ሕወሃት አዲስ አውዳሚ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበ።
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20🤪11😡9👍4😁2🥰1👏1🕊1
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ስርጭት
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል።
እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል።
የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።
በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴሊሺየስ በላይ ይሆናል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል።
እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል።
የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።
በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴሊሺየስ በላይ ይሆናል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍3
አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Photo
ኤርትራ ተመረጠች‼️
ኤርትራ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆና ተመረጠች።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በ85ኛው መደበኛ ስብሰባው ላይ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ ቁልፍ አጀንዳዎችን የተወያየ ሲሆን፣ በስብሰባውም ለድርጅቱ 81ኛ ጠቅላላ ጉባኤ መሪ የሚሆኑትን አካላት መርጧል።
በዚህም መሰረት የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኤርትራ የከፍተኛ አባል ሀገራትን ድምጽ በማግኘት ከጠቅላላ ጉባኤው ምክትል ፕሬዝዳንቶች አንዷ ሆናለች።
ኤርትራ ከተመረጡ ሌሎች 16 አገራት ጋር በመሆን የጸጥታው ምክር ቤት አምስት ቋሚ አባላትን (ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ሩሲያ፣ ብሪታንያ እና አሜሪካ) በመቀላቀል የጠቅላላ ጉባኤውን ቢሮ በጋራ ትመራለች።
በተጨማሪም ከእሷ ጋር እንደ አፍጋኒስታን፣ ፊንላንድ፣ ግብፅ፣ ሊባኖስ፣ ፓራጓይ እና ዚምባብዌ ያሉ ሀገራትም በምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጣቸውን ለመረዳት ተችሏል።
በተመሳሳይ ዕለት በምስጢር በተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት፣ የወቅቱ የባንግላዲሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካሊሉር ራህማን የ81ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል
ሚስተር ራህማን 99 ድምጽ በማግኘት የተመረጡ ሲሆን፣ ተፎካካሪያቸውን የቆጵሮሱን አንድሪያስ ካኩሪስን በ91 ድምጽ አሸንፈዋል። በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ሥራቸውን በይፋ የሚረከቡት ተመራጩ ፕሬዝዳንት ካሊሉር ራህማን ከአሸናፊነታቸው በኋላ ባደረጉት ንግግር፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሁኑ ወቅት ከባድ የፋይናንስ ቀውስ እና ዓለም አቀፍ የእምነት ማጣት ጉድለት እየገጠመው መሆኑን ጠቅሰው፣ አባል ሀገራቱ ድርጅቱ መለወጥና የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በተግባር ማሳየት እንዳለባቸውና በየብስ የሚደረገውን እያንዳንዱን አስተዋጽኦ ውጤታማ በማድረግ የጠፋውን እምነት መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል።
Via capital
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኤርትራ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆና ተመረጠች።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በ85ኛው መደበኛ ስብሰባው ላይ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ ቁልፍ አጀንዳዎችን የተወያየ ሲሆን፣ በስብሰባውም ለድርጅቱ 81ኛ ጠቅላላ ጉባኤ መሪ የሚሆኑትን አካላት መርጧል።
በዚህም መሰረት የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኤርትራ የከፍተኛ አባል ሀገራትን ድምጽ በማግኘት ከጠቅላላ ጉባኤው ምክትል ፕሬዝዳንቶች አንዷ ሆናለች።
ኤርትራ ከተመረጡ ሌሎች 16 አገራት ጋር በመሆን የጸጥታው ምክር ቤት አምስት ቋሚ አባላትን (ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ሩሲያ፣ ብሪታንያ እና አሜሪካ) በመቀላቀል የጠቅላላ ጉባኤውን ቢሮ በጋራ ትመራለች።
በተጨማሪም ከእሷ ጋር እንደ አፍጋኒስታን፣ ፊንላንድ፣ ግብፅ፣ ሊባኖስ፣ ፓራጓይ እና ዚምባብዌ ያሉ ሀገራትም በምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጣቸውን ለመረዳት ተችሏል።
በተመሳሳይ ዕለት በምስጢር በተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት፣ የወቅቱ የባንግላዲሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካሊሉር ራህማን የ81ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል
ሚስተር ራህማን 99 ድምጽ በማግኘት የተመረጡ ሲሆን፣ ተፎካካሪያቸውን የቆጵሮሱን አንድሪያስ ካኩሪስን በ91 ድምጽ አሸንፈዋል። በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ሥራቸውን በይፋ የሚረከቡት ተመራጩ ፕሬዝዳንት ካሊሉር ራህማን ከአሸናፊነታቸው በኋላ ባደረጉት ንግግር፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሁኑ ወቅት ከባድ የፋይናንስ ቀውስ እና ዓለም አቀፍ የእምነት ማጣት ጉድለት እየገጠመው መሆኑን ጠቅሰው፣ አባል ሀገራቱ ድርጅቱ መለወጥና የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በተግባር ማሳየት እንዳለባቸውና በየብስ የሚደረገውን እያንዳንዱን አስተዋጽኦ ውጤታማ በማድረግ የጠፋውን እምነት መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል።
Via capital
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤔25❤16👍5
"የአርሲው ጥቃት በሸኔ ታጣቂዎች የተፈጸመ ነው"፦ አቶ ሀይሉ አዱኛ
"የአርሲው ጥቃት ምርጫውን ለማደናቀፍ በሸኔ ታጣቂዎች የተፈጸመ ነው" የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ።
በጥቃቱ ከዚህም በላይ ጉዳት እንዳይደርስ ህዝቡና የኦሮሚያ ክልል የፀጥታ ሀይል መስዋዕትነት ከፍሏል ብለዋል። አሸባሪው ሸኔ ይህንን ጥቃት ያደረሰው ከታሪካዊ ጠላቶች ተልዕኮ ተቀብሎ የሀይማኖት ግጭት ለማስነሳት የነበረ ቢሆንም በህዝቡ አስተዋይነት ከሽፏል ብለዋል።
መከላከያ ሰራዊት፣የፌዴራል ፖሊስ የኦሮሚያ ክልል የፀጥታ ሀይል የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ እና አካባቢውን ለማረጋጋት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
"የአርሲው ጥቃት ምርጫውን ለማደናቀፍ በሸኔ ታጣቂዎች የተፈጸመ ነው" የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ።
በጥቃቱ ከዚህም በላይ ጉዳት እንዳይደርስ ህዝቡና የኦሮሚያ ክልል የፀጥታ ሀይል መስዋዕትነት ከፍሏል ብለዋል። አሸባሪው ሸኔ ይህንን ጥቃት ያደረሰው ከታሪካዊ ጠላቶች ተልዕኮ ተቀብሎ የሀይማኖት ግጭት ለማስነሳት የነበረ ቢሆንም በህዝቡ አስተዋይነት ከሽፏል ብለዋል።
መከላከያ ሰራዊት፣የፌዴራል ፖሊስ የኦሮሚያ ክልል የፀጥታ ሀይል የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ እና አካባቢውን ለማረጋጋት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪51❤14💔11😡7😢4👍2🙏2🤣2😁1🤯1
ነዳጅ በሁለት ዶላር ቀነሰ።
የነዳጅ ዋጋ በአለማቀፍ ደረጃ መጠነኛ ቅናሽ አሳየ።
የዋጋ ቅናሽ የተስተዋለው እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው።
አንድ ብሬንት ነዳጅ በርሚል 67 ሳንቲም ወይም 0.69 % ቅናሽ አሳይቷል ተብሏል።
በ97.14 ዶላር ሲሸጥ የነበረው አንድ በርሚል ነዳጅ ወደ 95.40 ዝቅ ማለቱ ተመላክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የነዳጅ ዋጋ በአለማቀፍ ደረጃ መጠነኛ ቅናሽ አሳየ።
የዋጋ ቅናሽ የተስተዋለው እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው።
አንድ ብሬንት ነዳጅ በርሚል 67 ሳንቲም ወይም 0.69 % ቅናሽ አሳይቷል ተብሏል።
በ97.14 ዶላር ሲሸጥ የነበረው አንድ በርሚል ነዳጅ ወደ 95.40 ዝቅ ማለቱ ተመላክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10👍3
የቻይናው ኩባንያ የአዲስአበባ አውቶቡሶችን ወደ ተፈጥሮ ጋዝ ተሽከርካሪዎች የመቀየር ሥራ ጀመረ
ኢትዮጵያ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችን ከናፍጣ ወደ ተፈጥሮ ጋዝ ለመቀየር የሚያስችል መጠነ ሰፊ ፕሮግራም የጀመረች ሲሆን፥ በቻይናው ኩባንያ የመጀመሪያው ማሻሻያ የተደረገለት አውቶቡስ በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ፍተሻውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን ቻይና ዴይሊ ዘግቧል።
በቻይናው ጂሲኤል አፍሪካ ኢንዱስትሪያል ግሩፕ የሚመራው ይህ መርሃ ግብር፥ ኢትዮጵያ ከውጭ በሚገባ ነዳጅ ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ እና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆነ የሕዝብ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የምታደርገው ሰፊ ጥረት አካል ነው ተብሏል።
ቻይና ዴይሊ እንደዘገበው፤ ፕሮጀክቱ፤ በአዲስ አበባ አገልግሎት የሚሰጡ ከ2,000 በላይ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችን በስምንት ወራት ውስጥ ለመቀየር ያለመ ነው።
በተጨማሪም የመንግሥት ንብረት የሆኑ የመርሴዲስ ቤንዝ አውቶቡሶችን ለመቀየር ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኢትዮጵያ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችን ከናፍጣ ወደ ተፈጥሮ ጋዝ ለመቀየር የሚያስችል መጠነ ሰፊ ፕሮግራም የጀመረች ሲሆን፥ በቻይናው ኩባንያ የመጀመሪያው ማሻሻያ የተደረገለት አውቶቡስ በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ፍተሻውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን ቻይና ዴይሊ ዘግቧል።
በቻይናው ጂሲኤል አፍሪካ ኢንዱስትሪያል ግሩፕ የሚመራው ይህ መርሃ ግብር፥ ኢትዮጵያ ከውጭ በሚገባ ነዳጅ ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ እና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆነ የሕዝብ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የምታደርገው ሰፊ ጥረት አካል ነው ተብሏል።
ቻይና ዴይሊ እንደዘገበው፤ ፕሮጀክቱ፤ በአዲስ አበባ አገልግሎት የሚሰጡ ከ2,000 በላይ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችን በስምንት ወራት ውስጥ ለመቀየር ያለመ ነው።
በተጨማሪም የመንግሥት ንብረት የሆኑ የመርሴዲስ ቤንዝ አውቶቡሶችን ለመቀየር ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤23👍10
እዳ ባለመከፈሉ ኢትዮጵያ ልትከሰስ❓‼️
#የኢትዮጵያ #ዩሮቦንድ አበዳሪዎች ያልተከፈለ ዕዳን በተመለከተ መንግሥትን ለመክሰስ የሕግ ሂደት መጀመራቸው ተዘገበ‼️
የኢትዮጵያ የዩሮቦንድ አበዳሪዎች ቡድን፣ መንግሥት ያልከፈለውን የ1 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ በተመለከተ ክስ ለመመሥረት የሚያስችላቸውን የሕግ ሂደት በይፋ መጀመራቸው ተዘገበ።
ብሉምበርግ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ምንጮች ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፤ የኢትዮጵያ ‘አድ ሆክ’ የቦንድ ባለቤቶች ኮሚቴ (Ethiopia Ad Hoc Bondholder Committee) አባላት፣ በእንግሊዝ ፍርድ ቤቶች ክስ ለመመሥረት ማቀዳቸውን የሚገልጽ የቅድመ-ክስ ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ባለፈው ሳምንት ለኢትዮጵያ መንግሥት ልከዋል።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት የመረጃው ምንጮች እንዳሉት፣ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰው ለማሳወቅ 14 ቀናት አሉት ያሉ ሲሆን፣ ሆኖም የጊዜ ገደቡ መቼ እንደሚጀምር በዝርዝር አላብራሩም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
#የኢትዮጵያ #ዩሮቦንድ አበዳሪዎች ያልተከፈለ ዕዳን በተመለከተ መንግሥትን ለመክሰስ የሕግ ሂደት መጀመራቸው ተዘገበ‼️
የኢትዮጵያ የዩሮቦንድ አበዳሪዎች ቡድን፣ መንግሥት ያልከፈለውን የ1 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ በተመለከተ ክስ ለመመሥረት የሚያስችላቸውን የሕግ ሂደት በይፋ መጀመራቸው ተዘገበ።
ብሉምበርግ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ምንጮች ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፤ የኢትዮጵያ ‘አድ ሆክ’ የቦንድ ባለቤቶች ኮሚቴ (Ethiopia Ad Hoc Bondholder Committee) አባላት፣ በእንግሊዝ ፍርድ ቤቶች ክስ ለመመሥረት ማቀዳቸውን የሚገልጽ የቅድመ-ክስ ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ባለፈው ሳምንት ለኢትዮጵያ መንግሥት ልከዋል።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት የመረጃው ምንጮች እንዳሉት፣ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰው ለማሳወቅ 14 ቀናት አሉት ያሉ ሲሆን፣ ሆኖም የጊዜ ገደቡ መቼ እንደሚጀምር በዝርዝር አላብራሩም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣14❤9👍7😢4🎉1
ችሎት ውስጥ የተፈፀመ አሰቃቂ ግድያ‼
ዛሬ ረፋድ ላይ በሆለታ ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት፣ የዕለቱን የችሎት ውሳኔ በማንበብ ላይ የነበሩ ዳኛ እና አንዲት ተከራካሪ ህይወታቸው ማለፉን አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ - ኢትዮጵያ አስታውቋል።
እንደ ምንጩ መረጃ፣ የቤተሰብ ክርክር ጉዳይን በመመልከት ላይ የነበሩት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ የፍርድ ውሳኔውን እያነበቡ ባሉበት ወቅት፣ ተከሳሹ በድንገት ባወጣው ሽጉጥ ዳኛዋን በጥይት በመምታት ህይወታቸውን ቀጥፏል።
በዚሁ አጋጣሚ በችሎቱ ላይ በጉዳዩ ላይ ይከራከሩ የነበሩት (ተከራካሪዋ) በተመሳሳይ ሁኔታ በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።
የሕግ ባለሙያዎችና ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን በጽኑ ያኮነኑ ሲሆን፤ ዳኞችና የሕግ ባለሙያዎች በሥራ ገበታቸው ላይ አስተማማኝ የደህንነት ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ በርካቶች በመጻፍ ላይ ይገኛሉ።
“አንድ ግለሰብ ታጥቆ ወደ ፍርድ ቤት አዳራሽ መግባት መቻሉ፣ የፍርድ ቤቶችን የጸጥታና የፍተሻ አሰራር ምን ያህል ደካማ እንደሆነ በአሳዛኝ ሁኔታ አሳይቷል” በማለት አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ የድርጊቱን አሳሳቢነት ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዛሬ ረፋድ ላይ በሆለታ ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት፣ የዕለቱን የችሎት ውሳኔ በማንበብ ላይ የነበሩ ዳኛ እና አንዲት ተከራካሪ ህይወታቸው ማለፉን አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ - ኢትዮጵያ አስታውቋል።
እንደ ምንጩ መረጃ፣ የቤተሰብ ክርክር ጉዳይን በመመልከት ላይ የነበሩት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ የፍርድ ውሳኔውን እያነበቡ ባሉበት ወቅት፣ ተከሳሹ በድንገት ባወጣው ሽጉጥ ዳኛዋን በጥይት በመምታት ህይወታቸውን ቀጥፏል።
በዚሁ አጋጣሚ በችሎቱ ላይ በጉዳዩ ላይ ይከራከሩ የነበሩት (ተከራካሪዋ) በተመሳሳይ ሁኔታ በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።
የሕግ ባለሙያዎችና ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን በጽኑ ያኮነኑ ሲሆን፤ ዳኞችና የሕግ ባለሙያዎች በሥራ ገበታቸው ላይ አስተማማኝ የደህንነት ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ በርካቶች በመጻፍ ላይ ይገኛሉ።
“አንድ ግለሰብ ታጥቆ ወደ ፍርድ ቤት አዳራሽ መግባት መቻሉ፣ የፍርድ ቤቶችን የጸጥታና የፍተሻ አሰራር ምን ያህል ደካማ እንደሆነ በአሳዛኝ ሁኔታ አሳይቷል” በማለት አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ የድርጊቱን አሳሳቢነት ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢30❤18👍4😡2
ወደኋላ አስር አመት‼️
ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀረበ፡፡
ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡
ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡
ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ እና ሆን ብሎ ድርጊቱን መፈፀሙን ከቀጠለ ድርጊቱ እንደ ወንጀል ጥፋት ተቀጥሮ በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በተጠቀሰው ድርጊት የድርጅት ስራ አስኪያጅ በግል በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው በወንጀሉ ተግባር ተባባሪ ከሆነ ወይንም ደረሰኝ ያለመስጠትን መከላከል የሚያስችል የቁጥጥር ሥርዓት ያልዘረጋ ከሆነ እንዲሆንም ተደንግጓል፡፡
በሌላ በኩል አንድ ግብር ከፋይ ግብር ከከፈለ በኋላ በ10 አመት ጊዜ ውስጥ በማንኛው ጊዜ እንደገና ሂሳቡ ተመርምሮ ወይም በኦዲት ተጨማሪ ግብር ሊጠየቅ ይችላል ይላል የረቂቅ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
ይህም በ10 ዓመት የተገደበው በኢትዮጵያ የንግድ ህግና የሂሳብ አያያዝ ህጎች መሰረት የሂሳብ ሰነዶች ተጠብቀው መቆየት ያለባቸው ለ10 ዓመታት ብቻ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡
ሌላው የታክስ አስተዳደር አዋጁ ማሻሻያ የያዘው አዲስ ነገር በታክስ ባለስልጣኑ እና በታክስ ከፋዩ መካከል የሚፈጠርን አለመግባባት መፍቻ ዘዴን ይመለከታል፡፡
ከዚህ ቀደም በነበረው ህግ ግብር ከፋዮች የተጣለባቸውን ግብር ተገቢ አይደለም ብለው ባመኑ ጊዜ መፍትሄ ፍለጋ በታክስ አስተዳደሩ ስር ለተቋቋመ የቅሬታ ሰሚ ፣ ለግብር ይግባኝ ኮሚሽን እና የህግ ትርጉምን በተመለከተ በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች እንዲመለከቱት የሚያስችል ስርዓት ነበር፡፡
ይህን ለማድረግ ግን ግብር ከፋዮች ቅድሚያ የተወሰነባቸውን ግብር ከ50 እስከ 75 በመቶ መክፈልም ይጠበቅባቸው ነበር፡፡
ያም ሆኖ መፍትሄ ለማግኘት ረዥም ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል በማብራሪያው ተጠቅሷል፡፡
በተሻሻለውና በረቂቅ ደረጃ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የታክስ አስተዳደር አዋጅ የተጠቀሰው አሰራር እንዳለ ሆኖ በአጭር ጊዜ አለመግባባቶችን ለመፍታት ያግዛል የተባለ የገለልተኛ አስማሚን አሰራር ስራ ላይ ያውላል ተብለዋል፡፡
ይህም አዲስ “የመስማማት ሥርዓት” በሚል አዋጁ እንዲዘረጋ በሚፈቅደው ገለልተኛ አስማሚ ግብር ከፋዩን እና ግብር ሰብሳቢውን በሚስጥራዊነት መርህዎች ጭምር የሚያስማማበት ሥርዓት ነው ተብሏል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀረበ፡፡
ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡
ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡
ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ እና ሆን ብሎ ድርጊቱን መፈፀሙን ከቀጠለ ድርጊቱ እንደ ወንጀል ጥፋት ተቀጥሮ በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በተጠቀሰው ድርጊት የድርጅት ስራ አስኪያጅ በግል በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው በወንጀሉ ተግባር ተባባሪ ከሆነ ወይንም ደረሰኝ ያለመስጠትን መከላከል የሚያስችል የቁጥጥር ሥርዓት ያልዘረጋ ከሆነ እንዲሆንም ተደንግጓል፡፡
በሌላ በኩል አንድ ግብር ከፋይ ግብር ከከፈለ በኋላ በ10 አመት ጊዜ ውስጥ በማንኛው ጊዜ እንደገና ሂሳቡ ተመርምሮ ወይም በኦዲት ተጨማሪ ግብር ሊጠየቅ ይችላል ይላል የረቂቅ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
ይህም በ10 ዓመት የተገደበው በኢትዮጵያ የንግድ ህግና የሂሳብ አያያዝ ህጎች መሰረት የሂሳብ ሰነዶች ተጠብቀው መቆየት ያለባቸው ለ10 ዓመታት ብቻ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡
ሌላው የታክስ አስተዳደር አዋጁ ማሻሻያ የያዘው አዲስ ነገር በታክስ ባለስልጣኑ እና በታክስ ከፋዩ መካከል የሚፈጠርን አለመግባባት መፍቻ ዘዴን ይመለከታል፡፡
ከዚህ ቀደም በነበረው ህግ ግብር ከፋዮች የተጣለባቸውን ግብር ተገቢ አይደለም ብለው ባመኑ ጊዜ መፍትሄ ፍለጋ በታክስ አስተዳደሩ ስር ለተቋቋመ የቅሬታ ሰሚ ፣ ለግብር ይግባኝ ኮሚሽን እና የህግ ትርጉምን በተመለከተ በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች እንዲመለከቱት የሚያስችል ስርዓት ነበር፡፡
ይህን ለማድረግ ግን ግብር ከፋዮች ቅድሚያ የተወሰነባቸውን ግብር ከ50 እስከ 75 በመቶ መክፈልም ይጠበቅባቸው ነበር፡፡
ያም ሆኖ መፍትሄ ለማግኘት ረዥም ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል በማብራሪያው ተጠቅሷል፡፡
በተሻሻለውና በረቂቅ ደረጃ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የታክስ አስተዳደር አዋጅ የተጠቀሰው አሰራር እንዳለ ሆኖ በአጭር ጊዜ አለመግባባቶችን ለመፍታት ያግዛል የተባለ የገለልተኛ አስማሚን አሰራር ስራ ላይ ያውላል ተብለዋል፡፡
ይህም አዲስ “የመስማማት ሥርዓት” በሚል አዋጁ እንዲዘረጋ በሚፈቅደው ገለልተኛ አስማሚ ግብር ከፋዩን እና ግብር ሰብሳቢውን በሚስጥራዊነት መርህዎች ጭምር የሚያስማማበት ሥርዓት ነው ተብሏል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15😢15🤷♂4👍3👀2😁1🤯1
#ስዕላዊመረጃ በአርሲ፣ አሰኮ ወረዳ ከሰሞኑ በደረሰው ጥቃት ዙርያ መሠረት ሚድያ ከመንግስት ምንጮች እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ያሰባሰበው አዲስ መረጃ!
ህይወታቸው እንዳለፈ የተረጋገጠ= 53
ያሉበት ያልታወቀ ሰዎች= 190
የቆሰሉ= 47
የታገቱና ገንዘብ የተጠየቀባቸው= 6
የተቃጠለ ቤት= 308
የተቃጠለ ቤተክርስቲያን= 2
ተፈናቅለው እሬቻ ማካኤል የተጠለሉ= 789
ተፈናቅለው ሱንቴ ማርያም የተጠለሉ= 691
ተፈናቅለው አሰኮ ከተማ የተቀመጡ= 262
ተፈናቅለው ሌንጫ ኦዳ፣ ወራንቡስ፣ ቦግዶ፣ ኮበሬ የተጠለሉ= 133
ጠቅላላ የተፈናቀሉ= 1,875
*የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ ለሚድያችን እንደተናገሩት ተኩሱ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ቆሟል፣ ነገር ግን የተፈናቀለው ህዝብ ወደ ቀዬው መመለስ አልቻለም።
ምንጭ :- | መሠረት ሚድያ |
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ህይወታቸው እንዳለፈ የተረጋገጠ= 53
ያሉበት ያልታወቀ ሰዎች= 190
የቆሰሉ= 47
የታገቱና ገንዘብ የተጠየቀባቸው= 6
የተቃጠለ ቤት= 308
የተቃጠለ ቤተክርስቲያን= 2
ተፈናቅለው እሬቻ ማካኤል የተጠለሉ= 789
ተፈናቅለው ሱንቴ ማርያም የተጠለሉ= 691
ተፈናቅለው አሰኮ ከተማ የተቀመጡ= 262
ተፈናቅለው ሌንጫ ኦዳ፣ ወራንቡስ፣ ቦግዶ፣ ኮበሬ የተጠለሉ= 133
ጠቅላላ የተፈናቀሉ= 1,875
*የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ ለሚድያችን እንደተናገሩት ተኩሱ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ቆሟል፣ ነገር ግን የተፈናቀለው ህዝብ ወደ ቀዬው መመለስ አልቻለም።
ምንጭ :- | መሠረት ሚድያ |
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢41💔17❤12👍3🕊2🤯1😱1🎉1🙉1
የዓለም የፕሬስ ነፃነት ታይቶ
በማይታወቅ ሁኔታ አሽቆልቁሏል
የድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ድርጅት (RSF) ባወጣው የ25ኛ ዓመት ዓለም አቀፍ መግለጫ መሠረት፣ በዓለም ዙሪያ የሚዲያ ነፃነት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ማሽቆልቆሉንና ጋዜጠኝነትን ወደ ወንጀል የመቀየር ሂደት መባባሱን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት አምባገነን መንግሥታት የሚዲያ ነፃነትን ለማፈን የብሔራዊ ደኅንነት ሕግጋትን እንደ መሣሪያ እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ድርጅቱ የገለጸ ሲሆን፣ ኖርዌይ ለ10ኛ ተከታታይ ዓመት 1ኛ ደረጃን በመያዝ የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስፈን ግንባር ቀደምነቷን አስመስክራለች። በአንጻሩ አሜሪካ በሚዲያ ላይ በሚሰነዘሩ የፖለቲካ ጥቃቶች ምክንያት በ7 ደረጃዎች በማሽቆልቆል 64ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በዚሁ ዓለም አቀፍ የደረጃ ሰንጠረዥ መሠረት ኢትዮጵያ ከ180 የዓለም ሀገራት መካከል 148ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፤ ለዚህም በሀገሪቱ አራት ጋዜጠኞች ከፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ ጋር በተያያዘ ክስ ለሦስት ዓመታት ታስረው መቆየታቸው በሕጋዊ መመዘኛ ዝቅተኛ ውጤት እንድታገኝ ማድረጉ ተገልጿል። ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሱዳን 161ኛ ደረጃን ስትይዝ፣ ኤርትራ ደግሞ 180ኛ በመሆን ከዓለም የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በማይታወቅ ሁኔታ አሽቆልቁሏል
የድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ድርጅት (RSF) ባወጣው የ25ኛ ዓመት ዓለም አቀፍ መግለጫ መሠረት፣ በዓለም ዙሪያ የሚዲያ ነፃነት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ማሽቆልቆሉንና ጋዜጠኝነትን ወደ ወንጀል የመቀየር ሂደት መባባሱን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት አምባገነን መንግሥታት የሚዲያ ነፃነትን ለማፈን የብሔራዊ ደኅንነት ሕግጋትን እንደ መሣሪያ እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ድርጅቱ የገለጸ ሲሆን፣ ኖርዌይ ለ10ኛ ተከታታይ ዓመት 1ኛ ደረጃን በመያዝ የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስፈን ግንባር ቀደምነቷን አስመስክራለች። በአንጻሩ አሜሪካ በሚዲያ ላይ በሚሰነዘሩ የፖለቲካ ጥቃቶች ምክንያት በ7 ደረጃዎች በማሽቆልቆል 64ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በዚሁ ዓለም አቀፍ የደረጃ ሰንጠረዥ መሠረት ኢትዮጵያ ከ180 የዓለም ሀገራት መካከል 148ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፤ ለዚህም በሀገሪቱ አራት ጋዜጠኞች ከፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ ጋር በተያያዘ ክስ ለሦስት ዓመታት ታስረው መቆየታቸው በሕጋዊ መመዘኛ ዝቅተኛ ውጤት እንድታገኝ ማድረጉ ተገልጿል። ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሱዳን 161ኛ ደረጃን ስትይዝ፣ ኤርትራ ደግሞ 180ኛ በመሆን ከዓለም የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍3
🚨 የአያቶላ አሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ከ4 ወራት በኋላ በሰኔ ወር ሊፈጸም ነው!
በመካከለኛው ምስራቅ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና እጅግ ግዙፍ የተባለለት የሽኝት ፕሮግራም ይፋ ሆኗል። ባለፈው የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም (የካቲት 28, 2026) በቴህራን በሚገኘው መኖሪያና ቢሯቸው ላይ በተሰነዘረ የጋራ የአሜሪካ እና የእስራኤል የአየር ጥቃት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተገደሉት የ86 ዓመቱ የኢራን የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ፣ ከናፈቁት የመጨረሻ ምኞታቸው ጋር በተያያዘ በማሽሃድ በሚገኘው ታዋቂው የኢማም ረዛ መቅደስ አጠገብ ሊቀበሩ መሆኑ ተረጋግጧል።
የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ጦር (IRGC) እንዳስታወቀው ታላቁ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በሰኔ 14 ቀን (June 21) አካባቢ የሚጀምር ሲሆን ለሦስት ቀናት የሚቆይና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢራናውያን የሚሳተፉበት አገር አቀፍ የሽኝት ሰልፍ በቴህራን፣ በቆም እና በማሽሃድ ከተሞች ላይ ይካሄዳል ተብሏል።
የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንደገለጹት በዚህ ታሪካዊ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ከ20 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ሊታደም ይችላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም በሰው ልጅ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ህዝባዊ ስብስብ ያደርገዋል። ይህ አስገራሚ የህዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ በ1989 የተከናወነውን እና 10 ሚሊዮን ህዝብ የተገኘበትን የቀድሞውን መሪ የአያቶላ ሩሆላ ኾሜኒን የቀብር ሥነ-ሥርዓት በእጅጉ የሚበልጥ እንደሚሆን ተነግሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በመካከለኛው ምስራቅ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና እጅግ ግዙፍ የተባለለት የሽኝት ፕሮግራም ይፋ ሆኗል። ባለፈው የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም (የካቲት 28, 2026) በቴህራን በሚገኘው መኖሪያና ቢሯቸው ላይ በተሰነዘረ የጋራ የአሜሪካ እና የእስራኤል የአየር ጥቃት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተገደሉት የ86 ዓመቱ የኢራን የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ፣ ከናፈቁት የመጨረሻ ምኞታቸው ጋር በተያያዘ በማሽሃድ በሚገኘው ታዋቂው የኢማም ረዛ መቅደስ አጠገብ ሊቀበሩ መሆኑ ተረጋግጧል።
የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ጦር (IRGC) እንዳስታወቀው ታላቁ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በሰኔ 14 ቀን (June 21) አካባቢ የሚጀምር ሲሆን ለሦስት ቀናት የሚቆይና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢራናውያን የሚሳተፉበት አገር አቀፍ የሽኝት ሰልፍ በቴህራን፣ በቆም እና በማሽሃድ ከተሞች ላይ ይካሄዳል ተብሏል።
የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንደገለጹት በዚህ ታሪካዊ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ከ20 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ሊታደም ይችላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም በሰው ልጅ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ህዝባዊ ስብስብ ያደርገዋል። ይህ አስገራሚ የህዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ በ1989 የተከናወነውን እና 10 ሚሊዮን ህዝብ የተገኘበትን የቀድሞውን መሪ የአያቶላ ሩሆላ ኾሜኒን የቀብር ሥነ-ሥርዓት በእጅጉ የሚበልጥ እንደሚሆን ተነግሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤22🤣14😢3👍2😱1
መሬት በ31.5 ኢንች አዘነበለች ፤ የከርሰ-ምድር ውሃ መውጣት ዋነኛው መንስኤ ነው ተብሏል።
የሰው ልጅ ከመሬት በታች ያለውን የከርሰ-ምድር ውሃ ከመጠን በላይ በመምጠጡ ምክንያት፣ መሬት የምትሽከረከርበት ዘንግ በ31.5 ኢንች (በግምት 80 ሳንቲም ሜትር) ወደ ምስራቅ መዛመሙን ሳይንቲስቶች ገለጹ።
ፖፑላር መካኒክስ የተባለው የሳይንስ መጽሔት በዛሬው እትሙ (ሰኔ 4 ቀን 2026 እ.ኤ.አ) ይፋ እንዳደረገው፣ ከ1993 እስከ 2010 እ.ኤ.አ ባሉት ዓመታት ውስጥ ብቻ የሰው ልጅ ወደ 2,150 ጊጋቶን የሚጠጋ የከርሰ-ምድር ውሃ ለተለያዩ አገልግሎቶች አውጥቷል።
ይህ የወጣው ውሃ በመጨረሻ ወደ ውቅያኖሶች የፈሰሰ ሲሆን፣ በፕላኔቷ ላይ የነበረውን የክብደት ስርጭት ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ተመራማሪዎች ሂደቱን ልክ አንድ የሚሽከረከር እሽክርክሪት ላይ በአንድ በኩል ትንሽ ክብደት ሲጨመርበት ሚዛኑን እንደሚስት አድርገውታል። ይህ ለውጥ በአየር ንብረት ላይ የሚያመጣው የረጅም ጊዜ ተጽዕኖ አሁንም ጥናት እየተደረገበት ሲሆን፣ የከርሰ-ምድር ውሃ መሟጠጥ ለባህር ወለል ከፍታ መጨመርም ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ተመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሰው ልጅ ከመሬት በታች ያለውን የከርሰ-ምድር ውሃ ከመጠን በላይ በመምጠጡ ምክንያት፣ መሬት የምትሽከረከርበት ዘንግ በ31.5 ኢንች (በግምት 80 ሳንቲም ሜትር) ወደ ምስራቅ መዛመሙን ሳይንቲስቶች ገለጹ።
ፖፑላር መካኒክስ የተባለው የሳይንስ መጽሔት በዛሬው እትሙ (ሰኔ 4 ቀን 2026 እ.ኤ.አ) ይፋ እንዳደረገው፣ ከ1993 እስከ 2010 እ.ኤ.አ ባሉት ዓመታት ውስጥ ብቻ የሰው ልጅ ወደ 2,150 ጊጋቶን የሚጠጋ የከርሰ-ምድር ውሃ ለተለያዩ አገልግሎቶች አውጥቷል።
ይህ የወጣው ውሃ በመጨረሻ ወደ ውቅያኖሶች የፈሰሰ ሲሆን፣ በፕላኔቷ ላይ የነበረውን የክብደት ስርጭት ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ተመራማሪዎች ሂደቱን ልክ አንድ የሚሽከረከር እሽክርክሪት ላይ በአንድ በኩል ትንሽ ክብደት ሲጨመርበት ሚዛኑን እንደሚስት አድርገውታል። ይህ ለውጥ በአየር ንብረት ላይ የሚያመጣው የረጅም ጊዜ ተጽዕኖ አሁንም ጥናት እየተደረገበት ሲሆን፣ የከርሰ-ምድር ውሃ መሟጠጥ ለባህር ወለል ከፍታ መጨመርም ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ተመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍8🤪4🤔2👀1
🔴 ቻይና ግዙፍ የዳታ ማዕከላትን በባህር ወለል ስር ማሰማራት ጀመረች፤ ባህሩ እንደ ተፈጥሯዊ ማቀዝቀዣ ያገለግላል!
የቴክኖሎጂው ልዕለ-ኃያል ቻይና የዓለማችንን የዲጂታል መሠረተ-ልማት አወቃቀር ሙሉ በሙሉ ሊቀይር የሚችል እጅግ አስደናቂ የፈጠራ ስራ በተግባር ማከናወን መጀመሯ ይፋ ሆኗል። ሀገሪቱ እጅግ ግዙፍ የሆኑ የዳታ ማዕከላትን (Data Centers) በቀጥታ በውቅያኖስ ወለል ላይ የማስቀመጥ እና ለንግድ አገልግሎት የማዋል ስራን በተሳካ ሁኔታ ጀምራለች።
ይህ ታይቶ የማይታወቅ አዲስ አሰራር የዳታ ማዕከላቱ ሰርቨሮች መረጃዎችን በከፍተኛ ፍጥነት በሚያሰሉበት ጊዜ የሚፈጥሩትን እጅግ ኃይለኛ ሙቀት ለማስወገድ ቀዝቃዛውን የባህር ውሃ እንደ ተፈጥሯዊ ማቀዝቀዣ የሚጠቀም ነው። ይህም በየብስ ላይ እንደሚደረገው ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ማቀዝቀዣ ማሽኖችን (Chillers) የመጠቀም አስፈላጊነትን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
ይህ የቴክኖሎጂ ስኬት ባህላዊ የዳታ ማዕከላት የሚጠይቁትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ በ22.8 በመቶ የሚቀንስ ሲሆን፣ ለባህላዊ ማቀዝቀዣ የሚባክነውን በሚሊዮን የሚቆጠር ሊትር ንጹህ የውሃ ፍጆታን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል። በተጨማሪም በየብስ ላይ ሊያዝ የሚችለውን ውድ የቦታ ስፋት በ90 በመቶ መታደግ ያስቻለ ሲሆን፣ ማዕከላቱ በቀጥታ በባህር ላይ ከተተከሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ጋር የተገናኙ በመሆኑ ሙሉ በሙሉ በአረንጓዴ እና ታዳሽ ኃይል የሚሰሩ ናቸው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የቴክኖሎጂው ልዕለ-ኃያል ቻይና የዓለማችንን የዲጂታል መሠረተ-ልማት አወቃቀር ሙሉ በሙሉ ሊቀይር የሚችል እጅግ አስደናቂ የፈጠራ ስራ በተግባር ማከናወን መጀመሯ ይፋ ሆኗል። ሀገሪቱ እጅግ ግዙፍ የሆኑ የዳታ ማዕከላትን (Data Centers) በቀጥታ በውቅያኖስ ወለል ላይ የማስቀመጥ እና ለንግድ አገልግሎት የማዋል ስራን በተሳካ ሁኔታ ጀምራለች።
ይህ ታይቶ የማይታወቅ አዲስ አሰራር የዳታ ማዕከላቱ ሰርቨሮች መረጃዎችን በከፍተኛ ፍጥነት በሚያሰሉበት ጊዜ የሚፈጥሩትን እጅግ ኃይለኛ ሙቀት ለማስወገድ ቀዝቃዛውን የባህር ውሃ እንደ ተፈጥሯዊ ማቀዝቀዣ የሚጠቀም ነው። ይህም በየብስ ላይ እንደሚደረገው ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ማቀዝቀዣ ማሽኖችን (Chillers) የመጠቀም አስፈላጊነትን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
ይህ የቴክኖሎጂ ስኬት ባህላዊ የዳታ ማዕከላት የሚጠይቁትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ በ22.8 በመቶ የሚቀንስ ሲሆን፣ ለባህላዊ ማቀዝቀዣ የሚባክነውን በሚሊዮን የሚቆጠር ሊትር ንጹህ የውሃ ፍጆታን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል። በተጨማሪም በየብስ ላይ ሊያዝ የሚችለውን ውድ የቦታ ስፋት በ90 በመቶ መታደግ ያስቻለ ሲሆን፣ ማዕከላቱ በቀጥታ በባህር ላይ ከተተከሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ጋር የተገናኙ በመሆኑ ሙሉ በሙሉ በአረንጓዴ እና ታዳሽ ኃይል የሚሰሩ ናቸው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤23👍5🏆2👏1
የአዲስ አበባ ከተማ የቀድሞ ከንቲባ አምባሳደር ዓሊ አብዶ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በ27ኛ ከንቲባነት ከ1990 እስከ 1995 ዓ.ል. የመሩት አምባሳደር ዓሊ አብዶ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰማ።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው፣ ዛሬ ሌሊት ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል። በአርሲ ድሬ ከተማ ከአባታቸው ከአቶ ዓሊ ሱለይማን እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አፀደ ወልደማሪያም የተወለዱት አምባሳደር ዓሊ፣ ከትዳር አጋራቸው ጋር በጋራ ያፈሯቸው ሁለት ሴት እና አንድ ወንድ ልጆች አሏቸው።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ በቆዩባቸው የሥራ ዘመናት ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን በቅንነት፣ በታማኝነትና በታታሪነት ሲያገለግሉ የነበሩ መሪ እንደነበሩ ተገልጿል።
የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው በዛሬው ዕለት ከጁምዓ ሶላት በኋላ፣ በዳለቲ አካባቢ በሚገኘው የሙስሊሞች መቃብር ስፍራ፤ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ይፈጸማል።
የኔቲዩብ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን እየተመኘ፤ አላህ (ሱ.ወ) ጀነተል ፊርዶስ ይወፍቃቸው ዘንድ ዱዓ ያደርጋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በ27ኛ ከንቲባነት ከ1990 እስከ 1995 ዓ.ል. የመሩት አምባሳደር ዓሊ አብዶ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰማ።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው፣ ዛሬ ሌሊት ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል። በአርሲ ድሬ ከተማ ከአባታቸው ከአቶ ዓሊ ሱለይማን እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አፀደ ወልደማሪያም የተወለዱት አምባሳደር ዓሊ፣ ከትዳር አጋራቸው ጋር በጋራ ያፈሯቸው ሁለት ሴት እና አንድ ወንድ ልጆች አሏቸው።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ በቆዩባቸው የሥራ ዘመናት ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን በቅንነት፣ በታማኝነትና በታታሪነት ሲያገለግሉ የነበሩ መሪ እንደነበሩ ተገልጿል።
የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው በዛሬው ዕለት ከጁምዓ ሶላት በኋላ፣ በዳለቲ አካባቢ በሚገኘው የሙስሊሞች መቃብር ስፍራ፤ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ይፈጸማል።
የኔቲዩብ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን እየተመኘ፤ አላህ (ሱ.ወ) ጀነተል ፊርዶስ ይወፍቃቸው ዘንድ ዱዓ ያደርጋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢12❤11👏5🎉2💔2👍1🕊1
በነገው እለት የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅4:30 – 9:00
👉መስቀል ፋላዎር፣ ወንግላዊት፣ ወሎ ሰፈር ጀርባ፣ ጎርጎርዮስ፣ ጎተራ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
👉ሰበታ ከተማ ፣ አለርት ሆስፒታል፣ ቻይና ቱቦ አካባቢ፣ ኢንዱስቲሪ መንደር እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 12፡00 – 7፡00
👉መቀለ ከተማ 03፣ አይደር ሪፌራል ሆስፒታል፣ አድሽምን፣ አዲሃ አክረም እና ደኤሮ አካባቢ፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 12፡00
👉መቀለ ከተማ 05፣ ኮንዶሚኒየም ሰፈር፣ ግብርና ብሮና ማይዱባ እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
👉አዳማ ፖስታ ቤት፣ አዳማ ሆስፒታል፣ ፍራንኮ፣ ፒኮክ፣ 105 አካባቢ፣ አኪሊስያ ሆስፕታል እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 6፡30
👉በወልድያ መቻሬ፣ አዳጎ፣ አሸዋ ሜዳ፣ አመያመጫ፣ ሁርጌሳ፣ ኡድመን፣ ልብሶ፣ ጊረና፣ መሀለምብ እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 12፡00 - 11፡00
👉የአዳሚ ቱሉ ገንዳ አርባ 132 ኪ.ቮ አግሮ ኢንዱትሪ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት በታወር ቁጥር 11 እና በታወር ቁጥር 12 መካከል በሚገኙ ኩርማ 33 ኪ.ቮ ኢንዱስትሪ ፓርክ 33 ኪ.ቮ እና ቡልቡላ 15 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ መስመሮች ይቋረጣሉ፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ነገ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅4:30 – 9:00
👉መስቀል ፋላዎር፣ ወንግላዊት፣ ወሎ ሰፈር ጀርባ፣ ጎርጎርዮስ፣ ጎተራ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
👉ሰበታ ከተማ ፣ አለርት ሆስፒታል፣ ቻይና ቱቦ አካባቢ፣ ኢንዱስቲሪ መንደር እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 12፡00 – 7፡00
👉መቀለ ከተማ 03፣ አይደር ሪፌራል ሆስፒታል፣ አድሽምን፣ አዲሃ አክረም እና ደኤሮ አካባቢ፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 12፡00
👉መቀለ ከተማ 05፣ ኮንዶሚኒየም ሰፈር፣ ግብርና ብሮና ማይዱባ እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
👉አዳማ ፖስታ ቤት፣ አዳማ ሆስፒታል፣ ፍራንኮ፣ ፒኮክ፣ 105 አካባቢ፣ አኪሊስያ ሆስፕታል እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 6፡30
👉በወልድያ መቻሬ፣ አዳጎ፣ አሸዋ ሜዳ፣ አመያመጫ፣ ሁርጌሳ፣ ኡድመን፣ ልብሶ፣ ጊረና፣ መሀለምብ እና አካባቢያቸው፣
✅ከጠዋቱ 12፡00 - 11፡00
👉የአዳሚ ቱሉ ገንዳ አርባ 132 ኪ.ቮ አግሮ ኢንዱትሪ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት በታወር ቁጥር 11 እና በታወር ቁጥር 12 መካከል በሚገኙ ኩርማ 33 ኪ.ቮ ኢንዱስትሪ ፓርክ 33 ኪ.ቮ እና ቡልቡላ 15 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ መስመሮች ይቋረጣሉ፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12👍7
ኦብነግ ከፋኖ ጋር መነጋገሩን ይፋ አደረገ
ከአንድ ወር በፊት በአስመራ ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የተገናኙት የኦብነግ አንጃ መሪ የሆኑት አብዱራህማን መህዲ ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ንግግር እያደረጉ መሆናቸውን አሳውቀዋል፡፡ አፍሪካን ኢንተለጀንስ ትናንት ባወጣው ዘገባ፣ ከሰላማዊ ትግል ራሱን ያገለለው የኦብነግ አንጃ ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ እና አማጺ ኃይሎች ጋር ጥምረት እንዲፈጥሩ ከግብጽ እና ኤርትራ መንግስታት ጫና እየተደረገባቸው መሆኑን ዘግቧል፡፡
የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች በጋራ እየተሰባሰቡ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው፤ ከሚሰባሰቡት ኃይሎች መካከል ኦብነግ አንዱ ነው ብሏል፡፡ እንደ ፋኖ፣ ህውሃት እና ኦነግ ሸኔ ካሉ ሀይሎች ጋር ጥምረት መፍጠራቸውን በአፍሪካ ኢንተለጀንስ የተጠየቁት የቡድኑ መሪ አብዱራህማን መህዲ፤ ‹‹ጥምረት የመፍጠር ደረጃ ላይ ባንደርስም፤ ከፋኖም ሆነ ሌሎች ሀይሎች ጋር ተነጋግረናል፤ ለመስራትም ዝግጁ ነን፤ ነገር ግን ውይጥቱ የመጨረሻ ደረጃ ላይ አልደረሰም›› በማለት መልሰዋል፡፡
አፍሪካን ኢንተለጀንስ እንደዘገባው፣ የኦብነግ አንጃ ከሌሎች ሀይሎች ጋር ትብብር እንዲፈጥር፣ በሱዳን፣ ኤርትራ እና ግብጽ መንግስታት ጫና እየተደረገበት ሲሆን፤ በቅርቡም በአስመራ እና በፖርት ሱዳን ስብሰባዎችን ማደረረጋቸውን ጠቅሷል፡፡via:- andafta
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከአንድ ወር በፊት በአስመራ ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የተገናኙት የኦብነግ አንጃ መሪ የሆኑት አብዱራህማን መህዲ ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ንግግር እያደረጉ መሆናቸውን አሳውቀዋል፡፡ አፍሪካን ኢንተለጀንስ ትናንት ባወጣው ዘገባ፣ ከሰላማዊ ትግል ራሱን ያገለለው የኦብነግ አንጃ ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ እና አማጺ ኃይሎች ጋር ጥምረት እንዲፈጥሩ ከግብጽ እና ኤርትራ መንግስታት ጫና እየተደረገባቸው መሆኑን ዘግቧል፡፡
የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች በጋራ እየተሰባሰቡ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው፤ ከሚሰባሰቡት ኃይሎች መካከል ኦብነግ አንዱ ነው ብሏል፡፡ እንደ ፋኖ፣ ህውሃት እና ኦነግ ሸኔ ካሉ ሀይሎች ጋር ጥምረት መፍጠራቸውን በአፍሪካ ኢንተለጀንስ የተጠየቁት የቡድኑ መሪ አብዱራህማን መህዲ፤ ‹‹ጥምረት የመፍጠር ደረጃ ላይ ባንደርስም፤ ከፋኖም ሆነ ሌሎች ሀይሎች ጋር ተነጋግረናል፤ ለመስራትም ዝግጁ ነን፤ ነገር ግን ውይጥቱ የመጨረሻ ደረጃ ላይ አልደረሰም›› በማለት መልሰዋል፡፡
አፍሪካን ኢንተለጀንስ እንደዘገባው፣ የኦብነግ አንጃ ከሌሎች ሀይሎች ጋር ትብብር እንዲፈጥር፣ በሱዳን፣ ኤርትራ እና ግብጽ መንግስታት ጫና እየተደረገበት ሲሆን፤ በቅርቡም በአስመራ እና በፖርት ሱዳን ስብሰባዎችን ማደረረጋቸውን ጠቅሷል፡፡via:- andafta
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤27🤔11👍5🏆3🤯1