ ሀገረ ስብከት 13 ምዕመናን መገደላቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል !
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ግንቦት 23 እና 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ያከናወነውን የክትትል እና የምርመራ መረጃ ዛሬ ይፋ አድርጓል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ "በምሥራቅ አርሲ 13 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን፣ ከ280 በላይ ምእመናን መፈናቀላቸውንና የ101 ዓመት ቤተ ክርስቲያን መቃጠሉን " ማሳወቃቸው ይታወሳል። የሟቾችን ዝርዝርም ይፋ ማድረጋቸው አይዘነጋም።
ኢሰመኮ ከአይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች እና ከመንግሥት አካላት አሰባሰብኩት ባለው መረጃ ፣ በጥቃቱ የመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላትና ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን፣ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን፣ የንብረት ውድመት እና ቃጠሎ መድረሱን ማረጋገጡን ገልጿል።
ኮሚሽኑ በምርመራ ሂደቱ አረጋገጥኩኝ እንዳለው፣ በአሰኮ ወረዳ ደለተ ጫፋ ቀበሌ ከግንቦት 22 ቀን ጀምሮ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በመስተዋሉ፣ በአካባቢው ሚሊሻዎችና የኦሮሚያ ጸረ ሽምቅ ፖሊስ እንዲሁም ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሸኔ) ብሎ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን መካከል ግጭት ተፈጥሯል።
ይህንን ግጭት ተከትሎ ታጣቂ ቡድኑ በፈጸመው ጥቃት ከአካባቢው መሸሽ ያልቻሉ ኃይሉ ንጉሴ እና ሰሙ አባይነህ በተባሉ ሁለት የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ እንዲሁም ከብቶች በመጠበቅ ላይ በነበረ ባቶ ሰፈኖ በተባለ አንድ የእስልምና እምነት ተከታይ በአጠቃላይ የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት ሊያልፍ ችሏል።
በተጨማሪም በጥቃቱ የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መቃጠሉን ኮሚሽኑ ያረጋገጠ ሲሆን የቢዮ ቡጡሌ የሼክ ሙስተፋ መስጅድ አጥር ላይ ጉዳት መድረሱን ቁጥራቸው በውል ባልታወቁ ቤቶች ላይ ቃጠሎ መከሰቱን እና በጤና ጣቢያ፣ በመኖሪያ ቤቶችና የንግድ መደብሮች ላይ ዘረፋ መፈጸሙን አስታውቋል።
በጥቃቱ ምክንያት ከ2,650 በላይ የሚገመቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውንም ኢሰመኮ አረጋግጧል።
ኢሰመኮ በአርሲ ዞን በሽርካ፣ በአሰኮ፣ በአንቆሎ ዋቤ፣ ጉና እና መርቲ ወረዳዎች ላይ በታጣቂዎቹ ሲፈጸሙ የነበሩ ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ እና ጥቃት ፈጻሚዎች ላይ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ በተለያዩ ጊዜያት ማሳሰቡን አስታውሷል።
በመሆኑም መንግሥት በአካባቢው ላይ በተደጋጋሚ መሰል ጥቃቶች መከሰት መቀጠላቸው አሳሳቢ መሆኑን ከግምት በማስገባት፣ በአስቸኳይ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችን በማሰማራት ሰላምና ደኅንነትን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስቧል።
በመንግሥትና በአጋር አካላት ለተፈናቃዮች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብና ወደ ቀያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ እንዲመቻች የጠየቀው ኮሚሽኑ፤ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በደረሰው ሞትና ጉዳት ማዘናቸውን ገልጸው፣ መንግሥት በቂ የጸጥታ ኃይል በመመደብ የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት መብቶች ለአደጋ እንዳይጋለጡ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
ኢሰመኮ ጉዳዩን አስመልክቶ ዝርዝር የምርመራ ሪፖርት ወደፊት ይፋ እንደሚያደርግ የገለጸ ሲሆን፤ የተፈጸሙ ጥቃቶችን በአግባቡ ሳያረጋግጡ የሚሰነዘሩ ፍረጃዎችና ቅስቀሳዎች ተጨማሪ ግጭት ሊቀሰቅሱ ስለሚችሉ፣ ማናቸውም ተቋማትም ሆኑ ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ አቅርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
" ሁለት የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ እንዲሁም አንድ የእስልምና እምነት ተከታይ በአጠቃላይ የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት አልፏል " - ኢሰመኮ
• የአርሲ ሀገረ ስብከት 13 ምዕመናን መገደላቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል !
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ግንቦት 23 እና 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ያከናወነውን የክትትል እና የምርመራ መረጃ ዛሬ ይፋ አድርጓል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ "በምሥራቅ አርሲ 13 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን፣ ከ280 በላይ ምእመናን መፈናቀላቸውንና የ101 ዓመት ቤተ ክርስቲያን መቃጠሉን " ማሳወቃቸው ይታወሳል። የሟቾችን ዝርዝርም ይፋ ማድረጋቸው አይዘነጋም።
ኢሰመኮ ከአይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች እና ከመንግሥት አካላት አሰባሰብኩት ባለው መረጃ ፣ በጥቃቱ የመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላትና ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን፣ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን፣ የንብረት ውድመት እና ቃጠሎ መድረሱን ማረጋገጡን ገልጿል።
ኮሚሽኑ በምርመራ ሂደቱ አረጋገጥኩኝ እንዳለው፣ በአሰኮ ወረዳ ደለተ ጫፋ ቀበሌ ከግንቦት 22 ቀን ጀምሮ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በመስተዋሉ፣ በአካባቢው ሚሊሻዎችና የኦሮሚያ ጸረ ሽምቅ ፖሊስ እንዲሁም ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሸኔ) ብሎ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን መካከል ግጭት ተፈጥሯል።
ይህንን ግጭት ተከትሎ ታጣቂ ቡድኑ በፈጸመው ጥቃት ከአካባቢው መሸሽ ያልቻሉ ኃይሉ ንጉሴ እና ሰሙ አባይነህ በተባሉ ሁለት የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ እንዲሁም ከብቶች በመጠበቅ ላይ በነበረ ባቶ ሰፈኖ በተባለ አንድ የእስልምና እምነት ተከታይ በአጠቃላይ የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት ሊያልፍ ችሏል።
በተጨማሪም በጥቃቱ የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መቃጠሉን ኮሚሽኑ ያረጋገጠ ሲሆን የቢዮ ቡጡሌ የሼክ ሙስተፋ መስጅድ አጥር ላይ ጉዳት መድረሱን ቁጥራቸው በውል ባልታወቁ ቤቶች ላይ ቃጠሎ መከሰቱን እና በጤና ጣቢያ፣ በመኖሪያ ቤቶችና የንግድ መደብሮች ላይ ዘረፋ መፈጸሙን አስታውቋል።
በጥቃቱ ምክንያት ከ2,650 በላይ የሚገመቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውንም ኢሰመኮ አረጋግጧል።
ኢሰመኮ በአርሲ ዞን በሽርካ፣ በአሰኮ፣ በአንቆሎ ዋቤ፣ ጉና እና መርቲ ወረዳዎች ላይ በታጣቂዎቹ ሲፈጸሙ የነበሩ ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ እና ጥቃት ፈጻሚዎች ላይ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ በተለያዩ ጊዜያት ማሳሰቡን አስታውሷል።
በመሆኑም መንግሥት በአካባቢው ላይ በተደጋጋሚ መሰል ጥቃቶች መከሰት መቀጠላቸው አሳሳቢ መሆኑን ከግምት በማስገባት፣ በአስቸኳይ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችን በማሰማራት ሰላምና ደኅንነትን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስቧል።
በመንግሥትና በአጋር አካላት ለተፈናቃዮች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብና ወደ ቀያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ እንዲመቻች የጠየቀው ኮሚሽኑ፤ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በደረሰው ሞትና ጉዳት ማዘናቸውን ገልጸው፣ መንግሥት በቂ የጸጥታ ኃይል በመመደብ የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት መብቶች ለአደጋ እንዳይጋለጡ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
ኢሰመኮ ጉዳዩን አስመልክቶ ዝርዝር የምርመራ ሪፖርት ወደፊት ይፋ እንደሚያደርግ የገለጸ ሲሆን፤ የተፈጸሙ ጥቃቶችን በአግባቡ ሳያረጋግጡ የሚሰነዘሩ ፍረጃዎችና ቅስቀሳዎች ተጨማሪ ግጭት ሊቀሰቅሱ ስለሚችሉ፣ ማናቸውም ተቋማትም ሆኑ ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ አቅርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪28❤24💔6👍3😢2🤷2😡2🙉1🙊1
ሰበር ዜና‼️
ኢራን ወደ እስራኤል ሚሳይል ተኮሰች።
እስራኤል ኢራን ለምትፈፅመው የሚሳኤል ጥቃት ዝግጁ ነኝ ማለቷን RT ዘግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኢራን ወደ እስራኤል ሚሳይል ተኮሰች።
እስራኤል ኢራን ለምትፈፅመው የሚሳኤል ጥቃት ዝግጁ ነኝ ማለቷን RT ዘግቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍16❤8🥰2🕊1👀1
በትግራይ ክልል ዛሬም የድሮን ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ።
ዛሬ እሁድ ግንቦት 30 ቀን አመሻሹ ላይ ከሽራሮ አቅራቢያ ሽምበኒላ በተባለ ስፍራ አዲስ የድሮን ጥቃት መፈጸሙ ታውቋል። ይህ በሶስት ቀናት ውስጥ በትግራይ የተፈጸመ ሁለተኛው ጥቃት ሲሆን ከቀናት በፊት የተካሄደውን ተመሳሳይ ጥቃት ተከትሎ ህወሓት ባወጣው መግለጫ የፌደራል መንግስቱን ማውገዙ ይታወሳል።
የዛሬው የድሮን ጥቃት የጦር መሳሪያ በጫኑ ተሽከርካሪዎች ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ተነግሯል። ከሁለት ቀናት በፊት የተካሄደው ጥቃትም በተመሳሳይ በወታደራዊ ተሽከርካሪዎች እና ታጣቂዎች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ዘግይተው የወጡ መረጃዎች ማመላከታቸው አይዘነጋም።
እነዚህ ጥቃቶች እየተፈጸሙ ያሉት፣ ህወሓት ክልሉን ወደ ማስተዳደር መመለሱን ማሳወቁን፣ እንዲሁም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በህወሓት እና በኤርትራ መንግስት መካከል እየተደረገ ነው ያሉትን ግንኙነት ማውገዛቸውን ተከትሎ ነው። የድሮን ጥቃቱ በተፈጸመበት በዚህ ሰዓትም የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግብጽ መግባታቸው ታውቋል።
የፕሬዝዳንቱ የግብጽ ጉብኝት ትኩረት በውል ባይታወቅም፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የህወሓትን እና የኤርትራ መንግስትን ጥምረት ከማውገዛቸው ባለፈ፣ በሁለቱ ቀናት የተፈጸሙት ጥቃቶች ከኤርትራ ድንበር አቅራቢያ እና የኤርትራ ሰራዊት አባላት በስፋት በሚታዩባቸው አካባቢዎች መሆናቸው፣ ጥቃቱ በኤርትራ እና በህወሓት መካከል ተፈጥሯል በተባለው አዲስ ግንኙነት ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ያሳያል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዛሬ እሁድ ግንቦት 30 ቀን አመሻሹ ላይ ከሽራሮ አቅራቢያ ሽምበኒላ በተባለ ስፍራ አዲስ የድሮን ጥቃት መፈጸሙ ታውቋል። ይህ በሶስት ቀናት ውስጥ በትግራይ የተፈጸመ ሁለተኛው ጥቃት ሲሆን ከቀናት በፊት የተካሄደውን ተመሳሳይ ጥቃት ተከትሎ ህወሓት ባወጣው መግለጫ የፌደራል መንግስቱን ማውገዙ ይታወሳል።
የዛሬው የድሮን ጥቃት የጦር መሳሪያ በጫኑ ተሽከርካሪዎች ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ተነግሯል። ከሁለት ቀናት በፊት የተካሄደው ጥቃትም በተመሳሳይ በወታደራዊ ተሽከርካሪዎች እና ታጣቂዎች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ዘግይተው የወጡ መረጃዎች ማመላከታቸው አይዘነጋም።
እነዚህ ጥቃቶች እየተፈጸሙ ያሉት፣ ህወሓት ክልሉን ወደ ማስተዳደር መመለሱን ማሳወቁን፣ እንዲሁም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በህወሓት እና በኤርትራ መንግስት መካከል እየተደረገ ነው ያሉትን ግንኙነት ማውገዛቸውን ተከትሎ ነው። የድሮን ጥቃቱ በተፈጸመበት በዚህ ሰዓትም የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግብጽ መግባታቸው ታውቋል።
የፕሬዝዳንቱ የግብጽ ጉብኝት ትኩረት በውል ባይታወቅም፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የህወሓትን እና የኤርትራ መንግስትን ጥምረት ከማውገዛቸው ባለፈ፣ በሁለቱ ቀናት የተፈጸሙት ጥቃቶች ከኤርትራ ድንበር አቅራቢያ እና የኤርትራ ሰራዊት አባላት በስፋት በሚታዩባቸው አካባቢዎች መሆናቸው፣ ጥቃቱ በኤርትራ እና በህወሓት መካከል ተፈጥሯል በተባለው አዲስ ግንኙነት ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ያሳያል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤21👍7👀3👏1😁1🕊1🤪1
የመካከለኛው ምስራቅ ሰማይ እሳት ለብሷል!
ኢራን በደርዘን የሚቆጠሩ የባለስቲክ ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል መተኮሷ ቀጣናው ወደ ከባድ ጦርነት እያመራ ነው።
በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ወደለየለት ቀውስ ተቀይሯል።
የኢስራኤል መከላከያ ሰራዊት ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በሰጠው እጅግ አስቸኳይ መግለጫ ኢራን በርካታ የባለስቲክ ሚሳኤሎችን በቀጥታ ወደ እስራኤል መተኮሷን ይፋ አድርጓል።
በአሁኑ ሰአት በሰሜናዊ የእስራኤል ከተሞች የአየር አደጋ ማስጠንቀቂያ ደወሎች በከፍተኛ ሁኔታ እያስተጋቡ ሲሆን ህዝቡ በአስቸኳይ ወደ መከላከያ መጠለያዎች እንዲገባ ጥብቅ መመሪያ ተላልፏል።
ይህ መጠነ-ሰፊ ጥቃት የተሰነዘረው እስራኤል ዛሬ ማለዳ ላይ በሊባኖስ ቤይሩት ዳሂዬህ አካባቢ ላይ ለፈጸመችው ከባድ የአየር ድብደባ ማዕበል ኢራን የአጸፋ እርምጃ እንደምትወስድ በይፋ ከዛተች በኋላ ነው።
ሁኔታውን ተከትሎ የዓለም አቀፍ ትኩረት የሳበ ሲሆን እንደ ኳታር ያሉ የጎረቤት ሀገራት የንግድ አውሮፕላኖቻቸው የኢራንን የአየር ክልል ሙሉ በሙሉ እንዲቀይሩና እንዲርቁ በአስቸኳይ እያዘዙ ነው።
ይህ የኢራን እርምጃ የቀጣናውን ጦርነት ወዴት ሊመራው ይችላል? እስራኤልስ ምን ዓይነት ከባድ የአጸፋ እርምጃ ትወስድ ይሆን የሚለው መላውን ዓለም በስጋት ውስጥ ጥሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኢራን በደርዘን የሚቆጠሩ የባለስቲክ ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል መተኮሷ ቀጣናው ወደ ከባድ ጦርነት እያመራ ነው።
በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ወደለየለት ቀውስ ተቀይሯል።
የኢስራኤል መከላከያ ሰራዊት ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በሰጠው እጅግ አስቸኳይ መግለጫ ኢራን በርካታ የባለስቲክ ሚሳኤሎችን በቀጥታ ወደ እስራኤል መተኮሷን ይፋ አድርጓል።
በአሁኑ ሰአት በሰሜናዊ የእስራኤል ከተሞች የአየር አደጋ ማስጠንቀቂያ ደወሎች በከፍተኛ ሁኔታ እያስተጋቡ ሲሆን ህዝቡ በአስቸኳይ ወደ መከላከያ መጠለያዎች እንዲገባ ጥብቅ መመሪያ ተላልፏል።
ይህ መጠነ-ሰፊ ጥቃት የተሰነዘረው እስራኤል ዛሬ ማለዳ ላይ በሊባኖስ ቤይሩት ዳሂዬህ አካባቢ ላይ ለፈጸመችው ከባድ የአየር ድብደባ ማዕበል ኢራን የአጸፋ እርምጃ እንደምትወስድ በይፋ ከዛተች በኋላ ነው።
ሁኔታውን ተከትሎ የዓለም አቀፍ ትኩረት የሳበ ሲሆን እንደ ኳታር ያሉ የጎረቤት ሀገራት የንግድ አውሮፕላኖቻቸው የኢራንን የአየር ክልል ሙሉ በሙሉ እንዲቀይሩና እንዲርቁ በአስቸኳይ እያዘዙ ነው።
ይህ የኢራን እርምጃ የቀጣናውን ጦርነት ወዴት ሊመራው ይችላል? እስራኤልስ ምን ዓይነት ከባድ የአጸፋ እርምጃ ትወስድ ይሆን የሚለው መላውን ዓለም በስጋት ውስጥ ጥሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤36👍5🕊3👏1😢1💔1🤪1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እስራኤል የአፀፋ ምላሽ ሰጠች‼️
በትናንትናው ዕለት ምሽት ኢራን ወደ እስራኤል ሚሳይል መተኮሷን ተከትሎ
በቀጠናው የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ቤዞች እና እስራኤል በጋራ በመሆን በኢራን አስራ አምስት ቦታዎች እንዲመቱ ፔንታጐን ይፋ አድርጓል።
📌ቴህራን አየር ማረፊያ
📌ናጃፋባድ ድሮን መሰብሰቢያ ቦታ
📌በመሪዎች ላይ የግድያ ሙከራዎች / IRGC ግቢ
📌የታብሪዝ የባለስቲክ ሚሳኤል ጣቢያ እንዲመቱ ፔንታጐን አሳውቋል።
እስራኤል በቴህራን የተለያዩ ቦታዎች ላይ ድብደባ ፈፅማለች።
ምስል:- ቴህራን
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በትናንትናው ዕለት ምሽት ኢራን ወደ እስራኤል ሚሳይል መተኮሷን ተከትሎ
በቀጠናው የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ቤዞች እና እስራኤል በጋራ በመሆን በኢራን አስራ አምስት ቦታዎች እንዲመቱ ፔንታጐን ይፋ አድርጓል።
📌ቴህራን አየር ማረፊያ
📌ናጃፋባድ ድሮን መሰብሰቢያ ቦታ
📌በመሪዎች ላይ የግድያ ሙከራዎች / IRGC ግቢ
📌የታብሪዝ የባለስቲክ ሚሳኤል ጣቢያ እንዲመቱ ፔንታጐን አሳውቋል።
እስራኤል በቴህራን የተለያዩ ቦታዎች ላይ ድብደባ ፈፅማለች።
ምስል:- ቴህራን
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤32👍4🤔3🥱3😡3👏1👌1
የነዳጅ ዋጋ በሶስት ዶላር ጨመረ።
የኢራን እና የእስራኤል ግጭት ማገርሸቱን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ማሳየቱ ተገልጿል።
ኢራን ትናንት በእስራኤል ላይ የፈፀመችው ጥቃት ለነዳጅ ዋጋው መጨመር "ቀዳሚ" ምክንያት መሆኑ ተገልጿል።
በዚህም አንድ በርሚል ያልተጣራ ነዳጅ ሲሸጥበት ከነበረው 93.41 ዶላር ወደ 96.24 ዶላር ከፍ ብሏል።
የነዳጅ ዋጋ ከባለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ በ50% ጭማሪ አሳይቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢራን እና የእስራኤል ግጭት ማገርሸቱን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ማሳየቱ ተገልጿል።
ኢራን ትናንት በእስራኤል ላይ የፈፀመችው ጥቃት ለነዳጅ ዋጋው መጨመር "ቀዳሚ" ምክንያት መሆኑ ተገልጿል።
በዚህም አንድ በርሚል ያልተጣራ ነዳጅ ሲሸጥበት ከነበረው 93.41 ዶላር ወደ 96.24 ዶላር ከፍ ብሏል።
የነዳጅ ዋጋ ከባለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ በ50% ጭማሪ አሳይቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20👍2😢2🙏2
ሰበር | ኢራን እስራኤል በወሰደችው እርምጃ ምክንያት የባብ አል ማንዳብ የባህር ወሽመጥን ሙሉ በሙሉ መዝጋቷን አሳወቀች።
12% የሚሆነው የዓለም ንግድ በዚህ በኩል ያልፋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
12% የሚሆነው የዓለም ንግድ በዚህ በኩል ያልፋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍10❤7😁6🤔4😢4🤪3🕊1🙊1
አየር መንገዱ በሚቀጥሉት ሶስት ወራት ውስጥ የአነስተኛ አውሮፕላኖች ግዥ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ አስታወቀ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአገር ውስጥ እና ለጎረቤት ሀገራት በረራዎች የሚያገለግሉ አነስተኛ የክልል አውሮፕላኖችን ለመግዛት በሚቀጥሉት ሶስት ወራት ውስጥ የመጨረሻ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ አስታውቋል።
አዲሶቹ አውሮፕላኖች በአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች እና በቅርብ ሀገራት ዙሪያ ያለውን የጉዞ ፍላጎት ይበልጥ ለማሳደግ ታስበው የሚገዙ ናቸው። አየር መንገዱ የትኞቹን የአውሮፕላን አይነቶች ለመግዛት እንዳቀደ እና ምን ያህል ወጪ እንደሚያደርግ በሚቀጥሉት ሳምንታት በሚያደርገው ግምገማ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአገር ውስጥ እና ለጎረቤት ሀገራት በረራዎች የሚያገለግሉ አነስተኛ የክልል አውሮፕላኖችን ለመግዛት በሚቀጥሉት ሶስት ወራት ውስጥ የመጨረሻ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ አስታውቋል።
አዲሶቹ አውሮፕላኖች በአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች እና በቅርብ ሀገራት ዙሪያ ያለውን የጉዞ ፍላጎት ይበልጥ ለማሳደግ ታስበው የሚገዙ ናቸው። አየር መንገዱ የትኞቹን የአውሮፕላን አይነቶች ለመግዛት እንዳቀደ እና ምን ያህል ወጪ እንደሚያደርግ በሚቀጥሉት ሳምንታት በሚያደርገው ግምገማ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍7
በኢትዮጵያ የጤና ስጋት የደቀነው የጫት ተጠቃሚነት መጨመር‼
በኢትዮጵያ በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ የመጣው የጫት ሱስ ስርጭት፣ በአገሪቱ የአእምሮ ጤና ላይ ከባድ አደጋ እየደቀነ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች አስጠነቀቁ።
የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የአእምሮ ህክምና ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳላማው እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የጫት ተጠቃሚዎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን ማደጉ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በቅርቡ ባወጣው መረጃ መሰረት፤ በሀገሪቱ የወጡ አዳዲስ የቁጥጥር ህጎችን ተከትሎ የአልኮል እና የሲጋራ ተጠቃሚነት መጠነኛ ቅናሽ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ ይህ የቁጥጥር ስራ በጫት ላይ ባለመዘርጋቱ የችግሩን ስፋት አባብሶታል።
ማንኛውም የሱስ ችግር በቀጥታ ከአንጎል ባዮሎጂካዊ አወቃቀር ጋር የተያያዘ በመሆኑ፤ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ ባለሙያዎቹ ያሳስባሉ።
በተጨማሪም የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በጫት ቁጥጥር ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በኢትዮጵያ በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ የመጣው የጫት ሱስ ስርጭት፣ በአገሪቱ የአእምሮ ጤና ላይ ከባድ አደጋ እየደቀነ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች አስጠነቀቁ።
የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የአእምሮ ህክምና ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳላማው እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የጫት ተጠቃሚዎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን ማደጉ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በቅርቡ ባወጣው መረጃ መሰረት፤ በሀገሪቱ የወጡ አዳዲስ የቁጥጥር ህጎችን ተከትሎ የአልኮል እና የሲጋራ ተጠቃሚነት መጠነኛ ቅናሽ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ ይህ የቁጥጥር ስራ በጫት ላይ ባለመዘርጋቱ የችግሩን ስፋት አባብሶታል።
ማንኛውም የሱስ ችግር በቀጥታ ከአንጎል ባዮሎጂካዊ አወቃቀር ጋር የተያያዘ በመሆኑ፤ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ ባለሙያዎቹ ያሳስባሉ።
በተጨማሪም የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በጫት ቁጥጥር ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍11❤10😁3🤪2💯1
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሱዳን
መንገደኞች በዶላር እንዲከፍሉ ወሰነ!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሱዳን ለሚገዙ የአውሮፕላን ትኬቶች ክፍያ በአሜሪካ ዶላር ብቻ እንዲፈጸም ያሳለፈው ውሳኔ በሀገሪቱ ከፍተኛ የምጣኔ ሀብትና የሕግ ክርክር አስነስቷል። አየር መንገዱ በፖርት ሱዳን የሱዳንን ፓውንድ መቀበል ያቆመው በሱዳን የገንዘብ ምንዛሬ አለመረጋጋትና ያገኘውን ገቢ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት ለማስተላለፍ በመቸገሩ እንደሆነ ገልጿል።
ይህ አዲስ መመሪያ ተጓዦች እጥረት ያለበትን የዶላር ምንዛሬ በጥቁር ገበያ ፍለጋ እንዲንከራተቱ ያስገደደ ሲሆን፣ ይህም በተራው ሕዝብ ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጫና ከመፍጠሩም በላይ ቀድሞውኑ የደከመውን የሀገሪቱን የሀገር ውስጥ ገንዘብ ዋጋ ይበልጥ ያዳክመዋል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
በሌላ በኩል፣ የሱዳን ባለሥልጣናትና የሕግ ባለሙያዎች የአየር መንገዱ ውሳኔ ከሀገሪቱ የፋይናንስ ደንብ ጋር ሊጋጭ ይችላል ሲሉ እየተከራከሩ ነው። እንደ እነሱ ገለጻ፣ ልዩ ፈቃድ ካልተሰጠ በስተቀር በማንኛውም የሀገሪቱ ክልል ውስጥ የሚደረጉ የንግድ ግብይቶች በሙሉ በሱዳን ፓውንድ መፈጸም አለባቸው የሚለውን የሀገር ውስጥ ሕግ የጣሰ ነው።
ይህ አወዛጋቢ እርምጃ በሱዳን ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ሌሎች ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ላይም ተመሳሳይ ተጽዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እየተነበዩ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
መንገደኞች በዶላር እንዲከፍሉ ወሰነ!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሱዳን ለሚገዙ የአውሮፕላን ትኬቶች ክፍያ በአሜሪካ ዶላር ብቻ እንዲፈጸም ያሳለፈው ውሳኔ በሀገሪቱ ከፍተኛ የምጣኔ ሀብትና የሕግ ክርክር አስነስቷል። አየር መንገዱ በፖርት ሱዳን የሱዳንን ፓውንድ መቀበል ያቆመው በሱዳን የገንዘብ ምንዛሬ አለመረጋጋትና ያገኘውን ገቢ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት ለማስተላለፍ በመቸገሩ እንደሆነ ገልጿል።
ይህ አዲስ መመሪያ ተጓዦች እጥረት ያለበትን የዶላር ምንዛሬ በጥቁር ገበያ ፍለጋ እንዲንከራተቱ ያስገደደ ሲሆን፣ ይህም በተራው ሕዝብ ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጫና ከመፍጠሩም በላይ ቀድሞውኑ የደከመውን የሀገሪቱን የሀገር ውስጥ ገንዘብ ዋጋ ይበልጥ ያዳክመዋል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
በሌላ በኩል፣ የሱዳን ባለሥልጣናትና የሕግ ባለሙያዎች የአየር መንገዱ ውሳኔ ከሀገሪቱ የፋይናንስ ደንብ ጋር ሊጋጭ ይችላል ሲሉ እየተከራከሩ ነው። እንደ እነሱ ገለጻ፣ ልዩ ፈቃድ ካልተሰጠ በስተቀር በማንኛውም የሀገሪቱ ክልል ውስጥ የሚደረጉ የንግድ ግብይቶች በሙሉ በሱዳን ፓውንድ መፈጸም አለባቸው የሚለውን የሀገር ውስጥ ሕግ የጣሰ ነው።
ይህ አወዛጋቢ እርምጃ በሱዳን ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ሌሎች ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ላይም ተመሳሳይ ተጽዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እየተነበዩ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15😢3👍2👌1
⁉️ የምስራቁ ጦርነት የኑሮአችንን ዋጋ እንዴት እያናጋው ነው? 💥
🚨የኃያላን መንግስታት ፍጥጫ እና የድንበር ጦርነቶች ከሩቅ የሚታዩ የዜና አርዕስቶች ብቻ አይደሉም፤ የኢትዮጵያን ገበያ እና የኪሳችንን አቅም በቀጥታ የሚፈትኑ ማዕበሎች እንጂ።
የሀገር ውስጥ ወቅታዊ ፈተናዎችን እና አጠቃላይ የአህጉራችንን እና የዓለምን ዜናዎች አቀናጅቶ የሚያቀርብላችሁን ስፑትኒክን አሁኑኑ ይከተሉ 👇
🔗 https://t.me/+r3LZG4PCAKI3NmMy
📣 @sputnik_ethiopia
🚨የኃያላን መንግስታት ፍጥጫ እና የድንበር ጦርነቶች ከሩቅ የሚታዩ የዜና አርዕስቶች ብቻ አይደሉም፤ የኢትዮጵያን ገበያ እና የኪሳችንን አቅም በቀጥታ የሚፈትኑ ማዕበሎች እንጂ።
የሀገር ውስጥ ወቅታዊ ፈተናዎችን እና አጠቃላይ የአህጉራችንን እና የዓለምን ዜናዎች አቀናጅቶ የሚያቀርብላችሁን ስፑትኒክን አሁኑኑ ይከተሉ 👇
🔗 https://t.me/+r3LZG4PCAKI3NmMy
📣 @sputnik_ethiopia
❤4👍2😡1
ምርጫ ቦርድ ነገ በልዩ የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ድምፅ የመስጠት ሂደት እንደሚከናወን ገለጸ
በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና በወታደራዊ ካምፖች በሚገኙ ልዩ ጣቢያዎች ነገ በልዩ ሁኔታ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት እንደሚከናወን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት ማስፈጸሙን አውስቷል።
በአሁን ሰዓት ቦርዱ ከምርጫ ክልል ጽህፈት ቤት ወደ ቦርዱ ማዕከል በመምጣት ላይ ያሉ ውጤቶችን የማረጋገጥ፣ የኦዲት ግኝት ያለባቸውን ውጤቶች የመመርመር እንዲሁም የተረጋገጡ ውጤቶችን ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ሥራ ላይ እንደሚገኝም አመልክቷል።
በተጨማሪም በፖለቲካ ፓርቲዎችና በግል ዕጩዎች የቀረቡ አቤቱታዎችን በሕግ ባለሙያ ጉባዔ አማካኝነት የማደራጀትና ምሥክር የመሥማት ሥራ እያከናወነ ነው።
በቀጣይም በተጠቀሰው ሂደት ያለፉ ውጤቶች ለቦርድ ውሣኔ በማቅረብ እና በማፀደቅ በሕጉ መሠረት ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግም ቦርዱ አስታውቋል።
ቦርዱ “በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 17” በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም የካምፑ ነዋሪዎችን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ እንዲሣተፉ በመራጭነት መመዝገቡ ይታወቃል።
በመሆኑም በካምፖቹ በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ድምፅ የመስጠት ሂደት ነገ እንደሚከናወን ቦርዱ በመረጃው አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና በወታደራዊ ካምፖች በሚገኙ ልዩ ጣቢያዎች ነገ በልዩ ሁኔታ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት እንደሚከናወን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት ማስፈጸሙን አውስቷል።
በአሁን ሰዓት ቦርዱ ከምርጫ ክልል ጽህፈት ቤት ወደ ቦርዱ ማዕከል በመምጣት ላይ ያሉ ውጤቶችን የማረጋገጥ፣ የኦዲት ግኝት ያለባቸውን ውጤቶች የመመርመር እንዲሁም የተረጋገጡ ውጤቶችን ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ሥራ ላይ እንደሚገኝም አመልክቷል።
በተጨማሪም በፖለቲካ ፓርቲዎችና በግል ዕጩዎች የቀረቡ አቤቱታዎችን በሕግ ባለሙያ ጉባዔ አማካኝነት የማደራጀትና ምሥክር የመሥማት ሥራ እያከናወነ ነው።
በቀጣይም በተጠቀሰው ሂደት ያለፉ ውጤቶች ለቦርድ ውሣኔ በማቅረብ እና በማፀደቅ በሕጉ መሠረት ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግም ቦርዱ አስታውቋል።
ቦርዱ “በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 17” በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም የካምፑ ነዋሪዎችን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ እንዲሣተፉ በመራጭነት መመዝገቡ ይታወቃል።
በመሆኑም በካምፖቹ በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ድምፅ የመስጠት ሂደት ነገ እንደሚከናወን ቦርዱ በመረጃው አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10🤪7👍3😁1
ኢሰመኮ በአርሲ ለተፈጸመው ጥቃት የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊትን ተጠያቂ አደረገ፤ ታጣቂ ቡድኑ ክሱን አስተባብሏል!
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ የተፈጸሙት ጥቃቶች መንግሥት «ሸኔ» ብሎ በሚጠራው በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት የተከወኑ ናቸው ሲል ከሰሰ። ታጣቂ ቡድኑ በበኩሉ ለደረሰው ጥቃት ኃላፊነት እንደማይወስድ አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ምርመራ ማድረጉን ተከትሎ ትላንት ባወጣው መግለጫ፣ “በቦታው በአካል በመገኘት፣ ከዐይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች፣ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ እና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት መረጃዎችና ማስረጃዎች መሰብሰቡን ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ የተፈጸሙት ጥቃቶች መንግሥት «ሸኔ» ብሎ በሚጠራው በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት የተከወኑ ናቸው ሲል ከሰሰ። ታጣቂ ቡድኑ በበኩሉ ለደረሰው ጥቃት ኃላፊነት እንደማይወስድ አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ምርመራ ማድረጉን ተከትሎ ትላንት ባወጣው መግለጫ፣ “በቦታው በአካል በመገኘት፣ ከዐይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች፣ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ እና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት መረጃዎችና ማስረጃዎች መሰብሰቡን ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪15❤13👍7
በሸረሪና የተፈፀመው የድሮን ጥቃት‼️
በዛሬው ዕለት በሱዳን ድንበር የድሮን ጥቃት ከመፈፀሙ በፊት በትናንትናው እለት የትግራይ አርሚ 13 ኮር 2 ታጣቂዎች በኤርትራ አድርገው በእግር ተጉዘው ወደ ሱዳን ለመሄድ ሸረሪና ደርሰው ነበር።
ከዚህ በተጨማሪ ዛሬ ሁለት ኦራል እና አምስት FSR የጦር መሳሪያ እና ሎጅስቲክስ የጫኑ መኪኖች ወደ ሸረሪና አቅንተው ነበር። በሱዳን የሚገኘው የአርሚ 70 ጦር አዛዥ ታጣቂዎቹን ለመቀበል ለዛሬ ሰኔ 1/2018 ዓ.ም ቀጠሮ ይዘው ነበር።
ዛሬ 5:45 ላይ የኢትዮጵያ አየር ሀይል በድሮን ጥቃት የፈፀመው በዚህ ምክንያት ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በዛሬው ዕለት በሱዳን ድንበር የድሮን ጥቃት ከመፈፀሙ በፊት በትናንትናው እለት የትግራይ አርሚ 13 ኮር 2 ታጣቂዎች በኤርትራ አድርገው በእግር ተጉዘው ወደ ሱዳን ለመሄድ ሸረሪና ደርሰው ነበር።
ከዚህ በተጨማሪ ዛሬ ሁለት ኦራል እና አምስት FSR የጦር መሳሪያ እና ሎጅስቲክስ የጫኑ መኪኖች ወደ ሸረሪና አቅንተው ነበር። በሱዳን የሚገኘው የአርሚ 70 ጦር አዛዥ ታጣቂዎቹን ለመቀበል ለዛሬ ሰኔ 1/2018 ዓ.ም ቀጠሮ ይዘው ነበር።
ዛሬ 5:45 ላይ የኢትዮጵያ አየር ሀይል በድሮን ጥቃት የፈፀመው በዚህ ምክንያት ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍13❤9👏3🕊2👌1