ከ54 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ54 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ።
ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ዙሪያ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት፤ ለምርጫው 54 ሚሊየን 571 ሺህ 871 መራጮች ተመዝግበዋል።
የምርጫውን ሂደት የአፍሪካ ህብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ልዑካን እንደሚታዘቡ ገልጸዋል።
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ54 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ።
ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ዙሪያ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት፤ ለምርጫው 54 ሚሊየን 571 ሺህ 871 መራጮች ተመዝግበዋል።
የምርጫውን ሂደት የአፍሪካ ህብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ልዑካን እንደሚታዘቡ ገልጸዋል።
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😁16❤6🤪4👍2😢2
በአራት አመት ውስጥ 7,400 ግጭቶች‼️
የአልጀዚራ የግጭት መቆጣጠሪያ እንደሚያሳየው ከ Janurary 2022 እስከ may 15/2026 ድረስ በኢትዮጵያ በመላ አገሪቱ ከ7,400 በላይ ግጭቶች ተመዝግበዋል።
ከግጭቶቹ ከግማሽ በላይ (3,719)
በአማራ ክልል በፋኖ እና በመንግሥት የፀጥታ ሀይሎች ጭምር የተመዘገቡ ናቸው።
በኦሮሚያ ክልል 2,735 ግጭቶች የተመዘገቡት በ OLA በሚመራው የትጥቅ አመጽ እና ከተለያዩ የጋራ ግጭቶች ጎን ለጎን ነው። ሌሎች ክልሎችም አለመረጋጋት አጋጥሟቸዋል፣ በትግራይ ክልል 262 ግጭቶች ሲመዘገቡ፣ በምዕራብ ጋምቤላ ክልል ደግሞ 144 ግጭቶች ተመዝግበዋል።
ከላይ ያለው ካርታ ባለፉት አራት አመታት ውስጥ በመላ ሀገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች የተፈፀሙ አጠቃላይ ግጭቶች መሆኑን አልጀዚራ ይፋ አድርጓል። (ayu)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአልጀዚራ የግጭት መቆጣጠሪያ እንደሚያሳየው ከ Janurary 2022 እስከ may 15/2026 ድረስ በኢትዮጵያ በመላ አገሪቱ ከ7,400 በላይ ግጭቶች ተመዝግበዋል።
ከግጭቶቹ ከግማሽ በላይ (3,719)
በአማራ ክልል በፋኖ እና በመንግሥት የፀጥታ ሀይሎች ጭምር የተመዘገቡ ናቸው።
በኦሮሚያ ክልል 2,735 ግጭቶች የተመዘገቡት በ OLA በሚመራው የትጥቅ አመጽ እና ከተለያዩ የጋራ ግጭቶች ጎን ለጎን ነው። ሌሎች ክልሎችም አለመረጋጋት አጋጥሟቸዋል፣ በትግራይ ክልል 262 ግጭቶች ሲመዘገቡ፣ በምዕራብ ጋምቤላ ክልል ደግሞ 144 ግጭቶች ተመዝግበዋል።
ከላይ ያለው ካርታ ባለፉት አራት አመታት ውስጥ በመላ ሀገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች የተፈፀሙ አጠቃላይ ግጭቶች መሆኑን አልጀዚራ ይፋ አድርጓል። (ayu)
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14😢7👍2
መረጃ‼️
የአፍሪካ ልማት ባንክ፣ ከአውሮፓውያኑ 2010 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ለኢትዮጵያ በኢንዱስትሪ ልማት ከአፍሪካ 54 አገራት መካከል 31ኛ ደረጃ ሠጣት።
በተጠቀሠው የ15 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ባንኩ ለኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት የሠጠው ነጥብ፣ ከ0 ነጥብ 47 ወደ 0 ነጥብ 52 አድጓል።
አገሪቱ በመካከለኛ የኢንዱስትሪ ልማት ደረጃ ላይ እንድትወሠን አስተዋጽኦ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል፣ ዋነኛው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፏ ደካማ አፈጻጸም እንደኾነ ሪፖርቱ ጠቅሷል።
ባንጻሩ፣ አገሪቱ በኢንቨስትመንት፣ መሠረተ ልማት እና የሰው ሀብት ልማት መካከለኛ ውጤት አስመዝግባለች።
ሞሮኮ፣ ደቡብ አፍሪካን በመቅደም በአፍሪካ ግንባር ቀደም በኢንዱስትሪ ልማት በከፍተኛ ደረጃ ያደገች አገር መኾኗን ሪፖርቱ አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአፍሪካ ልማት ባንክ፣ ከአውሮፓውያኑ 2010 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ለኢትዮጵያ በኢንዱስትሪ ልማት ከአፍሪካ 54 አገራት መካከል 31ኛ ደረጃ ሠጣት።
በተጠቀሠው የ15 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ባንኩ ለኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት የሠጠው ነጥብ፣ ከ0 ነጥብ 47 ወደ 0 ነጥብ 52 አድጓል።
አገሪቱ በመካከለኛ የኢንዱስትሪ ልማት ደረጃ ላይ እንድትወሠን አስተዋጽኦ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል፣ ዋነኛው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፏ ደካማ አፈጻጸም እንደኾነ ሪፖርቱ ጠቅሷል።
ባንጻሩ፣ አገሪቱ በኢንቨስትመንት፣ መሠረተ ልማት እና የሰው ሀብት ልማት መካከለኛ ውጤት አስመዝግባለች።
ሞሮኮ፣ ደቡብ አፍሪካን በመቅደም በአፍሪካ ግንባር ቀደም በኢንዱስትሪ ልማት በከፍተኛ ደረጃ ያደገች አገር መኾኗን ሪፖርቱ አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7😢7👍2🙊2
የፋይዳ መታወቂያ የተመዘገበን ስልክ ቁጥር በአካል እና በኢንተርኔት መቀየር የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱ ተገለጸ
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የፋይዳ መታወቂያ ያወጡበት ስልክ ቁጥር በተለያየ ምክንያት እጃቸው ላይ የሌለ ዜጎች በሌላ ስልክ ቁጥር እንዲቀይሩ እድል የሚሰጥ አሰራር መኖሩን አስታውቋል።
አሰራሩ የተዘረጋው ፋይዳ መታወቂያ የወሰዱበትን ስልክ ቁጥር ማግኘት ባለመቻላቸው የባንክ ሂሳብ ማንቀሳቀስን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን ማግኘት ለተቸገሩ ዜጎች ምላሽ ለመስጠት ነው ተብሏል።
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላት እና የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሳሚናስ ሰይፉ ለአሐዱ ሬድዮ እንደገለጹት፤ መረጃውን የምዝገባ ማሽኖች ባሉባቸው ጣቢያዎች በመገኘት ስልክ ቁጥር መቀየር እንደሚቻል ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት የበርካታ ሰዎች ስልክ ቁጥር፣ የስም እና የልደት ዘመን መረጃዎች በመሳሳታቸው ይስተካከልልን የሚል ጥያቄ በመቅረቡ የማስተካከል ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
መታወቂያቸው ላይ ያስመዘገቡትን ስልክ ቁጥር ማግኘት ለሚቸገሩ ዜጎች ሁለት አማራጮች መዘጋጀታቸውን ዳይሬክተሩ ለአሐዱ ገልጸዋል።
የመጀመሪያው አማራጭ ነዋሪዎች የቀድሞውን ስልክ ቁጥራቸውን ማግኘት የሚችሉ ከሆነ በራሳቸው የተቋሙ ድረ-ገጽ ውስጥ በመግባት መቀየር የሚችሉበት ነው ተብሏል።
ሁለተኛው አማራጭ ደግሞ የተመዘገቡበትን ስልክ ቁጥር ሙሉ በሙሉ ማግኘት ለማይችሉ ዜጎች የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል።
እነዚህ ወገኖች የፋይዳ ምዝገባ ማሽኖች ወደሚገኙባቸው ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ማስተካከል እንደሚችሉ አቶ ሳሚናስ ሰይፉ አስታውቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የፋይዳ መታወቂያ ያወጡበት ስልክ ቁጥር በተለያየ ምክንያት እጃቸው ላይ የሌለ ዜጎች በሌላ ስልክ ቁጥር እንዲቀይሩ እድል የሚሰጥ አሰራር መኖሩን አስታውቋል።
አሰራሩ የተዘረጋው ፋይዳ መታወቂያ የወሰዱበትን ስልክ ቁጥር ማግኘት ባለመቻላቸው የባንክ ሂሳብ ማንቀሳቀስን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን ማግኘት ለተቸገሩ ዜጎች ምላሽ ለመስጠት ነው ተብሏል።
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላት እና የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሳሚናስ ሰይፉ ለአሐዱ ሬድዮ እንደገለጹት፤ መረጃውን የምዝገባ ማሽኖች ባሉባቸው ጣቢያዎች በመገኘት ስልክ ቁጥር መቀየር እንደሚቻል ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት የበርካታ ሰዎች ስልክ ቁጥር፣ የስም እና የልደት ዘመን መረጃዎች በመሳሳታቸው ይስተካከልልን የሚል ጥያቄ በመቅረቡ የማስተካከል ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
መታወቂያቸው ላይ ያስመዘገቡትን ስልክ ቁጥር ማግኘት ለሚቸገሩ ዜጎች ሁለት አማራጮች መዘጋጀታቸውን ዳይሬክተሩ ለአሐዱ ገልጸዋል።
የመጀመሪያው አማራጭ ነዋሪዎች የቀድሞውን ስልክ ቁጥራቸውን ማግኘት የሚችሉ ከሆነ በራሳቸው የተቋሙ ድረ-ገጽ ውስጥ በመግባት መቀየር የሚችሉበት ነው ተብሏል።
ሁለተኛው አማራጭ ደግሞ የተመዘገቡበትን ስልክ ቁጥር ሙሉ በሙሉ ማግኘት ለማይችሉ ዜጎች የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል።
እነዚህ ወገኖች የፋይዳ ምዝገባ ማሽኖች ወደሚገኙባቸው ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ማስተካከል እንደሚችሉ አቶ ሳሚናስ ሰይፉ አስታውቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤29👍4👏1👌1
የእንግሊዝ መንግሥት የስደተኞችን ዕድሜ ለመለየት የኤአይ ቴክኖሎጂ ሊጠቀም ነው።
የእንግሊዝ መንግሥት በድንበር ላይ ያሉ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ዕድሜ በኤአይ (AI) ለመለየት የሚያስችል ቴክኖሎጂ አስጀምራለሁ ብሏል።
ቴክኖሎጂው በድንበር ላይ የተነሱ ፎቶግራፎችን በመተንተን የሰውን ዕድሜ የሚመረምር ሲሆን ከዚህ ቀደም ለዚሁ አገልግሎት ሥራ ላይ ከዋሉ የሰነድ ምርመራ እና የህክምና ምርመራዎች (ኤክስ-ሬይ እና ኤም.አር.አይ) የሚያግዝ ተጨማሪ አማራጭ ነው ተብሏል።
መረጃዎች እንደሚያሳዩት እ.ኤ.አ እስከ መጋቢት 2026 ባለው መረጃ መሠረት ከ6,400 በላይ ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ እንግሊዝ ህጻን ነን ብለው በማቅረባቸው ዕድሜያቸው ተጣርቷል። ከእነዚህ ውስጥ 43 በመቶ የሚሆኑት አዋቂዎች መሆናቸው ተረጋግጧል።
የቴክኖሎጂው ዝግጅት እና የሶስት ዓመት የሙከራ ጊዜ በድምሩ 322,000 ፓውንድ ወጪ እንደሚጠይቅ ሲሆን የሙከራ ሂደቱ በሚቀጥለው ዓመት ይጀምራል ተብሏል።
የአገሪቱ የድንበር ደኅንነት እና ጥገኝነት ሚኒስትር አሌክስ ኖሪስ፣ አዋቂዎች የሐሰት ዕድሜ በመጥቀስ ሥርዓቱን መበዝበዛቸው ለህጻናት መድረስ የነበረበትን ድጋፍ እያስተጓጎለ መሆኑን በመጥቀስ፣ ቴክኖሎጂውን መጠቀም አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸዋል።
Source : BBC
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የእንግሊዝ መንግሥት በድንበር ላይ ያሉ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ዕድሜ በኤአይ (AI) ለመለየት የሚያስችል ቴክኖሎጂ አስጀምራለሁ ብሏል።
ቴክኖሎጂው በድንበር ላይ የተነሱ ፎቶግራፎችን በመተንተን የሰውን ዕድሜ የሚመረምር ሲሆን ከዚህ ቀደም ለዚሁ አገልግሎት ሥራ ላይ ከዋሉ የሰነድ ምርመራ እና የህክምና ምርመራዎች (ኤክስ-ሬይ እና ኤም.አር.አይ) የሚያግዝ ተጨማሪ አማራጭ ነው ተብሏል።
መረጃዎች እንደሚያሳዩት እ.ኤ.አ እስከ መጋቢት 2026 ባለው መረጃ መሠረት ከ6,400 በላይ ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ እንግሊዝ ህጻን ነን ብለው በማቅረባቸው ዕድሜያቸው ተጣርቷል። ከእነዚህ ውስጥ 43 በመቶ የሚሆኑት አዋቂዎች መሆናቸው ተረጋግጧል።
የቴክኖሎጂው ዝግጅት እና የሶስት ዓመት የሙከራ ጊዜ በድምሩ 322,000 ፓውንድ ወጪ እንደሚጠይቅ ሲሆን የሙከራ ሂደቱ በሚቀጥለው ዓመት ይጀምራል ተብሏል።
የአገሪቱ የድንበር ደኅንነት እና ጥገኝነት ሚኒስትር አሌክስ ኖሪስ፣ አዋቂዎች የሐሰት ዕድሜ በመጥቀስ ሥርዓቱን መበዝበዛቸው ለህጻናት መድረስ የነበረበትን ድጋፍ እያስተጓጎለ መሆኑን በመጥቀስ፣ ቴክኖሎጂውን መጠቀም አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸዋል።
Source : BBC
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13👍4
ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ኮንጎ ገቡ
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ቴዎድሮስ በኢቦላ ወረርሽኝ በተጠቃችው ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አቅንተዋል።
ሀገሪቱ የተከሰተውን ወረርሽኝ ለመከላከል እየወሰደች ያለውን እርምጃ ይገመግማሉ ተብሏል።
በኢቦላ ሳቢያ 238 ሰዎች ሲሞቱ 1,077 ደግሞ መጠቃታቸው ተገልጿል። #npr
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ቴዎድሮስ በኢቦላ ወረርሽኝ በተጠቃችው ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አቅንተዋል።
ሀገሪቱ የተከሰተውን ወረርሽኝ ለመከላከል እየወሰደች ያለውን እርምጃ ይገመግማሉ ተብሏል።
በኢቦላ ሳቢያ 238 ሰዎች ሲሞቱ 1,077 ደግሞ መጠቃታቸው ተገልጿል። #npr
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17🥰3👍2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ነዳጅ በባቡር ኤክስፖርት‼️
አሜሪካ በኢራን ላይ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ምክንያት ኢራን ነዳጇን ወደ ቻይና እና ፓኪስታን በባቡር መስመር መላክ ጀመረች።
አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችው እገዳ 50 ቀናትን አስቆጥሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አሜሪካ በኢራን ላይ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ምክንያት ኢራን ነዳጇን ወደ ቻይና እና ፓኪስታን በባቡር መስመር መላክ ጀመረች።
አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችው እገዳ 50 ቀናትን አስቆጥሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤23👍10
#RemedialExamSchedule
የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል (አቅም ማሻሻያ) ፕሮግራም ፈተና ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም ለአምስት ቀናት እንደሚሰጥ ይታወቃል።
በተጠቀሱት ቀናት በሁለት ፈረቃ በጠዋት እና በከሰዓት መርሐግብር የሚሰጠው የሪሚዲያል ፕሮግራም (የተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች) የፈተና መርሐግብር ከላይ ተያይዟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል (አቅም ማሻሻያ) ፕሮግራም ፈተና ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም ለአምስት ቀናት እንደሚሰጥ ይታወቃል።
በተጠቀሱት ቀናት በሁለት ፈረቃ በጠዋት እና በከሰዓት መርሐግብር የሚሰጠው የሪሚዲያል ፕሮግራም (የተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች) የፈተና መርሐግብር ከላይ ተያይዟል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤8👍2
ለችግሩ ባንኩ ምላሽ ሰጥቷል‼️
የተሻሻለውን የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ሲያዘምኑ 'Passphrase' ጠይቆዎት ከነበረ ወደ አቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ በመሄድ አገልግሎቱን እንደገና በቀላሉ አስጀምረው መጠቀም የሚችሉ መሆኑን አስታውቋል።
መተግበሪያውን እስኪያስተካከሉ ድረስ አገልግሎቱን በ USSD *889# በኩል እንዲጠቀሙ በአክብሮት ገልጿል።
ከሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ጋር በተያያዘ በስልክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም አይነት የአሰራር ሂደት የሌለ መሆኑን በመረዳት እራስዎን ከአጭበርባሪዎች ይጠብቁ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የተሻሻለውን የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ሲያዘምኑ 'Passphrase' ጠይቆዎት ከነበረ ወደ አቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ በመሄድ አገልግሎቱን እንደገና በቀላሉ አስጀምረው መጠቀም የሚችሉ መሆኑን አስታውቋል።
መተግበሪያውን እስኪያስተካከሉ ድረስ አገልግሎቱን በ USSD *889# በኩል እንዲጠቀሙ በአክብሮት ገልጿል።
ከሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ጋር በተያያዘ በስልክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም አይነት የአሰራር ሂደት የሌለ መሆኑን በመረዳት እራስዎን ከአጭበርባሪዎች ይጠብቁ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17👍2🤣1
በደሴ ከተማ የውሻ እብደት በሽታ አሳሳቢ የማህበረሰብ ችግር እየሆነ መምጣቱ ተገለፀ
ባለፋት ዘጠኝ ወራት ውስጥ የውሻ ንክሻ ላጋጠማቸው ከ3መቶ በላይ ለሆኑ ሰዎች ህክምና መስጠቱን የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታውቋል፡፡
የሆስፒታሉ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ አቶ ብርሃኑ አዱኛ ከብስራት ሬድዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት አሁን ላይ የውሻ እብደት በሽታ አሳሳቢ የማኅበረሰብ ችግር እየሆነ ይገኛል።
ባለፋት ዘጠኝ ወራት በሆስፒታሉ ለ3 መቶ 3 የእብድ ውሻ ንክሻ ተጠርጣሪዎች እና ለ172 የኬሚካል መመረዝ ላጋጠማቸው ሰዎች ህክምና መሰጠቱን አስረድተዋል።
በደሴ ከተማ 34.3 በመቶ፣ በደቡብ ወሎ 29.4 በመቶ እንዲሁም በሰሜን ወሎ 21.5 በመቶ የሆነ ከፍተኛ የእብድ ውሻ ንክሻ ስርጭት ተመዝግቧል።
ግኝቱ በአካባቢው በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች የእብድ ውሻ ንክሻ በሽታ ስርጭት መስፋፋቱን የሚያሳይ መሆኑን አቶ ብርሀኑ ጠቅሰው ይህም በክልሉ እየጨመረ ያለውን የህብረተሰብ ጤና ስጋት አጉልቶ እንደሚሳይ ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል ።Via_dagu
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ባለፋት ዘጠኝ ወራት ውስጥ የውሻ ንክሻ ላጋጠማቸው ከ3መቶ በላይ ለሆኑ ሰዎች ህክምና መስጠቱን የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታውቋል፡፡
የሆስፒታሉ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ አቶ ብርሃኑ አዱኛ ከብስራት ሬድዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት አሁን ላይ የውሻ እብደት በሽታ አሳሳቢ የማኅበረሰብ ችግር እየሆነ ይገኛል።
ባለፋት ዘጠኝ ወራት በሆስፒታሉ ለ3 መቶ 3 የእብድ ውሻ ንክሻ ተጠርጣሪዎች እና ለ172 የኬሚካል መመረዝ ላጋጠማቸው ሰዎች ህክምና መሰጠቱን አስረድተዋል።
በደሴ ከተማ 34.3 በመቶ፣ በደቡብ ወሎ 29.4 በመቶ እንዲሁም በሰሜን ወሎ 21.5 በመቶ የሆነ ከፍተኛ የእብድ ውሻ ንክሻ ስርጭት ተመዝግቧል።
ግኝቱ በአካባቢው በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች የእብድ ውሻ ንክሻ በሽታ ስርጭት መስፋፋቱን የሚያሳይ መሆኑን አቶ ብርሀኑ ጠቅሰው ይህም በክልሉ እየጨመረ ያለውን የህብረተሰብ ጤና ስጋት አጉልቶ እንደሚሳይ ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል ።Via_dagu
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍2
ኢራን ሚሳይል ተኮሰች‼️
ኢራን ኩዌት ወደ ሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ባሊስቲክ ሚሳኤል አስወነጨፈች።
በጥቃቱ ቢያንስ 5 አሜሪካውያን እንደቆሰሉ ብሉምበርግ ዘግቧል።
ሁለት ሪፐር ሰው አልባ አውሮፕላኖች ክፉኛ ተጎድተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ኢራን ኩዌት ወደ ሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ባሊስቲክ ሚሳኤል አስወነጨፈች።
በጥቃቱ ቢያንስ 5 አሜሪካውያን እንደቆሰሉ ብሉምበርግ ዘግቧል።
ሁለት ሪፐር ሰው አልባ አውሮፕላኖች ክፉኛ ተጎድተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤25👍3🤔3😱1
ካናዳዊዉ ራፐር ድሬክ አርሰናል ፒኤስጂን ያሸንፋል ብሎ 1.5 ሚሊዮን ዶላር አስይዟል
ከአለማችን እዉቅ ራፐሮች አንዱ የሆነዉ ካናዳዊዉ ድምጻዊ ድሬክ አርሰናል የምሽቱን የአዉሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂን ረትቶ ሻምፒዮን ይሆናል ሲል 1.5 ሚሊዮን ዶላር ማስያዙ ተዘግቧል።
ድሬክ 1 ሚሊዮን ዶላሩን በቀጥታ አርሰናል የምሽቱን ፍጻሜ ያሸንፋል ፣ እንዲሁም ቡካዮ ሳካ አሲስት ወይም ግብ ያስቆጥራል ብሎ ያስያዘዉ ሲሆን ቀሪዉን 500 ሺህ ዶላር ደግሞ አርሰናል ጨዋታዉን 1 ለ 0 ያሸንፋል ሲል መድቦበታል።
ድሬክ ከዚህ ቀደም በስፖርታዊ ዉርርዶቹ ቀንቶት አያዉቅም ይባላል። እርሱ በተደጋጋሚ ያሸንፋሉ ብሎ ገንዘቡን ያስያዘባቸዉ ክለቦች ድል ሲቀናቸዉ አልታየም።
በ 2022 አርሰናል ሊድስን ያሸንፋል ብሎ አስይዞ ድል ቀንቶት የነበረ ቢሆንም በተመሳሳይ ትኬት ግን ባርሴሎና ሪያልማድሪድን ያሸንፋል ብሎ አስይዞ ባርሳ ተረትቶ ነበር። በተለያዩ የቦክስ ጨዋታዎችም ድሬክ በመቶሺዎች ያስያዘበት ተጨዋች በተደጋጋሚ ሲረታ እንጂ ሲያሸንፍ አልታየም።
ብዙሃኑ የስፖርት አፍቃሪያኖችም "የድሬክ እርግማን" ሲሉ ሽንፈቱን ይጠሩታል። ድሬክ ገንዘብ ያስያዘበት ቡድን ይረታል እንደማለት ነዉ። ዛሬስ ድሬክ አርሰናል አሸንፎለት ይህንን እርግማኑን ያስነሳ ይሆን የሚለዉ ጥያቄ በቡዳፔስት ምሽት 1 ሰዓት ላይ የሚጀምረው ጨዋታ ሲጠናቀቅ ምላሽ ያገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከአለማችን እዉቅ ራፐሮች አንዱ የሆነዉ ካናዳዊዉ ድምጻዊ ድሬክ አርሰናል የምሽቱን የአዉሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂን ረትቶ ሻምፒዮን ይሆናል ሲል 1.5 ሚሊዮን ዶላር ማስያዙ ተዘግቧል።
ድሬክ 1 ሚሊዮን ዶላሩን በቀጥታ አርሰናል የምሽቱን ፍጻሜ ያሸንፋል ፣ እንዲሁም ቡካዮ ሳካ አሲስት ወይም ግብ ያስቆጥራል ብሎ ያስያዘዉ ሲሆን ቀሪዉን 500 ሺህ ዶላር ደግሞ አርሰናል ጨዋታዉን 1 ለ 0 ያሸንፋል ሲል መድቦበታል።
ድሬክ ከዚህ ቀደም በስፖርታዊ ዉርርዶቹ ቀንቶት አያዉቅም ይባላል። እርሱ በተደጋጋሚ ያሸንፋሉ ብሎ ገንዘቡን ያስያዘባቸዉ ክለቦች ድል ሲቀናቸዉ አልታየም።
በ 2022 አርሰናል ሊድስን ያሸንፋል ብሎ አስይዞ ድል ቀንቶት የነበረ ቢሆንም በተመሳሳይ ትኬት ግን ባርሴሎና ሪያልማድሪድን ያሸንፋል ብሎ አስይዞ ባርሳ ተረትቶ ነበር። በተለያዩ የቦክስ ጨዋታዎችም ድሬክ በመቶሺዎች ያስያዘበት ተጨዋች በተደጋጋሚ ሲረታ እንጂ ሲያሸንፍ አልታየም።
ብዙሃኑ የስፖርት አፍቃሪያኖችም "የድሬክ እርግማን" ሲሉ ሽንፈቱን ይጠሩታል። ድሬክ ገንዘብ ያስያዘበት ቡድን ይረታል እንደማለት ነዉ። ዛሬስ ድሬክ አርሰናል አሸንፎለት ይህንን እርግማኑን ያስነሳ ይሆን የሚለዉ ጥያቄ በቡዳፔስት ምሽት 1 ሰዓት ላይ የሚጀምረው ጨዋታ ሲጠናቀቅ ምላሽ ያገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤28🤣14💔7👍2
ፒኤስጂ 1-1 አርሰናል
ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ደቂቃ አምርቷል !
የአርሰናል እና ፒኤስጂ ጨዋታ በመደበኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
ይህንንም ተከትሎ ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ሰላሳ ደቂቃ አምርቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ደቂቃ አምርቷል !
የአርሰናል እና ፒኤስጂ ጨዋታ በመደበኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
ይህንንም ተከትሎ ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ሰላሳ ደቂቃ አምርቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍12❤8🤪5🤯3👏1😁1😢1🙏1👌1🏆1
ሙሉ የተሽከርካሪ እገዳ ተጣለ‼️
በጋምቤላ ክልል ከነገ ጧት ጀምሮ በክልሉ የሚገኙ ማንኛውም ተሽከርካሪ እንቅስቃሴ የማይፈቀድና የተከለከለ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቀ።
ከነገ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከጧት ጀምሮ እስከ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ የተለየ የይለፍ ፊቃድ ካልተሰጠው በስተቀር ማንኛውም የመንግሥት፣ የንግድ እና የግል ተሽከርካሪዎች፣ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች/ባጃጅ እና ሞተር ሳይክል በሙሉ እንቅስቃሴ እንዲያቆሙ የተወሰነ ሲሆን ይህንን መመሪያ ተግባራዊ በማያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ የሆነ ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድባቸው መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር አቶ ዶሮ ካሩ አሳስበዋል።
ከነገ ግንቦት 23 ቀን 2018 እስከc ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም
በልዩነት የተፈቀደላቸው ለድንገተኛ ሥራ (Emergency) ብቻ የሚንቀሳቀሱ የመብራት ኃይል፣ የቴሌኮሙኒኬሽን እና አምቡላንሶች ሲሆን የይለፍ ወረቀት መያዝና ሲጠየቅ የማሳየት ኃላፊነትና ግዴታ እንዳለባቸውም ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በጋምቤላ ክልል ከነገ ጧት ጀምሮ በክልሉ የሚገኙ ማንኛውም ተሽከርካሪ እንቅስቃሴ የማይፈቀድና የተከለከለ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቀ።
ከነገ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከጧት ጀምሮ እስከ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ የተለየ የይለፍ ፊቃድ ካልተሰጠው በስተቀር ማንኛውም የመንግሥት፣ የንግድ እና የግል ተሽከርካሪዎች፣ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች/ባጃጅ እና ሞተር ሳይክል በሙሉ እንቅስቃሴ እንዲያቆሙ የተወሰነ ሲሆን ይህንን መመሪያ ተግባራዊ በማያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ የሆነ ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድባቸው መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር አቶ ዶሮ ካሩ አሳስበዋል።
ከነገ ግንቦት 23 ቀን 2018 እስከc ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም
በልዩነት የተፈቀደላቸው ለድንገተኛ ሥራ (Emergency) ብቻ የሚንቀሳቀሱ የመብራት ኃይል፣ የቴሌኮሙኒኬሽን እና አምቡላንሶች ሲሆን የይለፍ ወረቀት መያዝና ሲጠየቅ የማሳየት ኃላፊነትና ግዴታ እንዳለባቸውም ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤18👍4😡4
ዩቱዩብ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በሚሰሩ ቪዲዮዎች ላይ ዘመቻ ከፈተ።
የዓለም ትልቁ የቪዲዮ ማጋሪያ ፕላትፎርም የሆነው ዩቱዩብ (YouTube)፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም በArtificial Intelligence (AI) አማካኝነት በብዛት የሚመረቱ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ በርካታ ቻናሎችን ሙሉ በሙሉ መሰረዝ መጀመሩ ተሰምቷል።
እንደ አዳዲስ መረጃዎች ዘገባ ከሆነ፤ ከመድረኩ የተሰረዙት እነዚህ ቻናሎች ከመዘጋታቸው በፊት በአጠቃላይ ከ4.7 ቢሊዮን በላይ እይታዎችን (Views) ማሰባሰብ ችለው ነበር።
ዩቱዩብ ይህንን ጠንከር ያለ እርምጃ የወሰደው ተጠቃሚዎችን የሚያሳስቱና ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል፣ ጥራታቸውን ያልጠበቁና ሰዎችን የሚያሰለቹ ይዘቶችን ለመቀነስ እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያውን ታማኝነት እና ትክክለኛነት ለመጠበቅ በማሰብ እንደሆነ ታውቋል።
እነዚህ ቻናሎች ያለምንም የሰው ልጅ ተሳትፎ፣ በኮምፒውተር ፕሮግራሞች ብቻ በጅምላ የሚሰሩ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ ነበሩ።
በአሁኑ ጊዜ የAI መተግበሪያዎች እጅግ በጣም ፈጣን እና ቀላል በሆነ መንገድ በሺዎች የሚቆጠሩ ቪዲዮዎችን በደቂቃዎች ውስጥ ለመፍጠር ያስችላሉ።
ይህ ሁኔታ ደግሞ እንደ ዩቱዩብ ላሉ ትልልቅ የቴክኖሎጂ ተቋማት አዲስ ፈጠራን ከመደገፍ እና የሰዎችን እምነት በአግባቡ ከማስጠበቅ አንፃር ትልቅ የባላንስ ፈተና ሆኖባቸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የዓለም ትልቁ የቪዲዮ ማጋሪያ ፕላትፎርም የሆነው ዩቱዩብ (YouTube)፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም በArtificial Intelligence (AI) አማካኝነት በብዛት የሚመረቱ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ በርካታ ቻናሎችን ሙሉ በሙሉ መሰረዝ መጀመሩ ተሰምቷል።
እንደ አዳዲስ መረጃዎች ዘገባ ከሆነ፤ ከመድረኩ የተሰረዙት እነዚህ ቻናሎች ከመዘጋታቸው በፊት በአጠቃላይ ከ4.7 ቢሊዮን በላይ እይታዎችን (Views) ማሰባሰብ ችለው ነበር።
ዩቱዩብ ይህንን ጠንከር ያለ እርምጃ የወሰደው ተጠቃሚዎችን የሚያሳስቱና ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል፣ ጥራታቸውን ያልጠበቁና ሰዎችን የሚያሰለቹ ይዘቶችን ለመቀነስ እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያውን ታማኝነት እና ትክክለኛነት ለመጠበቅ በማሰብ እንደሆነ ታውቋል።
እነዚህ ቻናሎች ያለምንም የሰው ልጅ ተሳትፎ፣ በኮምፒውተር ፕሮግራሞች ብቻ በጅምላ የሚሰሩ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ ነበሩ።
በአሁኑ ጊዜ የAI መተግበሪያዎች እጅግ በጣም ፈጣን እና ቀላል በሆነ መንገድ በሺዎች የሚቆጠሩ ቪዲዮዎችን በደቂቃዎች ውስጥ ለመፍጠር ያስችላሉ።
ይህ ሁኔታ ደግሞ እንደ ዩቱዩብ ላሉ ትልልቅ የቴክኖሎጂ ተቋማት አዲስ ፈጠራን ከመደገፍ እና የሰዎችን እምነት በአግባቡ ከማስጠበቅ አንፃር ትልቅ የባላንስ ፈተና ሆኖባቸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👏26❤23👍9
በፋይዳ ምክንያት የታገዱ የዲያስፖራ ሂሳቦች‼️
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በፋይዳ ምክንያት የታገዱ የዲያስፖራ ሂሳቦች በጊዜያዊነት የሚከፈቱበትን አማራጭ መንገዶችን አሳውቋል።
ባንኩ የፋይዳ መለያ ቁጥርን ከባንክ ሂሳብ ጋር የማያያዝ ሂደት ላይ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል አዲስ ተለዋጭ አሰራር ይፋ ማድረጉን አሳውቋል።
ይህንን ያስታወቀው ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ለኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት በጻፈው ይፋዊ ደብዳቤ ነው።
ባንኩ በላከው መመሪያ መኖሪያቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ ያደረጉ የባንኩ ደንበኞች በጊዜያዊነት ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመር ሳያስፈልጋቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት በልዩ ሁኔታ እየተስተናገዱ መሆኑን ገልጿል።
" በባንካችን በኩል ከዚህ በፊት ደንበኞች ሂሳብ በሚከፍቱበት ወቅት የመኖሪያ አድራሻቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ እንደሆነ ማስረጃ ያቀረቡ እና በባንካችን የመረጃ ቋት ላይ የተመዘገበ ማስረጃ ያላቸው ደንበኞች ሂሳብ ያልታገደ መሆኑን እናሳውቃለን " ብሏል።
በተለያዩ ምክንያቶች ደንበኞች ውጭ እንደሚኖሩ በባንኩ የመረጃ ቋት ላይ ያላስመዘገቡ እና የባንክ ሂሳባቸው የታገደባቸው ደንበኞች ግን ብሔራዊ ባንክ ለባንኩ ባሳወቀው መሰረት ከዚህ በታች በተገለጸው አግባብ መስተናገድ የሚችሉ መሆኑን ገልጿል።
• በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የፋይዳ መለያ ቁጥር ማቅረብ ባይችሉም እንኳ፣ በውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚያረጋግጥ ማስረጃ በማቅረብ የእገዳው አካል እንዳይሆኑ ይደረጋል። ለዚህም እንደ፦
- የትምህርት ማስረጃ፣
- የህክምና ማስረጃ፣
- የውጭ ሀገር የመኖሪያ ፍቃድ (Residence Permit/ID)
- በህጋዊ አካል የተረጋገጠ በውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚገልጽ የውክልና ማስረጃ (በህጋዊ ወኪሎቻቸው በኩል) በማቅረብ ሂሳባቸውን ማንቀሳቀስ ይችላሉ።
• ዲፕሎማቶችን በተመለከተ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ መታወቂያቸውን በማሳየት ወይም ሂሳቡ የተከፈተው በዲፕሎማት መታወቂያ ከሆነ የእገዳው አካል ሳይሆኑ ሂሳባቸውን መጠቀም እንደሚችሉ ተገልጿል።
• አንድ ደንበኛ በውጭ ሀገር እንደሚኖር በሚመለከተው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ በኩል በኢሜል ማረጋገጫ ከተላከ፣ ባንኩ በጊዜያዊነት የጣለውን እገዳ አንስቶ ደንበኛው ሂሳቡን እንዲጠቀም ይፈቅዳል።
ደንበኞች ውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚያረጋግጡ ማስረጃዎችን ሂሳባቸው ለተከፈተበት ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ኢሜል ወይም በባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ለሚገኘው የዲያስፖራ ባንኪንግ ክፍል DiasporaBanking@cbe.com.et በመላክ የተጣለባቸው እገዳ በጊዜያዊነት እንዲነሳ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል።
ይህ መመሪያ በተባበሩት አረብ ኤምሬተስ ለሚኖሩ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ መመዝገብ የሚቻል በመሆኑ መመሪያው የማይመለከታቸው መሆኑን ባንኩ ገልጿል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በፋይዳ ምክንያት የታገዱ የዲያስፖራ ሂሳቦች በጊዜያዊነት የሚከፈቱበትን አማራጭ መንገዶችን አሳውቋል።
ባንኩ የፋይዳ መለያ ቁጥርን ከባንክ ሂሳብ ጋር የማያያዝ ሂደት ላይ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል አዲስ ተለዋጭ አሰራር ይፋ ማድረጉን አሳውቋል።
ይህንን ያስታወቀው ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ለኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት በጻፈው ይፋዊ ደብዳቤ ነው።
ባንኩ በላከው መመሪያ መኖሪያቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ ያደረጉ የባንኩ ደንበኞች በጊዜያዊነት ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመር ሳያስፈልጋቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት በልዩ ሁኔታ እየተስተናገዱ መሆኑን ገልጿል።
" በባንካችን በኩል ከዚህ በፊት ደንበኞች ሂሳብ በሚከፍቱበት ወቅት የመኖሪያ አድራሻቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ እንደሆነ ማስረጃ ያቀረቡ እና በባንካችን የመረጃ ቋት ላይ የተመዘገበ ማስረጃ ያላቸው ደንበኞች ሂሳብ ያልታገደ መሆኑን እናሳውቃለን " ብሏል።
በተለያዩ ምክንያቶች ደንበኞች ውጭ እንደሚኖሩ በባንኩ የመረጃ ቋት ላይ ያላስመዘገቡ እና የባንክ ሂሳባቸው የታገደባቸው ደንበኞች ግን ብሔራዊ ባንክ ለባንኩ ባሳወቀው መሰረት ከዚህ በታች በተገለጸው አግባብ መስተናገድ የሚችሉ መሆኑን ገልጿል።
• በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የፋይዳ መለያ ቁጥር ማቅረብ ባይችሉም እንኳ፣ በውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚያረጋግጥ ማስረጃ በማቅረብ የእገዳው አካል እንዳይሆኑ ይደረጋል። ለዚህም እንደ፦
- የትምህርት ማስረጃ፣
- የህክምና ማስረጃ፣
- የውጭ ሀገር የመኖሪያ ፍቃድ (Residence Permit/ID)
- በህጋዊ አካል የተረጋገጠ በውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚገልጽ የውክልና ማስረጃ (በህጋዊ ወኪሎቻቸው በኩል) በማቅረብ ሂሳባቸውን ማንቀሳቀስ ይችላሉ።
• ዲፕሎማቶችን በተመለከተ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ መታወቂያቸውን በማሳየት ወይም ሂሳቡ የተከፈተው በዲፕሎማት መታወቂያ ከሆነ የእገዳው አካል ሳይሆኑ ሂሳባቸውን መጠቀም እንደሚችሉ ተገልጿል።
• አንድ ደንበኛ በውጭ ሀገር እንደሚኖር በሚመለከተው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ በኩል በኢሜል ማረጋገጫ ከተላከ፣ ባንኩ በጊዜያዊነት የጣለውን እገዳ አንስቶ ደንበኛው ሂሳቡን እንዲጠቀም ይፈቅዳል።
ደንበኞች ውጭ ሀገር እንደሚኖሩ የሚያረጋግጡ ማስረጃዎችን ሂሳባቸው ለተከፈተበት ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ኢሜል ወይም በባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ለሚገኘው የዲያስፖራ ባንኪንግ ክፍል DiasporaBanking@cbe.com.et በመላክ የተጣለባቸው እገዳ በጊዜያዊነት እንዲነሳ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል።
ይህ መመሪያ በተባበሩት አረብ ኤምሬተስ ለሚኖሩ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ መመዝገብ የሚቻል በመሆኑ መመሪያው የማይመለከታቸው መሆኑን ባንኩ ገልጿል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10👍3
ሰበር :-
የአርሰናል እና የፔዤን ጨዋታ እያዩ የነበሩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የቦምብ ተፈፀመባቸው
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት በተከሰተ የቦምብ ፍንዳታ የተማሪዎች ህይወት ማለፉና በርካቶች መቁሰላቸው ተሰምቷል፡፡
አደጋው የተከሰተው ተማሪዎች በካምፓሱ አዳራሽ ውስጥ ተጨናንቀው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የእግር ኳስ ጨዋታን በፕሮጀክተር እየተከታተሉ በነበረበት ወቅት እንደሆነ ተገልጿል።
ከተማሪዎችና ከአካባቢው ነዋሪዎች በተገኘ መረጃ መሠረት፣ በፍንዳታው ሳቢያ በትንሹ የሁለት ተማሪዎች ህይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን፤ የሟቾች ቁጥር እስከ 3 ሊደርስ እንደሚችል ተጠቁሟል።
ህይወታቸው ያለፈው ተማሪዎች አስክሬን ዛሬ ጠዋት ወደ ቤተሰቦቻቸው ተሸኝቷል።
በተጨማሪም ከ30 በላይ ተማሪዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን፤ ተጎጂዎቹ በካምፓሱ ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
ፍንዳታው በተከሰተበት ወቅት በአዳራሹ ውስጥ ከፍተኛ የሰው ቁጥር በመኖሩና በመግቢያና መውጫዎች ላይ በተፈጠረው መረጋገጥ ሳቢያ የጉዳቱ መጠን ሊጨምር እንደቻለ የዓይን እማኞች ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአርሰናል እና የፔዤን ጨዋታ እያዩ የነበሩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የቦምብ ተፈፀመባቸው
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት በተከሰተ የቦምብ ፍንዳታ የተማሪዎች ህይወት ማለፉና በርካቶች መቁሰላቸው ተሰምቷል፡፡
አደጋው የተከሰተው ተማሪዎች በካምፓሱ አዳራሽ ውስጥ ተጨናንቀው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የእግር ኳስ ጨዋታን በፕሮጀክተር እየተከታተሉ በነበረበት ወቅት እንደሆነ ተገልጿል።
ከተማሪዎችና ከአካባቢው ነዋሪዎች በተገኘ መረጃ መሠረት፣ በፍንዳታው ሳቢያ በትንሹ የሁለት ተማሪዎች ህይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን፤ የሟቾች ቁጥር እስከ 3 ሊደርስ እንደሚችል ተጠቁሟል።
ህይወታቸው ያለፈው ተማሪዎች አስክሬን ዛሬ ጠዋት ወደ ቤተሰቦቻቸው ተሸኝቷል።
በተጨማሪም ከ30 በላይ ተማሪዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን፤ ተጎጂዎቹ በካምፓሱ ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
ፍንዳታው በተከሰተበት ወቅት በአዳራሹ ውስጥ ከፍተኛ የሰው ቁጥር በመኖሩና በመግቢያና መውጫዎች ላይ በተፈጠረው መረጋገጥ ሳቢያ የጉዳቱ መጠን ሊጨምር እንደቻለ የዓይን እማኞች ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19😢16💔6👍5😱4🤯1👀1
ደቡብ ሱዳን በድንበሯ ላይ የተገነባውን
የግብፅ ጦር ሠፈር እንዲዘጋ አዘዘች
የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግብፅ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው የላይኛው ናይል ግዛት ፓጋክ አካባቢ ያቋቋመችውን ወታደራዊ ጦር ሠፈር በአስቸኳይ እንድትዘጋ ማዘዙን የዓረብኛ የዜና ምንጮች በሰፊው ዘግበዋል።
ይህ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ የተገነባውና ወታደራዊ ሥልጠና የመስጠት እንዲሁም የናይል ወንዝ ፍሰትን የመቆጣጠር ስውር ዓላማ የነበረው ጦር ሠፈር፣ የሥልጠና ባለሙያዎችን ጨምሮ 260 የሚያህል የሰው ኃይል አሰማርቶ የነበረ መሆኑ ታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የግብፅ ጦር ሠፈር እንዲዘጋ አዘዘች
የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግብፅ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው የላይኛው ናይል ግዛት ፓጋክ አካባቢ ያቋቋመችውን ወታደራዊ ጦር ሠፈር በአስቸኳይ እንድትዘጋ ማዘዙን የዓረብኛ የዜና ምንጮች በሰፊው ዘግበዋል።
ይህ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ የተገነባውና ወታደራዊ ሥልጠና የመስጠት እንዲሁም የናይል ወንዝ ፍሰትን የመቆጣጠር ስውር ዓላማ የነበረው ጦር ሠፈር፣ የሥልጠና ባለሙያዎችን ጨምሮ 260 የሚያህል የሰው ኃይል አሰማርቶ የነበረ መሆኑ ታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤13👍5🤪4😢3👏2