የጦርነቱ አድማስ ይሰፋል-ኢራን‼️
የኢራን ጠቅላይ መሪ ከፍተኛ ወታደራዊ አማካሪ ለ CNN፡-
'ጦርነቱ ከቀጠለ እና አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን የባህር ላይ እገዳ ካልተነሳ ጦርነቱን ወደ ህንድ ውቅያኖስ ፣ቀይባህር (ባብ አል ማንዳብ ሰርጥ) እና ሜዲትራኒያን ባህር እናስፋፋለን። እስካሁን ጥቃት ስንፈጽምባቸው ከነበሩት የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች በተጨማሪ ሌሎች ቀጠናዎች ላይ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ቤዞች ላይ ጥቃት በመፈፀም ለጦርነቱ ሌላ ገጽታ እንሰጣለን'ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢራን ጠቅላይ መሪ ከፍተኛ ወታደራዊ አማካሪ ለ CNN፡-
'ጦርነቱ ከቀጠለ እና አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን የባህር ላይ እገዳ ካልተነሳ ጦርነቱን ወደ ህንድ ውቅያኖስ ፣ቀይባህር (ባብ አል ማንዳብ ሰርጥ) እና ሜዲትራኒያን ባህር እናስፋፋለን። እስካሁን ጥቃት ስንፈጽምባቸው ከነበሩት የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች በተጨማሪ ሌሎች ቀጠናዎች ላይ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ቤዞች ላይ ጥቃት በመፈፀም ለጦርነቱ ሌላ ገጽታ እንሰጣለን'ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍22❤8👀2👏1🕊1🤣1
መረጃ‼️
ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች – ኢትዮጵያ፣ የትግራይ ጸጥታ ኃይሎች በክልሉ መጠነ ሠፊ "አፈሳ" እና "የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ" እየተካሄደ መኾኑን በምርመራ ማረጋገጡን ገለጠ።
ድርጊቶቹ ከሚፈጸሙቧቸው አካባቢዎች መካከል፣ ሰሜን ምስራቅ ዞን፣ ማዕከላዊ ዞንና ምሥራቃዊ ዞን እንደሚገኙበት ተቋሙ ጠቅሷል።
ኾኖም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከመቀሌና ሌሎይ ጥቂት አካባቢዎች በስተቀር አፈሳው በመላዋ ትግራይ መስፋፋቱን ተቋሙ አስታውቋል።
አፈሳው ባብዛኛው ዒላማ ያደረገው የቀድሞ ተዋጊዎችንና ወጣቶችን እንደኾነ መረዳቱን የጠቀሠው ተቋሙ፣ በጦርነቱ ተዋጊ ያላዋጡ ቤተሰቦች አንድ ምልምል እንዲያዋጡ እየተገደዱ ይገኛሉ ብሏል።
ተቋሙ የትግራይ ባለሥልጣናት አፈሳውን ባስቸኳይ እንዲያስቆሙ፣ በጊዜያዊ ማቆያ የያዟቸውን ግለሰቦች እንዲለቁና ጊዜያዊ መጠለያዎችን ለሰብዓዊ መብት ተቋማት ክፍት እንዲያደርጉ የጠየቀ ሲኾን፣ አፍሪካ ኅብረት፣ አውሮፓ ኅብረትና አሜሪካም አፈሳው እንዲቆም ግፊት እንዲፈጥሩ ጥሪ አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች – ኢትዮጵያ፣ የትግራይ ጸጥታ ኃይሎች በክልሉ መጠነ ሠፊ "አፈሳ" እና "የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ" እየተካሄደ መኾኑን በምርመራ ማረጋገጡን ገለጠ።
ድርጊቶቹ ከሚፈጸሙቧቸው አካባቢዎች መካከል፣ ሰሜን ምስራቅ ዞን፣ ማዕከላዊ ዞንና ምሥራቃዊ ዞን እንደሚገኙበት ተቋሙ ጠቅሷል።
ኾኖም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከመቀሌና ሌሎይ ጥቂት አካባቢዎች በስተቀር አፈሳው በመላዋ ትግራይ መስፋፋቱን ተቋሙ አስታውቋል።
አፈሳው ባብዛኛው ዒላማ ያደረገው የቀድሞ ተዋጊዎችንና ወጣቶችን እንደኾነ መረዳቱን የጠቀሠው ተቋሙ፣ በጦርነቱ ተዋጊ ያላዋጡ ቤተሰቦች አንድ ምልምል እንዲያዋጡ እየተገደዱ ይገኛሉ ብሏል።
ተቋሙ የትግራይ ባለሥልጣናት አፈሳውን ባስቸኳይ እንዲያስቆሙ፣ በጊዜያዊ ማቆያ የያዟቸውን ግለሰቦች እንዲለቁና ጊዜያዊ መጠለያዎችን ለሰብዓዊ መብት ተቋማት ክፍት እንዲያደርጉ የጠየቀ ሲኾን፣ አፍሪካ ኅብረት፣ አውሮፓ ኅብረትና አሜሪካም አፈሳው እንዲቆም ግፊት እንዲፈጥሩ ጥሪ አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13👍7💊6👏1😁1👀1
ኤርትራ የንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት ገጠማት።
የውሃ ማጓጓዣ ታንከሮች ስራ ማቆማቸው ለዋሃ እጥረት መከሰት ምክንያት ሆኗል።
የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት ባስከተለው የሀይል እጥረት ኤርትራ ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩ ተገልጿል።
በዚሁ የሀይል እጥረት ሳቢያ ነዳጅ የሚጠቀሙ የውሃ ታንከሮች ስራ አቁመዋል ተብሏል።
የመጠጥ፣ የንፅህና እና ሌሎች አገልግሎት የሚውል በቂ የውሃ አቅርቦት አለመኖሩ ተመልክቷል። የውሃ እጥረት በከተማ እና በገጠር ዋነኛ ችግር ሆኗል ተብሏል። #awate
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የውሃ ማጓጓዣ ታንከሮች ስራ ማቆማቸው ለዋሃ እጥረት መከሰት ምክንያት ሆኗል።
የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት ባስከተለው የሀይል እጥረት ኤርትራ ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩ ተገልጿል።
በዚሁ የሀይል እጥረት ሳቢያ ነዳጅ የሚጠቀሙ የውሃ ታንከሮች ስራ አቁመዋል ተብሏል።
የመጠጥ፣ የንፅህና እና ሌሎች አገልግሎት የሚውል በቂ የውሃ አቅርቦት አለመኖሩ ተመልክቷል። የውሃ እጥረት በከተማ እና በገጠር ዋነኛ ችግር ሆኗል ተብሏል። #awate
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢10❤9🎉4👍3🙏2🕊1💔1🙊1
#ሰበር❗የድሮን ጥቃት ተፈፀመ‼️
ከኤርትራ ድንበር ስድስት ኪሎሜትር ርቀት በምትገኘው #ገምሃሎ (ሽራሮ አካባቢ) ዛሬ አዳሩን ከለሊቱ 6:30 ጀምሮ የድሮን ጥቃት መፈፀሙን ምንጮች ለአዩዘሀበሻ አረጋግጠዋል።
የድሮን ጥቃት ከተፈፀመ በኋላ ለረጅም ግዜ ፍንዳታ እና ቃጠሎ ተፈጥሮ እንደነበር ገልፀውልናል። በገምሃሎ አካባቢ የህወሓት አርሚ 13 በስፋት የሚንቀሳቀስበት ቀጠና ሲሆን ጥቃቱ የተፈፀመው ግን በጦር መሳሪያ መጋዘን ላይ ሳይሆን እንዳልቀረ ጠቁመዋል።
ድሮኗ ወደ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከኤርትራ ድንበር ስድስት ኪሎሜትር ርቀት በምትገኘው #ገምሃሎ (ሽራሮ አካባቢ) ዛሬ አዳሩን ከለሊቱ 6:30 ጀምሮ የድሮን ጥቃት መፈፀሙን ምንጮች ለአዩዘሀበሻ አረጋግጠዋል።
የድሮን ጥቃት ከተፈፀመ በኋላ ለረጅም ግዜ ፍንዳታ እና ቃጠሎ ተፈጥሮ እንደነበር ገልፀውልናል። በገምሃሎ አካባቢ የህወሓት አርሚ 13 በስፋት የሚንቀሳቀስበት ቀጠና ሲሆን ጥቃቱ የተፈፀመው ግን በጦር መሳሪያ መጋዘን ላይ ሳይሆን እንዳልቀረ ጠቁመዋል።
ድሮኗ ወደ
አዲሀገራይ፣አዲነብሪድ እና አዲ ዳዕሮ አሰሳ በማድረግ ላይ መሆኑን ገልፀዋል።(አዩ)@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍23❤8😡8😢3👏2🤯1👀1🤪1
Update❗የፖሊስ አዛዡ ተይዟል‼️
በአርሲ አሰኮ ወረዳ በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ አሳዛኝ ጭፍጨፋ መፈፀሙን ተከትሎ ከጥቃቱ ጀርባ የተጠረጠሩት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ አቶ አባቡ አብደላ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የሰላምና ፀጥታ ሀላፊው ደግሞ ለግዜው ተሰውረዋል፣ ያሉበት አልታወቀም። አነዚህ አመራሮች ከጥቃቱ ቀደም ብሎ ከመንግሥት የመጣ ጥይት በ118 ብር ግዙ በሚል ከገበሬው ብር በመሰብሰብ ጥይቱን ለገበሬው ሳይሰጡ ብሩን በመዝረፍ ዋነኛ ተዋናይ እንደሆኑ ትናንት መዘገባችን ይታወሳል።(ayu)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአርሲ አሰኮ ወረዳ በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ አሳዛኝ ጭፍጨፋ መፈፀሙን ተከትሎ ከጥቃቱ ጀርባ የተጠረጠሩት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ አቶ አባቡ አብደላ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የሰላምና ፀጥታ ሀላፊው ደግሞ ለግዜው ተሰውረዋል፣ ያሉበት አልታወቀም። አነዚህ አመራሮች ከጥቃቱ ቀደም ብሎ ከመንግሥት የመጣ ጥይት በ118 ብር ግዙ በሚል ከገበሬው ብር በመሰብሰብ ጥይቱን ለገበሬው ሳይሰጡ ብሩን በመዝረፍ ዋነኛ ተዋናይ እንደሆኑ ትናንት መዘገባችን ይታወሳል።(ayu)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤28🥱11👍4😢4🤔2🌚2👏1😁1💯1
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና በአርሲ ዞን በተፈጸሙ ጥቃቶች የሰው ህይወት ጠፋ
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ምርጫውን ለማደናቀፍና በህዝቡ ላይ ሽብር ለመፍጠር የታለሙ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች የስፖርት ውድድር (Champions League) በመመልከት ላይ እያሉ በተሰነዘረ ጥቃት አንድ ተማሪ ሲሞት 26 የሚሆኑት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ "ሸኔ" ተብሎ በሚጠራው ቡድን በተሰነዘረ ጥቃት አምስት የሚሊሻ አባላት፣ ሶስት የፖሊስ አባላት እና አራት ሲቪሎች መገደላቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በጥቃቱ አንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣ የመንግስት ጤና ጣቢያ እና የቀበሌ ጽህፈት ቤት መቃጠላቸው እንዲሁም 65 የግለሰብ ቤቶች መውደማቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም በሸርካ እና በእንቆሌ ዋቤ ወረዳዎች ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውና ታግተው የነበሩ ግለሰቦች ህይወት ማለፉ በመግለጫው ተጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ምርጫውን ለማደናቀፍና በህዝቡ ላይ ሽብር ለመፍጠር የታለሙ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች የስፖርት ውድድር (Champions League) በመመልከት ላይ እያሉ በተሰነዘረ ጥቃት አንድ ተማሪ ሲሞት 26 የሚሆኑት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ "ሸኔ" ተብሎ በሚጠራው ቡድን በተሰነዘረ ጥቃት አምስት የሚሊሻ አባላት፣ ሶስት የፖሊስ አባላት እና አራት ሲቪሎች መገደላቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በጥቃቱ አንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣ የመንግስት ጤና ጣቢያ እና የቀበሌ ጽህፈት ቤት መቃጠላቸው እንዲሁም 65 የግለሰብ ቤቶች መውደማቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም በሸርካ እና በእንቆሌ ዋቤ ወረዳዎች ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውና ታግተው የነበሩ ግለሰቦች ህይወት ማለፉ በመግለጫው ተጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡21❤18🤪4👍2
“ኢትዮጽያ ደሀ ሀገር ነች” ኤለን መስክ!
ኤለን መስክ ስለ ኢትዮጵያ ያጋራው ነገር በዚህ ሰአት ላይ በጣም መነጋገሪያ ሆኗል። 1 ፖስት ላይ ሼር ያደረገው ኤለን መስክ ኢትዮጵያም ድሃ ሀገር ነች። ኮሎናይዜሽን ሀገራትን ድሃ የሚያደርግ ቢሆን ኢትዮጵያ ሀብታም መሆን ነበረባት፤ ነገር ግን በጣም ድሃ ሀገር ነች። እንደዚሁም ደግሞ ቬትናም በፈረንሳይ ተገዝታለች፤ ነገር ግን አሁን ላይ ሀብታም ሀገር ነች። ስለዚህ ኮሎናይዜሽን ሀገራትን ድሃም ሀብታምም አያደርግም። እንደዚህ አይነት ነንሴንስ ነገር መቆም አለበት የሚለውን ፖስት ያጋራው ኤለን መስክ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ መነጋገሪያ ሆኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኤለን መስክ ስለ ኢትዮጵያ ያጋራው ነገር በዚህ ሰአት ላይ በጣም መነጋገሪያ ሆኗል። 1 ፖስት ላይ ሼር ያደረገው ኤለን መስክ ኢትዮጵያም ድሃ ሀገር ነች። ኮሎናይዜሽን ሀገራትን ድሃ የሚያደርግ ቢሆን ኢትዮጵያ ሀብታም መሆን ነበረባት፤ ነገር ግን በጣም ድሃ ሀገር ነች። እንደዚሁም ደግሞ ቬትናም በፈረንሳይ ተገዝታለች፤ ነገር ግን አሁን ላይ ሀብታም ሀገር ነች። ስለዚህ ኮሎናይዜሽን ሀገራትን ድሃም ሀብታምም አያደርግም። እንደዚህ አይነት ነንሴንስ ነገር መቆም አለበት የሚለውን ፖስት ያጋራው ኤለን መስክ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ መነጋገሪያ ሆኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍45💯20❤10😱7😢3👏1🤯1👌1🙊1
የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ የሁሉንም አሽከርካሪዎች ብቃት ዳግም ለመመዘን እየተሰናዳሁ ነው ብሏል፡፡
ይህም ሀሳብ በብዙዎች ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል፡፡
ለረጅም ዓመታት በአሽከርካሪነት ያሳለፉ የከባድ መኪና ሾፌሮች ከዚህ ሁሉ ዘመን በኋላ ዳግም ለፈተና የምንቀመጠው እንዴት ነው የሚል ጥያቄን ያነሳሉ፡፡
ከዓመታት የማሽከርከር ልምድ በኋላ እንደ አዲስ ብቃትን ለመመዘን ስራ የሚሰራውስ ምን ውጤትን ለማምጣት ነው ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ይህም ሀሳብ በብዙዎች ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል፡፡
ለረጅም ዓመታት በአሽከርካሪነት ያሳለፉ የከባድ መኪና ሾፌሮች ከዚህ ሁሉ ዘመን በኋላ ዳግም ለፈተና የምንቀመጠው እንዴት ነው የሚል ጥያቄን ያነሳሉ፡፡
ከዓመታት የማሽከርከር ልምድ በኋላ እንደ አዲስ ብቃትን ለመመዘን ስራ የሚሰራውስ ምን ውጤትን ለማምጣት ነው ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11🤣8👍3🙉2😢1🤪1😡1
የማስታወቂያ ግብዣ
የተከበራችሁ ቤተሰቦች ከ36,000 በላይ ተከታይ ባለው እና በደቂቃዎች ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝ ባለው በዚህ የቴሌግራም ቻናል ላይ ምርትና አገልግሎታችሁን ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንድታስተዋውቁ በአክብሮት ተጋብዛችኋል‼
✔Youtube ቻናል …
✔የትምህርት ተቋማት…...
✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…...
✔የትራንስፖርት አገልግሎት…....
✔ኤጀንሲዎች……
✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች......
✔ሌሎችም የምትሰጧቸውን አገልግሎቶች.....ማስተዋወቅ የምትፈልጉ በዚህ በኩል ኑ 👇
መልዕክት መቀበያ:—@Addis_reporter_bot
የተከበራችሁ ቤተሰቦች ከ36,000 በላይ ተከታይ ባለው እና በደቂቃዎች ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝ ባለው በዚህ የቴሌግራም ቻናል ላይ ምርትና አገልግሎታችሁን ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንድታስተዋውቁ በአክብሮት ተጋብዛችኋል‼
✔Youtube ቻናል …
✔የትምህርት ተቋማት…...
✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…...
✔የትራንስፖርት አገልግሎት…....
✔ኤጀንሲዎች……
✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች......
✔ሌሎችም የምትሰጧቸውን አገልግሎቶች.....ማስተዋወቅ የምትፈልጉ በዚህ በኩል ኑ 👇
መልዕክት መቀበያ:—@Addis_reporter_bot
❤3👍3
አዲስ ሪፖርተር - NEWS
#ሰበር❗የድሮን ጥቃት ተፈፀመ‼️ ከኤርትራ ድንበር ስድስት ኪሎሜትር ርቀት በምትገኘው #ገምሃሎ (ሽራሮ አካባቢ) ዛሬ አዳሩን ከለሊቱ 6:30 ጀምሮ የድሮን ጥቃት መፈፀሙን ምንጮች ለአዩዘሀበሻ አረጋግጠዋል። የድሮን ጥቃት ከተፈፀመ በኋላ ለረጅም ግዜ ፍንዳታ እና ቃጠሎ ተፈጥሮ እንደነበር ገልፀውልናል። በገምሃሎ አካባቢ የህወሓት አርሚ 13 በስፋት የሚንቀሳቀስበት ቀጠና ሲሆን ጥቃቱ የተፈፀመው ግን በጦር መሳሪያ…
የድሮን ጥቃቱ ዝርዝር መረጃ ደርሶናል‼️
ትናንት ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ከለሊቱ 6፡30 እስከ 7፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በሰሜን ምዕራብ ትግራይ ገምሃሎ ከሰንቤል አካባቢ ወደ ባደም በሚሄድ የህወሓት ወታደራዊ ኮንቮይ ላይ የድሮን ጥቃት መፈፀሙን መዘገባችን ይታወሳል።
ጥቃቱ የተፈፀመው የህወሃት አርሚ 13 ኮር 1 በ27 ተሽከርካሪዎች ሎጂስቲክስ፣ መሳሪያና ተተኳሽ ጭነው እየተጓዙ በነበረው ወቅት መሆኑን የአካባቢው ምንጮች ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
እንደ የአካባቢው ምንጮች ገለጻ ድንገት በተፈፀመው የድሮን ጥቃት
📍5 ተሳቢ መኪናዎች፣2 ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች(ኦራል) እና 4 ፒካፕ መኪኖች ላይ ከፍተኛ የንብረት ውድመት ደርሷል።
📍በርካታ የሰራዊቱ አባላት ቆስለዋል፣ የቆሰሉትም በሽራሮ፣ በሺሬ እና በመቀሌ ወደሚገኙ ሆስፒታሎች እየተወሰዱ ነው።
📌 የሞቱት አስኬረን እየተሰበሰበ ነው፣26 በጅምላ ተቀብረዋል።
ጥቃቱን ተከትሎ በሰልፍ ሲጓዙ የነበሩት ወታደሮች የተበታተኑ ሲሆን ወታደራዊ መሪዎቹ አሁንም የተበተኑትን አባላት ለመሰብሰብና ለማዋሃድ ሁለት የፍተሻ ጣቢያዎችን እያዘጋጁ ነው።
ጥቃቱ የተፈፀመበት አካባቢ በጸጥታ ኃይሎች ተከቧል። እስካሁን ድረስ ከመንግስትም ሆነ ከትግራይ ኦፊሴላዊ ጎን ምንም አይነት ተጨማሪ መግለጫ አልተሰጠም።
Via : አዩዘሀበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👉26 በጅምላ ተቀብረዋል።
ትናንት ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ከለሊቱ 6፡30 እስከ 7፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በሰሜን ምዕራብ ትግራይ ገምሃሎ ከሰንቤል አካባቢ ወደ ባደም በሚሄድ የህወሓት ወታደራዊ ኮንቮይ ላይ የድሮን ጥቃት መፈፀሙን መዘገባችን ይታወሳል።
ጥቃቱ የተፈፀመው የህወሃት አርሚ 13 ኮር 1 በ27 ተሽከርካሪዎች ሎጂስቲክስ፣ መሳሪያና ተተኳሽ ጭነው እየተጓዙ በነበረው ወቅት መሆኑን የአካባቢው ምንጮች ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
እንደ የአካባቢው ምንጮች ገለጻ ድንገት በተፈፀመው የድሮን ጥቃት
📍5 ተሳቢ መኪናዎች፣2 ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች(ኦራል) እና 4 ፒካፕ መኪኖች ላይ ከፍተኛ የንብረት ውድመት ደርሷል።
📍በርካታ የሰራዊቱ አባላት ቆስለዋል፣ የቆሰሉትም በሽራሮ፣ በሺሬ እና በመቀሌ ወደሚገኙ ሆስፒታሎች እየተወሰዱ ነው።
📌 የሞቱት አስኬረን እየተሰበሰበ ነው፣26 በጅምላ ተቀብረዋል።
ጥቃቱን ተከትሎ በሰልፍ ሲጓዙ የነበሩት ወታደሮች የተበታተኑ ሲሆን ወታደራዊ መሪዎቹ አሁንም የተበተኑትን አባላት ለመሰብሰብና ለማዋሃድ ሁለት የፍተሻ ጣቢያዎችን እያዘጋጁ ነው።
ጥቃቱ የተፈፀመበት አካባቢ በጸጥታ ኃይሎች ተከቧል። እስካሁን ድረስ ከመንግስትም ሆነ ከትግራይ ኦፊሴላዊ ጎን ምንም አይነት ተጨማሪ መግለጫ አልተሰጠም።
Via : አዩዘሀበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤21👏7👍4🫡3😢2🙊2✍1😱1💔1🤪1
የተባበሩት መንግስታት ዓለም ለከፍተኛ ሙቀት እንዲዘጋጅ አሳሰበ
የተባበሩት መንግስታት የዓለም የአየር ንብረት ድርጅት ዓለም ለከፍተኛ ሙቀት እንዲዘጋጅ አስጠንቅቋል ።
በቀጣዮቹ ወራት በብዙ የዓለም ክፍሎች ከፍተኛ ሙቀት፣ ድርቅ እና ከባድ የአየር ንብረት ሊከሰቱ እንደሚችሉም ገልጿል።
ድርጅቱ ከሰኔ እስከ ነሐሴ ባለው ጊዜ በአብዛኛው የዓለም ክፍል ከመደበኛው በላይ ሙቀት እንደሚመዘገብ ተንብዮዋል
ይህ ሁኔታ በግብርና፣ በውሃ አቅርቦት እና በምግብ ዋስትና ላይ ተጨማሪ ጫና ሊያሳድር ይችላል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የተባበሩት መንግስታት የዓለም የአየር ንብረት ድርጅት ዓለም ለከፍተኛ ሙቀት እንዲዘጋጅ አስጠንቅቋል ።
በቀጣዮቹ ወራት በብዙ የዓለም ክፍሎች ከፍተኛ ሙቀት፣ ድርቅ እና ከባድ የአየር ንብረት ሊከሰቱ እንደሚችሉም ገልጿል።
ድርጅቱ ከሰኔ እስከ ነሐሴ ባለው ጊዜ በአብዛኛው የዓለም ክፍል ከመደበኛው በላይ ሙቀት እንደሚመዘገብ ተንብዮዋል
ይህ ሁኔታ በግብርና፣ በውሃ አቅርቦት እና በምግብ ዋስትና ላይ ተጨማሪ ጫና ሊያሳድር ይችላል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍3👀2
"የታገደብን 24 ቢሊዮን ዶላር ሳይለቀቅልን አንደራደርም" - የሞጅታባ አማካሪ
ኢራን በአሜሪካ የታገደባት ገንዘብ እንዲለቀቅ ለአደራዳሪዎች መጠየቋ ተገለጸ።
የኑክሌያር ጦር መሳሪያ እና የሆርሙዝ ሰርጥ አድርጋ የቆየችው ቴህራን፣ በውጭ ሀገር የሚገኘው ገንዘቧም እንዲለቀቅላት ጠይቃለች።
የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኮሚኒ አማካሪ የሆኑት ሞህሰን ረዛይ "የገንዘብ ጉዳይም የውይይቱ አካል ሆኖ ቀጥሏል" ሲሉ ተናግረዋል።
ረዛይ "የተያዘብን ገንዘብ የኢኮኖሚ ማዕቀብ አካል መሆኑን ስለምናውቅ ከዋሽንግተን ጋር ያለውን የድርድር ሂደት ሊጎዳው ይችላል" ሲሉም ስጋታቸውን አንጸባርቀዋል።
አማካሪው አክለውም "የታገደብን 24 ቢሊዮን ዶላር ሳይለቀቅልን አንደራደርም" ብለዋል።
"ይህ ውሳኔያችንን አሜሪካ በድርድሩ ምን ያክል ግልጽ እንደሆነች እንፈትንበታለን" ሲሉ አብራርተዋል።
አማካሪው በማብራሪያቸው ቴህራን በእያንዳንዱ ውይይት ተጨባጭ እርምጃ ማየት እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኢራን በአሜሪካ የታገደባት ገንዘብ እንዲለቀቅ ለአደራዳሪዎች መጠየቋ ተገለጸ።
የኑክሌያር ጦር መሳሪያ እና የሆርሙዝ ሰርጥ አድርጋ የቆየችው ቴህራን፣ በውጭ ሀገር የሚገኘው ገንዘቧም እንዲለቀቅላት ጠይቃለች።
የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኮሚኒ አማካሪ የሆኑት ሞህሰን ረዛይ "የገንዘብ ጉዳይም የውይይቱ አካል ሆኖ ቀጥሏል" ሲሉ ተናግረዋል።
ረዛይ "የተያዘብን ገንዘብ የኢኮኖሚ ማዕቀብ አካል መሆኑን ስለምናውቅ ከዋሽንግተን ጋር ያለውን የድርድር ሂደት ሊጎዳው ይችላል" ሲሉም ስጋታቸውን አንጸባርቀዋል።
አማካሪው አክለውም "የታገደብን 24 ቢሊዮን ዶላር ሳይለቀቅልን አንደራደርም" ብለዋል።
"ይህ ውሳኔያችንን አሜሪካ በድርድሩ ምን ያክል ግልጽ እንደሆነች እንፈትንበታለን" ሲሉ አብራርተዋል።
አማካሪው በማብራሪያቸው ቴህራን በእያንዳንዱ ውይይት ተጨባጭ እርምጃ ማየት እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤21👍3🤔3😁2
የድሮን ጥቃት ተፈፅሞብናል-ህወሓት‼️
የፌደራል መንግሥቱ በጀት፣ ነዳጅ፣ መድሃኒት፣ ገንዘብ ወዘተ. በመዝጋት ተጨማሪ ጭካኔዎችን በመፈጸም ሊያሸንፋቸው ያልቻሉትን በድሮን ለማጥፋት ጥቃት እየፈፀመ ነው:-ህወሓት‼️
የፌደራል መንግስቱ በትግራይ ላይ ጦርነት እንደገና መጀመሩ አገዛዙ ያለ ጦርነት ሊተርፍ እንደማይችል በግልጽ ያረጋግጣል ብሏል።
ለትግራይ ህዝብ አድልዎ፣ በጀት መዝጋት፣ የድሮን ጥቃት፣ ወዘተ አይገባውም ነበር ያለ ሲሆን የትግራይ ህዝብ የሰላም እና የትዕግስት ጥያቄ እንደ ፍርሃት ተቆጥሯል ብሏል።
የትግራይ ህዝብ በክህደት ሊሸነፍ እንደማይችል መታወቅ አለበት ሲል አክሏል።
በሽራሮ ታችኛው አዲያቦ ለሊት ላይ በተፈፀመው የድሮን ጥቃት በትግራይ ሰራዊት አባላት ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት ደርሷል እንዲሁም በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የክልሉ መንግሥት በትግርኛ ካስተላለፈው መግለጫ ተመልክተናል።
በመጨረሻም የፌደራል መንግሥቱ ክልሉን ወደማይቋረጥ ቀውስ ውስጥ እየከተተው ስለሆነ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ እናሳስባለን'ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የፌደራል መንግሥቱ በጀት፣ ነዳጅ፣ መድሃኒት፣ ገንዘብ ወዘተ. በመዝጋት ተጨማሪ ጭካኔዎችን በመፈጸም ሊያሸንፋቸው ያልቻሉትን በድሮን ለማጥፋት ጥቃት እየፈፀመ ነው:-ህወሓት‼️
የፌደራል መንግስቱ በትግራይ ላይ ጦርነት እንደገና መጀመሩ አገዛዙ ያለ ጦርነት ሊተርፍ እንደማይችል በግልጽ ያረጋግጣል ብሏል።
ለትግራይ ህዝብ አድልዎ፣ በጀት መዝጋት፣ የድሮን ጥቃት፣ ወዘተ አይገባውም ነበር ያለ ሲሆን የትግራይ ህዝብ የሰላም እና የትዕግስት ጥያቄ እንደ ፍርሃት ተቆጥሯል ብሏል።
የትግራይ ህዝብ በክህደት ሊሸነፍ እንደማይችል መታወቅ አለበት ሲል አክሏል።
በሽራሮ ታችኛው አዲያቦ ለሊት ላይ በተፈፀመው የድሮን ጥቃት በትግራይ ሰራዊት አባላት ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት ደርሷል እንዲሁም በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የክልሉ መንግሥት በትግርኛ ካስተላለፈው መግለጫ ተመልክተናል።
በመጨረሻም የፌደራል መንግሥቱ ክልሉን ወደማይቋረጥ ቀውስ ውስጥ እየከተተው ስለሆነ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ እናሳስባለን'ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣28❤25🤔5👍3💔2😢1🕊1🤪1
አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Photo
ፊልድ ማርሻሉ ስለ ጽምዶ‼️
ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ አዲስ ለተመረቁ ወታደራዊ መኮንኖች ትእዛዝ ሰጡ።
‹‹እናነት ወደ ሰራዊቱ ስትቀላቀሉ ጣረሞት ላይ ያለውን ባንዳ ጨርሳችሁ ማስወገድ ይኖርባችኋል›› ሲሉ ዛሬ ለተመረቁ መኮንኖች ትእዛዝ ሰጥተዋል፡፡
ጽምዶን በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግረዋል፡፡
ፊልድ ማርሻሉ ህልማቸው መክኗል፣ የጥፋት እጃቸው ተቆርጧል፣ ወሮ በላዎችን ተዋጓቸው የሚሉ አገላለጾች በመጠቀም ባወዛጋቢ ንግግር ተከስተዋል፡፡
‹‹ጠላቶቻችን ጽምዶ ብለው መጥተዋል›› ያሉ ሲሆን፤ ሊበትኑን የዶለቱ ኃይሎች ህልማቸው መክኗል ሲሉም ተደምጠዋል፡፡
‹‹ማወቅ ያለባችሁ ጽምዶ አሁን የመጣ ጉዳይ አይደለም፤ ጽምዶ የ1960ዎቹ ስትራቴጂ ነው፤ የ60ዎቹ ትውልድ ማለት የዛሬ ጽምዶ ማለት ነው፤ የዚያን ዘመን ትውልድ ማርክሲዝም ሌኒኒዝም እያለ ታሪካዊ ጠላቶቻችንን እየጋበዘ፣ ሞቃዲሾ እና ካይሮ እየሄደ፤ የሱዳን፣ ግብጽ እና ኤርትራ ቅንጅት በመፍጠር ኢትዮጵያን ከባህር በር የማባረር ዘመን ነበር፤ የ1960ዎቹ ትውልድ›› በማለት የአሁኑን ጽምዶ ከ60ዎቹ ትውልድ እንቅስቃሴ ጋር አጋምደው አብራርተዋል፡፡
ቀጥለውም፣ ‹‹ያን ጊዜ ካይሮ እና ሞቃዲሾ ሄደው ደጅ የጠኑ የዚያድ ባሬ እና የፈርኦን ቤተሰብ ተላላኪዎች ግንባር ፈጥረው የዛሬ 60 አመት ኢትዮጵያን ከባህር በር በማባረር፤ ኢትዮጵያን በእርስ በርስ ጦርነት በማዳከም፣ በቀጠናው ተርጉም ያላት አገር እንዳትሆን አድርገዋል›› በማለት የ60ዎቹን የፖለቲካ ኃይሎች ተችተዋል፡፡
በወቅቱ ከባህር በር የተገፋንው ‹ጠላቶቻችን› ጎበዝ ስለሆኑ አይደለም ያሉም ሲሆን፤ ‹‹የተሳካላቸው እነርሱ ባንዳ ስላገኙ ነው›› በማለት ተናግረዋል፡፡
‹‹አሁንም እየተደረገ ያለው እርሱ ነው፤ ያን ጊዜ የነበሩ ባንዳዎች መልካቸውን ቀይረው እንጂ ያሉት እነርሱ ናቸው›› በማለት በጽምዶ እንቅስቃሴ ውስጥ ያሉ የአገር ውስጥ ኃይሎችን ባንዳ በማለት ጠርተዋል፡፡
‹‹ታሪካዊ ጠላቶች እና ምቀኛ ጎረቤታችን ተቀናጅተው የውስጥ ባንዳ ቀጥረው፤ አገራችሁን ለማፍረስ እየሰሩ ያለበት ጊዜ ነው፤ ነገር ግን እድሜ ለመከላከያ ሰራዊት አከርካሪያቸውን መትቶ ተሸመድምደው ጣረሞት ላይ ያሉበት ጊዜ ላይ ነን›› ሲሉም አክለዋል፡፡
‹‹እናነት ወደ ሰራዊቱ ስትቀላቀሉ ጣረሞት ላይ ያለውን ባንዳ ጨርሳችሁ ማስወገድ ይኖርባችኋል›› ሲሉ ዛሬ ለተመረቁ መኮንኖች ትእዛዝ ሰጥተዋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ አዲስ ለተመረቁ ወታደራዊ መኮንኖች ትእዛዝ ሰጡ።
‹‹እናነት ወደ ሰራዊቱ ስትቀላቀሉ ጣረሞት ላይ ያለውን ባንዳ ጨርሳችሁ ማስወገድ ይኖርባችኋል›› ሲሉ ዛሬ ለተመረቁ መኮንኖች ትእዛዝ ሰጥተዋል፡፡
ጽምዶን በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግረዋል፡፡
ፊልድ ማርሻሉ ህልማቸው መክኗል፣ የጥፋት እጃቸው ተቆርጧል፣ ወሮ በላዎችን ተዋጓቸው የሚሉ አገላለጾች በመጠቀም ባወዛጋቢ ንግግር ተከስተዋል፡፡
‹‹ጠላቶቻችን ጽምዶ ብለው መጥተዋል›› ያሉ ሲሆን፤ ሊበትኑን የዶለቱ ኃይሎች ህልማቸው መክኗል ሲሉም ተደምጠዋል፡፡
‹‹ማወቅ ያለባችሁ ጽምዶ አሁን የመጣ ጉዳይ አይደለም፤ ጽምዶ የ1960ዎቹ ስትራቴጂ ነው፤ የ60ዎቹ ትውልድ ማለት የዛሬ ጽምዶ ማለት ነው፤ የዚያን ዘመን ትውልድ ማርክሲዝም ሌኒኒዝም እያለ ታሪካዊ ጠላቶቻችንን እየጋበዘ፣ ሞቃዲሾ እና ካይሮ እየሄደ፤ የሱዳን፣ ግብጽ እና ኤርትራ ቅንጅት በመፍጠር ኢትዮጵያን ከባህር በር የማባረር ዘመን ነበር፤ የ1960ዎቹ ትውልድ›› በማለት የአሁኑን ጽምዶ ከ60ዎቹ ትውልድ እንቅስቃሴ ጋር አጋምደው አብራርተዋል፡፡
ቀጥለውም፣ ‹‹ያን ጊዜ ካይሮ እና ሞቃዲሾ ሄደው ደጅ የጠኑ የዚያድ ባሬ እና የፈርኦን ቤተሰብ ተላላኪዎች ግንባር ፈጥረው የዛሬ 60 አመት ኢትዮጵያን ከባህር በር በማባረር፤ ኢትዮጵያን በእርስ በርስ ጦርነት በማዳከም፣ በቀጠናው ተርጉም ያላት አገር እንዳትሆን አድርገዋል›› በማለት የ60ዎቹን የፖለቲካ ኃይሎች ተችተዋል፡፡
በወቅቱ ከባህር በር የተገፋንው ‹ጠላቶቻችን› ጎበዝ ስለሆኑ አይደለም ያሉም ሲሆን፤ ‹‹የተሳካላቸው እነርሱ ባንዳ ስላገኙ ነው›› በማለት ተናግረዋል፡፡
‹‹አሁንም እየተደረገ ያለው እርሱ ነው፤ ያን ጊዜ የነበሩ ባንዳዎች መልካቸውን ቀይረው እንጂ ያሉት እነርሱ ናቸው›› በማለት በጽምዶ እንቅስቃሴ ውስጥ ያሉ የአገር ውስጥ ኃይሎችን ባንዳ በማለት ጠርተዋል፡፡
‹‹ታሪካዊ ጠላቶች እና ምቀኛ ጎረቤታችን ተቀናጅተው የውስጥ ባንዳ ቀጥረው፤ አገራችሁን ለማፍረስ እየሰሩ ያለበት ጊዜ ነው፤ ነገር ግን እድሜ ለመከላከያ ሰራዊት አከርካሪያቸውን መትቶ ተሸመድምደው ጣረሞት ላይ ያሉበት ጊዜ ላይ ነን›› ሲሉም አክለዋል፡፡
‹‹እናነት ወደ ሰራዊቱ ስትቀላቀሉ ጣረሞት ላይ ያለውን ባንዳ ጨርሳችሁ ማስወገድ ይኖርባችኋል›› ሲሉ ዛሬ ለተመረቁ መኮንኖች ትእዛዝ ሰጥተዋል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤35🤪35👍11👀2🙊2😎2💯1
መረጃ‼️
የሶማሊላንድ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አብዲራህማን ዳሂግ ባካል፣ ሶማሊላንድ በባሕር በር ዙሪያ አሁንም ከኢትዮጵያ ጋር ለመተባበር ዝግጁ መኾኗን ለሪፖርተር በሠጡት ቃለ ምልልስ ገለጡ።
ኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት መብት አላት ብላ ሶማሊላንድ እንደምታምን የተናገሩት ባካል፣ ኢትዮጵያ በርበራ ወደብን እንደፈለገች መጠቀም ትችላለች ማለታቸውን ጋዜጣው ጠቅሷል።
ኢትዮጵያ በበርበራ ወደብ አግኝቻለሁ ያለችው የ19 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ባካል ኢትዮጵያ ወደቡን በሙሉ አቅሙ እስካሁን አልተጠቀመችበትም የሚል አጭር ምላሽ መስጠታቸውን ተገልጧል።
ኢትዮጵያ የሶማሊላንድን ቁልፍ አጋርነት ከግምት አስገብታ አንድ ቀን ለሶማሊላንድ እውቅና ትሠጣለች የሚል እምነት እንዳላቸው ባካል የገለጡት ሲኾን፣ ኾኖም ኢትዮጵያ እውቅና እንድትሠጣት ሶማሊላንድ ግፊት ማድረግ እንደማትፈልግ ተናግረዋል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሶማሊላንድ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አብዲራህማን ዳሂግ ባካል፣ ሶማሊላንድ በባሕር በር ዙሪያ አሁንም ከኢትዮጵያ ጋር ለመተባበር ዝግጁ መኾኗን ለሪፖርተር በሠጡት ቃለ ምልልስ ገለጡ።
ኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት መብት አላት ብላ ሶማሊላንድ እንደምታምን የተናገሩት ባካል፣ ኢትዮጵያ በርበራ ወደብን እንደፈለገች መጠቀም ትችላለች ማለታቸውን ጋዜጣው ጠቅሷል።
ኢትዮጵያ በበርበራ ወደብ አግኝቻለሁ ያለችው የ19 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ባካል ኢትዮጵያ ወደቡን በሙሉ አቅሙ እስካሁን አልተጠቀመችበትም የሚል አጭር ምላሽ መስጠታቸውን ተገልጧል።
ኢትዮጵያ የሶማሊላንድን ቁልፍ አጋርነት ከግምት አስገብታ አንድ ቀን ለሶማሊላንድ እውቅና ትሠጣለች የሚል እምነት እንዳላቸው ባካል የገለጡት ሲኾን፣ ኾኖም ኢትዮጵያ እውቅና እንድትሠጣት ሶማሊላንድ ግፊት ማድረግ እንደማትፈልግ ተናግረዋል ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤22🥰6👍2👏1
የትምህርት ሚኒስቴር ፈተና በማውጣት መምህራንን የሚያግዝ Application ወደ ሥራ አስገባ 🔥
ትምህርት ሚኒስቴር የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን የሥራ ጫና ለመቀነስ እና የትምህርትን ጥራት ለማረጋገጥ የሚያስችል “ኤጀንቲክ መምህር ረዳት” (Agentic AI Teacher Assistant) የተሰኘ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያ አበልጽጎ በሙከራ ደረጃ ስራ ላይ አውሏል።
ይህ ቴክኖሎጂ ሙሉ በሙሉ ያለኢንተርኔት የሚሰራ ሲሆን፣ በማዕከላዊ ሰርቨር ወይም በክላውድ ቴክኖሎጂ ላይ ሳይመሰረት በአካባቢያዊ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተጭኖ አገልግሎት የሚሰጥ ነው።
በተጨማሪም መተግበሪያው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን መጽሐፍት በሙሉ ዳታሴት በመውሰድና በማስተካከል የተዘጋጀ ነው።
በመተግበሪያው ምን ምን ነገሮች ማከናወን ይቻላል ?
- የትምህርት እቅድ (Lesson Plan) ማዘጋጀት፣
- ደረጃቸውን የጠበቁ የፈተና ጥያቄዎችንና አሳይመንቶችን ማመንጨት፣
- የማስተማሪያ ስልቶችን በራሱ ማቀናጀት ይችላል።
በማንኛውም ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ ኮምፒውተር ላይ ተጭኖ የሚሰራ ቀላል ሞዴልበማንኛውም ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ ኮምፒውተር ላይ ተጭኖ የሚሰራ ነውም ተብሎለታል።
በኢንተርኔት ኔትወርክ በሌላቸው የገጠርና ራቅ ያሉ አካባቢዎች ያለምንም ወጪ እና መቆራረጥ በመስራትም በከተማና በገጠር ትምህርት ቤቶች መካከል ያለውን ያጠባል ተብሎ ታምኖበታል።
በሙከራ ደረጃ የሚገኘው ይኸው መተግበሪያ ቀጣይ የማስፋፊያ ሥራዎቹ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በሚንቀሳቀሰው የኢትዮጵያ የትምህርት ለውጥ ኦፕሬሽን (ETOL) ፕሮጀክት ድጋፍ እየተከናወነ ይገኛል ተብሏል።
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ትምህርት ሚኒስቴር የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን የሥራ ጫና ለመቀነስ እና የትምህርትን ጥራት ለማረጋገጥ የሚያስችል “ኤጀንቲክ መምህር ረዳት” (Agentic AI Teacher Assistant) የተሰኘ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያ አበልጽጎ በሙከራ ደረጃ ስራ ላይ አውሏል።
ይህ ቴክኖሎጂ ሙሉ በሙሉ ያለኢንተርኔት የሚሰራ ሲሆን፣ በማዕከላዊ ሰርቨር ወይም በክላውድ ቴክኖሎጂ ላይ ሳይመሰረት በአካባቢያዊ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተጭኖ አገልግሎት የሚሰጥ ነው።
በተጨማሪም መተግበሪያው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን መጽሐፍት በሙሉ ዳታሴት በመውሰድና በማስተካከል የተዘጋጀ ነው።
በመተግበሪያው ምን ምን ነገሮች ማከናወን ይቻላል ?
- የትምህርት እቅድ (Lesson Plan) ማዘጋጀት፣
- ደረጃቸውን የጠበቁ የፈተና ጥያቄዎችንና አሳይመንቶችን ማመንጨት፣
- የማስተማሪያ ስልቶችን በራሱ ማቀናጀት ይችላል።
በማንኛውም ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ ኮምፒውተር ላይ ተጭኖ የሚሰራ ቀላል ሞዴልበማንኛውም ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ ኮምፒውተር ላይ ተጭኖ የሚሰራ ነውም ተብሎለታል።
በኢንተርኔት ኔትወርክ በሌላቸው የገጠርና ራቅ ያሉ አካባቢዎች ያለምንም ወጪ እና መቆራረጥ በመስራትም በከተማና በገጠር ትምህርት ቤቶች መካከል ያለውን ያጠባል ተብሎ ታምኖበታል።
በሙከራ ደረጃ የሚገኘው ይኸው መተግበሪያ ቀጣይ የማስፋፊያ ሥራዎቹ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በሚንቀሳቀሰው የኢትዮጵያ የትምህርት ለውጥ ኦፕሬሽን (ETOL) ፕሮጀክት ድጋፍ እየተከናወነ ይገኛል ተብሏል።
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣26❤15👍5👏1🤪1
ሰኔና ሰኞ‼️
“ሰኔ እና ሰኞ” ሲገጥሙ ጥፋት ይከተላል የሚለው ልማዳዊ ፍርሃት መሰረተ ቢስ መሆኑን ባለሙያዎች ገለጹ‼️
በኢትዮጵያ ማህበረሰብ ዘንድ "ሰኔ እና ሰኞ" መግጠማቸው እንደ መጥፎ ዕድል ወይም የጥፋት ምልክት ተደርጎ የመወሰድ ልማድ ለዘመናት ሲነገር ቆይቷል። ሐሳባቸውን ለመናኸሪያ ሬዲዮ የገለጹት የታሪክ ባለሙያው አቶ በላይ ስጦታው፣ ቀናቱ መግጠማቸው በራሱ የሚፈጥረው ምንም ዓይነት ለየት ያለ ጥፋት እንደሌለና ማህበረሰቡ እነዚህን መሰረተ ቢስ ልማዳዊ አመለካከቶች ሊቀይር እንደሚገባ ገልጸዋል።
በታሪክ ሂደት ውስጥ ሰኔ እና ሰኞ የገጠሙባቸው በርካታ ዓመታት ተመዝግበዋል። በእነዚህ ዓመታትም ሆኑ በሌሎች ወቅቶች በርካታ ጉዳዮችን መነሻ ያደረጉ አውዳሚ ጦርነቶችና ከዚያም የከፋ አሰቃቂ ክስተቶች መከሰታቸውን ታሪክን በማጣቀስ አብራርተዋል። ነገር ግን ክስተቶቹ በቀጥታ ሰኔ ወር ከሰኞ ከመግጠሙ ጋር ሳይሆን ልክ እንደ ሌሎች ቀናት የገጠሙ ተራ ክስተቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። የሰኔ እና ሰኞ ክስተቶች መፈጠር የሰዎች ውሳኔና የተፈጥሮ መስተጋብር ውጤቶች እንጂ ቀናትን ተከትለው የሚመጡ ባለመሆናቸው፣ ማህበረሰቡ ከሰኔ እና ሰኞ ጋር ተያይዘው የሚነገሩ ልማዳዊ ፍርሃቶችን አስቀርቶ፣ ወቅቱን ለተለያዩ ጠቃሚ ጉዳዮች ሊጠቀምበት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ሌላኛው ያነጋገራቸው የፎክሎር ባለሙያ አቶ ንጉሡ ወዳጅነህ እንደሚሉት፣ ይህ አባባል ምንም ዓይነት ሃይማኖታዊ ድጋፍም ሆነ ሳይንሳዊ ማስረጃ የሌለው መሆኑን አንስተዋል። አባባሉ በማኅበረሰቡ ዘንድ እስከ አሁን ድረስ በስፋት ጥቅም ላይ ሊውል የቻለበት በርካታ ምክንያቶች መኖራቸውን በመጠቆም፤ ለማሳያነትም ከሰኔ እና ሰኞ መገጣጠም ጋር ተያይዘው የተመዘገቡ አጋጣሚዎች ማህበረሰቡ ነገሮቹን እንዲያያይዛቸው ማድረጉን ጠቁመዋል።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ በኢትዮጵያ በረጅም ዓመታት ታሪክ ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም መጥፎ ድርጊቶች ተከትለው እንደሚመጡ በማህበረሰቡ ዘንድ ቢታመንም፤ ይህ ግን ምንም ዓይነት መሠረት የሌለው መሆኑን ባለሙያዎቹ አመላክተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
“ሰኔ እና ሰኞ” ሲገጥሙ ጥፋት ይከተላል የሚለው ልማዳዊ ፍርሃት መሰረተ ቢስ መሆኑን ባለሙያዎች ገለጹ‼️
በኢትዮጵያ ማህበረሰብ ዘንድ "ሰኔ እና ሰኞ" መግጠማቸው እንደ መጥፎ ዕድል ወይም የጥፋት ምልክት ተደርጎ የመወሰድ ልማድ ለዘመናት ሲነገር ቆይቷል። ሐሳባቸውን ለመናኸሪያ ሬዲዮ የገለጹት የታሪክ ባለሙያው አቶ በላይ ስጦታው፣ ቀናቱ መግጠማቸው በራሱ የሚፈጥረው ምንም ዓይነት ለየት ያለ ጥፋት እንደሌለና ማህበረሰቡ እነዚህን መሰረተ ቢስ ልማዳዊ አመለካከቶች ሊቀይር እንደሚገባ ገልጸዋል።
በታሪክ ሂደት ውስጥ ሰኔ እና ሰኞ የገጠሙባቸው በርካታ ዓመታት ተመዝግበዋል። በእነዚህ ዓመታትም ሆኑ በሌሎች ወቅቶች በርካታ ጉዳዮችን መነሻ ያደረጉ አውዳሚ ጦርነቶችና ከዚያም የከፋ አሰቃቂ ክስተቶች መከሰታቸውን ታሪክን በማጣቀስ አብራርተዋል። ነገር ግን ክስተቶቹ በቀጥታ ሰኔ ወር ከሰኞ ከመግጠሙ ጋር ሳይሆን ልክ እንደ ሌሎች ቀናት የገጠሙ ተራ ክስተቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። የሰኔ እና ሰኞ ክስተቶች መፈጠር የሰዎች ውሳኔና የተፈጥሮ መስተጋብር ውጤቶች እንጂ ቀናትን ተከትለው የሚመጡ ባለመሆናቸው፣ ማህበረሰቡ ከሰኔ እና ሰኞ ጋር ተያይዘው የሚነገሩ ልማዳዊ ፍርሃቶችን አስቀርቶ፣ ወቅቱን ለተለያዩ ጠቃሚ ጉዳዮች ሊጠቀምበት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ሌላኛው ያነጋገራቸው የፎክሎር ባለሙያ አቶ ንጉሡ ወዳጅነህ እንደሚሉት፣ ይህ አባባል ምንም ዓይነት ሃይማኖታዊ ድጋፍም ሆነ ሳይንሳዊ ማስረጃ የሌለው መሆኑን አንስተዋል። አባባሉ በማኅበረሰቡ ዘንድ እስከ አሁን ድረስ በስፋት ጥቅም ላይ ሊውል የቻለበት በርካታ ምክንያቶች መኖራቸውን በመጠቆም፤ ለማሳያነትም ከሰኔ እና ሰኞ መገጣጠም ጋር ተያይዘው የተመዘገቡ አጋጣሚዎች ማህበረሰቡ ነገሮቹን እንዲያያይዛቸው ማድረጉን ጠቁመዋል።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ በኢትዮጵያ በረጅም ዓመታት ታሪክ ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም መጥፎ ድርጊቶች ተከትለው እንደሚመጡ በማህበረሰቡ ዘንድ ቢታመንም፤ ይህ ግን ምንም ዓይነት መሠረት የሌለው መሆኑን ባለሙያዎቹ አመላክተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍14❤12😁5🤪3🤯2😡2👏1👌1🤡1
ኤርትራ ስለ ፅምዶ ደብዳቤ ፃፈች‼️
ኤርትራ 'ፅምዶ በህዝቡ የመጣ እንጂ በመሪዎች አይደለም' የሚል ይዘት ያለው ደብዳቤ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ላከች።
ኤርትራ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ (ዩኤንኤስጂ) የላከችው ደብዳቤ ምስጋና በማቅረብ የጀመረ ሲሆን ከፌዴራል መንግሥቱ እውቅና ውጪ በኤርትራ እና ትግራይ "በማህበረሰብ ላይ የተመሰረተ ከአንድ አመት በላይ ተከታታይ የህዝብ ለህዝብ ውይይት፣ የማህበረሰብ ውይይቶች፣ የባህል ልውውጦች እና በራስ መተማመንን የሚያጎለብቱ ተግባራት “ጽምዶ ንሰላም"(መተሳሰብ ለሰላም) በሚል ሀገር በቀል መሪ ቃል መጀመሩን ገልጿል።
ይህ ህዝባዊ ዘመቻ እምነትን መልሶ ለመገንባት፣ ማህበራዊ ትስስርን ወደነበረበት ለመመለስ እና በአመታት ግጭት እና መለያየት ህይወታቸው በእጅጉ የተጎዳ ማህበረሰቦችን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው ብሏል።
የፅምዶ ጠቀሜታ በእንቅስቃሴው ላይ ብቻ ሳይሆን በኦርጋኒክ እና በአካባቢው ባለቤትነት ላይ ነው፣በእራሳቸው የማህበረሰቡ አባላት የሚመራ፣ በዋናነት በጋራ ድንበሮች የሚኖሩ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች እና ቤተሰቦች፣ በውይይት እና ቀጥተኛ ሰብዓዊ ተሳትፎ መግባባትን፣ ፈውስ እና አብሮ መኖርን ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነትን ያሳያል።
በባህላዊ እሴቶች፣ በመከባበር እና በጋራ ኃላፊነት በተመሰረቱ ተግባራዊ ተግባራት እርቅን እንዴት ማሳደግ እንደሚቻል ያሳያል።
ውጥኑ የተባበሩት መንግስታት ሰላምን ለማስቀጠል እና ህዝብን ያማከለ የሰላም ግንባታን የሚደግፉ መርሆዎች ትርጉም ያለው ምሳሌ ይሰጣል።
ለዚህ ማሳያ ይሆናል የተባለ ተጓዳኝ ቪዲዮ ከደብዳቤው ጋር አብሮ መላኩን በደብዳቤው ላይ ተጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኤርትራ 'ፅምዶ በህዝቡ የመጣ እንጂ በመሪዎች አይደለም' የሚል ይዘት ያለው ደብዳቤ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ላከች።
ኤርትራ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ (ዩኤንኤስጂ) የላከችው ደብዳቤ ምስጋና በማቅረብ የጀመረ ሲሆን ከፌዴራል መንግሥቱ እውቅና ውጪ በኤርትራ እና ትግራይ "በማህበረሰብ ላይ የተመሰረተ ከአንድ አመት በላይ ተከታታይ የህዝብ ለህዝብ ውይይት፣ የማህበረሰብ ውይይቶች፣ የባህል ልውውጦች እና በራስ መተማመንን የሚያጎለብቱ ተግባራት “ጽምዶ ንሰላም"(መተሳሰብ ለሰላም) በሚል ሀገር በቀል መሪ ቃል መጀመሩን ገልጿል።
ይህ ህዝባዊ ዘመቻ እምነትን መልሶ ለመገንባት፣ ማህበራዊ ትስስርን ወደነበረበት ለመመለስ እና በአመታት ግጭት እና መለያየት ህይወታቸው በእጅጉ የተጎዳ ማህበረሰቦችን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው ብሏል።
የፅምዶ ጠቀሜታ በእንቅስቃሴው ላይ ብቻ ሳይሆን በኦርጋኒክ እና በአካባቢው ባለቤትነት ላይ ነው፣በእራሳቸው የማህበረሰቡ አባላት የሚመራ፣ በዋናነት በጋራ ድንበሮች የሚኖሩ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች እና ቤተሰቦች፣ በውይይት እና ቀጥተኛ ሰብዓዊ ተሳትፎ መግባባትን፣ ፈውስ እና አብሮ መኖርን ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነትን ያሳያል።
በባህላዊ እሴቶች፣ በመከባበር እና በጋራ ኃላፊነት በተመሰረቱ ተግባራዊ ተግባራት እርቅን እንዴት ማሳደግ እንደሚቻል ያሳያል።
ውጥኑ የተባበሩት መንግስታት ሰላምን ለማስቀጠል እና ህዝብን ያማከለ የሰላም ግንባታን የሚደግፉ መርሆዎች ትርጉም ያለው ምሳሌ ይሰጣል።
ለዚህ ማሳያ ይሆናል የተባለ ተጓዳኝ ቪዲዮ ከደብዳቤው ጋር አብሮ መላኩን በደብዳቤው ላይ ተጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14🤪14👍8🥰3😎1