አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Photo
የአሜሪካ መንግስት በአፍሪካ የቪዛ አገልግሎት መስጫ ቦታዎችን ወደ 20 ብቻ ሊቀንስ ነው‼️
👉 አዲስ አበባ አገልግሎቷን እንደምትቀጥል ተረጋግጧል
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ የቪዛ ማስተናገጃ ማዕከላቱን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ መወሰኑን ይፋ አደረገ።
ይህ አዲስ መመሪያ የትራምፕ አስተዳደር በስደት ላይ የጀመረውን ጠንካራ የቁጥጥር ፖሊሲ ይበልጥ ለማጥበቅ ከሚያደርገው ጥረት ጋር የተያያዘ ነው።
እስካሁን ድረስ በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ወደ 50 የሚጠጉ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች የቪዛ ማመልከቻዎችን ሲቀበሉ የነበረ ቢሆንም፣ አዲሱ እቅድ ይህንን ቁጥር ወደ 20 "ማዕከላት" ብቻ ዝቅ የሚያደርግ ይሆናል።
እንደ አሶሺየትድ ፕሬስ ዘገባ እና ከውስጥ ባለስልጣናት በተገኘ መረጃ መሠረት፣ ይሄው አሰራር በሚቀጥሉት ሳምንታት (በሰኔ ወር ውስጥ) ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።
በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ በፀደቀው በዚህ መመሪያ መሠረት፣ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ሙሉ የቪዛ አገልግሎት መስጠቷን እንድትቀጥል ከተመረጡት 20 ጥቂት ማዕከላት መካከል አንዷ ሆናለች።
ይህም ማለት በኢትዮጵያ የሚገኙ አመልካቾች ያለምንም እንግልት መደበኛ የቪዛ አገልግሎታቸውን ከአዲስ አበባ ማግኘት ይችላሉ።
ይሁን እንጂ ይህ ውሳኔ ማዕከል ባልሆኑ ሀገራት ዜጎች ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የጉዞ ጫና ያሳድራል።
በእነዚህ ሀገራት የሚገኙ የአሜሪካ ቆንስላዎች መደበኛ የቪዛ አገልግሎት መስጠታቸውን የሚያቆሙ በመሆኑ፣ ዜጎቹ ቪዛ ለማግኘት ድንበር አቋርጠው አዲስ አበባን ወደመሳሰሉ የቪዛ ማዕከላት ለመጓዝ ይገደዳሉ። ይህም ተጨማሪ የጉዞ ወጪን እና የጊዜ መዘግየትን ያስከትላል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ አገልግሎታቸው በሚቀነስባቸው ሀገራት የሚገኙ ኤምባሲዎች ሙሉ በሙሉ የማይዘጉ ሲሆን፣ ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጡ ድንገተኛ ድጋፎችን እና ልዩ የዲፕሎማቲክ ጉዳዮችን ማስተናገዳቸውን ይቀጥላሉ ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👉 አዲስ አበባ አገልግሎቷን እንደምትቀጥል ተረጋግጧል
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ የቪዛ ማስተናገጃ ማዕከላቱን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ መወሰኑን ይፋ አደረገ።
ይህ አዲስ መመሪያ የትራምፕ አስተዳደር በስደት ላይ የጀመረውን ጠንካራ የቁጥጥር ፖሊሲ ይበልጥ ለማጥበቅ ከሚያደርገው ጥረት ጋር የተያያዘ ነው።
እስካሁን ድረስ በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ወደ 50 የሚጠጉ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች የቪዛ ማመልከቻዎችን ሲቀበሉ የነበረ ቢሆንም፣ አዲሱ እቅድ ይህንን ቁጥር ወደ 20 "ማዕከላት" ብቻ ዝቅ የሚያደርግ ይሆናል።
እንደ አሶሺየትድ ፕሬስ ዘገባ እና ከውስጥ ባለስልጣናት በተገኘ መረጃ መሠረት፣ ይሄው አሰራር በሚቀጥሉት ሳምንታት (በሰኔ ወር ውስጥ) ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።
በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ በፀደቀው በዚህ መመሪያ መሠረት፣ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ሙሉ የቪዛ አገልግሎት መስጠቷን እንድትቀጥል ከተመረጡት 20 ጥቂት ማዕከላት መካከል አንዷ ሆናለች።
ይህም ማለት በኢትዮጵያ የሚገኙ አመልካቾች ያለምንም እንግልት መደበኛ የቪዛ አገልግሎታቸውን ከአዲስ አበባ ማግኘት ይችላሉ።
ይሁን እንጂ ይህ ውሳኔ ማዕከል ባልሆኑ ሀገራት ዜጎች ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የጉዞ ጫና ያሳድራል።
በእነዚህ ሀገራት የሚገኙ የአሜሪካ ቆንስላዎች መደበኛ የቪዛ አገልግሎት መስጠታቸውን የሚያቆሙ በመሆኑ፣ ዜጎቹ ቪዛ ለማግኘት ድንበር አቋርጠው አዲስ አበባን ወደመሳሰሉ የቪዛ ማዕከላት ለመጓዝ ይገደዳሉ። ይህም ተጨማሪ የጉዞ ወጪን እና የጊዜ መዘግየትን ያስከትላል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ አገልግሎታቸው በሚቀነስባቸው ሀገራት የሚገኙ ኤምባሲዎች ሙሉ በሙሉ የማይዘጉ ሲሆን፣ ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጡ ድንገተኛ ድጋፎችን እና ልዩ የዲፕሎማቲክ ጉዳዮችን ማስተናገዳቸውን ይቀጥላሉ ተብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍5🙈1
የቻይናው መከላከያ ተቋም “የአሜሪካን ድብቅ ተዋጊ አውሮፕላኖች በኤአይ (AI) መከታተል ችያለሁ” ማለቱ መነጋገሪያ ሆኗል
አንድ ጂንጋን (Jingan) የተሰኘ የቻይና የግል መከላከያ ቴክኖሎጂ ተቋም፣ በቅርቡ በኢራን ግጭት ወቅት “ጂንግቺ” በተሰኘው የሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) የጦርነት ክትትል ስርዓቱ አማካኝነት አራት የአሜሪካ “ቢ-2 ስፒሪት” (B-2 Spirit) ድብቅ ስውር ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖችን መከታተል መቻሉን ገለጸ።
የቴክኖሎጂ ተቋሙ አውሮፕላኖቹ “ፔትሮ 41 እስከ 44” (Petro 41 to 44) በሚሉ የመገናኛ ኮዶች ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የጠቀሰ ሲሆን፣ ከአውሮፕላኖቹ የወጡ የሬዲዮ ሞገዶችን በመጥለፍ እና በኤአይ (AI) አማካኝነት የበረራ መስመራቸውን መልሶ መገንባት መቻሉን ተናግሯል። ይሁን እንጂ ተቋሙ ይህንን አስገራሚ ክስ የሚያረጋግጥ እስካሁን ያቀረበው ምንም ዓይነት ተጨባጭ ማስረጃ የለም።
እንደ ጂንጋን ገለጻ ከሆነ፣ ስርአቱ ግጭቱ ከመቀስቀሱ ሳምንታት በፊት የሳተላይት ምስሎችን፣ የበረራ መረጃዎችን እና ግልጽ የሆኑ የመረጃ ምንጮችን (open-source intelligence) በማቀናጀት በኢራን አቅራቢያ እያደገ የመጣውን የአሜሪካ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ቀድሞ መለየት ችሎ ነበር። ተቋሙ አራቱ የቢ-2 ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች የተከታተላቸው አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ኢላማዎች ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ መሆኑን አስታውቋል።
ይሁን እንጂ ይህ የቻይናው ተቋም ይፋ ያደረገው መረጃ በተናጠል በገለልተኛ ወገን ያልተረጋገጠ ሲሆን፣ እጅግ ዘመናዊ እና በራዳር እንዳይታዩ ተደርገው የተሰሩት ስውር አውሮፕላኖች ተለይተው ስለመገኘታቸው የሚገልጸው ዘገባ እስካሁን ድረስ በማስረጃ አልተደገፈም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አንድ ጂንጋን (Jingan) የተሰኘ የቻይና የግል መከላከያ ቴክኖሎጂ ተቋም፣ በቅርቡ በኢራን ግጭት ወቅት “ጂንግቺ” በተሰኘው የሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) የጦርነት ክትትል ስርዓቱ አማካኝነት አራት የአሜሪካ “ቢ-2 ስፒሪት” (B-2 Spirit) ድብቅ ስውር ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖችን መከታተል መቻሉን ገለጸ።
የቴክኖሎጂ ተቋሙ አውሮፕላኖቹ “ፔትሮ 41 እስከ 44” (Petro 41 to 44) በሚሉ የመገናኛ ኮዶች ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የጠቀሰ ሲሆን፣ ከአውሮፕላኖቹ የወጡ የሬዲዮ ሞገዶችን በመጥለፍ እና በኤአይ (AI) አማካኝነት የበረራ መስመራቸውን መልሶ መገንባት መቻሉን ተናግሯል። ይሁን እንጂ ተቋሙ ይህንን አስገራሚ ክስ የሚያረጋግጥ እስካሁን ያቀረበው ምንም ዓይነት ተጨባጭ ማስረጃ የለም።
እንደ ጂንጋን ገለጻ ከሆነ፣ ስርአቱ ግጭቱ ከመቀስቀሱ ሳምንታት በፊት የሳተላይት ምስሎችን፣ የበረራ መረጃዎችን እና ግልጽ የሆኑ የመረጃ ምንጮችን (open-source intelligence) በማቀናጀት በኢራን አቅራቢያ እያደገ የመጣውን የአሜሪካ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ቀድሞ መለየት ችሎ ነበር። ተቋሙ አራቱ የቢ-2 ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች የተከታተላቸው አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ኢላማዎች ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ መሆኑን አስታውቋል።
ይሁን እንጂ ይህ የቻይናው ተቋም ይፋ ያደረገው መረጃ በተናጠል በገለልተኛ ወገን ያልተረጋገጠ ሲሆን፣ እጅግ ዘመናዊ እና በራዳር እንዳይታዩ ተደርገው የተሰሩት ስውር አውሮፕላኖች ተለይተው ስለመገኘታቸው የሚገልጸው ዘገባ እስካሁን ድረስ በማስረጃ አልተደገፈም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19👍10🤣3🤔2
ጅቡቲ በዳመርጆግ የነዳጅ ማከማቻ ግንባታ ላይ የኢትዮጵያን ድጋፍና ተሳትፎ እየጠበቀች መሆኑን ገለጸች
የጅቡቲ ወደቦች እና ነፃ ቀጠናዎች ባለስልጣን በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ በኩል በሚገኘው አዲሱ የዳመርጆግ ፈሳሽ ጭነት ወደብ ላይ የነዳጅ ማከማቻ ዴፖ ግንባታ ለመጀመር በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያን ተሳትፎና የገንዘብ ድጋፍ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ሰብሳቢ አቡበከር ኦማር ሀዲ ለካፒታል እንደገለፁት ፣ ዘመናዊው የነዳጅ ወደብ ወደ ስራ እንዲገባ የነዳጅ ማራገፊያ ዴፖ ግንባታ ይቀረዋል።
ለዚህም ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር ድርድር እያደረገ ሲሆን፣ ተቋሙ ሐምሌ 1 ቀን በሚጀምረው አዲስ የበጀት አመት በጀት አፀድቆ ለስራው እንደሚመጣ ይጠበቃል ሲሉ ነው የገለፁት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የጅቡቲ ወደቦች እና ነፃ ቀጠናዎች ባለስልጣን በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ በኩል በሚገኘው አዲሱ የዳመርጆግ ፈሳሽ ጭነት ወደብ ላይ የነዳጅ ማከማቻ ዴፖ ግንባታ ለመጀመር በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያን ተሳትፎና የገንዘብ ድጋፍ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ሰብሳቢ አቡበከር ኦማር ሀዲ ለካፒታል እንደገለፁት ፣ ዘመናዊው የነዳጅ ወደብ ወደ ስራ እንዲገባ የነዳጅ ማራገፊያ ዴፖ ግንባታ ይቀረዋል።
ለዚህም ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር ድርድር እያደረገ ሲሆን፣ ተቋሙ ሐምሌ 1 ቀን በሚጀምረው አዲስ የበጀት አመት በጀት አፀድቆ ለስራው እንደሚመጣ ይጠበቃል ሲሉ ነው የገለፁት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17🤣3👍2
⚡️ "የኢራን ድሮኖች በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ከባድ ጥቃት ሰነዘሩ"
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ቀጠናዊ ጦርነት ተከትሎ፣ የኢራን ድሮኖች በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋናው የመንገደኞች ተርሚናል (T1) ላይ ከባድ ጥቃት ማድረሳቸውን የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እና የመከላከያ ሚኒስቴር በይፋ አስታውቀዋል። ጥቃቱ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱንና በርካታ ሰዎችን ማቁሰሉ ተገልጿል።
📌 ጥቃቱን ተከትሎ የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የአደጋ ጊዜ እቅድን ያነቀሳቀሰ ሲሆን፣ ሁሉንም የንግድ በረራዎች በማቋረጥ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ የነበሩ አውሮፕላኖችን ወደ ጎረቤት ሀገራት አማራጭ አውሮፕላን ማረፊያዎች እንዲቀየሩ አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ቀጠናዊ ጦርነት ተከትሎ፣ የኢራን ድሮኖች በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋናው የመንገደኞች ተርሚናል (T1) ላይ ከባድ ጥቃት ማድረሳቸውን የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እና የመከላከያ ሚኒስቴር በይፋ አስታውቀዋል። ጥቃቱ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱንና በርካታ ሰዎችን ማቁሰሉ ተገልጿል።
📌 ጥቃቱን ተከትሎ የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የአደጋ ጊዜ እቅድን ያነቀሳቀሰ ሲሆን፣ ሁሉንም የንግድ በረራዎች በማቋረጥ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ የነበሩ አውሮፕላኖችን ወደ ጎረቤት ሀገራት አማራጭ አውሮፕላን ማረፊያዎች እንዲቀየሩ አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7👍3🙏3👏2
የምርጫ ቦርድ ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም አካል ራሱን አሸናፊ አድርጎ ከመግለጽ ይቆጠብ":-ኢሰመጉ‼️
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ባወጣው የምርጫ መታዘብ ቅድመ መግለጫ ላይ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጥብቅ ማሳሰቢያ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም ግለሰብ፣ የፖለቲካ ድርጅት ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ጊዜያዊ ውጤት በማጋራት ማኅበረሰቡን ከማደናገር እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
የምልከታ ስፋት፦ኢሰመጉ ባሰማራቸው 433 ታዛቢዎች አማካኝነት ከ800 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን ተከታትሏል።
⚠️ የተስተዋሉ ዋና ዋና ተግዳሮቶች፦
* የአዲሱ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥልት መጀመሩ የሚበረታታ ቢሆንም፣ የአስፈጻሚዎች ሥልጠና ማነስ ለመራጮች መጨናነቅና ለሰዓት መራዘም ምክንያት ሆኗል።
* በበርካታ አካባቢዎች የትራንስፖርት መቋረጥ፣ በአዲስ አበባ የሰልፍ አስተባባሪዎች ማነስ እና በመራጮች ላይ የደረሰ የእንግልት ሰዓት።
* በሐዋሳና አካባቢው በሚገኙ ውስን ጣቢያዎች የምርጫ አስፈጻሚዎች በሚስጥራዊ ድምፅ መስጫ ቦታ በመግባት የሥነ-ልቦና ጫና ማድረጋቸው እና ያልተመረጡ ወረቀቶችን ወደ ሳጥን ማስገባት የመሳሰሉ የነፃነት መብትን የገደቡ ክስተቶች መታየታቸው።
✅ በበጎ ጎን የተነሱ ነጥቦች፦
* የመራጮች ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ በቂ የቁሳቁስ አቅርቦት እና በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች የጎላ የጸጥታ መደፍረስ ሳይኖር ሂደቱ መጠናቀቁ።
"ኢሰመጉ ምርጫ ቦርድ በአንጻራዊነት ስኬታማና ሰላማዊ ምርጫ ማከናወኑን በመግለጽ ዕውቅና የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ግን የተስተዋሉ ችግሮችን በዝርዝር ለይቶ እንዲያርም ጥሪ አቅርቧል።"
@Addis_Reporter
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ባወጣው የምርጫ መታዘብ ቅድመ መግለጫ ላይ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጥብቅ ማሳሰቢያ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም ግለሰብ፣ የፖለቲካ ድርጅት ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ጊዜያዊ ውጤት በማጋራት ማኅበረሰቡን ከማደናገር እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
የምልከታ ስፋት፦ኢሰመጉ ባሰማራቸው 433 ታዛቢዎች አማካኝነት ከ800 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን ተከታትሏል።
⚠️ የተስተዋሉ ዋና ዋና ተግዳሮቶች፦
* የአዲሱ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥልት መጀመሩ የሚበረታታ ቢሆንም፣ የአስፈጻሚዎች ሥልጠና ማነስ ለመራጮች መጨናነቅና ለሰዓት መራዘም ምክንያት ሆኗል።
* በበርካታ አካባቢዎች የትራንስፖርት መቋረጥ፣ በአዲስ አበባ የሰልፍ አስተባባሪዎች ማነስ እና በመራጮች ላይ የደረሰ የእንግልት ሰዓት።
* በሐዋሳና አካባቢው በሚገኙ ውስን ጣቢያዎች የምርጫ አስፈጻሚዎች በሚስጥራዊ ድምፅ መስጫ ቦታ በመግባት የሥነ-ልቦና ጫና ማድረጋቸው እና ያልተመረጡ ወረቀቶችን ወደ ሳጥን ማስገባት የመሳሰሉ የነፃነት መብትን የገደቡ ክስተቶች መታየታቸው።
✅ በበጎ ጎን የተነሱ ነጥቦች፦
* የመራጮች ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ በቂ የቁሳቁስ አቅርቦት እና በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች የጎላ የጸጥታ መደፍረስ ሳይኖር ሂደቱ መጠናቀቁ።
"ኢሰመጉ ምርጫ ቦርድ በአንጻራዊነት ስኬታማና ሰላማዊ ምርጫ ማከናወኑን በመግለጽ ዕውቅና የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ግን የተስተዋሉ ችግሮችን በዝርዝር ለይቶ እንዲያርም ጥሪ አቅርቧል።"
@Addis_Reporter
😁23❤16👍5🤪4🤔1
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት መልእክት አስተላለፉ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ ::
"በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን::"
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ ::
"በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን::"
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤37🙏10👍3
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኢራን የኩዌት አየር መንገድን በዚ መልኩ ነው ያወደመችው በዚህ ጥቃት 63 ሰዎች ቀላል እና ከባድ ጉዳት የደርሰባቸው ሲሆን የሞቾች ቁጥርም ከአንድ ሊበልጥ እንደሚችል እየተናገሩ ይገኛል"
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16💔7🤯3👍2👏1😢1
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፦
⏰ ከጠዋቱ 2:00-12:00
👉 በአዳማ ሪጅን አዳማ ቆርቆሮ፣
⏰ ከጠዋቱ 2:00-11:00
አዳማ ፈትል ፋብሪካ፣ ሬድሬስ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ፣ አህዋን ፋብሪካ
⏰ ከጠዋቱ 2:30-9:00
👉 በአዳማ ሪጅን ከአዋሽ መልካሳ ወደ አዱላላና አሮሪቲ፣
⏰ ከጠዋቱ 2:30-7:00
👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን አስኮ ገብርኤል፣ ሳንሱሲ፣ እያሱ ምንጭ፣ ብርጭቆ ኮንዶሚኒየም፣ ከታ አፍያ ዴቄት፣
⏰ ከጠዋቱ 3:00 እስከ ምሽቱ 4:00 ድረስ
👉 በደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን ኬኬ ብርድ ልብስ ፋብሪካ፣ ቂሊንጦ ኮንዶሚኒየም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አስቱ ዩኒቨርስቲ እና ኢንዱስትሪ መንደር፣ ዋልያ ቢራ
⏰ ከጠዋቱ 6:00-9:00
👉 በምዕረብ አደስ አበባ ሪጅን ስልጤ ሰፈር፣ አጃምባ ኮንዶሚኒየም
⏰ ከቀኑ 7፡00- 11፡00
👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ሸጎሌ አንበሳ ጋራዥ፣ ሸጎሌ መንደር-7፣ ፊናንስ፣ አበበ ቢቂላ፣ ኳስ ሜዳ፣ መሳለሚያ
⏰ ከቀኑ 7:30-10:30
👉 በሽረ ረጅን እደጋ አርቢ፣ ማይ ቐንታል
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻች የጥገና ሥራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፦
⏰ ከጠዋቱ 2:00-12:00
👉 በአዳማ ሪጅን አዳማ ቆርቆሮ፣
⏰ ከጠዋቱ 2:00-11:00
አዳማ ፈትል ፋብሪካ፣ ሬድሬስ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ፣ አህዋን ፋብሪካ
⏰ ከጠዋቱ 2:30-9:00
👉 በአዳማ ሪጅን ከአዋሽ መልካሳ ወደ አዱላላና አሮሪቲ፣
⏰ ከጠዋቱ 2:30-7:00
👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን አስኮ ገብርኤል፣ ሳንሱሲ፣ እያሱ ምንጭ፣ ብርጭቆ ኮንዶሚኒየም፣ ከታ አፍያ ዴቄት፣
⏰ ከጠዋቱ 3:00 እስከ ምሽቱ 4:00 ድረስ
👉 በደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን ኬኬ ብርድ ልብስ ፋብሪካ፣ ቂሊንጦ ኮንዶሚኒየም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አስቱ ዩኒቨርስቲ እና ኢንዱስትሪ መንደር፣ ዋልያ ቢራ
⏰ ከጠዋቱ 6:00-9:00
👉 በምዕረብ አደስ አበባ ሪጅን ስልጤ ሰፈር፣ አጃምባ ኮንዶሚኒየም
⏰ ከቀኑ 7፡00- 11፡00
👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ሸጎሌ አንበሳ ጋራዥ፣ ሸጎሌ መንደር-7፣ ፊናንስ፣ አበበ ቢቂላ፣ ኳስ ሜዳ፣ መሳለሚያ
⏰ ከቀኑ 7:30-10:30
👉 በሽረ ረጅን እደጋ አርቢ፣ ማይ ቐንታል
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻች የጥገና ሥራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍11❤9⚡2
በ130 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች መዝገብ ላይ ያልተገኙ እና ካርድ ያልያዙ መራጮች እንዲመርጡ መደረጋቸውን ኅብረት ለምርጫ ገለጸ
የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ (CECOE / ኅብረት ለምርጫ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተከናወነውን 7ኛውን ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ አስመልክቶ ዛሬ ረቡዕ ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ የትዝብት ሪፖርቱ፣ በ130 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች መዝገብ ላይ ያልተገኙ እና ካርድ ያልያዙ፣ በእያንዳንዱ ጣቢያ ከአንድ እስከ 10 የሚሆኑ መራጮች እንዲመርጡ መደረጋቸውን ገለጸ።
እንዲሁም በስምንት የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ደግሞ ከ10 በላይ ሰዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሳይገኝ እና የመራጭነት ካርድ ሳይዙ እንዲመርጡ መፈቀዱንም ኅብረቱ በምርጫ ትዝብት ጊዜያዊ ሪፖርቱ ላይ አስታውቋል።
ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,506 የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ2,458 ጣቢያዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት የተከለከለ ሰው እንዳልነበር መታዘቡን ጠቅሷል፤ ይሁንና በ46 የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ከ1 እስከ 10 ግለሰቦች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት መከልከላቸው ተገልጿል።
በሁለት ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ደግሞ ከ10 በላይ ሰዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት መከልከላቸውን የኅብረቱ ሰብሳቢ ተናግረዋል።
Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ (CECOE / ኅብረት ለምርጫ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተከናወነውን 7ኛውን ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ አስመልክቶ ዛሬ ረቡዕ ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ የትዝብት ሪፖርቱ፣ በ130 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች መዝገብ ላይ ያልተገኙ እና ካርድ ያልያዙ፣ በእያንዳንዱ ጣቢያ ከአንድ እስከ 10 የሚሆኑ መራጮች እንዲመርጡ መደረጋቸውን ገለጸ።
እንዲሁም በስምንት የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ደግሞ ከ10 በላይ ሰዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሳይገኝ እና የመራጭነት ካርድ ሳይዙ እንዲመርጡ መፈቀዱንም ኅብረቱ በምርጫ ትዝብት ጊዜያዊ ሪፖርቱ ላይ አስታውቋል።
ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,506 የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ2,458 ጣቢያዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት የተከለከለ ሰው እንዳልነበር መታዘቡን ጠቅሷል፤ ይሁንና በ46 የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ከ1 እስከ 10 ግለሰቦች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት መከልከላቸው ተገልጿል።
በሁለት ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ደግሞ ከ10 በላይ ሰዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት መከልከላቸውን የኅብረቱ ሰብሳቢ ተናግረዋል።
Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16😁11👍5
ይህንን ያውቃሉ❓❓
የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ በወረዳ ጽሕፈት ቤቶቹ የሚሰጣቸውን የኩነት (የልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞትና ጉዲፈቻ) ማስረጃዎችን የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት ተገልጋዮች ይዘው መቅረብ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችንና ደጋፊ ሰነዶችን እንደሚከተለው ያሳውቃል።
ለእያንዳንዱ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ልዩ ቅድመ ሁኔታዎች
1. የልደት ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ፦ በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የልደት ማስረጃ
አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሁለቱ አንዱ ወላጅ በአካል ሲገኝ ነው (የወላጆች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ያስፈልጋል)።
ምዝገባው በሞግዚትነት ከሆነ የፍርድ ቤት የሞግዚትነት ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ፦ ባለጉዳዩ በአካል መቅረብ አለበት። በአካል መቅረብ ካልቻለ፣ ጉዳዩን የሚገልጽ ልዩ ውክልና ከወካይና ተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።
2. የጋብቻ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የጋብቻ ማስረጃ መያዝ።
ለግልባጭ ወይም ለእርማት አገልግሎት፦ የተጋቢዎች ሁለት ሁለት (2) ጉርድ ፎቶግራፍ።
በውክልና የሚጠየቅ ከሆነ (ለእርማት፣ ዕድሳትና ግልባጭ)፦ ባልና ሚስት ጉዳዩን በግልጽ የሚያሳይ ውክልና፣ የወካዮች እና የተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ወይም የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው።
3. የፍቺ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የፍቺ ማስረጃ
የህግ አስገዳጅነቱ የተረጋገጠ የፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
4. የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
በወረዳ የተመዘገበ የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት እና የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰነድ
ጉዲፈቻ አድራጊዎች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በመያዝ በአካል መቅረብ አለባቸው።
ጉዳዩ በውክልና ከሆነ፣ይህንኑ የሚያስረዳ ልዩ ውክልና መቅረብ አለበት።
5. የሞት ማስረጃ ለማረጋገጥ
በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የሞት ማስረጃ የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት
ከሟች ጋር አብሮ ይኖር የነበረ ሰው፣ እርሱ ከሌለ የሟች የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመዶች፣ እነዚህም ከሌሉ የቅርብ ጎረቤት ወይም ስለሟቹ መሞት የሚያውቅ ማንኛውም ሰው የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በማቅረብ ማስመዝገብና ማረጋገጥ ይችላል።
ሟች የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ከሆስፒታል የተሰጠ የማሳወቂያ ወረቀት መቅረብ አለበት።
ማሳሰቢያ፡- ለሁሉም ከላይ ለተዘረዘሩት የኩነት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስፈልግ ደጋፊ ሰነድ
• የታደሰ ብሔራዊ መታወቂያ / የታደሰ ፓስፖርት / የትውልደ ኢትዮጵያ የውጭ ዜግነት መታወቂያ (የቢጫ ካርድ)።
• ከዝቅተኛው አስተዳደር ጽ/ቤት መደበኛ ነዋሪነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ / የስደተኛነት ማስረጃ / የመኖሪያ ፈቃድ።
• ከሚሰራበት መስሪያ ቤት ባልደረባነቱንና ዜግነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ ከመስሪያ ቤቱ መታወቂያ ጋር / የመከላከያ ሰራዊት ከሆነ የመከላከያ ሰራዊት መታወቂያ መያዝ
• የጠፋ ሰርተፍኬት ግልባጭ ለመውሰድ፦ ከፖሊስ የተሰጠ የጠፋ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ግዴታ ነው።
• ከወረዳ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከወረዳው ስለመውጣታቸው የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ያስፈልጋቸዋል።
• ከክፍለ ከተማ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከሰነዱ በስተጀርባ የማረጋገጫ ማህተም ማረፍ ይኖርበታል።
• ከውጭ ሀገር የሚመጣ ውክልና፦ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በፌደራል ሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ መረጋገጥ አለበት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ በወረዳ ጽሕፈት ቤቶቹ የሚሰጣቸውን የኩነት (የልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞትና ጉዲፈቻ) ማስረጃዎችን የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት ተገልጋዮች ይዘው መቅረብ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችንና ደጋፊ ሰነዶችን እንደሚከተለው ያሳውቃል።
ለእያንዳንዱ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ልዩ ቅድመ ሁኔታዎች
1. የልደት ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ፦ በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የልደት ማስረጃ
አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሁለቱ አንዱ ወላጅ በአካል ሲገኝ ነው (የወላጆች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ያስፈልጋል)።
ምዝገባው በሞግዚትነት ከሆነ የፍርድ ቤት የሞግዚትነት ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ፦ ባለጉዳዩ በአካል መቅረብ አለበት። በአካል መቅረብ ካልቻለ፣ ጉዳዩን የሚገልጽ ልዩ ውክልና ከወካይና ተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።
2. የጋብቻ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የጋብቻ ማስረጃ መያዝ።
ለግልባጭ ወይም ለእርማት አገልግሎት፦ የተጋቢዎች ሁለት ሁለት (2) ጉርድ ፎቶግራፍ።
በውክልና የሚጠየቅ ከሆነ (ለእርማት፣ ዕድሳትና ግልባጭ)፦ ባልና ሚስት ጉዳዩን በግልጽ የሚያሳይ ውክልና፣ የወካዮች እና የተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ወይም የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው።
3. የፍቺ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የፍቺ ማስረጃ
የህግ አስገዳጅነቱ የተረጋገጠ የፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
4. የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
በወረዳ የተመዘገበ የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት እና የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰነድ
ጉዲፈቻ አድራጊዎች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በመያዝ በአካል መቅረብ አለባቸው።
ጉዳዩ በውክልና ከሆነ፣ይህንኑ የሚያስረዳ ልዩ ውክልና መቅረብ አለበት።
5. የሞት ማስረጃ ለማረጋገጥ
በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የሞት ማስረጃ የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት
ከሟች ጋር አብሮ ይኖር የነበረ ሰው፣ እርሱ ከሌለ የሟች የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመዶች፣ እነዚህም ከሌሉ የቅርብ ጎረቤት ወይም ስለሟቹ መሞት የሚያውቅ ማንኛውም ሰው የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በማቅረብ ማስመዝገብና ማረጋገጥ ይችላል።
ሟች የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ከሆስፒታል የተሰጠ የማሳወቂያ ወረቀት መቅረብ አለበት።
ማሳሰቢያ፡- ለሁሉም ከላይ ለተዘረዘሩት የኩነት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስፈልግ ደጋፊ ሰነድ
• የታደሰ ብሔራዊ መታወቂያ / የታደሰ ፓስፖርት / የትውልደ ኢትዮጵያ የውጭ ዜግነት መታወቂያ (የቢጫ ካርድ)።
• ከዝቅተኛው አስተዳደር ጽ/ቤት መደበኛ ነዋሪነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ / የስደተኛነት ማስረጃ / የመኖሪያ ፈቃድ።
• ከሚሰራበት መስሪያ ቤት ባልደረባነቱንና ዜግነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ ከመስሪያ ቤቱ መታወቂያ ጋር / የመከላከያ ሰራዊት ከሆነ የመከላከያ ሰራዊት መታወቂያ መያዝ
• የጠፋ ሰርተፍኬት ግልባጭ ለመውሰድ፦ ከፖሊስ የተሰጠ የጠፋ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ግዴታ ነው።
• ከወረዳ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከወረዳው ስለመውጣታቸው የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ያስፈልጋቸዋል።
• ከክፍለ ከተማ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከሰነዱ በስተጀርባ የማረጋገጫ ማህተም ማረፍ ይኖርበታል።
• ከውጭ ሀገር የሚመጣ ውክልና፦ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በፌደራል ሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ መረጋገጥ አለበት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍5
ኢትዮጵያና አይ ኤም ኤፍ (አይኤምኤፍ) የ468 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሱ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል።
ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው።
በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከቀጠናዊ ቀውሶች ጋር ተያይዞ የመጣውን ትልቅ ውጫዊ ጫና በመቋቋም ረገድ ከፍተኛ ጥንካሬ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ፣ ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ አሁንም እያደገ በመምጣቱ በኢኮኖሚው የወደፊት ጉዞ ላይ የሚታዩት ስጋቶች መጨመራቸውን አይ ኤም ኤፍ አስጠንቅቋል።
የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መረጋጋት በዘላቂነት ለማስቀጠልም ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቁልፍ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን የጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን አጠናክሮ መቀጠልን፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ግልጽነትና አሠራር ይበልጥ ማሻሻልን እንዲሁም የአገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን በማጠናከር የወጪ አያያዝን በጥንቃቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል።
ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው።
በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከቀጠናዊ ቀውሶች ጋር ተያይዞ የመጣውን ትልቅ ውጫዊ ጫና በመቋቋም ረገድ ከፍተኛ ጥንካሬ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ፣ ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ አሁንም እያደገ በመምጣቱ በኢኮኖሚው የወደፊት ጉዞ ላይ የሚታዩት ስጋቶች መጨመራቸውን አይ ኤም ኤፍ አስጠንቅቋል።
የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መረጋጋት በዘላቂነት ለማስቀጠልም ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቁልፍ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን የጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን አጠናክሮ መቀጠልን፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ግልጽነትና አሠራር ይበልጥ ማሻሻልን እንዲሁም የአገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን በማጠናከር የወጪ አያያዝን በጥንቃቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስቧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
💔10❤4🤪4👍3🤯1👀1
"በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ምርጫ ሰኔ 2 ይካሄዳል" - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመራጮች ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን እንደሚያካሂድ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በዛሬው ዕለት በሪፖርቱ ጠቅሶት ነበር።
ይህንን አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጡበት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በተለየ ቀን እንደሚካሄድ አረጋግጠዋል።
ሆኖም ህብረቱ "June-8 / ሰኔ 1" ቀን እንደሚካሄድ ሪፖርቱ ቢጠቅስም፥ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ግን ምርጫው በእነዚህ ልዩ ጣቢያዎች የሚካሄደው #ሰኔ_2 መሆኑን ነው የገለጹት።
ይህ የተፈጠረበትን ምክንያትም ቦርዱ ያለበትን የተጨናነቀ ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ውጤቶቹም "በፍጥነት ተጠቃለው መቅረብ የሚችሉ ውጤቶች በመሆናቸው " ነው ሲሉ ቦርዱ ከሌሎች ውጤቶች ጋር አብሮ የሚያቀርባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ካምፖች 28,632 እንዲሁም በሚሊተሪ ካምፖች 126,498 ሺ መራጮች መመዝገባቸው መገለጹ ይታወሳል።
በተጨማሪም ህብረቱ የተጠናቀቀ ውጤት የሚገለጽበትን ቀን በተመለከተ ህብረቱ ሰኔ 4 መሆኑን በሪፖርቱ ጠቅሷል።
የቦርዱ ሰብሳቢ በበኩላቸው ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ቦርዱ ከገጠመው የድምጽ በይፋ የማሳወቅ ሥራ እስከ 20 ቀን የመግፋት መብት እንዳለውም ጠቁመዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመራጮች ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን እንደሚያካሂድ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በዛሬው ዕለት በሪፖርቱ ጠቅሶት ነበር።
ይህንን አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጡበት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በተለየ ቀን እንደሚካሄድ አረጋግጠዋል።
ሆኖም ህብረቱ "June-8 / ሰኔ 1" ቀን እንደሚካሄድ ሪፖርቱ ቢጠቅስም፥ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ግን ምርጫው በእነዚህ ልዩ ጣቢያዎች የሚካሄደው #ሰኔ_2 መሆኑን ነው የገለጹት።
ይህ የተፈጠረበትን ምክንያትም ቦርዱ ያለበትን የተጨናነቀ ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ውጤቶቹም "በፍጥነት ተጠቃለው መቅረብ የሚችሉ ውጤቶች በመሆናቸው " ነው ሲሉ ቦርዱ ከሌሎች ውጤቶች ጋር አብሮ የሚያቀርባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ካምፖች 28,632 እንዲሁም በሚሊተሪ ካምፖች 126,498 ሺ መራጮች መመዝገባቸው መገለጹ ይታወሳል።
በተጨማሪም ህብረቱ የተጠናቀቀ ውጤት የሚገለጽበትን ቀን በተመለከተ ህብረቱ ሰኔ 4 መሆኑን በሪፖርቱ ጠቅሷል።
የቦርዱ ሰብሳቢ በበኩላቸው ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ቦርዱ ከገጠመው የድምጽ በይፋ የማሳወቅ ሥራ እስከ 20 ቀን የመግፋት መብት እንዳለውም ጠቁመዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪8❤6👍3
ኢዜማ፣ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን በንጹሃን ላይ ለተፈጸመው ጥቃት መንግሥት አስፈላጊውን ማጣራት አድርጎ ኃላፊነት የሚወስዱ አካላትን በመለየት "ሕጋዊ የእርምት እርምጃ" እንዲወስድ ጠየቀ።
ፓርቲው፣ "ማንነትን" ወይም "ኃይማኖትን" መሠረት ባደረገ ጥቃት በርካታ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የኾኑ ዜጎች ለጊዜው "ማንነቱ ባልታወቀ" አካል እንደተገደሉ፣ ቤተክርስቲያን እንደተቃጠለና ከጥቃቱ የሸሹ ነዋሪዎች ከቀያቸው እንደተሠደዱ መረዳቱን ገልጧል።
ለዚህ ዐይነቱ "ማንነትን መሠረት" ያደረገ ጥቃት ምንጬ የአገሪቱ ፖለቲካ "በማንነት ላይ የተመሠረተ" መኾኑ ነው ያለው ፓርቲው፣ በማንነት ላይ የተመሠረተው ፖለቲካ መፍትሔ እንዲበጀለት የኹሉም ባለድርሻ አካላት የቤት ሥራ መኾኑን አጽንዖት ሠጥቷል።
ኢዜማ፣ በምስራቅ አርሲ ዞን ውስጥ በንጹሃን ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በመከላከል ረገድ የአካባቢው አስተዳደርና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በተደጋጋሚ ተፈትነው ወድቀዋል በማለት ተችቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ፓርቲው፣ "ማንነትን" ወይም "ኃይማኖትን" መሠረት ባደረገ ጥቃት በርካታ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የኾኑ ዜጎች ለጊዜው "ማንነቱ ባልታወቀ" አካል እንደተገደሉ፣ ቤተክርስቲያን እንደተቃጠለና ከጥቃቱ የሸሹ ነዋሪዎች ከቀያቸው እንደተሠደዱ መረዳቱን ገልጧል።
ለዚህ ዐይነቱ "ማንነትን መሠረት" ያደረገ ጥቃት ምንጬ የአገሪቱ ፖለቲካ "በማንነት ላይ የተመሠረተ" መኾኑ ነው ያለው ፓርቲው፣ በማንነት ላይ የተመሠረተው ፖለቲካ መፍትሔ እንዲበጀለት የኹሉም ባለድርሻ አካላት የቤት ሥራ መኾኑን አጽንዖት ሠጥቷል።
ኢዜማ፣ በምስራቅ አርሲ ዞን ውስጥ በንጹሃን ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በመከላከል ረገድ የአካባቢው አስተዳደርና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በተደጋጋሚ ተፈትነው ወድቀዋል በማለት ተችቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤32👍9🤪9😡5🙏2👏1💯1
ሕወሃት አዲስ አውዳሚ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበ።
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20🤪11😡9👍4😁2🥰1👏1🕊1
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ስርጭት
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል።
እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል።
የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።
በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴሊሺየስ በላይ ይሆናል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል።
እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል።
የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።
በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴሊሺየስ በላይ ይሆናል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍3