1447ኛው የዒድ አልአድሃ በዓል ረቡዕ ይውላል።
ዛሬ በሳዑዲ አረቢያ ጨረቃ በመታየቷ የዙል-ሂጃ ወር መግባቱ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (የዓረፋ) በዓል ዕሮብ ረቡዕ ግንቦት 19 ተከብሮ ይውላል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዛሬ በሳዑዲ አረቢያ ጨረቃ በመታየቷ የዙል-ሂጃ ወር መግባቱ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (የዓረፋ) በዓል ዕሮብ ረቡዕ ግንቦት 19 ተከብሮ ይውላል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤20👍6🤔1
የማስታወቂያ ግብዣ
የተከበራችሁ ቤተሰቦች ከ36,000 በላይ ተከታይ ባለው እና በደቂቃዎች ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝ ባለው በዚህ የቴሌግራም ቻናል ላይ ምርትና አገልግሎታችሁን ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንድታስተዋውቁ በአክብሮት ተጋብዛችኋል‼
✔Youtube ቻናል …
✔የትምህርት ተቋማት…...
✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…...
✔የትራንስፖርት አገልግሎት…....
✔ኤጀንሲዎች……
✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች......
✔ሌሎችም የምትሰጧቸውን አገልግሎቶች.....ማስተዋወቅ የምትፈልጉ በዚህ በኩል ኑ 👇
መልዕክት መቀበያ:—@Addis_reporter_bot
የተከበራችሁ ቤተሰቦች ከ36,000 በላይ ተከታይ ባለው እና በደቂቃዎች ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝ ባለው በዚህ የቴሌግራም ቻናል ላይ ምርትና አገልግሎታችሁን ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንድታስተዋውቁ በአክብሮት ተጋብዛችኋል‼
✔Youtube ቻናል …
✔የትምህርት ተቋማት…...
✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…...
✔የትራንስፖርት አገልግሎት…....
✔ኤጀንሲዎች……
✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች......
✔ሌሎችም የምትሰጧቸውን አገልግሎቶች.....ማስተዋወቅ የምትፈልጉ በዚህ በኩል ኑ 👇
መልዕክት መቀበያ:—@Addis_reporter_bot
👍5❤3
ጠሚ አብይ አዋጭ አይደለም ያሉት የባቡር ፕሮጀክት ግንባታ ዳግም ተጀመረ።
በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ግንባታው ተቋርጦ የቆየው የአዋሽ - ኮምቦልቻ - መቀሌ የባቡር ፕሮጀክት ዳግም ሊጀመር መሆኑ ተገለጸ። ፕሮጀክቱ ከመቋረጡ በፊት መጠነኛ የግንባታ ስራዎች ብቻ ቀርተውት የነበረ ቢሆንም ባለፉት ጊዜያት የሀዲድ ቁሳቁሶች ለስርቆትና ለብክነት ተጋልጠው ቆይተዋል። ፕሮጀክቱ ከቆመበት እንዲቀጥልም የህዝብ ተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብበት ቆይቷል። ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በሰጡት ማብራሪያ ፕሮጀክቱ በ2.6 ቢሊዮን ዶላር ብድር የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰው ከመቀሌ ኮምቦልቻ የሚመላለስ በቂ ምርት ባለመኖሩ ፕሮጀክቱ በኢኮኖሚ ረገድ አዋጭ እንዳልሆነና የወጣበትን ወጪ በ50 ዓመታት ውስጥ እንኳ መመለስ እንደማይችል መግለጻቸው ይታወሳል።
ይሁን እንጂ ባለፉት ጥቂት ቀናት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በባቡር መስመሩ ላይ የደረሱ ጉዳቶችን ጠግነው ወደ ስራ የሚያስገቡ ሰራተኞችን ለመቅጠር የቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል። ዛሬ እሁድ ደግሞ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በፕሮጀክቱ ሳይት ላይ በመገኘት ግንባታውን ከቆመበት ለማስቀጠልና አጠናቆ ወደ አገልግሎት ለማስገባት ስራ መጀመሩን ገልጸዋል።
የአዋሽ - ኮምቦልቻ - ሀራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት አማራ፣ ትግራይ እና አፋር ክልሎችን ከጅቡቲና ከዓሳብ ወደቦች ጋር በማገናኘት ረገድ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ፋይዳ እንዳለው ይነገራል። ፕሮጀክቱን ሲያከናውን የነበረው የቱርክ ኩባንያ ከግንባታው መቋረጥ ጋር ተያይዞ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በህግ እየተካሰሰ በመሆኑ ቀሪው ስራ በሀገር ውስጥ ባለሙያዎችና ኩባንያዎች ብቻ እንደሚከናወን ታውቋል። የአማራ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሀሰን ሙሐመድ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ስራ መጀመሩን አረጋግጠዋል።
@Addis_Reporter
በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ግንባታው ተቋርጦ የቆየው የአዋሽ - ኮምቦልቻ - መቀሌ የባቡር ፕሮጀክት ዳግም ሊጀመር መሆኑ ተገለጸ። ፕሮጀክቱ ከመቋረጡ በፊት መጠነኛ የግንባታ ስራዎች ብቻ ቀርተውት የነበረ ቢሆንም ባለፉት ጊዜያት የሀዲድ ቁሳቁሶች ለስርቆትና ለብክነት ተጋልጠው ቆይተዋል። ፕሮጀክቱ ከቆመበት እንዲቀጥልም የህዝብ ተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብበት ቆይቷል። ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በሰጡት ማብራሪያ ፕሮጀክቱ በ2.6 ቢሊዮን ዶላር ብድር የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰው ከመቀሌ ኮምቦልቻ የሚመላለስ በቂ ምርት ባለመኖሩ ፕሮጀክቱ በኢኮኖሚ ረገድ አዋጭ እንዳልሆነና የወጣበትን ወጪ በ50 ዓመታት ውስጥ እንኳ መመለስ እንደማይችል መግለጻቸው ይታወሳል።
ይሁን እንጂ ባለፉት ጥቂት ቀናት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በባቡር መስመሩ ላይ የደረሱ ጉዳቶችን ጠግነው ወደ ስራ የሚያስገቡ ሰራተኞችን ለመቅጠር የቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል። ዛሬ እሁድ ደግሞ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በፕሮጀክቱ ሳይት ላይ በመገኘት ግንባታውን ከቆመበት ለማስቀጠልና አጠናቆ ወደ አገልግሎት ለማስገባት ስራ መጀመሩን ገልጸዋል።
የአዋሽ - ኮምቦልቻ - ሀራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት አማራ፣ ትግራይ እና አፋር ክልሎችን ከጅቡቲና ከዓሳብ ወደቦች ጋር በማገናኘት ረገድ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ፋይዳ እንዳለው ይነገራል። ፕሮጀክቱን ሲያከናውን የነበረው የቱርክ ኩባንያ ከግንባታው መቋረጥ ጋር ተያይዞ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በህግ እየተካሰሰ በመሆኑ ቀሪው ስራ በሀገር ውስጥ ባለሙያዎችና ኩባንያዎች ብቻ እንደሚከናወን ታውቋል። የአማራ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሀሰን ሙሐመድ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ስራ መጀመሩን አረጋግጠዋል።
@Addis_Reporter
❤34👍7😁5🤪4👏1🎉1🙏1👌1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሁለት የአሜሪካ የጦር ጄቶች በአየር ላይ ተጋጭተው ተከሰከሱ
በአሜሪካ አይዳሆ ግዛት በሚገኘው የነፋስ ተራራ የባህር ኃይል ጣቢያ በተካሄደው የ"Gunfighter Skies" የአየር ትዕይንት ላይ፣ ሁለት የአሜሪካ ባህር ኃይል EA-18G Growler የጦር ጄቶች በአየር ላይ ተጋጭተው መከስከሳቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት እና የዐይን እማኞች ገልጸዋል።
ሁለቱ የኤሌክትሮኒክስ ውጊያ አውሮፕላኖች የአየር ላይ ትዕይንት እያሳዩ ባሉበት ወቅት የተጋጩ ሲሆን፣ ከጣቢያው በስተሰሜን ምዕራብ 2 ማይል ርቀት ላይ መከስከሳቸው ተረጋግጧል።ከአደጋው በኋላ በቪዲዮ ምስሎች ላይ 4 አብራሪዎች በአየር ላይ በፓራሹት አማካኝነት ከአውሮፕላኖቹ እራሳቸውን አውጥተው ሲወርዱ ታይተዋል።
አደጋውን ተከትሎ የጦር ሰፈሩ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በቦታው ላይ የማዳን ስራ እያከናወኑ ይገኛል። ስለ አብራሪዎቹ ወቅታዊ የጤና ሁኔታ ዝርዝር መረጃ አልወጣም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአሜሪካ አይዳሆ ግዛት በሚገኘው የነፋስ ተራራ የባህር ኃይል ጣቢያ በተካሄደው የ"Gunfighter Skies" የአየር ትዕይንት ላይ፣ ሁለት የአሜሪካ ባህር ኃይል EA-18G Growler የጦር ጄቶች በአየር ላይ ተጋጭተው መከስከሳቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት እና የዐይን እማኞች ገልጸዋል።
ሁለቱ የኤሌክትሮኒክስ ውጊያ አውሮፕላኖች የአየር ላይ ትዕይንት እያሳዩ ባሉበት ወቅት የተጋጩ ሲሆን፣ ከጣቢያው በስተሰሜን ምዕራብ 2 ማይል ርቀት ላይ መከስከሳቸው ተረጋግጧል።ከአደጋው በኋላ በቪዲዮ ምስሎች ላይ 4 አብራሪዎች በአየር ላይ በፓራሹት አማካኝነት ከአውሮፕላኖቹ እራሳቸውን አውጥተው ሲወርዱ ታይተዋል።
አደጋውን ተከትሎ የጦር ሰፈሩ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በቦታው ላይ የማዳን ስራ እያከናወኑ ይገኛል። ስለ አብራሪዎቹ ወቅታዊ የጤና ሁኔታ ዝርዝር መረጃ አልወጣም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍6😢6🙏3🤣3
ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን በደቡባዊ የአገራቸው ድንበር መከላከያው እንዲጠናከር ትዕዛዝ ሰጡ።
ከሰሜን ኮሪያ የተለያዩ ዕዞች ከተውጣጡ ወታደራዊ ሀላፊዎች ጋር ስለዝግጁነት መክረዋል ኪም ጆንግ ኡን።
ከዕዝና ብርጌድ አዛዦች ጋር የተወያዩት ኪም በደቡባዊ የሰሜን ኮሪያ ክፍል ያለው ድንበር ላይ ዝግጅት እንዲደረግ ማሳሰባቸው ለደቡብ ኮሪያ ፖለቲከኞች አዲስ ወታደራዊ ስጋት ጋርጦባቸዋል ።
ሊቀሰቀስ የሚችልን ማንኛውንም ጦርነት ለመቀልበስ የጦሩን ትጥቅ ማዘመን፣ቁልፍ ዕዞችን ማጠናከር እና መሰል ዝግጅቶች እንዲደረጉም ጥሪ ቀርቧል።
በደቡብ ኮሪያ እና አሜሪካ መካከል ያለው ወታደራዊ ትስስር ስጋት የሆነባቸው ኪሞቹ በተለያየ ጊዜ የሚፈፀምብንን ወታደራዊ ትንኮሳ መመከት አለብን የሚል ዕምነት አላቸውም ተብሏል።
በፒዮንግያንግ እና ሴዑል መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት መልኩን እየለወጠ መምጣቱን የሚጠቁም ትዕዛዝ ሆኖም ተመዝግቧል።
ኪም ጆንግ ኡን አዳዲስ የጦር መሳሪያ ስርዓቶች ወደ ውጊያ አውድ እንዲገቡ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ መስጠታቸውም አይዘነጋም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ከሰሜን ኮሪያ የተለያዩ ዕዞች ከተውጣጡ ወታደራዊ ሀላፊዎች ጋር ስለዝግጁነት መክረዋል ኪም ጆንግ ኡን።
ከዕዝና ብርጌድ አዛዦች ጋር የተወያዩት ኪም በደቡባዊ የሰሜን ኮሪያ ክፍል ያለው ድንበር ላይ ዝግጅት እንዲደረግ ማሳሰባቸው ለደቡብ ኮሪያ ፖለቲከኞች አዲስ ወታደራዊ ስጋት ጋርጦባቸዋል ።
ሊቀሰቀስ የሚችልን ማንኛውንም ጦርነት ለመቀልበስ የጦሩን ትጥቅ ማዘመን፣ቁልፍ ዕዞችን ማጠናከር እና መሰል ዝግጅቶች እንዲደረጉም ጥሪ ቀርቧል።
በደቡብ ኮሪያ እና አሜሪካ መካከል ያለው ወታደራዊ ትስስር ስጋት የሆነባቸው ኪሞቹ በተለያየ ጊዜ የሚፈፀምብንን ወታደራዊ ትንኮሳ መመከት አለብን የሚል ዕምነት አላቸውም ተብሏል።
በፒዮንግያንግ እና ሴዑል መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት መልኩን እየለወጠ መምጣቱን የሚጠቁም ትዕዛዝ ሆኖም ተመዝግቧል።
ኪም ጆንግ ኡን አዳዲስ የጦር መሳሪያ ስርዓቶች ወደ ውጊያ አውድ እንዲገቡ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ መስጠታቸውም አይዘነጋም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10👍6
በኢትዮጵያ የዲጂታል ኦቲዝም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ተገለፀ
ልጆች ረጅም ሰዓት በስልክና በቪዲዮ ጌሞች ላይ ማሳለፋቸው፣ መናገር የሚችሉ ሆነው ከተወለዱ በኋላ አንደበታቸው እንዲያዝ እያደረገ መምጣቱ ተገልጿል።
ይህም በተፈጥሮ ከሚመጣ ኦቲዝም ባልተናነሰ ለዲጂታል ኦቲዝም እያጋለጣቸው መሆኑን ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት ወላጆች ልጆቻቸው ሲያለቅሱ ወይም ሲያስቸግሩ ስልካቸውን ሰጥተው ዝም ማሰኘትን እንደ ዋነኛ አማራጭ መውሰዳቸው በትውልዱ ላይ ትልቅ አደጋ እየጋረጠ ይገኛልም ብለዋል።
ዲጂታል ኦቲዝም የሚባለው ስያሜ ልጆች ከስክሪን ጋር ረጅም ጊዜ በማጥፋታቸው ሳቢያ የሚፈጠር የተግባቦትና የማህበራዊ ግንኙነት ክፍተት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ሸዋጌጥ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቷ ላይ እየተስተዋለ የመጣው የህፃናት ስልክ አጠቃቀም ጤነኛ ሆነው የተወለዱ ህፃናትን ሳይቀር መናገር አቅቷቸው ወደ ማህበራቸው እንዲመጡ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጇ ልጆች ዝም ብለው ስልክ ላይ ጊዜ ካጠፉ አያወሩም፤ ቃላት ማውጣት ያለበት ላንቃቸውም ዝም እያለ ነው የሚሄደው ያሉ ሲሆን ፣ በሕክምና ሲረጋገጥም "ዲጂታል ኦቲዝም" ሆኖባቸው የተገኙ የብዙ ህፃናት ቁጥር በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ትልቁ ሥራ ወላጆች ላይ እንደሚጣልና በተለይም ህፃናት ትምህርት ቤት ከመግባታቸው በፊት ባለው ከ1 እስከ 4 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ልጆች ረጅም ሰዓት በስልክና በቪዲዮ ጌሞች ላይ ማሳለፋቸው፣ መናገር የሚችሉ ሆነው ከተወለዱ በኋላ አንደበታቸው እንዲያዝ እያደረገ መምጣቱ ተገልጿል።
ይህም በተፈጥሮ ከሚመጣ ኦቲዝም ባልተናነሰ ለዲጂታል ኦቲዝም እያጋለጣቸው መሆኑን ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት ወላጆች ልጆቻቸው ሲያለቅሱ ወይም ሲያስቸግሩ ስልካቸውን ሰጥተው ዝም ማሰኘትን እንደ ዋነኛ አማራጭ መውሰዳቸው በትውልዱ ላይ ትልቅ አደጋ እየጋረጠ ይገኛልም ብለዋል።
ዲጂታል ኦቲዝም የሚባለው ስያሜ ልጆች ከስክሪን ጋር ረጅም ጊዜ በማጥፋታቸው ሳቢያ የሚፈጠር የተግባቦትና የማህበራዊ ግንኙነት ክፍተት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ሸዋጌጥ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቷ ላይ እየተስተዋለ የመጣው የህፃናት ስልክ አጠቃቀም ጤነኛ ሆነው የተወለዱ ህፃናትን ሳይቀር መናገር አቅቷቸው ወደ ማህበራቸው እንዲመጡ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጇ ልጆች ዝም ብለው ስልክ ላይ ጊዜ ካጠፉ አያወሩም፤ ቃላት ማውጣት ያለበት ላንቃቸውም ዝም እያለ ነው የሚሄደው ያሉ ሲሆን ፣ በሕክምና ሲረጋገጥም "ዲጂታል ኦቲዝም" ሆኖባቸው የተገኙ የብዙ ህፃናት ቁጥር በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ትልቁ ሥራ ወላጆች ላይ እንደሚጣልና በተለይም ህፃናት ትምህርት ቤት ከመግባታቸው በፊት ባለው ከ1 እስከ 4 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10😢4👍3💯3🙊1
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን "ጊዜው እያለቀ ነው" ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ
በመካከለኛው ምስራቅ ባለው የጂኦፖለቲካ ውጥረት ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ ለዋጋው መጨመር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም የሚደረገው ድርድር በመቀዝቀዙ ለኢራን "ጊዜው እያለቀ ነው" ሲሉ ማስጠንቀቃቸው በምክንያትነት ተጠቅሷል።
የዓለምን 20 በመቶ የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ትራንስፖርት የሚያስተናግደው የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት፣ በአቡ ዳቢ የሚገኘው የባራካ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ አቅራቢያ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃ እሳት መነሳ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ስጋት መፍጠሩን ቢቢሲ ዘግቧል።
በዛሬው ዕለት ብሬንት የተሰኘው ድፍድፍ ነዳጅ በ1.7 በመቶ በመጨመር አንድ በርሜል በ111.13 ዶላር ደርሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በመካከለኛው ምስራቅ ባለው የጂኦፖለቲካ ውጥረት ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ ለዋጋው መጨመር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም የሚደረገው ድርድር በመቀዝቀዙ ለኢራን "ጊዜው እያለቀ ነው" ሲሉ ማስጠንቀቃቸው በምክንያትነት ተጠቅሷል።
የዓለምን 20 በመቶ የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ትራንስፖርት የሚያስተናግደው የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት፣ በአቡ ዳቢ የሚገኘው የባራካ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ አቅራቢያ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃ እሳት መነሳ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ስጋት መፍጠሩን ቢቢሲ ዘግቧል።
በዛሬው ዕለት ብሬንት የተሰኘው ድፍድፍ ነዳጅ በ1.7 በመቶ በመጨመር አንድ በርሜል በ111.13 ዶላር ደርሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11😢6👍3
“ግብፅ በግብርና ምርት ራሷን መቻል እንደማትችል ልታውቁ ይገባል” - ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ አል ሲሲ
የግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ አል ሲሲ ግብፅ በግብርና ምርት ሙሉ በሙሉ ራስን የመቻል ግብ ላይ መድረስ እንደማትችል በይፋ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን የተናገሩት፣ በአባይ ውሃ ከለማ በኋላ ተርፎ ወደ ሜዲቴራኒያን ባህር የሚቀላቀለውን የግብርና ፍሳሽ ውሃ በማጣራትና ወደ በረሃማ ቦታዎች በመግፋት ለድጋሚ ጥቅም ለማዋል የታለመ ግዙፍ ፕሮጀክት በምርቃት ወቅት ባደረጉት ንግግር ነው።
የ16 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ ፕሮጀክት ግብፅ በአሮጌው የአባይ ሸለቆ ግብርና ላይ ውሎ ተርፎ ወደ ሜዲቴራኒያን ባህር የሚፈሰውን ውሃ፣ ባህሩ ውስጥ ከመቀላቀሉ በፊት በመጥለፍና በማጣራት ለበረሃማው "ጊዛ" ግብርና እንዲውል የሚያደርግ የ800 ቢሊዮን የግብፅ ፓውንድ (16 ቢሊዮን ዶላር) ፕሮጀክት በይፋ አስጀምራለች።
ይህ ፕሮጀክት በዝቅተኛ ቦታ ላይ የሚገኘውን ያገለገለ የግብርና ፍሳሽ ውሃ፣ እጅግ ግዙፍ በሆኑ የፓምፕ ጣቢያዎች በመታገዝ ወደ ከፍታማው በረሃ እንዲወጣ የሚያደርግ ነው።
ፕሮጀክቱ የተበከለውንና ጨዋማ የሆነውን ውሃ በዘመናዊ መንገድ በማጣራት ለግብርና ምርት ዝግጁ ያደርጋል።
ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በዚሁ መድረክ ባደረጉት ንግግር፣ ግብፅ ምንም ያህል ብትጥር በምግብ ዋስትና ራሷን መቻል እንደማትችል ለህዝባቸው በግልጽ ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንቱ ሲናገሩ “በግብርና ምርት ሙሉ በሙሉ ራስን መቻል ይቻላል ብላችሁ እንዳታስቡ ፤ ቢያንስ እንደ ግብፅ ባሉ አገራት... ምንም ያህል ብንጥር ራስን ሙሉ በሙሉ መቻል ፈጽሞ የማይቻል ነገር ነው። እኛ የፈለግነውን ሁሉ ለማምረት የሚያስችል በቂ መሬትና ውሃ ስለሌለን ራሳችንን ሙሉ በሙሉ መቻል አንችልም” ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ አል ሲሲ ግብፅ በግብርና ምርት ሙሉ በሙሉ ራስን የመቻል ግብ ላይ መድረስ እንደማትችል በይፋ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን የተናገሩት፣ በአባይ ውሃ ከለማ በኋላ ተርፎ ወደ ሜዲቴራኒያን ባህር የሚቀላቀለውን የግብርና ፍሳሽ ውሃ በማጣራትና ወደ በረሃማ ቦታዎች በመግፋት ለድጋሚ ጥቅም ለማዋል የታለመ ግዙፍ ፕሮጀክት በምርቃት ወቅት ባደረጉት ንግግር ነው።
የ16 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ ፕሮጀክት ግብፅ በአሮጌው የአባይ ሸለቆ ግብርና ላይ ውሎ ተርፎ ወደ ሜዲቴራኒያን ባህር የሚፈሰውን ውሃ፣ ባህሩ ውስጥ ከመቀላቀሉ በፊት በመጥለፍና በማጣራት ለበረሃማው "ጊዛ" ግብርና እንዲውል የሚያደርግ የ800 ቢሊዮን የግብፅ ፓውንድ (16 ቢሊዮን ዶላር) ፕሮጀክት በይፋ አስጀምራለች።
ይህ ፕሮጀክት በዝቅተኛ ቦታ ላይ የሚገኘውን ያገለገለ የግብርና ፍሳሽ ውሃ፣ እጅግ ግዙፍ በሆኑ የፓምፕ ጣቢያዎች በመታገዝ ወደ ከፍታማው በረሃ እንዲወጣ የሚያደርግ ነው።
ፕሮጀክቱ የተበከለውንና ጨዋማ የሆነውን ውሃ በዘመናዊ መንገድ በማጣራት ለግብርና ምርት ዝግጁ ያደርጋል።
ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በዚሁ መድረክ ባደረጉት ንግግር፣ ግብፅ ምንም ያህል ብትጥር በምግብ ዋስትና ራሷን መቻል እንደማትችል ለህዝባቸው በግልጽ ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንቱ ሲናገሩ “በግብርና ምርት ሙሉ በሙሉ ራስን መቻል ይቻላል ብላችሁ እንዳታስቡ ፤ ቢያንስ እንደ ግብፅ ባሉ አገራት... ምንም ያህል ብንጥር ራስን ሙሉ በሙሉ መቻል ፈጽሞ የማይቻል ነገር ነው። እኛ የፈለግነውን ሁሉ ለማምረት የሚያስችል በቂ መሬትና ውሃ ስለሌለን ራሳችንን ሙሉ በሙሉ መቻል አንችልም” ብለዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤24🤷♂3👍2😢1
ዶናልድ ትራምፕ ያጋሯቸው ምስሎች‼️
📌የመጀመሪያው ምስል ኦርቢት ላይ ሆነው ቀይ በተን ተጭነው የኑክሌያር ቦንብ ጥቃት ሲፈፅሙ የሚያሳይ ሲሆን ይህንን ተከትሎ በኢራን ላይ የኑክሌያር ቦንብ ሊጠቀሙ ይሆን? የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
📌ሁለተኛው ምስል ደግሞ ኢራንን ከሁሉም አቅጣጫ ጥቃት ሲዘነዝሩ የሚያሳይ ሲሆን ይህም በኢራን ላይ ጥቃት ሊክፈቱ እንዳሰቡ የሚያሳይ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
📌የመጀመሪያው ምስል ኦርቢት ላይ ሆነው ቀይ በተን ተጭነው የኑክሌያር ቦንብ ጥቃት ሲፈፅሙ የሚያሳይ ሲሆን ይህንን ተከትሎ በኢራን ላይ የኑክሌያር ቦንብ ሊጠቀሙ ይሆን? የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
📌ሁለተኛው ምስል ደግሞ ኢራንን ከሁሉም አቅጣጫ ጥቃት ሲዘነዝሩ የሚያሳይ ሲሆን ይህም በኢራን ላይ ጥቃት ሊክፈቱ እንዳሰቡ የሚያሳይ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16😢8👍5🤣3🥰1
የ500 ሚሊዮን ዶላር ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ሊካሄድ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንኩ ነገ ማክሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2016 ዓ.ም 500 ሚሊዮን ዶላር ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እንደሚካሄድ ይፋ አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንኩ ነገ ማክሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2016 ዓ.ም 500 ሚሊዮን ዶላር ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እንደሚካሄድ ይፋ አድርጓል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍9
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰርን በተመለከተ ይህን ብሏል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ያላስተሳሰሩ ደንበኞች የባንክ አገልግሎት ማግኘት አይችሉም። በመሆኑም ባንካችን ያዘጋጀውን የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) በመጠቀም ወይም ወደሚቀርባችሁ የባንካችን ቅርንጫፍ በመሄድ ሂሳባችሁን እንድታስተሳስሩ እንገልፃለን ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ያላስተሳሰሩ ደንበኞች የባንክ አገልግሎት ማግኘት አይችሉም። በመሆኑም ባንካችን ያዘጋጀውን የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) በመጠቀም ወይም ወደሚቀርባችሁ የባንካችን ቅርንጫፍ በመሄድ ሂሳባችሁን እንድታስተሳስሩ እንገልፃለን ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍2😁2👏1
የቀብር ዋጋ ጭማሪ‼️
የቀብር አገልግሎት የዋጋ ማሻሻያ የማሕበረሰቡን ጫና ለመቀነስ መሆኑን አዲስ አበባ መጅሊስ አስታወቀ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት (መጅሊስ) በጀናዛ ማረፊያ ቦታዎች ላይ ያደረገው የዋጋ ማሻሻያ ተገልጋዮችን ከተጨማሪ ወጪ ለመታደግ የተደረገ መሆኑን አስታወቀ።
የምክር ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሪያድ ጀማል እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል የነበረው አሰራር ለብልሹ አሰራር የተጋለጠና ወጥነት የጎደለው ነበር። ይህንን ለመቅረፍ መጅሊሱ ባለፉት 9 ወራት ውስጥ ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የመሠረተ ልማትና የሸሪዓዊ አቀባበር ሥርዓት ማሻሻያ ሥራዎችን አከናውኗል።
በአዲሱ ማሻሻያ መሠረት የሕፃናት ቀብር 2,000 ብር፣ የአዋቂ ደግሞ 4,000 ብር ሆኗል።ይህም ቀደም ሲል ተገልጋዮች ለብሎኬት ግዢ ያወጡት የነበረውን ከ2,200 እስከ 2,800 ብር ተጨማሪ ወጪ የሚያስቀር ሲሆን፣ ከአሁን በኋላ እስከ 28 የሚደርሰው የብሎኬት አቅርቦት በራሱ በመጅሊሱ የሚሸፈን ይሆናል።
በበጎ ፈቃደኝነት የጀናዛ እጥበትና ሽኝት በሚያደርጉ ተቋማት ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ እንዳልተደረገባቸውና ምክር ቤቱ አሰራሩን ለማዘመን የተለያዩ መመሪያዎችን አጽድቆ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ዋና ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የቀብር አገልግሎት የዋጋ ማሻሻያ የማሕበረሰቡን ጫና ለመቀነስ መሆኑን አዲስ አበባ መጅሊስ አስታወቀ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት (መጅሊስ) በጀናዛ ማረፊያ ቦታዎች ላይ ያደረገው የዋጋ ማሻሻያ ተገልጋዮችን ከተጨማሪ ወጪ ለመታደግ የተደረገ መሆኑን አስታወቀ።
የምክር ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሪያድ ጀማል እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል የነበረው አሰራር ለብልሹ አሰራር የተጋለጠና ወጥነት የጎደለው ነበር። ይህንን ለመቅረፍ መጅሊሱ ባለፉት 9 ወራት ውስጥ ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የመሠረተ ልማትና የሸሪዓዊ አቀባበር ሥርዓት ማሻሻያ ሥራዎችን አከናውኗል።
በአዲሱ ማሻሻያ መሠረት የሕፃናት ቀብር 2,000 ብር፣ የአዋቂ ደግሞ 4,000 ብር ሆኗል።ይህም ቀደም ሲል ተገልጋዮች ለብሎኬት ግዢ ያወጡት የነበረውን ከ2,200 እስከ 2,800 ብር ተጨማሪ ወጪ የሚያስቀር ሲሆን፣ ከአሁን በኋላ እስከ 28 የሚደርሰው የብሎኬት አቅርቦት በራሱ በመጅሊሱ የሚሸፈን ይሆናል።
በበጎ ፈቃደኝነት የጀናዛ እጥበትና ሽኝት በሚያደርጉ ተቋማት ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ እንዳልተደረገባቸውና ምክር ቤቱ አሰራሩን ለማዘመን የተለያዩ መመሪያዎችን አጽድቆ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ዋና ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤21😁17👍5🙊3
መረጃ‼️
የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት በአገሪቱ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ደኅንነት እንዲያስጠብቅ ጠየቁ።
ጌዲዮን ይህን ጥያቄ ያቀረቡት፣ ዛሬ ከሳዑዲ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዋሊድ ኤልክረጂ ጋር በተወያዩበት ወቅት መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባሠራጨው መረጃ ገልጧል።
ጌዲዮን፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ለኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች ሕጋዊ የሥራ እድሎችን እንዲያመቻችም መጠየቃቸውን ሚንስቴሩ ጠቅሷል።
ሚንስትር ዋሊድ፣ ሕጋዊ የሠራተኞች ፍልሠት ኢትዮጵያዊያን ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ ቅጥር እድል እንዲያገኙ ለማስቻል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ተብሏል።
የሳዑዲ ዓረቢያ ፍርድ ቤት ከአደንዛዥ እጽ ዝውውር ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት የጣለባቸው በርካታ ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ በውይይቱ ወቅት ይነሳ አይነሳ መረጃው አላመለከትም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት በአገሪቱ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ደኅንነት እንዲያስጠብቅ ጠየቁ።
ጌዲዮን ይህን ጥያቄ ያቀረቡት፣ ዛሬ ከሳዑዲ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዋሊድ ኤልክረጂ ጋር በተወያዩበት ወቅት መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባሠራጨው መረጃ ገልጧል።
ጌዲዮን፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ለኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች ሕጋዊ የሥራ እድሎችን እንዲያመቻችም መጠየቃቸውን ሚንስቴሩ ጠቅሷል።
ሚንስትር ዋሊድ፣ ሕጋዊ የሠራተኞች ፍልሠት ኢትዮጵያዊያን ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ ቅጥር እድል እንዲያገኙ ለማስቻል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ተብሏል።
የሳዑዲ ዓረቢያ ፍርድ ቤት ከአደንዛዥ እጽ ዝውውር ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት የጣለባቸው በርካታ ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ በውይይቱ ወቅት ይነሳ አይነሳ መረጃው አላመለከትም።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍6😡1
“ጥቃቱን ለጊዜው ትቼዋለሁ”ትራምፕ
። ። ። ። ። : : : : : : : : : :
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊፈፅሙት የነበረውን ጥቃት ማራዘማቸውን አሳውቀዋል።
የባህረ ሰላጤው አገራት ሳውዲ አረቢያ፣ኳታርና አረብ ኤሚሬቶች እንዲሁም ሌሎች አገራት ኢራን ላይ ጥቃት እንዳይሰነዝር ጠይቀውኛል ብለዋል ትራምፕ።
ለማክሰኞ ቀን ተቆርጦለት የነበረው ጥቃት ለዲፕሎማሲ ጊዜ መግዣ በሚል ለአሁኑ ቆሟል።
በዕርግጥ ጥቃቱ ለሁለት እና ሶስት ቀናት ያህል እንደተራዘመ መነገሩ ያን ያህል ዘላቂ ሰላም ላያመጣ ይችላል።
ፔንታጎን ቢያንስ ለአሁኑ እርምጃ እንዳይወስድ በትራምፕ ታዟል።
ትራምፕ ኢራን ጋር ያለው ውይይት በጎ ባለመሆኑ ነገ ወደ ጥቃቱ እንመለሳለን በሚልም ዝተዋል።
የትኛውም ስምምነት ቴህራን ኑክሌር ቦምብ እንዳትታጠቅ ማድረግ አለበት የሪፐብሊካኑ ዕምነት ነው።
ፕሬዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያቸው ላይ ተቀባይነት የሌለው ሀሳብ ኢራን የምተቀርብ ከሆነ የጦር ሚኒስቴሩ(ፔንታጎን) ወደ ጥቃት ለመመለስ በተጠንቀ ቅ ላይ እንዲቆይም አዘዋል።
ትራምፕ ማክሰኞ የያዙትን ጥቃት አራዘሙ እንጂ ኢራን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ለማድረስ አሁንም ተዘጋጅተዋል ተብሏል።
ኢራን የመደራደሪያ ነጥቧን በፓኪስታን በኩል ለአሜሪካ መላኳም የሚዘነጋ አይደለም።
ዘገባው የአር ቲ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
። ። ። ። ። : : : : : : : : : :
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊፈፅሙት የነበረውን ጥቃት ማራዘማቸውን አሳውቀዋል።
የባህረ ሰላጤው አገራት ሳውዲ አረቢያ፣ኳታርና አረብ ኤሚሬቶች እንዲሁም ሌሎች አገራት ኢራን ላይ ጥቃት እንዳይሰነዝር ጠይቀውኛል ብለዋል ትራምፕ።
ለማክሰኞ ቀን ተቆርጦለት የነበረው ጥቃት ለዲፕሎማሲ ጊዜ መግዣ በሚል ለአሁኑ ቆሟል።
በዕርግጥ ጥቃቱ ለሁለት እና ሶስት ቀናት ያህል እንደተራዘመ መነገሩ ያን ያህል ዘላቂ ሰላም ላያመጣ ይችላል።
ፔንታጎን ቢያንስ ለአሁኑ እርምጃ እንዳይወስድ በትራምፕ ታዟል።
ትራምፕ ኢራን ጋር ያለው ውይይት በጎ ባለመሆኑ ነገ ወደ ጥቃቱ እንመለሳለን በሚልም ዝተዋል።
የትኛውም ስምምነት ቴህራን ኑክሌር ቦምብ እንዳትታጠቅ ማድረግ አለበት የሪፐብሊካኑ ዕምነት ነው።
ፕሬዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያቸው ላይ ተቀባይነት የሌለው ሀሳብ ኢራን የምተቀርብ ከሆነ የጦር ሚኒስቴሩ(ፔንታጎን) ወደ ጥቃት ለመመለስ በተጠንቀ ቅ ላይ እንዲቆይም አዘዋል።
ትራምፕ ማክሰኞ የያዙትን ጥቃት አራዘሙ እንጂ ኢራን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ለማድረስ አሁንም ተዘጋጅተዋል ተብሏል።
ኢራን የመደራደሪያ ነጥቧን በፓኪስታን በኩል ለአሜሪካ መላኳም የሚዘነጋ አይደለም።
ዘገባው የአር ቲ ነው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12🥱11🤣6👍2🥰2🤯2👏1😢1
የኢራን ፓርላማ የአሜሪካውን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ለሚገድል ማንኛውም ሰው 50 ሚሊዮን ዩሮ (ወደ 58 ሚሊዮን ዶላር ገደማ) የመንግስት የገንዘብ ሽልማት የሚሰጥ አዲስ የህግ ረቂቅ እያዘጋጀ መሆኑ ታወቀ
ይህ በኢራን ከፍተኛ ህግ አውጪዎች ደረጃ እየተመከረበት ያለው አዲስ የህግ ረቂቅ “የእስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ እና የደህንነት ሃይሎች የአረባዊ እርምጃ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፥ መንግስት ለግድያው የተመደበውን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በይፋ እንዲከፍል የሚያስገድድ ነው።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ በሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው እንደተናገሩት፥ ይህ እርምጃ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራን ወታደራዊ መሪዎችን እና አዛዦችን ለገደሉበት አጸፋዊ ምላሽ የተዘጋጀ ነው።
አዚዚ አክለውም ዶናልድ ትራምፕ፣ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የአሜሪካ መካከለኛው ዕዝ (CENTCOM) ዋና አዛዥ በዋናነት መገደል እንዳለባቸው ገልጸው፥ ይህንን የግድያ እርምጃ “ሃይማኖታዊ እና ርዕዮተ-ዓለማዊ ተልዕኮ” ሲሉ ጠርተውታል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ባለፈው መጋቢት ወር ላይ በርካታ የኢራን የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች የትራምፕን ግድያ ዘመቻ የሚደግፉ እና ለዚሁ ተግባር የሚውል የገንዘብ ማሰባሰቢያ ጥሪዎችን የያዙ የጽሑፍ መልዕክቶች ደርሷቸው እንደነበር ተገልጿል።
በተያያዘም በቅርቡ ይፋ የሆኑ የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከኢራን ጋር ግንኙነት አለው የተባለ አንድ ተላላኪ ግለሰብ ትራምፕን ለመግደል በቅድሚያ 5 ሺህ ዶላር ተከፍሎት ሲንቀሳቀስ እንደነበር ተደርሶበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ይህ በኢራን ከፍተኛ ህግ አውጪዎች ደረጃ እየተመከረበት ያለው አዲስ የህግ ረቂቅ “የእስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ እና የደህንነት ሃይሎች የአረባዊ እርምጃ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፥ መንግስት ለግድያው የተመደበውን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በይፋ እንዲከፍል የሚያስገድድ ነው።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ በሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው እንደተናገሩት፥ ይህ እርምጃ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራን ወታደራዊ መሪዎችን እና አዛዦችን ለገደሉበት አጸፋዊ ምላሽ የተዘጋጀ ነው።
አዚዚ አክለውም ዶናልድ ትራምፕ፣ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የአሜሪካ መካከለኛው ዕዝ (CENTCOM) ዋና አዛዥ በዋናነት መገደል እንዳለባቸው ገልጸው፥ ይህንን የግድያ እርምጃ “ሃይማኖታዊ እና ርዕዮተ-ዓለማዊ ተልዕኮ” ሲሉ ጠርተውታል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ባለፈው መጋቢት ወር ላይ በርካታ የኢራን የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች የትራምፕን ግድያ ዘመቻ የሚደግፉ እና ለዚሁ ተግባር የሚውል የገንዘብ ማሰባሰቢያ ጥሪዎችን የያዙ የጽሑፍ መልዕክቶች ደርሷቸው እንደነበር ተገልጿል።
በተያያዘም በቅርቡ ይፋ የሆኑ የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከኢራን ጋር ግንኙነት አለው የተባለ አንድ ተላላኪ ግለሰብ ትራምፕን ለመግደል በቅድሚያ 5 ሺህ ዶላር ተከፍሎት ሲንቀሳቀስ እንደነበር ተደርሶበታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣20❤14👍4👏2😢1😎1
በሱሉልታ የእገታ ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩ አራት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ
አዲሱ ነጋሽ ፣ደሮ ተሾመ፣ ደጀኔ ተስፋና ቶላ አለሙ የተባሉ አራት ወጣቶች ነዋሪነታቸው በኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ኑኑ ሳዩ ቀበሌ ነው።ወጣቶቹ በአካባቢያቸው የሚታወቁት የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ሲሆን በመዝናኛ ስፍራም ሆነ በተለያዩ ቦታውች የማይነጣጠሉ ጓደኛማቾች መሆናቸዉን የወረዳዉ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ሙሉ ጉደታ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ከቅርብ ግዜያት ወዲህ ግን የተለየና የተለወጠ እንቅስቃሴ በአካባቢው ያሣዩ እንደነበረም ይገልፃሉ።
ወጣቶቹ በአካባቢው ማሕበረሠብ ውስጥ ትዝብት ውስጥ ወድቀው ባሉበት ወቅት ጥር 5 ቀን 2017 ዓም ምሽት አልጌ ሠዮ በተባለ ስፍራ ያልተፈቀደ የጦር መሠርያ በመታጠቅ በአካባቢው ነዋሪ የሆኑት አራት ግለሠቦች አግተው በመውሰድ ከአንድ መቶ እስከ ሑለት መቶ ሺሕ ብር ድረስ ቤተሠቦቻቸው እንዲያመጡ በማስገደድ ቆይተዋል። ከጥቅምት 21 እስከ ጥር 5 ቀን 2017 ዓም ድረስ በዚሑ አካባቢ ለአራት ወራት የእገታ ወንጀል ሲፈፅሙ በመቆየት ገንዘብ ቤተሠቦቻቸውን ጠይቀው የሰጡትን ሲለቁ መክፍል አንችልም ያሉት ደግሞ ልጆቻቸውን ጭምር በማገት ተደራራቢ ወንጀል ሲፈፅሙ እንደነበረ በማስረጃ ተረጋግጧል፡፡
ወጣቶቹ አንድ ግለሠብን አግተው በመውሠድ ለወራት ባዘጋጁት ስፍራ በማስቀመጥ ካቆዩት በኃላ 200 ሺ ብር እንዲያመጣ ጠይቀውት የለኝም በማለቱ ፣ እሱን በመልቀቅ በእርሱ ፋንታ ልጁን አግተው በመውሰድ 300 ሺሕ ብር ተቀብለዋል፡፡የተቋቋመው የፀጥታ ግብረ ኃይል ሙሉ መረጃ ከደረሰዉ በኃላ ባደረገዉ ክትትል አራቱንም በቁጥጥር ስር አዉሏል፡፡ፖሊስም አስፈላጊ ማጣራት ካደረገ በኃላ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለአቃቢ ሕግ ይልካል። አቃቢ ሕግም ስድስት ክሶችን መስርቷል፡፡
ክሱን የተመለከተው የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራቱ ተከሳሾች በሰላማዊ ሠው መሐል ገብተው ሕገወጥ የጦር መሣርያ ታጥቀው ጨለማን ተገን በማድረግ ከፍተኛ የውብድና ተግባር በመፈፀማቸው ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓም በዋለው ችሎት እያንዳዳቸው በአስራ ስምንት አመት እስራት እንዲቀጡ የወሠነባቸው መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር ሙሉ ጉደታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
Via : dagu
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አዲሱ ነጋሽ ፣ደሮ ተሾመ፣ ደጀኔ ተስፋና ቶላ አለሙ የተባሉ አራት ወጣቶች ነዋሪነታቸው በኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ኑኑ ሳዩ ቀበሌ ነው።ወጣቶቹ በአካባቢያቸው የሚታወቁት የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ሲሆን በመዝናኛ ስፍራም ሆነ በተለያዩ ቦታውች የማይነጣጠሉ ጓደኛማቾች መሆናቸዉን የወረዳዉ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ሙሉ ጉደታ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ከቅርብ ግዜያት ወዲህ ግን የተለየና የተለወጠ እንቅስቃሴ በአካባቢው ያሣዩ እንደነበረም ይገልፃሉ።
ወጣቶቹ በአካባቢው ማሕበረሠብ ውስጥ ትዝብት ውስጥ ወድቀው ባሉበት ወቅት ጥር 5 ቀን 2017 ዓም ምሽት አልጌ ሠዮ በተባለ ስፍራ ያልተፈቀደ የጦር መሠርያ በመታጠቅ በአካባቢው ነዋሪ የሆኑት አራት ግለሠቦች አግተው በመውሰድ ከአንድ መቶ እስከ ሑለት መቶ ሺሕ ብር ድረስ ቤተሠቦቻቸው እንዲያመጡ በማስገደድ ቆይተዋል። ከጥቅምት 21 እስከ ጥር 5 ቀን 2017 ዓም ድረስ በዚሑ አካባቢ ለአራት ወራት የእገታ ወንጀል ሲፈፅሙ በመቆየት ገንዘብ ቤተሠቦቻቸውን ጠይቀው የሰጡትን ሲለቁ መክፍል አንችልም ያሉት ደግሞ ልጆቻቸውን ጭምር በማገት ተደራራቢ ወንጀል ሲፈፅሙ እንደነበረ በማስረጃ ተረጋግጧል፡፡
ወጣቶቹ አንድ ግለሠብን አግተው በመውሠድ ለወራት ባዘጋጁት ስፍራ በማስቀመጥ ካቆዩት በኃላ 200 ሺ ብር እንዲያመጣ ጠይቀውት የለኝም በማለቱ ፣ እሱን በመልቀቅ በእርሱ ፋንታ ልጁን አግተው በመውሰድ 300 ሺሕ ብር ተቀብለዋል፡፡የተቋቋመው የፀጥታ ግብረ ኃይል ሙሉ መረጃ ከደረሰዉ በኃላ ባደረገዉ ክትትል አራቱንም በቁጥጥር ስር አዉሏል፡፡ፖሊስም አስፈላጊ ማጣራት ካደረገ በኃላ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለአቃቢ ሕግ ይልካል። አቃቢ ሕግም ስድስት ክሶችን መስርቷል፡፡
ክሱን የተመለከተው የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራቱ ተከሳሾች በሰላማዊ ሠው መሐል ገብተው ሕገወጥ የጦር መሣርያ ታጥቀው ጨለማን ተገን በማድረግ ከፍተኛ የውብድና ተግባር በመፈፀማቸው ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓም በዋለው ችሎት እያንዳዳቸው በአስራ ስምንት አመት እስራት እንዲቀጡ የወሠነባቸው መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር ሙሉ ጉደታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
Via : dagu
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍3🤯2😢2
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት 667 የፈተና ማዕከላት ተዘጋጁ
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ገለፀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለፋና እንደገለጹት÷ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልል ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ÷ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።
ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩንም አንስተዋል።
ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ሉት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ገለፀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለፋና እንደገለጹት÷ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልል ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ÷ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።
ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩንም አንስተዋል።
ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ሉት።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7😁6👍2
ቡና ለገበያ አውጡ‼️
በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ምክንያት የቡና ዋጋ ስለማይጨምር፣ አምራችና ነጋዴዎች ምርታቸውን ለገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው ተገለጸ‼️
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበለ የመካከለኛው ምስራቅን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚቀሰቀሱ ግጭቶች ምክንያት የቡና ዋጋ ሊጨምር ይችላል በሚል የተሳሳተ መረጃ ነጋዴዎች ኪሳራ ውስጥ እንዳይገቡ አሳስበዋል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና ምርቷ በስፋት የምትታወቀው ብራዚል ከሰኔ ወር ጀምሮ 78 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ለገበያ ስለምታቀርብ፣ የሀገራችን አምራችና ነጋዴዎች ከዛ አስቀድመው ገበያ ላይ ቢያወጡት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ የቡና ዋጋ በቶን 30 በመቶ ያህል መቀነሱን የገለጹት ዶክተር አዱኛ፤ ምንም እንኳን ለሀገራችን ጉዳት ሆኖ የሚታይ ባይሆንም የቬትናምና የብራዚል ቡና ወደ ገበያ ከገባ ከዚህ በታች ሊወርድ ስለሚችል ምርቱን ባለው ገበያ ማቅረብ ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያን ጨምሮ ቬትናምና ብራዚል በዚህ ዓመት ከፍተኛ የቡና ምርት ማምረታቸው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊከማች ይችላል ተብሎ ከተገመተው 8 ሚሊዮን ቶን በላይ የቡና ምርት እንዲኖር እንደሚያደርግና ይህም ለዋጋው መቀነስ አንዱ ምክንያት እንደሆነ ገልፀዋል።
የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ በማጓጓዣው ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ ስለሚያሳድር በገበያው ላይ ተግዳሮት ቢፈጥርም፣ በቡና ዋጋ ላይ ግን ለውጥ እንደማይኖር ነው የተናገሩት።
የኢትዮጵያ የቡና ምርት ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በዋጋም በገበያም የተሻለ እንደሆነና እስካሁንም ከደረጃ 4 በላይ የሆኑ የቡና ዓይነቶችን ብቻ ለዓለም አቀፉ ገበያ በማቅረብ ታዋቂነትንና የገበያ ትስስርን የመፍጠር ሂደቱ ውጤታማ እንዳደረገው ተናግረዋል።
በዘንድሮው የቡና ሽያጭም ኢትዮጵያ 320 ሺህ ሜትሪክ ቶን ቡና ወደ ውጭ ገበያ የላከች ሲሆን፣ ከዚህም 2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደተገኘ አመልክተዋል።
የቡና አምራችና ነጋዴዎች በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ምክንያት የቡና ዋጋ ይጨምራል በሚል ቡና ማከማቸት እንደሌለባቸውና ምርታቸውን ባለው ገበያ መሸጥ እንዳለባቸው ተመላክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ምክንያት የቡና ዋጋ ስለማይጨምር፣ አምራችና ነጋዴዎች ምርታቸውን ለገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው ተገለጸ‼️
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበለ የመካከለኛው ምስራቅን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚቀሰቀሱ ግጭቶች ምክንያት የቡና ዋጋ ሊጨምር ይችላል በሚል የተሳሳተ መረጃ ነጋዴዎች ኪሳራ ውስጥ እንዳይገቡ አሳስበዋል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና ምርቷ በስፋት የምትታወቀው ብራዚል ከሰኔ ወር ጀምሮ 78 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ለገበያ ስለምታቀርብ፣ የሀገራችን አምራችና ነጋዴዎች ከዛ አስቀድመው ገበያ ላይ ቢያወጡት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ የቡና ዋጋ በቶን 30 በመቶ ያህል መቀነሱን የገለጹት ዶክተር አዱኛ፤ ምንም እንኳን ለሀገራችን ጉዳት ሆኖ የሚታይ ባይሆንም የቬትናምና የብራዚል ቡና ወደ ገበያ ከገባ ከዚህ በታች ሊወርድ ስለሚችል ምርቱን ባለው ገበያ ማቅረብ ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያን ጨምሮ ቬትናምና ብራዚል በዚህ ዓመት ከፍተኛ የቡና ምርት ማምረታቸው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊከማች ይችላል ተብሎ ከተገመተው 8 ሚሊዮን ቶን በላይ የቡና ምርት እንዲኖር እንደሚያደርግና ይህም ለዋጋው መቀነስ አንዱ ምክንያት እንደሆነ ገልፀዋል።
የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ በማጓጓዣው ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ ስለሚያሳድር በገበያው ላይ ተግዳሮት ቢፈጥርም፣ በቡና ዋጋ ላይ ግን ለውጥ እንደማይኖር ነው የተናገሩት።
የኢትዮጵያ የቡና ምርት ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በዋጋም በገበያም የተሻለ እንደሆነና እስካሁንም ከደረጃ 4 በላይ የሆኑ የቡና ዓይነቶችን ብቻ ለዓለም አቀፉ ገበያ በማቅረብ ታዋቂነትንና የገበያ ትስስርን የመፍጠር ሂደቱ ውጤታማ እንዳደረገው ተናግረዋል።
በዘንድሮው የቡና ሽያጭም ኢትዮጵያ 320 ሺህ ሜትሪክ ቶን ቡና ወደ ውጭ ገበያ የላከች ሲሆን፣ ከዚህም 2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደተገኘ አመልክተዋል።
የቡና አምራችና ነጋዴዎች በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ምክንያት የቡና ዋጋ ይጨምራል በሚል ቡና ማከማቸት እንደሌለባቸውና ምርታቸውን ባለው ገበያ መሸጥ እንዳለባቸው ተመላክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍4
⚡️ እስራኤል በጋዛ፣ ሊባኖስ እና ሶሪያ 1,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ገደማ መሬት መቆጣጠሯ ተገለጠ!
የፋይናንሻል ታይምስ ባደረገው አዲስ ትንተና መሠረት፣ ከጥቅምት 7 ጥቃት በኋላ እስራኤል በጋዛ፣ በሊባኖስ እና በሶሪያ በድምሩ የሀገሪቱን የ1949 ድንበር 5% የሚያክል (1,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር) መሬት በቁጥጥሯ ሥር አውላለች።
በደቡብ ሊባኖስ፦ ከተያዘው መሬት ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው እዚህ የሚገኝ ሲሆን፣ እስራኤል ሄዝቦላህን ወደ ኋላ ለመግፋት በሚል እስከ 12 ኪሎ ሜትር ዘልቃ በመግባት “የደህንነት ቀጠና” ፈጥራለች። ሙሉ መንደሮች የወደሙ ሲሆን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር ሁኔታውን “ከጋዛው ሞዴል” ጋር አነጻጽረውታል።
በጋዛ ሰርጥ፦ የእስራኤል ጦር በአሁኑ ወቅት ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የጋዛ ግዛት የተቆጣጠረ ሲሆን፣ ተጨማሪ የደህንነት ቀጠናዎችን በመፍጠሩ ምክንያት የጋዛ ህዝብ ከጦርነቱ በፊት ከነበረው ይዞታው 40% በሚሆነው ጠባብ መሬት ላይ ተጨናንቆ እንዲኖር ተገዷል።
በሶሪያ፦ እስራኤል ከኮረብታማው የሄርሞን ተራራ በስተደቡብ ያለውን የድንበር አካባቢ ወደ 233 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚጠጋ መሬት ተቆጣጥራለች።
ኔታንያሁ ጦራቸው ከሊባኖስ “አይወጣም” ማለታቸውን ተከትሎ፣ እንዲሁም የእስራኤል ቀኝ አክራሪ ሚኒስትሮች በቦታው ላይ አዳዲስ ሰፈራዎች እንዲመሰረቱና “ሊታኒ ወንዝ” አዲሱ ድንበር እንዲሆን መጠየቃቸው፣ ይዞታው ቋሚ ሊሆን ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት በጎረቤት ሀገራት ላይ ፈጥሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የፋይናንሻል ታይምስ ባደረገው አዲስ ትንተና መሠረት፣ ከጥቅምት 7 ጥቃት በኋላ እስራኤል በጋዛ፣ በሊባኖስ እና በሶሪያ በድምሩ የሀገሪቱን የ1949 ድንበር 5% የሚያክል (1,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር) መሬት በቁጥጥሯ ሥር አውላለች።
በደቡብ ሊባኖስ፦ ከተያዘው መሬት ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው እዚህ የሚገኝ ሲሆን፣ እስራኤል ሄዝቦላህን ወደ ኋላ ለመግፋት በሚል እስከ 12 ኪሎ ሜትር ዘልቃ በመግባት “የደህንነት ቀጠና” ፈጥራለች። ሙሉ መንደሮች የወደሙ ሲሆን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር ሁኔታውን “ከጋዛው ሞዴል” ጋር አነጻጽረውታል።
በጋዛ ሰርጥ፦ የእስራኤል ጦር በአሁኑ ወቅት ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የጋዛ ግዛት የተቆጣጠረ ሲሆን፣ ተጨማሪ የደህንነት ቀጠናዎችን በመፍጠሩ ምክንያት የጋዛ ህዝብ ከጦርነቱ በፊት ከነበረው ይዞታው 40% በሚሆነው ጠባብ መሬት ላይ ተጨናንቆ እንዲኖር ተገዷል።
በሶሪያ፦ እስራኤል ከኮረብታማው የሄርሞን ተራራ በስተደቡብ ያለውን የድንበር አካባቢ ወደ 233 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚጠጋ መሬት ተቆጣጥራለች።
ኔታንያሁ ጦራቸው ከሊባኖስ “አይወጣም” ማለታቸውን ተከትሎ፣ እንዲሁም የእስራኤል ቀኝ አክራሪ ሚኒስትሮች በቦታው ላይ አዳዲስ ሰፈራዎች እንዲመሰረቱና “ሊታኒ ወንዝ” አዲሱ ድንበር እንዲሆን መጠየቃቸው፣ ይዞታው ቋሚ ሊሆን ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት በጎረቤት ሀገራት ላይ ፈጥሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😡10❤7👍6
የአዋሽ-ኮምቦልቻ-ሐራ ገበያ የባቡር መስመር ግንባታ ከዓመታት መቋረጥ በኋላ ዳግም ተጀመረ!
በአዋሽ-ኮምቦልቻ-ሐራ ገበያ መስመር ላይ ተቋርጦ የነበረው የ1.7 ቢሊዮን ዶላር የባቡር መስመር ግንባታ፣ ከዓመታት መዘግየት በኋላ በይፋ ዳግም መጀመሩ ተገለጸ።
ይህ 392 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኤሌክትሪክ ባቡር መስመር፣ የአማራ ክልል ዋና ዋና የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከላትን ከአዲስ አበባ-ጂቡቲ የባቡር ኮሪደር ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ለሀገሪቱ የጭነትና የሰው ትራንስፖርት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
ግንባታው በ2015 እ.ኤ.አ. በቱርኩ "ያፒ መርከዚ" ኩባንያ የተጀመረ ቢሆንም፣ በኖቬምበር 2020 በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ምክንያት መሠረተ ልማቶቹ ላይ ጉዳት ደርሶና ውሎች ተስተጓጉለው ሥራው ቆሞ ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት በአካባቢው ያለው የጸጥታ ሁኔታ በመሻሻሉ ሠራተኞችና መሣሪያዎች ወደ ሳይት የተመለሱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ባቡር ኮርፖሬሽን የጥገና እና መልሶ ግንባታ ሥራው በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአዋሽ-ኮምቦልቻ-ሐራ ገበያ መስመር ላይ ተቋርጦ የነበረው የ1.7 ቢሊዮን ዶላር የባቡር መስመር ግንባታ፣ ከዓመታት መዘግየት በኋላ በይፋ ዳግም መጀመሩ ተገለጸ።
ይህ 392 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኤሌክትሪክ ባቡር መስመር፣ የአማራ ክልል ዋና ዋና የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከላትን ከአዲስ አበባ-ጂቡቲ የባቡር ኮሪደር ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ለሀገሪቱ የጭነትና የሰው ትራንስፖርት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
ግንባታው በ2015 እ.ኤ.አ. በቱርኩ "ያፒ መርከዚ" ኩባንያ የተጀመረ ቢሆንም፣ በኖቬምበር 2020 በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ምክንያት መሠረተ ልማቶቹ ላይ ጉዳት ደርሶና ውሎች ተስተጓጉለው ሥራው ቆሞ ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት በአካባቢው ያለው የጸጥታ ሁኔታ በመሻሻሉ ሠራተኞችና መሣሪያዎች ወደ ሳይት የተመለሱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ባቡር ኮርፖሬሽን የጥገና እና መልሶ ግንባታ ሥራው በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15👍4🤣4