አዲስ ሪፖርተር - NEWS
35.8K subscribers
16.9K photos
414 videos
21 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
ኢራን ሚሳይል ተኮሰች‼️
ኢራን ኩዌት ወደ ሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ባሊስቲክ ሚሳኤል አስወነጨፈች።

በጥቃቱ ቢያንስ 5 አሜሪካውያን እንደቆሰሉ ብሉምበርግ ዘግቧል።
ሁለት ሪፐር ሰው አልባ አውሮፕላኖች ክፉኛ ተጎድተዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
25👍3🤔3😱1
ካናዳዊዉ ራፐር ድሬክ አርሰናል ፒኤስጂን ያሸንፋል ብሎ 1.5 ሚሊዮን ዶላር አስይዟል

ከአለማችን እዉቅ ራፐሮች አንዱ የሆነዉ ካናዳዊዉ ድምጻዊ ድሬክ አርሰናል የምሽቱን የአዉሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂን ረትቶ ሻምፒዮን ይሆናል ሲል 1.5 ሚሊዮን ዶላር ማስያዙ ተዘግቧል።

ድሬክ 1 ሚሊዮን ዶላሩን በቀጥታ አርሰናል የምሽቱን ፍጻሜ ያሸንፋል ፣ እንዲሁም ቡካዮ ሳካ አሲስት ወይም ግብ ያስቆጥራል ብሎ ያስያዘዉ ሲሆን ቀሪዉን 500 ሺህ ዶላር ደግሞ አርሰናል ጨዋታዉን 1 ለ 0 ያሸንፋል ሲል መድቦበታል።

ድሬክ ከዚህ ቀደም በስፖርታዊ ዉርርዶቹ ቀንቶት አያዉቅም ይባላል። እርሱ በተደጋጋሚ ያሸንፋሉ ብሎ ገንዘቡን ያስያዘባቸዉ ክለቦች ድል ሲቀናቸዉ አልታየም።

በ 2022 አርሰናል ሊድስን ያሸንፋል ብሎ አስይዞ ድል ቀንቶት የነበረ ቢሆንም በተመሳሳይ ትኬት ግን ባርሴሎና ሪያልማድሪድን ያሸንፋል ብሎ አስይዞ ባርሳ ተረትቶ ነበር። በተለያዩ የቦክስ ጨዋታዎችም ድሬክ በመቶሺዎች ያስያዘበት ተጨዋች በተደጋጋሚ ሲረታ እንጂ ሲያሸንፍ አልታየም።

ብዙሃኑ የስፖርት አፍቃሪያኖችም "የድሬክ እርግማን" ሲሉ ሽንፈቱን ይጠሩታል። ድሬክ ገንዘብ ያስያዘበት ቡድን ይረታል እንደማለት ነዉ። ዛሬስ ድሬክ አርሰናል አሸንፎለት ይህንን እርግማኑን ያስነሳ ይሆን የሚለዉ ጥያቄ በቡዳፔስት ምሽት 1 ሰዓት ላይ የሚጀምረው ጨዋታ ሲጠናቀቅ ምላሽ ያገኛል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
28🤣14💔7👍2
ፒኤስጂ 1-1 አርሰናል

ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ደቂቃ አምርቷል !

የአርሰናል እና ፒኤስጂ ጨዋታ በመደበኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።

ይህንንም ተከትሎ ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ሰላሳ ደቂቃ አምርቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍128🤪5🤯3👏1😁1😢1🙏1👌1🏆1
ፒኤስጂ በመለያ ምት አርሰናልን አሸንፎ በድጋሚ የአዉሮፓ ሻምፒዮን ሆኗል። አርሰናል አሳዛኝ ተሸናፊ ነዉ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣36👍159👀2👏1😁1🙊1😡1
ሙሉ የተሽከርካሪ እገዳ ተጣለ‼️

በጋምቤላ ክልል ከነገ ጧት ጀምሮ በክልሉ የሚገኙ ማንኛውም ተሽከርካሪ እንቅስቃሴ የማይፈቀድና የተከለከለ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቀ።

ከነገ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከጧት ጀምሮ እስከ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ የተለየ የይለፍ ፊቃድ ካልተሰጠው በስተቀር ማንኛውም የመንግሥት፣ የንግድ እና የግል ተሽከርካሪዎች፣ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች/ባጃጅ እና ሞተር ሳይክል በሙሉ እንቅስቃሴ እንዲያቆሙ የተወሰነ ሲሆን ይህንን መመሪያ ተግባራዊ በማያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ የሆነ ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድባቸው መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር አቶ ዶሮ ካሩ አሳስበዋል።

ከነገ ግንቦት 23 ቀን 2018 እስከc ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም
በልዩነት የተፈቀደላቸው  ለድንገተኛ ሥራ (Emergency) ብቻ የሚንቀሳቀሱ የመብራት ኃይል፣ የቴሌኮሙኒኬሽን እና አምቡላንሶች ሲሆን የይለፍ ወረቀት መያዝና ሲጠየቅ የማሳየት ኃላፊነትና ግዴታ  እንዳለባቸውም ተገልጿል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
18👍4😡4
ዩቱዩብ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በሚሰሩ ቪዲዮዎች ላይ ዘመቻ ከፈተ።

የዓለም ትልቁ የቪዲዮ ማጋሪያ ፕላትፎርም የሆነው ዩቱዩብ (YouTube)፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም በArtificial Intelligence (AI) አማካኝነት በብዛት የሚመረቱ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ በርካታ ቻናሎችን ሙሉ በሙሉ መሰረዝ መጀመሩ ተሰምቷል።

እንደ አዳዲስ መረጃዎች ዘገባ ከሆነ፤ ከመድረኩ የተሰረዙት እነዚህ ቻናሎች ከመዘጋታቸው በፊት በአጠቃላይ ከ4.7 ቢሊዮን በላይ እይታዎችን (Views) ማሰባሰብ ችለው ነበር።

ዩቱዩብ ይህንን ጠንከር ያለ እርምጃ የወሰደው ተጠቃሚዎችን የሚያሳስቱና ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል፣ ጥራታቸውን ያልጠበቁና ሰዎችን የሚያሰለቹ ይዘቶችን ለመቀነስ እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያውን ታማኝነት እና ትክክለኛነት ለመጠበቅ በማሰብ እንደሆነ ታውቋል።

እነዚህ ቻናሎች ያለምንም የሰው ልጅ ተሳትፎ፣ በኮምፒውተር ፕሮግራሞች ብቻ በጅምላ የሚሰሩ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ ነበሩ።

በአሁኑ ጊዜ የAI መተግበሪያዎች እጅግ በጣም ፈጣን እና ቀላል በሆነ መንገድ በሺዎች የሚቆጠሩ ቪዲዮዎችን በደቂቃዎች ውስጥ ለመፍጠር ያስችላሉ።

ይህ ሁኔታ ደግሞ እንደ ዩቱዩብ ላሉ ትልልቅ የቴክኖሎጂ ተቋማት አዲስ ፈጠራን ከመደገፍ እና የሰዎችን እምነት በአግባቡ ከማስጠበቅ አንፃር ትልቅ የባላንስ ፈተና ሆኖባቸዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👏2623👍9
በፋይዳ ምክንያት የታገዱ የዲያስፖራ ሂሳቦች‼️
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በፋይዳ ምክንያት የታገዱ የዲያስፖራ ሂሳቦች በጊዜያዊነት የሚከፈቱበትን አማራጭ መንገዶችን አሳውቋል።

ባንኩ የፋይዳ መለያ ቁጥርን ከባንክ ሂሳብ ጋር የማያያዝ ሂደት ላይ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል አዲስ ተለዋጭ አሰራር ይፋ ማድረጉን አሳውቋል።

ይህንን ያስታወቀው ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ለኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት በጻፈው ይፋዊ ደብዳቤ ነው።

ባንኩ በላከው መመሪያ መኖሪያቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ ያደረጉ የባንኩ ደንበኞች በጊዜያዊነት ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመር ሳያስፈልጋቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት በልዩ ሁኔታ እየተስተናገዱ መሆኑን ገልጿል።

" በባንካችን በኩል ከዚህ በፊት ደንበኞች ሂሳብ በሚከፍቱበት ወቅት የመኖሪያ አድራሻቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ እንደሆነ ማስረጃ ያቀረቡ እና በባንካችን የመረጃ ቋት ላይ የተመዘገበ ማስረጃ ያላቸው ደንበኞች ሂሳብ ያልታገደ መሆኑን እናሳውቃለን " ብሏል።

በተለያዩ ምክንያቶች ደንበኞች ውጭ እንደሚኖሩ በባንኩ የመረጃ ቋት ላይ ያላስመዘገቡ እና የባንክ ሂሳባቸው የታገደባቸው ደንበኞች ግን ብሔራዊ ባንክ ለባንኩ ባሳወቀው መሰረት ከዚህ በታች በተገለጸው አግባብ መስተናገድ የሚችሉ መሆኑን ገልጿል።

• በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የፋይዳ መለያ ቁጥር ማቅረብ ባይችሉም እንኳ፣ በውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚያረጋግጥ ማስረጃ በማቅረብ የእገዳው አካል እንዳይሆኑ ይደረጋል።  ለዚህም እንደ፦
- የትምህርት ማስረጃ፣
- የህክምና ማስረጃ፣
- የውጭ ሀገር የመኖሪያ ፍቃድ (Residence Permit/ID)
- በህጋዊ አካል የተረጋገጠ በውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚገልጽ የውክልና ማስረጃ (በህጋዊ ወኪሎቻቸው በኩል) በማቅረብ ሂሳባቸውን ማንቀሳቀስ ይችላሉ።

• ዲፕሎማቶችን በተመለከተ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ መታወቂያቸውን በማሳየት ወይም ሂሳቡ የተከፈተው በዲፕሎማት መታወቂያ ከሆነ የእገዳው አካል ሳይሆኑ ሂሳባቸውን መጠቀም እንደሚችሉ ተገልጿል።

• አንድ ደንበኛ በውጭ ሀገር እንደሚኖር በሚመለከተው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ በኩል በኢሜል ማረጋገጫ ከተላከ፣ ባንኩ በጊዜያዊነት የጣለውን እገዳ አንስቶ ደንበኛው ሂሳቡን እንዲጠቀም ይፈቅዳል።

ደንበኞች ውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚያረጋግጡ ማስረጃዎችን ሂሳባቸው ለተከፈተበት ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ኢሜል ወይም በባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ለሚገኘው የዲያስፖራ ባንኪንግ ክፍል DiasporaBanking@cbe.com.et በመላክ የተጣለባቸው እገዳ በጊዜያዊነት እንዲነሳ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል።

ይህ መመሪያ በተባበሩት አረብ ኤምሬተስ ለሚኖሩ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ መመዝገብ የሚቻል በመሆኑ መመሪያው የማይመለከታቸው መሆኑን ባንኩ ገልጿል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
10👍3
ሰበር :-

የአርሰናል እና የፔዤን ጨዋታ እያዩ የነበሩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የቦምብ ተፈፀመባቸው

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት በተከሰተ የቦምብ ፍንዳታ የተማሪዎች ህይወት ማለፉና በርካቶች መቁሰላቸው ተሰምቷል፡፡

አደጋው የተከሰተው ተማሪዎች በካምፓሱ አዳራሽ ውስጥ ተጨናንቀው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የእግር ኳስ ጨዋታን በፕሮጀክተር እየተከታተሉ በነበረበት ወቅት እንደሆነ ተገልጿል።

ከተማሪዎችና ከአካባቢው ነዋሪዎች በተገኘ መረጃ መሠረት፣ በፍንዳታው ሳቢያ በትንሹ የሁለት ተማሪዎች ህይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን፤ የሟቾች ቁጥር እስከ 3 ሊደርስ እንደሚችል ተጠቁሟል።

ህይወታቸው ያለፈው ተማሪዎች አስክሬን ዛሬ ጠዋት ወደ ቤተሰቦቻቸው ተሸኝቷል።

በተጨማሪም ከ30 በላይ ተማሪዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን፤ ተጎጂዎቹ በካምፓሱ ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።

ፍንዳታው በተከሰተበት ወቅት በአዳራሹ ውስጥ ከፍተኛ የሰው ቁጥር በመኖሩና በመግቢያና መውጫዎች ላይ በተፈጠረው መረጋገጥ ሳቢያ የጉዳቱ መጠን ሊጨምር እንደቻለ የዓይን እማኞች ገልጸዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
19😢16💔6👍5😱4🤯1👀1
ደቡብ ሱዳን በድንበሯ ላይ የተገነባውን
የግብፅ ጦር ሠፈር እንዲዘጋ  አዘዘች

የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግብፅ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው የላይኛው ናይል ግዛት ፓጋክ አካባቢ ያቋቋመችውን ወታደራዊ ጦር ሠፈር በአስቸኳይ እንድትዘጋ ማዘዙን የዓረብኛ የዜና ምንጮች በሰፊው ዘግበዋል።

ይህ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ የተገነባውና ወታደራዊ ሥልጠና የመስጠት እንዲሁም የናይል ወንዝ ፍሰትን የመቆጣጠር ስውር ዓላማ የነበረው ጦር ሠፈር፣ የሥልጠና ባለሙያዎችን ጨምሮ 260 የሚያህል የሰው ኃይል አሰማርቶ የነበረ መሆኑ ታውቋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
13👍5🤪4😢3👏2
ነገ ኢትዮጵያ ትመርጣለች

በፓርቲዎች ስም 10 ሺህ 437 ዕጩዎች እንዲሁም 80 የግል ተወዳዳሪዎች  ለመመረጥ ተዘጋጅተዋል

42 የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰኞው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደሩ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቋል

ቦርዱ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።

የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 057 ሺህ 871 መራጮች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ በፓርቲዎች ስም 10 ሺህ 437 ዕጩዎች እንዲሁም 80 የግል ተወዳዳሪዎች ለምርጫ መቅረባቸውን ይፋ አድርገዋል።

ቦርዱ የምርጫ ቁሳቁሶችን ሙሉ በሙሉ ማድረሱን፣ የዜጎችን ግንዛቤ ለማሳደግ በ5 ቋንቋዎች 19 የሕዝብ ክርክሮችን ማደራጀቱንና ከ250 ሺህ በላይ የታዛቢዎች ባጅ ማሰራጨቱን ሰብሳቢዋ ገልፀዋል።
 
ምርጫውን የአፍሪካ ኅብረት፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት እና የሀገር ውስጥ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ይታዘባሉ።
 
በምርጫ ቦርድ የግዜ ሠለዳ መሠረት የድምጽ ውጤት ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣2410👍5😢3🤪3
የዓሳ ቆዳ ለቃጠሎ ህክምና፤ በብራዚል ሐኪሞች የተገኘው አስደናቂና አነስተኛ ወጪ የሚጠይቅ ፈውስ
 
በብራዚል የሚገኙ ተመራማሪዎችና የሕክምና ባለሙያዎች በከባድ የእሳት ቃጠሎ የተጎዱ ሰዎችን ለማከም ልዩ በሆነ ዘዴ የተዘጋጀ የዓሳ ቆዳን በመጠቀም አስደናቂ ስኬት እያስመዘገቡ ይገኛሉ። ይህ አዲስ የሕክምና ፈጠራ የተጎጂዎችን ስቃይ በከፍተኛ ሁኔታ ከመቀነሱም በላይ የሕክምና ወጪን በግማሽ ያህል ያቀለለ መሆኑ ተገልጿል።
 
የሴአራ ፌደራል ዩኒቨርሲቲ (Federal University of Ceará) ተመራማሪዎች እንዳረጋገጡት፣ የቲላፒያ ዓሳ ቆዳ ለሰው ልጅ ቆዳ መፈወስ እጅግ አስፈላጊ የሆኑትን ‘ታይፕ 1’ ኮላጅን (Collagen) የተሰኙ ፕሮቲኖችን እና ከፍተኛ እርጥበትን በውስጡ ይዟል። ይህም የቆሰለው አካል በፍጥነት እንዲያገግም እና ከበሽታ አምጪ ተህዋስያን እንዲጠበቅ ያደርገዋል ብለዋል።
 
ቀደም ሲል በብራዚል የቆዳ ባንኮች እጥረት በመኖሩ ምክንያት ለቃጠሎ ተጎጂዎች የሚደረገው መደበኛ ሕክምና በየቀኑ የሚቀያይር ፋሻ እና የቃጠሎ ክሬም በመጠቀም የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም ለታካሚዎቹ ከፍተኛ ስቃይ የሚፈጥር ነበር።
 
አዲሱ የቲላፒያ ቆዳ ሕክምና ግን አንዴ ከቆሰለው አካል ላይ ከተለጠፈ በኋላ በተፈጥሮ እስኪላጥ ድረስ ለቀናት የሚቆይ በመሆኑ፣ ፋሻ በየቀኑ የመቀየርን ስቃይ ሙሉ በሙሉ ያስቀረና ፈውስን የሚያፋጥን ሆኗል። የወጪው መቶኛም ከመደበኛው ሕክምና ጋር ሲነጻጸር እስከ 50 በመቶ ቅናሽ አለው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
11👍8🤔2👏1