አዲስ ሪፖርተር - NEWS
35.8K subscribers
17K photos
415 videos
21 files
3.01K links
🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !

=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !

🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addisreporter_bot

#ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Download Telegram
በነገሌ ቦረና የተገነባው የገዳ አውሮፕላን ማረፊያ  ተመረቀ

ይህ አውሮፕላን ማረፊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻ ሲሆን፣ እንደ ቦይንግ 737 ማክስ ያሉ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለው ተገልጿል።

​በምረቃው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ  እንደተናገሩት፣ አውሮፕላን ማረፊያው የአካባቢውንና ድንበር ተሻጋሪ የንግድ ልውውጥን እንዲሁም ቱሪዝምን ለማሳደግ አልሞ በሳምንት ሦስት በረራዎችን ያስተናግዳል።

​"የምንገነባው እያንዳንዱ አውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል፣ የክልሎችን ኢኮኖሚ ያነቃቃል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በፈረንጆቹ 2026 80ኛ ዓመቱን የያዘውና የአፍሪካ ኩራት የሆነው አየር መንገድ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ነው ብለዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
11🤪7👍3
የጀነራሉ እገታ እና ያሉበት መታወቅ!

ጀነራሉ መታገታቸው ተረጋገጠ፡፡ አንድ ወር ለሚሆን ጊዜ ከአደባባይ የጠፉት ጀነራሉ፤ መታገታቸውን የፈረንሳዩ ጋዜጣ ይፋ አድርጓል፡፡ ጀነራሉ ወደ አዲስአበባ እንዳይጓዙ እና ለፌዴራል መንግስት ባለስልጣናት ጋር እንዳይገናኙ በሚል ነው የታገቱት ተብሏል፡፡

ጀነራሉ ታግተዋል፡፡ የተረጋገጠ መረጃ ነው፡፡ ህውሃት ከአንድር ወር በፊት ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን ፕሬዝዳንት አድርጎ ጀነራል ታደሰ ላይ መፈንቅለ መንግስት ካከናወነ በኋላ፤ ጀነራሉ ጠፍተው ከርመዋል፡፡ ከዚህ የመፈንቅለ አስተዳደር በኋላ በአደባባይ ያልታዩት ጀነራል ታደሰ፤ የት ጠፉ በሚልም ብዙ ሲጠየቅ ነበር፡፡ ለዚህ ጥያቄ መልስ የሚሆን መረጃ ዛሬ ይፋ ሆኗል፡፡

ታማኙ የፈረንሳይ ጋዜጣ አፍሪካን ኢንተለጀንስ ስለ ጉዳዩ ሰማሁት ያለውን መረጃ ምንጮቹን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡ ጀነራል ታደሰ ወረደ ከመቀሌ እንዳይወጡ እና እንዳይንቀሳቀሱ ታግተው እንደሚገኙ አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ ‹‹ጀነራሉ ወደ አዲስአበባ እንዳይጓዙ በዚያም ከፌዴራል ባለስልጣናት ጋር እንዳይገናኙ በሚል በህውሃት ቁጥጥር ስር ናቸው›› በማለት ዘግቧል፡፡

የአፍሪካን ኢንተለጀንስ ዘገባ እንደሚያመላክተው፣ ይህ እገዳ የተጣለው በጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ እና ጌታቸው ረዳ አሰባሳቢነት ባለፈው ሳምንት በአዲስአበባ ምክርቤት መመስረቱን ተከትሎ ነው፡፡ የእነ ጀነራል ፃድቃን የአዲስአበባው ምክርቤት ሕውሓትን ባጭር ጊዜ አስወግዶ ክልሉን ለመቆጣጠር አቅዷል፡፡ ህውሓት ጀነራል ታደሰ ወደ አዲስአበባ ኮብልለው ከአዲሱ ምክርቤት ጋር እዳይቀላቀሉ በሚል ነው ጀነራል ታደሰን የቁም እስረኛ ያደረጋቸው ብሏል ዘገባው፡፡ ጀነራሉ ብዙ ሚስጥር የሚያውቁ እና ህውሃት አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ሰው በመሆናቸው እንደሆነ ጋዜጣው አብራርቷል፡፡

ከአፍሪካን ኢንተለጀንስ መረጃ መረዳት እንደተቻለው ህውሓት ጀነራሉን ለማገት የወሰነው በሁለት አበይት ምክንያቶች ናቸው፡፡ አንደኛው ጀነራሉ የእነፃድቃንን ምክርቤት እንዳይቀላቀሉ በሚል ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጀነራሉ እጅ ላይ በርካታ የሕውሓት ሚስጥሮች በመኖራቸው ነው፡፡

Via : Yene tube

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
22👍3😈1
ከ6ሺ በላይ ለሚሆኑ የአዕምሮ ህሙማን ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የሚያግዝ ህክምና ተሰጠ
 
ይህ የህክምና ዓይነት በአእምሮ ጤና አውድ ውስጥ የተሃድሶ ህክምና የሚባል ሲሆን የአእምሮ ህመም ያለባቸው ሰዎች በህብረተሰቡ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተሳታፊ እንዲሆኑና ጥራት ያለው ሕይወት እንዲመሩ የሚረዳ የህክምና እና ድጋፍ ሂደት ነው።
 
በዚህም የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ6ሺህ334 ዜጎች የተሀድሶ የህክምና አገልግሎት መስጠቱን የሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አብዩ የኔአለም ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
 
ህክምናው  ​ታካሚው የዕለት ከዕለት ተግባራቱን በራሱ እንዲያከናውን የሚረዳ ራስን መንከባከብ ፣ ንፅህናን መጠበቅ እና  ከሰዎች ጋር እንዴት መግባባትና ጤናማ ግንኙነት መፍጠር እንደሚቻል የሚሰጥ ነው።
 
በተጨማሪም የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ  የሙያ እና ስራ ስልጠና እንዲሁም ​ከሆስፒታል የወጡ ታካሚዎች በቀጥታ ወደ ማህበረሰቡ ከመቀላቀላቸው በፊት የቅርብ ክትትል የሚደረግባቸው ጊዜያዊ ማቆያዎችን ማመቻቸትን ይጨምራል።
 
ታካሚው በተቻለ መጠን በሌሎች ላይ ጥገኝነቱ እንዲቀንስ ፣ያለ አድልዎና ማግለል በቤተሰብና በሰፈር ውስጥ እንዲይኖር የሚያስችል ሲሆን ህመሙ ተመልሶ እንዳይቀሰቀስ  ራሱን እንዲጠብቅ ይረዳል ሲሉ አቶ  አብዩ የኔአለም ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
 
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
14👍2🤯1🤩1
#ሰበር-መረጃ‼️
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣን ተነሱ‼️
የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ እና የቅርብ ሰው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከስልጣን መነሳታቸውን መሰረት ሚዲያ ዘግቧል።

ዲያቆን ዳንኤል የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ የነበሩ ሲሆን፤ ከተቋሙ ሰራተኞች በተነሳባቸው ቅሬታ ምክንያት ከቦርድ ሰብሳቢነታቸው ተነስተዋል ሲል የዜና ጣብያው ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።

በምትካቸውም የኮሙኒኬሽን ሚኒስትሯ ወይዘሯ እናትአለም መለስ ተተክተዋል።

ይህን የስልጣን ሽግሽግ በተመለከተ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንም ሆነ ከመንግሥት በኩል የተባለ ነገር የለም።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣3819👍8👏3🤪2🙊2🥰1🤔1🎉1🏆1
ግንቦት 24 ሥራ ዝግ ነው‼️
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም በፌዴራል እና ክልል መንግሥታዊ ተቋማት እንዲሁም የግል ተቋማት ሥራ ዝግ ሆኖ ይውላል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄደውን የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል።

ቦርዱ፦

- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

- የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ እንዲያከነውኑ ፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት እንደማያስገድድ አሳውቋል።

- የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ አረበታቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
17👍6👏2🤪1
መረጃ‼️

የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ፣ በግል የጤና ተቋማትና መድኃኒት መደብሮች ውስጥ የሚቀጠሩ አዲስ ባለሙያዎች ከዚህ በኋላ የቅጥር ውል ሲፈጽሙ በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥት የጤና መዋቅሮች እውቅና እንዲኾን አዘዘ።

የግል የጤና ተቋማት አዲስ የሚቀጥሯቸው ባለሙያዎች ሥራ ከጀመሩበት ቀን አንስቶ ሙሉ መረጃቸውን ለክልሉ ጤና ቢሮ መላክ እንዳለባቸውም መታዘዛቸውንም ቢሮው በክልሉ ለሚገኙ 21 የዞን የጤና መምሪያዎች ከጻፈው ደብዳቤ ላይ ዋዜማ ተመልክታለች።

ቢሮው፣ በግል የጤና ተቋማትና መድኃኒት መደብሮች ውስጥ ለሚቀጠሩ አዲስ ባለሙያዎች የሚከፈላቸው ደመወዝ በመንግሥት የጤና ተቋማት ውስጥ ለሚሠሩ ባለሙያዎች ከሚከፈላቸው ደመወዝ ማነስ እንደሌለበት ጭምር ትዕዛዝ አስተላልፏል።

በደብዳቤው ላይ የተጠቀሱትን ትዕዛዞች ተፈጻሚ በማያደርጉ የግል የጤና ተቋማት ላይ አስፈላጊውን ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድም ቢሮው አስጠንቋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
20👍4👏1😁1🙊1
ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል ተጠርጥረው በናይሮቢ ታስረው የነበሩ ሁለት የቦረና ሀገር ሽማግሌዎች በዋስ ተለቀቁ

ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል ተጠርጥረው ከሁለት ሳምንት በፊት ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ታስረው የነበሩ የኬንያ ማርሳቢት ካውንቲ ተወላጅ የሆኑ ሁለት የቦረና የሀገር ሽማግሌዎች፣ 14 ሚሊዮን የኬንያ ሺሊንግ (17.3 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር) የሚያወጣ የንብረት ዋስትና በማስያዝ ተለቀቁ።

ወደ ናይሮቡ ተወስደው የነበሩት የቀድሞው የጎሎሌ መንደር አስተዳዳሪ አቶ ደባሳ ደምቢ እና የሶሎሎ ነዋሪና የማኅበረሰብ መሪ የሆኑት አቶ ጉራቻ ደምበላ ትናንት ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ምሽት ላይ ከእስር መፈታታቸውን ጠበቃቸው አቶ ቀና ጎሊቻ ገልጸዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
12👍3
ግጭቱ ለሊቱን በድጋሚ ተጀምሯል።

አሜሪካ ወደ ኢራን መተኮስ ጀምራለች።

ኢራንም አፀፋ እየሰጠች ነው።

ትላንት ምሽት ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱ አይቀሬ መሆኑን ምልክት ሰጥተው ነበር።

ስለ አጋማሹ ምርጫ ውጤት አልጨነቅም እስከማለት ደርሰው ነበር።

ሁለቱ ወገኖች የኢድ ለሊት ሲወራወሩ ነው ያደሩት።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
11👍9😢5😡3🤪2🕊1🙊1
ሂውማን ራይትስ ዎች፣ የኮሎምቢያ ተዋጊ ቅጥረኞች ለሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለመዋጋት የተሠለፉት በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ተቀጥረው መኾኑን አዲስ ባወጣው የምርመራ ሪፖርት አስታወቀ።

ድርጅቱ፣ ኮሎምቢያዊያን ቅጥረኞቹ ሱዳን ከመግባታቸው በፊት በኢምሬቶች ወታደራዊ ጦር ሠፈሮች በኩል እንዳለፉና ሥልጠና እንደወሠዱ ማረጋገጡን ገልጧል።

ቅጥረኞቹን በመቅጠር የተሳተፈው፣ 'ግሎባል ሴኩሪቲ ሠርቪስስ ግሩፕ' የተባለ ከኢምሬቶች መንግሥት ጋር ግንኙነት ያለው የግል የጸጥታ ኩባንያ ነው ተብሏል።

ሂውማን ራይትስ ዎች፣ ሌሎች አገራት የኢምሬቶች ባለሥልጣናትን ጨምሮ በጉዳዩ ተሳታፊዎች ላይ ማዕቀብ እንዲጣል የሚያስችል ምርመራ እንዲደረግ ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል።

አገራት ከኢምሬቶች ጋር ያላቸውን ወታደራዊ ትብብርና ለአገሪቱ የጦር መሳሪያ መሸጥ እንዲያቆሙ የጠየቀው ድርጅቱ፣ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ደሞ ኢምሬቶች ለፈጥኖ ደራሹ ኃይል ድጋፍ መስጠት እንድታቆም በባለሥልጣናቷ ላይ ግፊት እንዲያደርጉ ጥሪ አድርጓል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
12👍2
‘ዶናልድ ትራምፕ’ የተባለው ጎሽ ከእርድ ተረፈ

በባንግላዲሽ ወርቃማ ፀጉር ስላለው ‘ዶናልድ ትራምፕ’ ተብሎ የተሰየመውና በሰፊው የተነገረለት አልቢኖ ጎሽ ለዒድ አል-አድሃ በዓል ላይ ሊታረድ የነበረ ቢሆንም በመንግሥት ጣልቃ ገብነት ሕይወቱ ተርፏል።

700 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ይህ እንስሳ፣ በባንግላዲሽ እጅግ አልፎ አልፎ የሚገኝ ዝርያ በመሆኑና በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ባሳየው ዝና ምክንያት የሕዝብ ትኩረት መሳብ ችሏል።

ገዢዎች እንስሳውን ለመግዛት ከፍተኛ ፍላጎት ባሳዩበት ወቅት፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት ባደረጉት አስቸኳይ ጣልቃ ገብነት ለገዢው ገንዘብ ተመላሽ ተደርጓል።

ይህ ልዩ ጎሽ ለደኅንነቱ ሲባል ከእርድ ተርፎ በዳካ ወደሚገኘው ብሔራዊ መካነ አራዊት እንዲዛወር መደረጉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣2418👍4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔴 ሰበር መረጃ‼️
በስትራቴጂካዊቷ የኢራን የወደብ ከተማ ባንደር አባስ ሦስት ከባድ ፍንዳታዎች ተሰሙ፤ አሜሪካ በኢራን የድሮን ጣቢያ ላይ "ራስን የመከላከል" ጥቃት መፈጸሟን አረጋገጠች‼️
ትናንት ማታ ግንቦት 19/2018 ዓ.ም በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ በምትገኘው ስልታዊዋ የኢራን የወደብ እና የባህር ኃይል መሠረት ከተማ ባንደር አባስ (Bandar Abbas) ምሥራቃዊ ክፍል ሦስት እጅግ ከባድ የሆኑ የፍንዳታ ድምፆች ተሰምተዋል። ፍንዳታውን ተከትሎም የኢራን የአየር መከላከያ ሥርዓቶች (Air defenses) ለአጭር ደቂቃዎች ተንቀሳቅሰው እንደነበር የሀገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። 
የአሜሪካ መከላከያ ባለሥልጣናት ለዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እንደገለጹት፤ የአሜሪካ ጦር ኃይል በባንደር አባስ የሚገኝን የኢራን የድሮን መቆጣጠሪያ ጣቢያ (Ground control station) በአየር ጥቃት መቷል። ይህ እርምጃ የተወሰደው ኢራን በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ላይ ስጋት የሆኑ 4 የጥቃት ድሮኖችን ካስወነጨፈች እና በአሜሪካ ከተመቱ በኋላ፥ አምስተኛውን ድሮን ለመከላከል የተሰነዘረ ስልታዊ እርምጃ መሆኑን ዋሽንግተን አስታውቃለች። 
ይህንን ተከትሎ ኢራን አሜሪካ ይህንን ጥቃት የፈፀመችው ከኩዮት የጦር ሰፈር በመነሳት ነው ያለች ሲሆን ኢራን በኩዬት በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ቤዝ ላይ ጥቃት ፈፅማለች።
ኩዬት አብዛኞቹን የኢራን ሚሳኤሎች እና ድሮን ማክሸፏን ገልፃለች።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
19👍3🥱3👏1🤔1
ብሔራዊ ባንክ በቁጠባና ብድር ማኅበራት ላይ ቀጥተኛ ቁጥጥር ሊጀምር ነው ተባለ‼️

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የቁጠባና ብድር ማኅበራትን በቀጥታ ለመቆጣጠር የወሰነው እርምጃ፣ ዘርፉ ለሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር መሸሸጊያ እንዳይሆን ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር የፋይናንስ ባለሙያ ገልፀዋል።

ባለሙያው አቶ ገመቹ ብርሃኑ፤ ማኅበራቱ ከብሔራዊ ባንክ ቁጥጥር ውጪ መቆየታቸው በፋይናንስ ገበያው ላይ ከፍተኛ መዛባትና የደህንነት ስጋት ደቅነው መቆየታቸውን ጠቁመዋል።

የፋይናንስ ባለሙያው አቶ ገመቹ ብርሃኑ እንደገለጹት፤ እስካሁን ማኅበራቱ የብሔራዊ ባንክ የቁጥጥር ማዕቀፍ ውስጥ አለመኖራቸው ለሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ወይም "መኒ ላውንድሪንግ"ሰፊ በር ከፍቶ ቆይቷል።

ሕገ-ወጥ ገንዘብ ያላቸው አካላት የገንዘቡን ምንጭ ለመደበቅ በአባላት ቁጠባ ስም በትናንሹ እየከፋፈሉ ወደ ማኅበራቱ በማስገባት፣ ወደ ሕጋዊ የባንክ ሥርዓት እንዲቀላቀል ሲያደርጉት መቆየታቸውን ባለሙያው ጠቁመዋል።

አዲሱ አሰራር ግን ይህንን የገንዘብ ማጠብ ሥራ ለመቆጣጠር ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ከጣቢያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ አብራርተዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
7👍7
የ ዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ዋና ዳሪክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም
ወደ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) ማቅናታቸውን ገልፅው አያይዘው እንዲ ብለዋል.

​የኢቦላ ወረርሽኝ በድጋሚ አገርሽቷል። የኢቱሪ ግዛት ደግሞ የችግሩ ዋነኛ ሰለባ ሆኗል። በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት መሪነት፣ ከዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ቡድኖቻችን፣ ከአጋሮቻችን እና  የጤና ባለሙያዎች ጋር በመሆን በቦታው እገኛለሁ።
​ይህች አገር የኢቦላ ወረርሽኝን 16 ጊዜ ድል አድርጋለች። 17ኛው ጊዜም ከዚህ የተለየ አይሆንም። ነገር ግን አሁን፣ በጋራ መነሳት አለብን።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
17👍9
አሜሪካ ኩባን ለመምታት‼️
የአሜሪካ ወታደሮች እና የጦር መሳሪያዎች ኩባን ለማጥቃት ዝግጅታቸውን ጨርሰው የትራምፕን የመጨረሻ ትእዛዝ ብቻ እየጠበቁ መሆኑን ፖለቲኮ ዘግቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
11😡11😱3👍2😁1🥱1
ወታደራዊ አፈሳ‼️
ህወሓት ከቅርብ ቀናት ወዲህ አስገዳጅ የወጣቶች ወታደራዊ አፈሳ እያካሄደ መሆኑንና ይህም ህዝብን በጭንቅ ውስጥ  የከተተ ሆኗል።
ህወሃት ላለፉት ሁለት ሳምንት በለሊት ጭምር ቤት ለቤት ወታደራዊ አፈሳ ጀምሯል።
ይህ ሁኔታ ነዋሪው ላይ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።
የህወሓት ተቃዋሚ ናቸው የተባሉ የመንግስትም የግልም ታጣቂዎች መሳሪያቸው እየተወሰደባቸው ይገኛል።ህወሓት " እያካሄደ  ያለውን አስገዳጅ አፈሳ ለማስቆም ፓለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ሥራዎች እንዲሰሩ ስምረት ፓርቲ እንዲሁም ሳልሳዊ ወያኔ ፓርቲ ጠይቀዋል።
ምስል:- በAI የተቀናበረ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
13🤔11😢8🥰2👍1👀1🙊1
የኢትዮጵያ የሰው ሀብት ልማት መገታቱን እና የትምህርት ጥራት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አንድ አዲስ የዓለም ባንክ ሪፖርት ጠቆመ

በሪፖርቱ የቀረቡት መረጃዎች እንደሚያሳዩት ሀገሪቱ ጥራት ያለው ትውልድ ከመገንባት አኳያ የከፋ ቀውስ ውስጥ የምትገኝ ሲሆን ይህም የወደፊት የኢኮኖሚ ዕድገቷንና የዜጎቿን የነፍስ ወከፍ ገቢ በእጅጉ የሚገድብ ሆኖ ተገኝቷል።

Via : መሠረት ሚድያ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
12👍5🤔2😢2😁1
ውድ የአዲስ ሪፖርተር ተከታታዮቻችን ማስታወቂያ ማሰራት የምትፈልጉ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል👇
@Addis_reporter_bot
4👍3
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ከቀናት በፊት  የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ማሻሻያ (Update) አድርጓል።

ይህን ማሻሻያ ተከትሎ ቁጥራቸው ቀላል ያልሆነ ደንበኞች ከፍተኛ የአገልግሎት መስተጓጎል እየገጠማቸው መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ ደንበኞች ቅሬታ ከሆነ መተግበሪያው አፕዴት ከተደረገ በኋላ፦
- አንዳንዴ ሙሉ በሙሉ ስታክ የማድረግ፣
- Passphrase አስገቡ የማለት፣
- "Unexpected error occurred!" የሚል የቴክኒክ ስህተት መልዕክት የማሳየት፣
- የመዘግየት እና ምንም አለማሳየት ችግር እየገጠማቸው መሆኑን ጠቁመዋል።

ቃላቸውን የሰጡን የባንኩ ደንበኞች ችግሩን ለመፍታት በአካል ወደ ባንክ ቅርንጫፍ ቢያመሩም ከቅርንጫፎቹ የተሰጣቸው ምላሽ " ችግሩ ከአቅማቸው በላይ " መሆኑን እንደነገሯቸው ገልጸዋል።

በዚህ ችግር ምክንያት ስራ ለመስራት፣ እንቅስቃሴ ለማድረግ ማቸገራቸውንና ለከፍተኛ እንግልት መዳረጋቸውን ጠቁመዋል።

ወደ 951 ቢደውሉም ረጅም ደቂቃ የሚያስተናግዳቸውን እያገኙ እንዳልሆነ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምሽቱን ይፋዊ ማብራሪያ ሰጥቷል።

አዲስ መተግበሪያ በማስተዋወቁ ምክንያት በተወሰኑ ደንበኞች ላይ የአገልግሎት መስተጓጎል ማጋጠሙን አምኖ ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን፣ ችግሩን በአፋጣኝ ለመፍታት ርብርብ እያደረገ መሆኑን እና ደንበኞች በ951 የጥሪ ማዕከል ወይም ባዘጋጀው የዋትስአፕ ማህበራዊ ገጽ (https://chat.whatsapp.com/BFR1h7SrAti091qznFEP4u) በኩል ድጋፍ ማግኘት እንደሚችሉ አስታውቋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
18👍6