መረጃ‼️
የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት በአገሪቱ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ደኅንነት እንዲያስጠብቅ ጠየቁ።
ጌዲዮን ይህን ጥያቄ ያቀረቡት፣ ዛሬ ከሳዑዲ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዋሊድ ኤልክረጂ ጋር በተወያዩበት ወቅት መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባሠራጨው መረጃ ገልጧል።
ጌዲዮን፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ለኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች ሕጋዊ የሥራ እድሎችን እንዲያመቻችም መጠየቃቸውን ሚንስቴሩ ጠቅሷል።
ሚንስትር ዋሊድ፣ ሕጋዊ የሠራተኞች ፍልሠት ኢትዮጵያዊያን ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ ቅጥር እድል እንዲያገኙ ለማስቻል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ተብሏል።
የሳዑዲ ዓረቢያ ፍርድ ቤት ከአደንዛዥ እጽ ዝውውር ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት የጣለባቸው በርካታ ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ በውይይቱ ወቅት ይነሳ አይነሳ መረጃው አላመለከትም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት በአገሪቱ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ደኅንነት እንዲያስጠብቅ ጠየቁ።
ጌዲዮን ይህን ጥያቄ ያቀረቡት፣ ዛሬ ከሳዑዲ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዋሊድ ኤልክረጂ ጋር በተወያዩበት ወቅት መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባሠራጨው መረጃ ገልጧል።
ጌዲዮን፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ለኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች ሕጋዊ የሥራ እድሎችን እንዲያመቻችም መጠየቃቸውን ሚንስቴሩ ጠቅሷል።
ሚንስትር ዋሊድ፣ ሕጋዊ የሠራተኞች ፍልሠት ኢትዮጵያዊያን ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ ቅጥር እድል እንዲያገኙ ለማስቻል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ተብሏል።
የሳዑዲ ዓረቢያ ፍርድ ቤት ከአደንዛዥ እጽ ዝውውር ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት የጣለባቸው በርካታ ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ በውይይቱ ወቅት ይነሳ አይነሳ መረጃው አላመለከትም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍6😡1
“ጥቃቱን ለጊዜው ትቼዋለሁ”ትራምፕ
። ። ። ። ። : : : : : : : : : :
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊፈፅሙት የነበረውን ጥቃት ማራዘማቸውን አሳውቀዋል።
የባህረ ሰላጤው አገራት ሳውዲ አረቢያ፣ኳታርና አረብ ኤሚሬቶች እንዲሁም ሌሎች አገራት ኢራን ላይ ጥቃት እንዳይሰነዝር ጠይቀውኛል ብለዋል ትራምፕ።
ለማክሰኞ ቀን ተቆርጦለት የነበረው ጥቃት ለዲፕሎማሲ ጊዜ መግዣ በሚል ለአሁኑ ቆሟል።
በዕርግጥ ጥቃቱ ለሁለት እና ሶስት ቀናት ያህል እንደተራዘመ መነገሩ ያን ያህል ዘላቂ ሰላም ላያመጣ ይችላል።
ፔንታጎን ቢያንስ ለአሁኑ እርምጃ እንዳይወስድ በትራምፕ ታዟል።
ትራምፕ ኢራን ጋር ያለው ውይይት በጎ ባለመሆኑ ነገ ወደ ጥቃቱ እንመለሳለን በሚልም ዝተዋል።
የትኛውም ስምምነት ቴህራን ኑክሌር ቦምብ እንዳትታጠቅ ማድረግ አለበት የሪፐብሊካኑ ዕምነት ነው።
ፕሬዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያቸው ላይ ተቀባይነት የሌለው ሀሳብ ኢራን የምተቀርብ ከሆነ የጦር ሚኒስቴሩ(ፔንታጎን) ወደ ጥቃት ለመመለስ በተጠንቀ ቅ ላይ እንዲቆይም አዘዋል።
ትራምፕ ማክሰኞ የያዙትን ጥቃት አራዘሙ እንጂ ኢራን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ለማድረስ አሁንም ተዘጋጅተዋል ተብሏል።
ኢራን የመደራደሪያ ነጥቧን በፓኪስታን በኩል ለአሜሪካ መላኳም የሚዘነጋ አይደለም።
ዘገባው የአር ቲ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
። ። ። ። ። : : : : : : : : : :
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊፈፅሙት የነበረውን ጥቃት ማራዘማቸውን አሳውቀዋል።
የባህረ ሰላጤው አገራት ሳውዲ አረቢያ፣ኳታርና አረብ ኤሚሬቶች እንዲሁም ሌሎች አገራት ኢራን ላይ ጥቃት እንዳይሰነዝር ጠይቀውኛል ብለዋል ትራምፕ።
ለማክሰኞ ቀን ተቆርጦለት የነበረው ጥቃት ለዲፕሎማሲ ጊዜ መግዣ በሚል ለአሁኑ ቆሟል።
በዕርግጥ ጥቃቱ ለሁለት እና ሶስት ቀናት ያህል እንደተራዘመ መነገሩ ያን ያህል ዘላቂ ሰላም ላያመጣ ይችላል።
ፔንታጎን ቢያንስ ለአሁኑ እርምጃ እንዳይወስድ በትራምፕ ታዟል።
ትራምፕ ኢራን ጋር ያለው ውይይት በጎ ባለመሆኑ ነገ ወደ ጥቃቱ እንመለሳለን በሚልም ዝተዋል።
የትኛውም ስምምነት ቴህራን ኑክሌር ቦምብ እንዳትታጠቅ ማድረግ አለበት የሪፐብሊካኑ ዕምነት ነው።
ፕሬዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያቸው ላይ ተቀባይነት የሌለው ሀሳብ ኢራን የምተቀርብ ከሆነ የጦር ሚኒስቴሩ(ፔንታጎን) ወደ ጥቃት ለመመለስ በተጠንቀ ቅ ላይ እንዲቆይም አዘዋል።
ትራምፕ ማክሰኞ የያዙትን ጥቃት አራዘሙ እንጂ ኢራን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ለማድረስ አሁንም ተዘጋጅተዋል ተብሏል።
ኢራን የመደራደሪያ ነጥቧን በፓኪስታን በኩል ለአሜሪካ መላኳም የሚዘነጋ አይደለም።
ዘገባው የአር ቲ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12🥱11🤣6👍2🥰2🤯2👏1😢1
የኢራን ፓርላማ የአሜሪካውን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ለሚገድል ማንኛውም ሰው 50 ሚሊዮን ዩሮ (ወደ 58 ሚሊዮን ዶላር ገደማ) የመንግስት የገንዘብ ሽልማት የሚሰጥ አዲስ የህግ ረቂቅ እያዘጋጀ መሆኑ ታወቀ
ይህ በኢራን ከፍተኛ ህግ አውጪዎች ደረጃ እየተመከረበት ያለው አዲስ የህግ ረቂቅ “የእስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ እና የደህንነት ሃይሎች የአረባዊ እርምጃ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፥ መንግስት ለግድያው የተመደበውን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በይፋ እንዲከፍል የሚያስገድድ ነው።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ በሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው እንደተናገሩት፥ ይህ እርምጃ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራን ወታደራዊ መሪዎችን እና አዛዦችን ለገደሉበት አጸፋዊ ምላሽ የተዘጋጀ ነው።
አዚዚ አክለውም ዶናልድ ትራምፕ፣ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የአሜሪካ መካከለኛው ዕዝ (CENTCOM) ዋና አዛዥ በዋናነት መገደል እንዳለባቸው ገልጸው፥ ይህንን የግድያ እርምጃ “ሃይማኖታዊ እና ርዕዮተ-ዓለማዊ ተልዕኮ” ሲሉ ጠርተውታል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ባለፈው መጋቢት ወር ላይ በርካታ የኢራን የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች የትራምፕን ግድያ ዘመቻ የሚደግፉ እና ለዚሁ ተግባር የሚውል የገንዘብ ማሰባሰቢያ ጥሪዎችን የያዙ የጽሑፍ መልዕክቶች ደርሷቸው እንደነበር ተገልጿል።
በተያያዘም በቅርቡ ይፋ የሆኑ የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከኢራን ጋር ግንኙነት አለው የተባለ አንድ ተላላኪ ግለሰብ ትራምፕን ለመግደል በቅድሚያ 5 ሺህ ዶላር ተከፍሎት ሲንቀሳቀስ እንደነበር ተደርሶበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ይህ በኢራን ከፍተኛ ህግ አውጪዎች ደረጃ እየተመከረበት ያለው አዲስ የህግ ረቂቅ “የእስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ እና የደህንነት ሃይሎች የአረባዊ እርምጃ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፥ መንግስት ለግድያው የተመደበውን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በይፋ እንዲከፍል የሚያስገድድ ነው።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ በሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው እንደተናገሩት፥ ይህ እርምጃ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራን ወታደራዊ መሪዎችን እና አዛዦችን ለገደሉበት አጸፋዊ ምላሽ የተዘጋጀ ነው።
አዚዚ አክለውም ዶናልድ ትራምፕ፣ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የአሜሪካ መካከለኛው ዕዝ (CENTCOM) ዋና አዛዥ በዋናነት መገደል እንዳለባቸው ገልጸው፥ ይህንን የግድያ እርምጃ “ሃይማኖታዊ እና ርዕዮተ-ዓለማዊ ተልዕኮ” ሲሉ ጠርተውታል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ባለፈው መጋቢት ወር ላይ በርካታ የኢራን የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች የትራምፕን ግድያ ዘመቻ የሚደግፉ እና ለዚሁ ተግባር የሚውል የገንዘብ ማሰባሰቢያ ጥሪዎችን የያዙ የጽሑፍ መልዕክቶች ደርሷቸው እንደነበር ተገልጿል።
በተያያዘም በቅርቡ ይፋ የሆኑ የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከኢራን ጋር ግንኙነት አለው የተባለ አንድ ተላላኪ ግለሰብ ትራምፕን ለመግደል በቅድሚያ 5 ሺህ ዶላር ተከፍሎት ሲንቀሳቀስ እንደነበር ተደርሶበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣20❤14👍4👏2😢1😎1
በሱሉልታ የእገታ ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩ አራት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ
አዲሱ ነጋሽ ፣ደሮ ተሾመ፣ ደጀኔ ተስፋና ቶላ አለሙ የተባሉ አራት ወጣቶች ነዋሪነታቸው በኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ኑኑ ሳዩ ቀበሌ ነው።ወጣቶቹ በአካባቢያቸው የሚታወቁት የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ሲሆን በመዝናኛ ስፍራም ሆነ በተለያዩ ቦታውች የማይነጣጠሉ ጓደኛማቾች መሆናቸዉን የወረዳዉ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ሙሉ ጉደታ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ከቅርብ ግዜያት ወዲህ ግን የተለየና የተለወጠ እንቅስቃሴ በአካባቢው ያሣዩ እንደነበረም ይገልፃሉ።
ወጣቶቹ በአካባቢው ማሕበረሠብ ውስጥ ትዝብት ውስጥ ወድቀው ባሉበት ወቅት ጥር 5 ቀን 2017 ዓም ምሽት አልጌ ሠዮ በተባለ ስፍራ ያልተፈቀደ የጦር መሠርያ በመታጠቅ በአካባቢው ነዋሪ የሆኑት አራት ግለሠቦች አግተው በመውሰድ ከአንድ መቶ እስከ ሑለት መቶ ሺሕ ብር ድረስ ቤተሠቦቻቸው እንዲያመጡ በማስገደድ ቆይተዋል። ከጥቅምት 21 እስከ ጥር 5 ቀን 2017 ዓም ድረስ በዚሑ አካባቢ ለአራት ወራት የእገታ ወንጀል ሲፈፅሙ በመቆየት ገንዘብ ቤተሠቦቻቸውን ጠይቀው የሰጡትን ሲለቁ መክፍል አንችልም ያሉት ደግሞ ልጆቻቸውን ጭምር በማገት ተደራራቢ ወንጀል ሲፈፅሙ እንደነበረ በማስረጃ ተረጋግጧል፡፡
ወጣቶቹ አንድ ግለሠብን አግተው በመውሠድ ለወራት ባዘጋጁት ስፍራ በማስቀመጥ ካቆዩት በኃላ 200 ሺ ብር እንዲያመጣ ጠይቀውት የለኝም በማለቱ ፣ እሱን በመልቀቅ በእርሱ ፋንታ ልጁን አግተው በመውሰድ 300 ሺሕ ብር ተቀብለዋል፡፡የተቋቋመው የፀጥታ ግብረ ኃይል ሙሉ መረጃ ከደረሰዉ በኃላ ባደረገዉ ክትትል አራቱንም በቁጥጥር ስር አዉሏል፡፡ፖሊስም አስፈላጊ ማጣራት ካደረገ በኃላ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለአቃቢ ሕግ ይልካል። አቃቢ ሕግም ስድስት ክሶችን መስርቷል፡፡
ክሱን የተመለከተው የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራቱ ተከሳሾች በሰላማዊ ሠው መሐል ገብተው ሕገወጥ የጦር መሣርያ ታጥቀው ጨለማን ተገን በማድረግ ከፍተኛ የውብድና ተግባር በመፈፀማቸው ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓም በዋለው ችሎት እያንዳዳቸው በአስራ ስምንት አመት እስራት እንዲቀጡ የወሠነባቸው መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር ሙሉ ጉደታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
Via : dagu
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አዲሱ ነጋሽ ፣ደሮ ተሾመ፣ ደጀኔ ተስፋና ቶላ አለሙ የተባሉ አራት ወጣቶች ነዋሪነታቸው በኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ኑኑ ሳዩ ቀበሌ ነው።ወጣቶቹ በአካባቢያቸው የሚታወቁት የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ሲሆን በመዝናኛ ስፍራም ሆነ በተለያዩ ቦታውች የማይነጣጠሉ ጓደኛማቾች መሆናቸዉን የወረዳዉ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ሙሉ ጉደታ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ከቅርብ ግዜያት ወዲህ ግን የተለየና የተለወጠ እንቅስቃሴ በአካባቢው ያሣዩ እንደነበረም ይገልፃሉ።
ወጣቶቹ በአካባቢው ማሕበረሠብ ውስጥ ትዝብት ውስጥ ወድቀው ባሉበት ወቅት ጥር 5 ቀን 2017 ዓም ምሽት አልጌ ሠዮ በተባለ ስፍራ ያልተፈቀደ የጦር መሠርያ በመታጠቅ በአካባቢው ነዋሪ የሆኑት አራት ግለሠቦች አግተው በመውሰድ ከአንድ መቶ እስከ ሑለት መቶ ሺሕ ብር ድረስ ቤተሠቦቻቸው እንዲያመጡ በማስገደድ ቆይተዋል። ከጥቅምት 21 እስከ ጥር 5 ቀን 2017 ዓም ድረስ በዚሑ አካባቢ ለአራት ወራት የእገታ ወንጀል ሲፈፅሙ በመቆየት ገንዘብ ቤተሠቦቻቸውን ጠይቀው የሰጡትን ሲለቁ መክፍል አንችልም ያሉት ደግሞ ልጆቻቸውን ጭምር በማገት ተደራራቢ ወንጀል ሲፈፅሙ እንደነበረ በማስረጃ ተረጋግጧል፡፡
ወጣቶቹ አንድ ግለሠብን አግተው በመውሠድ ለወራት ባዘጋጁት ስፍራ በማስቀመጥ ካቆዩት በኃላ 200 ሺ ብር እንዲያመጣ ጠይቀውት የለኝም በማለቱ ፣ እሱን በመልቀቅ በእርሱ ፋንታ ልጁን አግተው በመውሰድ 300 ሺሕ ብር ተቀብለዋል፡፡የተቋቋመው የፀጥታ ግብረ ኃይል ሙሉ መረጃ ከደረሰዉ በኃላ ባደረገዉ ክትትል አራቱንም በቁጥጥር ስር አዉሏል፡፡ፖሊስም አስፈላጊ ማጣራት ካደረገ በኃላ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለአቃቢ ሕግ ይልካል። አቃቢ ሕግም ስድስት ክሶችን መስርቷል፡፡
ክሱን የተመለከተው የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራቱ ተከሳሾች በሰላማዊ ሠው መሐል ገብተው ሕገወጥ የጦር መሣርያ ታጥቀው ጨለማን ተገን በማድረግ ከፍተኛ የውብድና ተግባር በመፈፀማቸው ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓም በዋለው ችሎት እያንዳዳቸው በአስራ ስምንት አመት እስራት እንዲቀጡ የወሠነባቸው መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር ሙሉ ጉደታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
Via : dagu
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍3🤯2😢2
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት 667 የፈተና ማዕከላት ተዘጋጁ
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ገለፀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለፋና እንደገለጹት÷ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልል ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ÷ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።
ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩንም አንስተዋል።
ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ሉት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ገለፀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለፋና እንደገለጹት÷ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልል ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ÷ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።
ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩንም አንስተዋል።
ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ሉት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7😁6👍2
ቡና ለገበያ አውጡ‼️
በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ምክንያት የቡና ዋጋ ስለማይጨምር፣ አምራችና ነጋዴዎች ምርታቸውን ለገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው ተገለጸ‼️
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበለ የመካከለኛው ምስራቅን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚቀሰቀሱ ግጭቶች ምክንያት የቡና ዋጋ ሊጨምር ይችላል በሚል የተሳሳተ መረጃ ነጋዴዎች ኪሳራ ውስጥ እንዳይገቡ አሳስበዋል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና ምርቷ በስፋት የምትታወቀው ብራዚል ከሰኔ ወር ጀምሮ 78 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ለገበያ ስለምታቀርብ፣ የሀገራችን አምራችና ነጋዴዎች ከዛ አስቀድመው ገበያ ላይ ቢያወጡት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ የቡና ዋጋ በቶን 30 በመቶ ያህል መቀነሱን የገለጹት ዶክተር አዱኛ፤ ምንም እንኳን ለሀገራችን ጉዳት ሆኖ የሚታይ ባይሆንም የቬትናምና የብራዚል ቡና ወደ ገበያ ከገባ ከዚህ በታች ሊወርድ ስለሚችል ምርቱን ባለው ገበያ ማቅረብ ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያን ጨምሮ ቬትናምና ብራዚል በዚህ ዓመት ከፍተኛ የቡና ምርት ማምረታቸው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊከማች ይችላል ተብሎ ከተገመተው 8 ሚሊዮን ቶን በላይ የቡና ምርት እንዲኖር እንደሚያደርግና ይህም ለዋጋው መቀነስ አንዱ ምክንያት እንደሆነ ገልፀዋል።
የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ በማጓጓዣው ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ ስለሚያሳድር በገበያው ላይ ተግዳሮት ቢፈጥርም፣ በቡና ዋጋ ላይ ግን ለውጥ እንደማይኖር ነው የተናገሩት።
የኢትዮጵያ የቡና ምርት ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በዋጋም በገበያም የተሻለ እንደሆነና እስካሁንም ከደረጃ 4 በላይ የሆኑ የቡና ዓይነቶችን ብቻ ለዓለም አቀፉ ገበያ በማቅረብ ታዋቂነትንና የገበያ ትስስርን የመፍጠር ሂደቱ ውጤታማ እንዳደረገው ተናግረዋል።
በዘንድሮው የቡና ሽያጭም ኢትዮጵያ 320 ሺህ ሜትሪክ ቶን ቡና ወደ ውጭ ገበያ የላከች ሲሆን፣ ከዚህም 2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደተገኘ አመልክተዋል።
የቡና አምራችና ነጋዴዎች በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ምክንያት የቡና ዋጋ ይጨምራል በሚል ቡና ማከማቸት እንደሌለባቸውና ምርታቸውን ባለው ገበያ መሸጥ እንዳለባቸው ተመላክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ምክንያት የቡና ዋጋ ስለማይጨምር፣ አምራችና ነጋዴዎች ምርታቸውን ለገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው ተገለጸ‼️
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበለ የመካከለኛው ምስራቅን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚቀሰቀሱ ግጭቶች ምክንያት የቡና ዋጋ ሊጨምር ይችላል በሚል የተሳሳተ መረጃ ነጋዴዎች ኪሳራ ውስጥ እንዳይገቡ አሳስበዋል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና ምርቷ በስፋት የምትታወቀው ብራዚል ከሰኔ ወር ጀምሮ 78 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ለገበያ ስለምታቀርብ፣ የሀገራችን አምራችና ነጋዴዎች ከዛ አስቀድመው ገበያ ላይ ቢያወጡት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ የቡና ዋጋ በቶን 30 በመቶ ያህል መቀነሱን የገለጹት ዶክተር አዱኛ፤ ምንም እንኳን ለሀገራችን ጉዳት ሆኖ የሚታይ ባይሆንም የቬትናምና የብራዚል ቡና ወደ ገበያ ከገባ ከዚህ በታች ሊወርድ ስለሚችል ምርቱን ባለው ገበያ ማቅረብ ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያን ጨምሮ ቬትናምና ብራዚል በዚህ ዓመት ከፍተኛ የቡና ምርት ማምረታቸው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊከማች ይችላል ተብሎ ከተገመተው 8 ሚሊዮን ቶን በላይ የቡና ምርት እንዲኖር እንደሚያደርግና ይህም ለዋጋው መቀነስ አንዱ ምክንያት እንደሆነ ገልፀዋል።
የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ በማጓጓዣው ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ ስለሚያሳድር በገበያው ላይ ተግዳሮት ቢፈጥርም፣ በቡና ዋጋ ላይ ግን ለውጥ እንደማይኖር ነው የተናገሩት።
የኢትዮጵያ የቡና ምርት ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በዋጋም በገበያም የተሻለ እንደሆነና እስካሁንም ከደረጃ 4 በላይ የሆኑ የቡና ዓይነቶችን ብቻ ለዓለም አቀፉ ገበያ በማቅረብ ታዋቂነትንና የገበያ ትስስርን የመፍጠር ሂደቱ ውጤታማ እንዳደረገው ተናግረዋል።
በዘንድሮው የቡና ሽያጭም ኢትዮጵያ 320 ሺህ ሜትሪክ ቶን ቡና ወደ ውጭ ገበያ የላከች ሲሆን፣ ከዚህም 2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደተገኘ አመልክተዋል።
የቡና አምራችና ነጋዴዎች በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ምክንያት የቡና ዋጋ ይጨምራል በሚል ቡና ማከማቸት እንደሌለባቸውና ምርታቸውን ባለው ገበያ መሸጥ እንዳለባቸው ተመላክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍4
⚡️ እስራኤል በጋዛ፣ ሊባኖስ እና ሶሪያ 1,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ገደማ መሬት መቆጣጠሯ ተገለጠ!
የፋይናንሻል ታይምስ ባደረገው አዲስ ትንተና መሠረት፣ ከጥቅምት 7 ጥቃት በኋላ እስራኤል በጋዛ፣ በሊባኖስ እና በሶሪያ በድምሩ የሀገሪቱን የ1949 ድንበር 5% የሚያክል (1,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር) መሬት በቁጥጥሯ ሥር አውላለች።
በደቡብ ሊባኖስ፦ ከተያዘው መሬት ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው እዚህ የሚገኝ ሲሆን፣ እስራኤል ሄዝቦላህን ወደ ኋላ ለመግፋት በሚል እስከ 12 ኪሎ ሜትር ዘልቃ በመግባት “የደህንነት ቀጠና” ፈጥራለች። ሙሉ መንደሮች የወደሙ ሲሆን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር ሁኔታውን “ከጋዛው ሞዴል” ጋር አነጻጽረውታል።
በጋዛ ሰርጥ፦ የእስራኤል ጦር በአሁኑ ወቅት ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የጋዛ ግዛት የተቆጣጠረ ሲሆን፣ ተጨማሪ የደህንነት ቀጠናዎችን በመፍጠሩ ምክንያት የጋዛ ህዝብ ከጦርነቱ በፊት ከነበረው ይዞታው 40% በሚሆነው ጠባብ መሬት ላይ ተጨናንቆ እንዲኖር ተገዷል።
በሶሪያ፦ እስራኤል ከኮረብታማው የሄርሞን ተራራ በስተደቡብ ያለውን የድንበር አካባቢ ወደ 233 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚጠጋ መሬት ተቆጣጥራለች።
ኔታንያሁ ጦራቸው ከሊባኖስ “አይወጣም” ማለታቸውን ተከትሎ፣ እንዲሁም የእስራኤል ቀኝ አክራሪ ሚኒስትሮች በቦታው ላይ አዳዲስ ሰፈራዎች እንዲመሰረቱና “ሊታኒ ወንዝ” አዲሱ ድንበር እንዲሆን መጠየቃቸው፣ ይዞታው ቋሚ ሊሆን ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት በጎረቤት ሀገራት ላይ ፈጥሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የፋይናንሻል ታይምስ ባደረገው አዲስ ትንተና መሠረት፣ ከጥቅምት 7 ጥቃት በኋላ እስራኤል በጋዛ፣ በሊባኖስ እና በሶሪያ በድምሩ የሀገሪቱን የ1949 ድንበር 5% የሚያክል (1,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር) መሬት በቁጥጥሯ ሥር አውላለች።
በደቡብ ሊባኖስ፦ ከተያዘው መሬት ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው እዚህ የሚገኝ ሲሆን፣ እስራኤል ሄዝቦላህን ወደ ኋላ ለመግፋት በሚል እስከ 12 ኪሎ ሜትር ዘልቃ በመግባት “የደህንነት ቀጠና” ፈጥራለች። ሙሉ መንደሮች የወደሙ ሲሆን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር ሁኔታውን “ከጋዛው ሞዴል” ጋር አነጻጽረውታል።
በጋዛ ሰርጥ፦ የእስራኤል ጦር በአሁኑ ወቅት ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የጋዛ ግዛት የተቆጣጠረ ሲሆን፣ ተጨማሪ የደህንነት ቀጠናዎችን በመፍጠሩ ምክንያት የጋዛ ህዝብ ከጦርነቱ በፊት ከነበረው ይዞታው 40% በሚሆነው ጠባብ መሬት ላይ ተጨናንቆ እንዲኖር ተገዷል።
በሶሪያ፦ እስራኤል ከኮረብታማው የሄርሞን ተራራ በስተደቡብ ያለውን የድንበር አካባቢ ወደ 233 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚጠጋ መሬት ተቆጣጥራለች።
ኔታንያሁ ጦራቸው ከሊባኖስ “አይወጣም” ማለታቸውን ተከትሎ፣ እንዲሁም የእስራኤል ቀኝ አክራሪ ሚኒስትሮች በቦታው ላይ አዳዲስ ሰፈራዎች እንዲመሰረቱና “ሊታኒ ወንዝ” አዲሱ ድንበር እንዲሆን መጠየቃቸው፣ ይዞታው ቋሚ ሊሆን ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት በጎረቤት ሀገራት ላይ ፈጥሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡10❤7👍6
የአዋሽ-ኮምቦልቻ-ሐራ ገበያ የባቡር መስመር ግንባታ ከዓመታት መቋረጥ በኋላ ዳግም ተጀመረ!
በአዋሽ-ኮምቦልቻ-ሐራ ገበያ መስመር ላይ ተቋርጦ የነበረው የ1.7 ቢሊዮን ዶላር የባቡር መስመር ግንባታ፣ ከዓመታት መዘግየት በኋላ በይፋ ዳግም መጀመሩ ተገለጸ።
ይህ 392 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኤሌክትሪክ ባቡር መስመር፣ የአማራ ክልል ዋና ዋና የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከላትን ከአዲስ አበባ-ጂቡቲ የባቡር ኮሪደር ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ለሀገሪቱ የጭነትና የሰው ትራንስፖርት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
ግንባታው በ2015 እ.ኤ.አ. በቱርኩ "ያፒ መርከዚ" ኩባንያ የተጀመረ ቢሆንም፣ በኖቬምበር 2020 በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ምክንያት መሠረተ ልማቶቹ ላይ ጉዳት ደርሶና ውሎች ተስተጓጉለው ሥራው ቆሞ ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት በአካባቢው ያለው የጸጥታ ሁኔታ በመሻሻሉ ሠራተኞችና መሣሪያዎች ወደ ሳይት የተመለሱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ባቡር ኮርፖሬሽን የጥገና እና መልሶ ግንባታ ሥራው በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአዋሽ-ኮምቦልቻ-ሐራ ገበያ መስመር ላይ ተቋርጦ የነበረው የ1.7 ቢሊዮን ዶላር የባቡር መስመር ግንባታ፣ ከዓመታት መዘግየት በኋላ በይፋ ዳግም መጀመሩ ተገለጸ።
ይህ 392 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኤሌክትሪክ ባቡር መስመር፣ የአማራ ክልል ዋና ዋና የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከላትን ከአዲስ አበባ-ጂቡቲ የባቡር ኮሪደር ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ለሀገሪቱ የጭነትና የሰው ትራንስፖርት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
ግንባታው በ2015 እ.ኤ.አ. በቱርኩ "ያፒ መርከዚ" ኩባንያ የተጀመረ ቢሆንም፣ በኖቬምበር 2020 በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ምክንያት መሠረተ ልማቶቹ ላይ ጉዳት ደርሶና ውሎች ተስተጓጉለው ሥራው ቆሞ ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት በአካባቢው ያለው የጸጥታ ሁኔታ በመሻሻሉ ሠራተኞችና መሣሪያዎች ወደ ሳይት የተመለሱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ባቡር ኮርፖሬሽን የጥገና እና መልሶ ግንባታ ሥራው በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍4🤣4
ደረሰኝ ሳይሰጡ ሽያጭ የፈፀሙ ግብር ከፋዩች ቅጣትን ከ50 ሺህ ብር ወደ 100 ሺህ ብር ከፍ እንዲል የሚያደርግ የታክስ አስተዳደር የማሻሻያ አዋጅ ተዘጋጀ
በዛሬዉ እለት ለ10 አመት ሲሰራበት የቆየዉን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት እና ባለሙያዎች ጋር የግብአት መሰባሰብ ዉይይት አድርጓል።
በዚህ የማሻሻያ ረቂቅ ዉስጥ ተሻሽለው ከቀረቡ ነጥቦች መካከል ደረሰኝ ሳይሰጡ ሽያጭ የሚፈፅሙ ግብር ከፋዩች ላይ ከዚህ ቀደም ቅጣት ተብሎ ተቀምጦ የነበረዉን የገንዘብ ቅጣት ከፍ ያደረገ ህግ ተቀምጦበታል።
በዚህም 50 ሺህ ብር ቅጣትን ያስቀምጥ የነበረዉን በማሻሻል የ100 ሺህ ብር ቅጣት የሚጥል አዲስ ህግ በረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ ላይ ተቀምጧል።
ይህም በእያንዳንዱ ደረሰኝ የደረሰኙ ዋጋ ከግምት ዉስጥም የማይገባ ነዉ ተብሏል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ የህግ አማካሪዉ አቶ ዋሲሁን አባተ እንደገለፁት "የተቀመጠዉ ገንዘቡ መጠን በግብር ከፋዩ ዘንድ እንደ አንድ ወጪ ታሳቢ እየተደረገ መጥቷል፤ ይህ ደግሞ ህገወጥነቱን እየጨመረ እንዲመጣ እያደረገ መጥቷል ብለዋል"።
ለዚህም ማሻሻያ እንዲደረግበት ሆኖ መቀመጡን ለዉይይቱ ተሳታፊዎች አስረድተዋል ።
በዚህ ሽያጭ ደረሰኝ ሳይሰጡ ሽያጭ በሚፈፅሙ ግብር ከፋይ በዚህ ድርጊት ከሁለት ጊዜ በላይ ከተገኙ ግን ወደ እስር የሚወስድ አስተዳደራዊ ቅጣት እንደሚኖር አያይዘዉ ገልፀዋል።
ቁምነገር አየለ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በዛሬዉ እለት ለ10 አመት ሲሰራበት የቆየዉን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት እና ባለሙያዎች ጋር የግብአት መሰባሰብ ዉይይት አድርጓል።
በዚህ የማሻሻያ ረቂቅ ዉስጥ ተሻሽለው ከቀረቡ ነጥቦች መካከል ደረሰኝ ሳይሰጡ ሽያጭ የሚፈፅሙ ግብር ከፋዩች ላይ ከዚህ ቀደም ቅጣት ተብሎ ተቀምጦ የነበረዉን የገንዘብ ቅጣት ከፍ ያደረገ ህግ ተቀምጦበታል።
በዚህም 50 ሺህ ብር ቅጣትን ያስቀምጥ የነበረዉን በማሻሻል የ100 ሺህ ብር ቅጣት የሚጥል አዲስ ህግ በረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ ላይ ተቀምጧል።
ይህም በእያንዳንዱ ደረሰኝ የደረሰኙ ዋጋ ከግምት ዉስጥም የማይገባ ነዉ ተብሏል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ የህግ አማካሪዉ አቶ ዋሲሁን አባተ እንደገለፁት "የተቀመጠዉ ገንዘቡ መጠን በግብር ከፋዩ ዘንድ እንደ አንድ ወጪ ታሳቢ እየተደረገ መጥቷል፤ ይህ ደግሞ ህገወጥነቱን እየጨመረ እንዲመጣ እያደረገ መጥቷል ብለዋል"።
ለዚህም ማሻሻያ እንዲደረግበት ሆኖ መቀመጡን ለዉይይቱ ተሳታፊዎች አስረድተዋል ።
በዚህ ሽያጭ ደረሰኝ ሳይሰጡ ሽያጭ በሚፈፅሙ ግብር ከፋይ በዚህ ድርጊት ከሁለት ጊዜ በላይ ከተገኙ ግን ወደ እስር የሚወስድ አስተዳደራዊ ቅጣት እንደሚኖር አያይዘዉ ገልፀዋል።
ቁምነገር አየለ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10😡7👍3
የዶላር ዋጋ ወደ 159.98 ብር ከፍ አለ፤ ብሔራዊ ባንክ ካቀረበው የውጭ ምንዛሬ ከእጥፍ በላይ ፍላጎት ቀረበበት
አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ የዶላር አማካይ የማሸነፊያ ዋጋ 159.98 ብር መድረሱን ይፋ አደረገ።
ባንኩ ይፋ ባደረገው መግለጫ መሠረት፣ በገበያው ውስጥ አሁንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት መኖሩን የሚያሳዩ ውጤቶች ተመዝግበዋል።
ብሔራዊ ባንኩ ለዚህ ልዩ ጨረታ 500 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ያቀረበ ቢሆንም፣ ከንግድ ባንኮች በኩል የቀረበው አጠቃላይ የፍላጎት መጠን ግን ከቀረበው አቅርቦት በእጥፍ በመጨመር 1.06 ቢሊዮን (አንድ ቢሊዮን ከስድሳ ሚሊዮን) ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል።
በጨረታው ላይ በአጠቃላይ 30 የንግድ ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 14ቱ ባንኮች ብቻ ጨረታውን አሸንፈው የውጭ ምንዛሬውን ማግኘት ችለዋል።
የዕለቱ የምንዛሬ ተመን ዝርዝር፦
1. የማሸነፊያ አማካይ ክብደት ዋጋ (Weighted Average Rate): 159.9865 ብር
2. የመቁረጫ ዋጋ (Marginal/Cut-off Rate): 159.6299 ብር
3. ከፍተኛው የቀረበ የማሸነፊያ ዋጋ:160.9064 ብር
4. ዝቅተኛው የቀረበ የማሸነፊያ ዋጋ:157.3005 ብር
ብሔራዊ ባንክ ከሁለት ወራት በፊት ባካሄደው ተመሳሳይ ጨረታ 70 ሚሊዮን ዶላር አቅርቦ የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ የአንድ ዶላር አማካይ ዋጋ 157 ብር ከ46 ሳንቲም ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ የዶላር አማካይ የማሸነፊያ ዋጋ 159.98 ብር መድረሱን ይፋ አደረገ።
ባንኩ ይፋ ባደረገው መግለጫ መሠረት፣ በገበያው ውስጥ አሁንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት መኖሩን የሚያሳዩ ውጤቶች ተመዝግበዋል።
ብሔራዊ ባንኩ ለዚህ ልዩ ጨረታ 500 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ያቀረበ ቢሆንም፣ ከንግድ ባንኮች በኩል የቀረበው አጠቃላይ የፍላጎት መጠን ግን ከቀረበው አቅርቦት በእጥፍ በመጨመር 1.06 ቢሊዮን (አንድ ቢሊዮን ከስድሳ ሚሊዮን) ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል።
በጨረታው ላይ በአጠቃላይ 30 የንግድ ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 14ቱ ባንኮች ብቻ ጨረታውን አሸንፈው የውጭ ምንዛሬውን ማግኘት ችለዋል።
የዕለቱ የምንዛሬ ተመን ዝርዝር፦
1. የማሸነፊያ አማካይ ክብደት ዋጋ (Weighted Average Rate): 159.9865 ብር
2. የመቁረጫ ዋጋ (Marginal/Cut-off Rate): 159.6299 ብር
3. ከፍተኛው የቀረበ የማሸነፊያ ዋጋ:160.9064 ብር
4. ዝቅተኛው የቀረበ የማሸነፊያ ዋጋ:157.3005 ብር
ብሔራዊ ባንክ ከሁለት ወራት በፊት ባካሄደው ተመሳሳይ ጨረታ 70 ሚሊዮን ዶላር አቅርቦ የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ የአንድ ዶላር አማካይ ዋጋ 157 ብር ከ46 ሳንቲም ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20😢5😱4👍3
ትራምፕ ሌላ ጦርነት ሊጀምሩ ነው‼️
ትራምፕ በኩባ ላይ ጦርነት ለመጀመር እያሰቡ መሆኑን ፖለቲኮ ዘግቧል።
"ትራምፕ እና አማካሪዎቹ በኩባ ላይ እየተደረገ ያለው ጫና ባለመስራቱ እንደተበሳጩ እና ወታደራዊ አማራጭን ለመጠቀም እያጤኑ መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል። አሜሪካ ጦርነት ከጀመረች ኩባ እፋለማለሁ ብላለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ትራምፕ በኩባ ላይ ጦርነት ለመጀመር እያሰቡ መሆኑን ፖለቲኮ ዘግቧል።
"ትራምፕ እና አማካሪዎቹ በኩባ ላይ እየተደረገ ያለው ጫና ባለመስራቱ እንደተበሳጩ እና ወታደራዊ አማራጭን ለመጠቀም እያጤኑ መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል። አሜሪካ ጦርነት ከጀመረች ኩባ እፋለማለሁ ብላለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17😢5🙉3👍2🤷♂1😈1👀1
በኦሮሚያ ክልል ታጣቂዎች በሕዝብ አውቶብስ ላይ ተኩስ በመክፈት ተሳፋሪዎችን አገቱ
በኦሮሚያ ክልል ከገብረ ጉራቻ ወደ ፍቼ በሚወስደው መንገድ አሊደሮ በተባለ አካባቢ ታጣቂዎች ሕዝብ ጭኖ እየተጓዘ በነበረ ልዩ የሕዝብ አውቶብስ ላይ ተኩስ በመክፈትና ተሽከርካሪውን አስገድደው በማስቆም ከሦስት ሰዎች በቀር ሁሉንም ተሳፋሪዎች አፍነው መውሰዳቸውን የካቢኔ ሹፌሮች ገለጹ።
የአውቶብሱን መስታወትና ጎማዎች በመምታት የተፈጸመውን ይህንን ጥቃት ተከትሎ፣ አካባቢው ለዓመታት የታጠቁ ወንበዴዎች እገታ፣ ዘረፋና ግድያ የሚፈጽሙበት ቢሆንም በጉዳቱ ግዝፈት ልክ ትኩረት እንዳልተሰጠው የተጠቆመ ሲሆን፤ የሕግ አስከባሪዎች ተሳፋሪዎችን ለማዳን ሕይወታቸውን ጭምር እየከፈሉ መሆኑ ቢመሰገንም፣ የአፈና ወንጀሉን ከስር መሰረት ለመንቀልና ሾፌሮችን፣ ረዳቶችንና ተሳፋሪዎችን ከአደጋ ለመጠበቅ የአሠራር ግምገማ በማድረግ አዳዲስ ስልቶችን መከተልና በቂ ጥበቃ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በኦሮሚያ ክልል ከገብረ ጉራቻ ወደ ፍቼ በሚወስደው መንገድ አሊደሮ በተባለ አካባቢ ታጣቂዎች ሕዝብ ጭኖ እየተጓዘ በነበረ ልዩ የሕዝብ አውቶብስ ላይ ተኩስ በመክፈትና ተሽከርካሪውን አስገድደው በማስቆም ከሦስት ሰዎች በቀር ሁሉንም ተሳፋሪዎች አፍነው መውሰዳቸውን የካቢኔ ሹፌሮች ገለጹ።
የአውቶብሱን መስታወትና ጎማዎች በመምታት የተፈጸመውን ይህንን ጥቃት ተከትሎ፣ አካባቢው ለዓመታት የታጠቁ ወንበዴዎች እገታ፣ ዘረፋና ግድያ የሚፈጽሙበት ቢሆንም በጉዳቱ ግዝፈት ልክ ትኩረት እንዳልተሰጠው የተጠቆመ ሲሆን፤ የሕግ አስከባሪዎች ተሳፋሪዎችን ለማዳን ሕይወታቸውን ጭምር እየከፈሉ መሆኑ ቢመሰገንም፣ የአፈና ወንጀሉን ከስር መሰረት ለመንቀልና ሾፌሮችን፣ ረዳቶችንና ተሳፋሪዎችን ከአደጋ ለመጠበቅ የአሠራር ግምገማ በማድረግ አዳዲስ ስልቶችን መከተልና በቂ ጥበቃ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢16❤14💔12👍4
መረጃ‼️
የኦሮሚያ ክልል የጸጥታና አሥተዳድር ቢሮ፣ የመንግሥትን የሠላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ማኅበረሰቡ የተቀላቀሉ የቀድሞ የ"ሸኔ" ታጣቂዎችንና ቤተሰቦቻቸውን ቡድኑ እየገደለ፣ አፍኖ እየወሠደና ቤታቸውን እያቃጠለ ይገኛል ሲል ከሠሠ።
በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች አርሶ አደሮችን የመዝረፍ፣ ሰዎችን አግቶ የማስለቀቂያ ገንዘብ የመጠየቅና ባለሀብቶችን በማስፈራራት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ የመቀበል ወንጀሎችን የሚፈጽሙት የ"ሸኔ" ታጣቂዎች ናቸው ሲል የከሠሠው ቢሮው፣ ታጣቂዎቹ ከሻዕቢያ፣ ከሕወሃትና ሌሎች ጠላቶች ተልእኮ የሚቀበሉ ናቸው በማለት ጭምር ወንጅሏል።
ጥቂቶቹ ታጣቂዎች "ከተራ ዝርፊያ" ያለፈ ምንም ዓይነት ፖለቲካዊ ዓላማ እንደሌላቸው የቢሮው ኃላፊ ኮሚሽነር ጄነራል አራርሳ መርዳሳ መናገራቸውን ቢሮው በይፋዊ ማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሠራጨው መረጃ ገልጿል።
ኮሚሽነር ጄነራል አራርሳ፣ የመንግሥትን የሠላም ጥሪ በማይቀበሉ ታጣቂዎች ላይ የጸጥታ ኃይሎች አስፈላጊውን ርምጃ ይወስዳሉ ማለታቸውንም ከቢሮው መረጃ ላይ ተመልክተናል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኦሮሚያ ክልል የጸጥታና አሥተዳድር ቢሮ፣ የመንግሥትን የሠላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ማኅበረሰቡ የተቀላቀሉ የቀድሞ የ"ሸኔ" ታጣቂዎችንና ቤተሰቦቻቸውን ቡድኑ እየገደለ፣ አፍኖ እየወሠደና ቤታቸውን እያቃጠለ ይገኛል ሲል ከሠሠ።
በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች አርሶ አደሮችን የመዝረፍ፣ ሰዎችን አግቶ የማስለቀቂያ ገንዘብ የመጠየቅና ባለሀብቶችን በማስፈራራት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ የመቀበል ወንጀሎችን የሚፈጽሙት የ"ሸኔ" ታጣቂዎች ናቸው ሲል የከሠሠው ቢሮው፣ ታጣቂዎቹ ከሻዕቢያ፣ ከሕወሃትና ሌሎች ጠላቶች ተልእኮ የሚቀበሉ ናቸው በማለት ጭምር ወንጅሏል።
ጥቂቶቹ ታጣቂዎች "ከተራ ዝርፊያ" ያለፈ ምንም ዓይነት ፖለቲካዊ ዓላማ እንደሌላቸው የቢሮው ኃላፊ ኮሚሽነር ጄነራል አራርሳ መርዳሳ መናገራቸውን ቢሮው በይፋዊ ማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሠራጨው መረጃ ገልጿል።
ኮሚሽነር ጄነራል አራርሳ፣ የመንግሥትን የሠላም ጥሪ በማይቀበሉ ታጣቂዎች ላይ የጸጥታ ኃይሎች አስፈላጊውን ርምጃ ይወስዳሉ ማለታቸውንም ከቢሮው መረጃ ላይ ተመልክተናል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪10❤7👍4✍2🙉2👏1😁1😢1
አርሰናል የዋንጫ ባለቤት መሆኑን ተከትሎ ከአቶ ጌታቸው ረዳ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ተላለፈ
የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ባለቤት መሆኑን ተከትሎ፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ "Bravo Arsenal" በማለት ለክለቡና ለደጋፊዎቹ ያላቸውን አድናቆትና ደስታ ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ባለቤት መሆኑን ተከትሎ፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ "Bravo Arsenal" በማለት ለክለቡና ለደጋፊዎቹ ያላቸውን አድናቆትና ደስታ ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤43😁41👍16🤪6👏3🥱2🥰1🎉1👌1😎1
ጥንቃቄ‼️
በፋይዳ ማጣመር ስም እንዳይጭበረበሩ‼️
ደንበኞች የባንክ ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያቸው ጋር እንዲያጣምሩ የተጀመረውን ሥራ አንዳንድ አጭበርባሪዎች እንደአጋጣሚ ለመጠቀም እየሞከሩ መሆኑ ተደርሶበታል።
በመሆኑም ደንበኞች የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች በማድረግ ራሳቸውን ከአጭበርባሪዎች እንዲከላከሉ ባንኩ አሳውቋል፡
• በባንኩ ቅርንጫፎች በመገኘት ወይም ባንካችን ያዘጋጀውን የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) በመጠቀም ብቻ የሂሳብ ቁጥርዎን ከፋይዳ መታወቂያዎ ጋር ያስተሳስሩ፤
• የማስተሳሰሩ ሥራ በስልክ ተደውሎ ወይም በማህበራዊ ሚዲያ በሚላኩ መልእክቶች የማይሠራ መሆኑን ተገንዝበው መሰል ጥያቄዎችን አያስተናግዱ፤
• ባሉበት በበይነ መረብ ለማስተሳሰር ሲሞክሩ እርዳታ ከፈለጉ ከማያውቁት ወይም በሚገባ ከማያምኑት ሰው እገዛ አይጠይቁ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በፋይዳ ማጣመር ስም እንዳይጭበረበሩ‼️
ደንበኞች የባንክ ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያቸው ጋር እንዲያጣምሩ የተጀመረውን ሥራ አንዳንድ አጭበርባሪዎች እንደአጋጣሚ ለመጠቀም እየሞከሩ መሆኑ ተደርሶበታል።
በመሆኑም ደንበኞች የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች በማድረግ ራሳቸውን ከአጭበርባሪዎች እንዲከላከሉ ባንኩ አሳውቋል፡
• በባንኩ ቅርንጫፎች በመገኘት ወይም ባንካችን ያዘጋጀውን የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) በመጠቀም ብቻ የሂሳብ ቁጥርዎን ከፋይዳ መታወቂያዎ ጋር ያስተሳስሩ፤
• የማስተሳሰሩ ሥራ በስልክ ተደውሎ ወይም በማህበራዊ ሚዲያ በሚላኩ መልእክቶች የማይሠራ መሆኑን ተገንዝበው መሰል ጥያቄዎችን አያስተናግዱ፤
• ባሉበት በበይነ መረብ ለማስተሳሰር ሲሞክሩ እርዳታ ከፈለጉ ከማያውቁት ወይም በሚገባ ከማያምኑት ሰው እገዛ አይጠይቁ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍5
#EU : የአውሮፓ ኅብረት ከሁለት ዓመት በፊት በኢትዮጵያውያን ላይ የጣለውን የቪዛ ገደብ ማንሳቱን አስታውቋል።
" የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ በአውሮፓ የሚኖሩ ዜጎቹን ለመቀበል ያሳየው ተባባሪነት አናሳ ነው " በሚል በኢትዮጵያውያን ላይ የቪዛ ገደብ ተጥሎ ቆይቷል።
የአውሮፓ ኅብረት ምክር ቤት አሁን ባወጣው መግለጫ፤ በኅብረቱ አባል አገራት ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በመለየት እና ወደ አገራቸው በመመለስ ረገድ መሻሻሎች ስለታዩ ገደቡ እንዲነሳ ተወስኗል።
ተጠሎ የነበረው እግዳ ምን ነበር ?
- አባል ሀገራት ኢትዮጵያውያን በሚያቀርቧቸው ማስረጃዎች መሠረት ቪዛ ሲጠይቁ የሚያስፈልጓቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ማንሳት (waiving requirements) እንዳይችሉ፤
- የኅብረቱ አባል ሀገራት ከሁለት ጊዜ በላይ ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ለመግባት የሚያስችለውን ቪዛ ለኢትዮጵያውያን መስጠት እንደማይችሉ ፤
- የዲፕሎማቲክ ወይም የሰርቪስ ፓስፖርት የያዙ ኢትዮጵያውያን ቪዛ ሲፈልጉ መደበኛ የቪዛ ክፍያ ለመክፈል እንደሚገደዱ፤
- መደበኛ ቪዛ ለማግኘት የሚጠበቀው የ15 ቀን ጊዜ ወደ 45 ቀን ከፍ እንዲል ... ተወስኖ ነበር።
አሁን ግን ይህ የቪዛ እገዳ ተነስቷል።
በሌላ በኩል፣ ከዚህ ቀደም በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ መስጠት አቋርጦት የነበረውን የበጀት ድጋፍ መልሶ አስጀምሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
" የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ በአውሮፓ የሚኖሩ ዜጎቹን ለመቀበል ያሳየው ተባባሪነት አናሳ ነው " በሚል በኢትዮጵያውያን ላይ የቪዛ ገደብ ተጥሎ ቆይቷል።
የአውሮፓ ኅብረት ምክር ቤት አሁን ባወጣው መግለጫ፤ በኅብረቱ አባል አገራት ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በመለየት እና ወደ አገራቸው በመመለስ ረገድ መሻሻሎች ስለታዩ ገደቡ እንዲነሳ ተወስኗል።
ተጠሎ የነበረው እግዳ ምን ነበር ?
- አባል ሀገራት ኢትዮጵያውያን በሚያቀርቧቸው ማስረጃዎች መሠረት ቪዛ ሲጠይቁ የሚያስፈልጓቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ማንሳት (waiving requirements) እንዳይችሉ፤
- የኅብረቱ አባል ሀገራት ከሁለት ጊዜ በላይ ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ለመግባት የሚያስችለውን ቪዛ ለኢትዮጵያውያን መስጠት እንደማይችሉ ፤
- የዲፕሎማቲክ ወይም የሰርቪስ ፓስፖርት የያዙ ኢትዮጵያውያን ቪዛ ሲፈልጉ መደበኛ የቪዛ ክፍያ ለመክፈል እንደሚገደዱ፤
- መደበኛ ቪዛ ለማግኘት የሚጠበቀው የ15 ቀን ጊዜ ወደ 45 ቀን ከፍ እንዲል ... ተወስኖ ነበር።
አሁን ግን ይህ የቪዛ እገዳ ተነስቷል።
በሌላ በኩል፣ ከዚህ ቀደም በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ መስጠት አቋርጦት የነበረውን የበጀት ድጋፍ መልሶ አስጀምሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍2
የሁለት ወራት ደመወዝ የለም-ህወሓት‼️
በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የህወሃት ቡድን፣ በትግራይ ክልል ለሚገኝ ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ የግንቦት እና የሰኔ ወራት ደመወዝ እንዳይከፈል የሚል ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈ።
ዶ/ር ደብረጽዮን ለክልሉ ዞኖች፣ ወረዳዎች እና ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ጭምር ባስተላለፉት የጽሁፍ ትዕዛዝ «ለሁለት ወራት ደሞዝ የለም፤ ይህንን ከወዲሁ እወቁት» ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ለውሳኔው እንደ ምክንያት የቀረበው የሀብት ውስንነት መኖሩ እና ፍትሃዊ የደመወዝ ማስተካከያ ለማድረግ መታሰቡ ቢሆንም፣ ቡድኑ «ፌደራሉ በጀት ከልክሎናል» በማለት አስቸኳይ የሀብት ማሰባሰብ ስራ እንዲጀምርም አዟል።
ይህ ይፋዊ መግለጫ «የበጀት እጥረት» ቢለውም፣ ታዛቢዎችና የፖለቲካ ተንታኞች ግን ውሳኔው ህወሃት ለሌላ አዲስ ጦርነትና ወታደራዊ ግጭት እያደረገው ያለውን ስውር ዝግጅት የሚያሳይ ግልጽ ማሳያ ነው ይላሉ።
ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ ክልል ትምህርት ግንቦት 30 እንዲያበቃ ወስኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የህወሃት ቡድን፣ በትግራይ ክልል ለሚገኝ ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ የግንቦት እና የሰኔ ወራት ደመወዝ እንዳይከፈል የሚል ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈ።
ዶ/ር ደብረጽዮን ለክልሉ ዞኖች፣ ወረዳዎች እና ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ጭምር ባስተላለፉት የጽሁፍ ትዕዛዝ «ለሁለት ወራት ደሞዝ የለም፤ ይህንን ከወዲሁ እወቁት» ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ለውሳኔው እንደ ምክንያት የቀረበው የሀብት ውስንነት መኖሩ እና ፍትሃዊ የደመወዝ ማስተካከያ ለማድረግ መታሰቡ ቢሆንም፣ ቡድኑ «ፌደራሉ በጀት ከልክሎናል» በማለት አስቸኳይ የሀብት ማሰባሰብ ስራ እንዲጀምርም አዟል።
ይህ ይፋዊ መግለጫ «የበጀት እጥረት» ቢለውም፣ ታዛቢዎችና የፖለቲካ ተንታኞች ግን ውሳኔው ህወሃት ለሌላ አዲስ ጦርነትና ወታደራዊ ግጭት እያደረገው ያለውን ስውር ዝግጅት የሚያሳይ ግልጽ ማሳያ ነው ይላሉ።
ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ ክልል ትምህርት ግንቦት 30 እንዲያበቃ ወስኗል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😁7👍6❤5🤔1🤪1
የ26 ኪሎ ግራም እጢ በተሳካ ኦፕሬሽን ተወገደ‼
በመቀሌ ዓይደር ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ14 ዓመታት በማህፀን እጢ ሲሰቃዩ የነበሩ የ56 ዓመት እናት፣ ከሦስት ሰዓታት በላይ በፈጀ አስቸጋሪ ቀዶ ጥገና የ26 ኪሎ ግራም እጢ ተወግዶላቸው እፎይታ አግኝተዋል።
📌እነዚህ እናት ቀደም ሲል በርካታ የሕክምና ሙከራዎችን ቢያደርጉም ሳይሳካላቸው የቀረ ሲሆን፣ አልፎ ተርፎም የተሳሳተ ምርመራ ተደርጎላቸው የቲቢ መድኃኒት እስከመውሰድ ደርሰው ነበር። በአሁኑ ወቅት ከቀዶ ጥገናው በኋላ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
📌የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ዶ/ር ተወልደብርሃን አብርሃ የተመራውና ዶ/ር ገብረኪሮስ ፀጋዛአብ፣ ዶ/ር ተኽላይ ዘርአይ፣ ዶ/ር ማርየ አለሜ እንዲሁም ማደንዘዣ ባለሙያዎችና ነርሶችን ያካተተው የሕክምና ቡድን ከፍተኛ ምስጋና ተችቶታል።
Via : Wasu Mohammed
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በመቀሌ ዓይደር ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ14 ዓመታት በማህፀን እጢ ሲሰቃዩ የነበሩ የ56 ዓመት እናት፣ ከሦስት ሰዓታት በላይ በፈጀ አስቸጋሪ ቀዶ ጥገና የ26 ኪሎ ግራም እጢ ተወግዶላቸው እፎይታ አግኝተዋል።
📌እነዚህ እናት ቀደም ሲል በርካታ የሕክምና ሙከራዎችን ቢያደርጉም ሳይሳካላቸው የቀረ ሲሆን፣ አልፎ ተርፎም የተሳሳተ ምርመራ ተደርጎላቸው የቲቢ መድኃኒት እስከመውሰድ ደርሰው ነበር። በአሁኑ ወቅት ከቀዶ ጥገናው በኋላ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
📌የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ዶ/ር ተወልደብርሃን አብርሃ የተመራውና ዶ/ር ገብረኪሮስ ፀጋዛአብ፣ ዶ/ር ተኽላይ ዘርአይ፣ ዶ/ር ማርየ አለሜ እንዲሁም ማደንዘዣ ባለሙያዎችና ነርሶችን ያካተተው የሕክምና ቡድን ከፍተኛ ምስጋና ተችቶታል።
Via : Wasu Mohammed
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤32🙏8👍7😱2👏1