🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ።
🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።
✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።
📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+r3LZG4PCAKI3NmMy
🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።
✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።
📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+r3LZG4PCAKI3NmMy
👍5❤1🤩1
ትራምፕ አስቸኳይ ስብሰባ ጠሩ‼️
ትራምፕ ኢራንን በተመለከተ አስቸኳይ የብሔራዊ የደህንነት ስብሰባ የጠሩ ሲሆን በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃን እንደገና ለማስጀመር እንዳሰቡ' - አክሲዮስ ዘግቧል።
በኢራን ላይ በቀሩ ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ ጥቃት ለመፈፀም ትራምፕ እቅድ እንዳላቸው ተነግሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ትራምፕ ኢራንን በተመለከተ አስቸኳይ የብሔራዊ የደህንነት ስብሰባ የጠሩ ሲሆን በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃን እንደገና ለማስጀመር እንዳሰቡ' - አክሲዮስ ዘግቧል።
በኢራን ላይ በቀሩ ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ ጥቃት ለመፈፀም ትራምፕ እቅድ እንዳላቸው ተነግሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍14👏4❤3😡3🫡2
መረጃ‼️
በኢትዮጵያ የአሜሪካ የርሃብ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት (ፈውስ ኔት)፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር መቋረጥ የምግብ እጥረት ቀውሱን አባብሶታል አለ።
በምግብ ለሥራ የምግብ ዋስትና ችግር ላለባቸው ዜጎች በበርካታ የአገሪቱ ክፍሎች የሚሠጠው ድጋፍ ከጥር ጀምሮ ተቋርጧል።
በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ሳቢያ የነዳጅና የምግብ ዋጋ መናር እንዲሁም የብር የመግዛት አቅም መቀነስና የግጭት ተጽዕኖዎች፣ በቤተሰቦች የምግብ ተደራሽነት ላይ ተጽዕኖ መፍጠራቸውን ተቋሙ ገልጧል።
ደረጃ 4 አስቸኳይ የምግብ እጥረት ቀውስ በግንቦት ወር በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ቆላማ አካባቢዎችና ባለፉት ወራት ጋምቤላ በገቡ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ላይ ይቀጥላል ተብሏል።
ደረጃ 3 ቀውስ በምሥራቅ ትግራይ፣ በሰሜን ምሥራቅ አማራ፣ በሰሜን አፋር፣ ኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎች የሚቀጥል ሲሆን፣ የተወሠኑ ቤተሰቦች ሁኔታ ወደ ደረጃ 4 ቀውስ ሊወርድ እንደሚችል ሪፖርቱ አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በኢትዮጵያ የአሜሪካ የርሃብ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት (ፈውስ ኔት)፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የሴፍቲ ኔት መርሃ ግብር መቋረጥ የምግብ እጥረት ቀውሱን አባብሶታል አለ።
በምግብ ለሥራ የምግብ ዋስትና ችግር ላለባቸው ዜጎች በበርካታ የአገሪቱ ክፍሎች የሚሠጠው ድጋፍ ከጥር ጀምሮ ተቋርጧል።
በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ሳቢያ የነዳጅና የምግብ ዋጋ መናር እንዲሁም የብር የመግዛት አቅም መቀነስና የግጭት ተጽዕኖዎች፣ በቤተሰቦች የምግብ ተደራሽነት ላይ ተጽዕኖ መፍጠራቸውን ተቋሙ ገልጧል።
ደረጃ 4 አስቸኳይ የምግብ እጥረት ቀውስ በግንቦት ወር በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ቆላማ አካባቢዎችና ባለፉት ወራት ጋምቤላ በገቡ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ላይ ይቀጥላል ተብሏል።
ደረጃ 3 ቀውስ በምሥራቅ ትግራይ፣ በሰሜን ምሥራቅ አማራ፣ በሰሜን አፋር፣ ኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎች የሚቀጥል ሲሆን፣ የተወሠኑ ቤተሰቦች ሁኔታ ወደ ደረጃ 4 ቀውስ ሊወርድ እንደሚችል ሪፖርቱ አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤15😢12👍3😡3🙏1
“ለሁሉም ነገር ተዘጋጅቻለሁ”ኢራን
የኢራኑ ቁልፍ ተደራዳሪ መሐመድ ጋሊባፍ”አገሬ ለሁሉም ምርጫዎች ተዘጋጅታለች”አሉ።
የኢራኑ ከፍተኛ ተደራዳሪ እና የፓርላማ አፈ ጉባዔ “ጦራችን ዝግጁ ነው፤የትኛውንም ምላሽ ይሰጣል ፤በየትኛውም መንገድ ተዘጋጅተናል “ማለታቸው የውጥረቱን አለመብረድ ጠቋሚ ያደርገዋል።
የተሳሳት ስሌት እና ውሳኔ ሁል ጊዜም ውጤቱ የተሳሳተ ነው ያሉት ጋሊባፍ ዓለም የተረዳችውም ይህኑን ነው ብለዋል።
ኢራን ያቀረበችውን ባለ14 ነጥብ እቅድ ከመቀበል ውጭ ሌላ ምርጫ የላቸውም ሲሉም ተደራዳሪው ቀድመው ሀሳብ መስጠታቸው አይዘነጋም።
ሌሎች አማራጮችን ለመውሰድ መሞከር ሙሉ ለሙሉ አግላይነትን የሚያንፀባርቅ ይሆናል በሚልም አሜሪካን አሳስበዋል።
በዋሽንግተንና ቴህራን መካከል ያለው የሆርሙዝ ሰርጥ ውጥረት የዓለምን ኢኮኖሚ ከመጉዳቱም ባሻገር ለኢራን አዲስ የመደራደሪያ ነጥብ ሆኗታልም ተብሏል።
ጋሊባፍ ጠንካራውን አስተያየት የሰጡት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ያቀረበችው ውጥን “ፈፅሞ ተቀባይነት የለውም “ማለታቸውን ተከትሎ ነው።
ዘገባው የሲ ኤን ኤን ነው።
በ-ቢኒያም ካሴ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢራኑ ቁልፍ ተደራዳሪ መሐመድ ጋሊባፍ”አገሬ ለሁሉም ምርጫዎች ተዘጋጅታለች”አሉ።
የኢራኑ ከፍተኛ ተደራዳሪ እና የፓርላማ አፈ ጉባዔ “ጦራችን ዝግጁ ነው፤የትኛውንም ምላሽ ይሰጣል ፤በየትኛውም መንገድ ተዘጋጅተናል “ማለታቸው የውጥረቱን አለመብረድ ጠቋሚ ያደርገዋል።
የተሳሳት ስሌት እና ውሳኔ ሁል ጊዜም ውጤቱ የተሳሳተ ነው ያሉት ጋሊባፍ ዓለም የተረዳችውም ይህኑን ነው ብለዋል።
ኢራን ያቀረበችውን ባለ14 ነጥብ እቅድ ከመቀበል ውጭ ሌላ ምርጫ የላቸውም ሲሉም ተደራዳሪው ቀድመው ሀሳብ መስጠታቸው አይዘነጋም።
ሌሎች አማራጮችን ለመውሰድ መሞከር ሙሉ ለሙሉ አግላይነትን የሚያንፀባርቅ ይሆናል በሚልም አሜሪካን አሳስበዋል።
በዋሽንግተንና ቴህራን መካከል ያለው የሆርሙዝ ሰርጥ ውጥረት የዓለምን ኢኮኖሚ ከመጉዳቱም ባሻገር ለኢራን አዲስ የመደራደሪያ ነጥብ ሆኗታልም ተብሏል።
ጋሊባፍ ጠንካራውን አስተያየት የሰጡት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ያቀረበችው ውጥን “ፈፅሞ ተቀባይነት የለውም “ማለታቸውን ተከትሎ ነው።
ዘገባው የሲ ኤን ኤን ነው።
በ-ቢኒያም ካሴ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤23👍2🤔1😢1
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘገየ አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
አቶ ዘገየ የግብርና ሚኒስቴርን ከ1968–1970 ዓ.ም እና ከ1983 - 1984 ዓ.ም በሚኒስትርነት ማገልገላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል፡፡
አቶ ዘገየ አስፋው መሬት ለአራሹ አዋጅ እንዲታወጅ ከፍተኛ ድርሻ ነበራቸው፡፡
አቶ ዘገየ አስፋው ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ አለም ተለይተዋል ሲል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናግሯል፡፡
ከዚህ አለም በሞት እስከተለዩ ድረስም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው እየሰሩ ነበር፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
አቶ ዘገየ የግብርና ሚኒስቴርን ከ1968–1970 ዓ.ም እና ከ1983 - 1984 ዓ.ም በሚኒስትርነት ማገልገላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል፡፡
አቶ ዘገየ አስፋው መሬት ለአራሹ አዋጅ እንዲታወጅ ከፍተኛ ድርሻ ነበራቸው፡፡
አቶ ዘገየ አስፋው ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ አለም ተለይተዋል ሲል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናግሯል፡፡
ከዚህ አለም በሞት እስከተለዩ ድረስም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው እየሰሩ ነበር፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
😢13❤12👏3👍2🏆1
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ ጉዳይ ላይ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ማስፈራሪያ እና ጫና እንደሚደርስባቸው ገለጹ!
ግንቦት 24 የሚካሄደውን 7ኛው አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ በአማራ ክልል እንቅስቃሴ የሚያደርጉ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የተለያዩ ማስፈራሪያዎች እንደሚደርስባቸው ለ “ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል።
ለደኅንነታቸው ሲባል ሥማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ እነዚህ የድርጅቶቹ አመራሮች፣ ማስፈራሪያ እና ጫናው ከሁለት ወገን የሚመጣ ነው ብለዋል።
በባሕር ዳር የሴቶችን ፖለቲካዊ ተሳትፎ መሰረት አድርጎ የሚሠራ የአንድ ድርጅት አመራር የሆኑ ግለሰብ እንደሚሉት “ሴቶች በምርጫ ሂደት ውስጥ ሊኖራቸው የሚገባውን የተሳትፎ ዓይነትና መጠን የሚያስተምር ፕሮጀክት ላይ ሴቶችን ‘አሠለጠንን’ የሚል መረጃ በራሳችን የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ከአጋራን በኋላ ተደጋጋሚ ስልኮች ተደወሉብን” በማለት ገልጸዋል።
አመራሯ ሲያብራሩ “በየቀኑ ሕዝብ እየገደለ የራሱን ዕድሜ የሚገዛን መንግሥት የምርጫ ቅቡልነት እንዲያገኝ ለማድረግ የምታደርጉትን እንቅስቃሴ አቁሙ የሚል ማስፈራሪያ ነው የሰጡን” ካሉ በኋላ፣ ይህ ማስፈራሪያ የመጣው ፋኖ ተብለው ከሚጠሩት እና በክልሉ ከመንግሥት ጋር ግጭት ውስጥ ካሉ አካላት፣ በስልክ እንደሆነ አስረድተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ግንቦት 24 የሚካሄደውን 7ኛው አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ በአማራ ክልል እንቅስቃሴ የሚያደርጉ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የተለያዩ ማስፈራሪያዎች እንደሚደርስባቸው ለ “ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል።
ለደኅንነታቸው ሲባል ሥማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ እነዚህ የድርጅቶቹ አመራሮች፣ ማስፈራሪያ እና ጫናው ከሁለት ወገን የሚመጣ ነው ብለዋል።
በባሕር ዳር የሴቶችን ፖለቲካዊ ተሳትፎ መሰረት አድርጎ የሚሠራ የአንድ ድርጅት አመራር የሆኑ ግለሰብ እንደሚሉት “ሴቶች በምርጫ ሂደት ውስጥ ሊኖራቸው የሚገባውን የተሳትፎ ዓይነትና መጠን የሚያስተምር ፕሮጀክት ላይ ሴቶችን ‘አሠለጠንን’ የሚል መረጃ በራሳችን የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ከአጋራን በኋላ ተደጋጋሚ ስልኮች ተደወሉብን” በማለት ገልጸዋል።
አመራሯ ሲያብራሩ “በየቀኑ ሕዝብ እየገደለ የራሱን ዕድሜ የሚገዛን መንግሥት የምርጫ ቅቡልነት እንዲያገኝ ለማድረግ የምታደርጉትን እንቅስቃሴ አቁሙ የሚል ማስፈራሪያ ነው የሰጡን” ካሉ በኋላ፣ ይህ ማስፈራሪያ የመጣው ፋኖ ተብለው ከሚጠሩት እና በክልሉ ከመንግሥት ጋር ግጭት ውስጥ ካሉ አካላት፣ በስልክ እንደሆነ አስረድተዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤9👍4👏2😁2
የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን ነው
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን መሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር)እንዳሉት፤ አሰራሩ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለመከላከል ያለመ ነው፡፡
ከዚህ በፊት ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጨረታ ባሸነፈ ድርጅት በኩል የተማሪዎችን የትምህርት ማስረጃ የሚያሳትሙበት አሰራር ለሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አጋላጭ ሆኖ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎቻቸውን ዲግሪ በአንድ ማዕከል ብቻ እንዲያሳትሙ ይደረጋል ብለዋል፡፡
አዲሱ ዲግሪ ታትሞ እስኪደርስ ድረስ ትምህርት ሚኒስቴር ዲግሪ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የድጋፍ ደብዳቤ እንደሚጽፍ ገልጸው፤ ህትመቱ በዚህ ዓመት እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
በ2017 ዓ.ም የተመረቁ ተማሪዎችን ጨምሮ ከዚህ በኋላ የሚመረቁትም ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓት መሰረት በአንድ ማዕከል የሚታተመውን ዲግሪ ብቻ እንዲወስዱ ይደረጋሉ ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ ከ2017 ዓ.ም በፊት ተመርቀው ነገር ግን ዲግሪያቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች በአዲሱ አሰራር ብቻ እንደሚስተናገዱ አመልክተዋል።
ፋና
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን መሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር)እንዳሉት፤ አሰራሩ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለመከላከል ያለመ ነው፡፡
ከዚህ በፊት ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጨረታ ባሸነፈ ድርጅት በኩል የተማሪዎችን የትምህርት ማስረጃ የሚያሳትሙበት አሰራር ለሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አጋላጭ ሆኖ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎቻቸውን ዲግሪ በአንድ ማዕከል ብቻ እንዲያሳትሙ ይደረጋል ብለዋል፡፡
አዲሱ ዲግሪ ታትሞ እስኪደርስ ድረስ ትምህርት ሚኒስቴር ዲግሪ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የድጋፍ ደብዳቤ እንደሚጽፍ ገልጸው፤ ህትመቱ በዚህ ዓመት እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
በ2017 ዓ.ም የተመረቁ ተማሪዎችን ጨምሮ ከዚህ በኋላ የሚመረቁትም ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓት መሰረት በአንድ ማዕከል የሚታተመውን ዲግሪ ብቻ እንዲወስዱ ይደረጋሉ ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ ከ2017 ዓ.ም በፊት ተመርቀው ነገር ግን ዲግሪያቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች በአዲሱ አሰራር ብቻ እንደሚስተናገዱ አመልክተዋል።
ፋና
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤25👍8
1 ሺህ 139 የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች በስነምግባር ጥሰት ተቀጡ‼️
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት 9 ወራት የብልሹ አሰራርና ስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 1 ሺህ 139 የአገልግሎቱ ሠራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃ ወሰደ፡፡
እርምጃ ከተወሰደባቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች መካከል 16 ሲሰናበቱ፤ 721 የደሞዝ ቅጣት የተቀጡ እንዲሁም 402 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ናቸው፡፡
አገልግሎቱ በ1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ ከወሰዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል 103 ሠራተኞች ላይ በደንበኞች የቀረበን ጥቆማ በመመርመር የወሰደው ነው፡፡ ቀሪ 1 ሺህ 36ቱ ተቋሙ በራሱ ግኝት አጣርቶ የወሰዳቸው እርምጃዎች ናቸው፡፡
ባለፉት ዘጠኝ ወራት አገልግሎቱ በሙስና መጠቆሚያ ዘመናዊ መተግበሪያ (Corruption Reporting App) እና በሌሎች አማራጮች ከደንበኞቹ የደረሱትን 427 ጥቆማዎችን መርምሮ በ103 ኃላፊዎችና ሠራተኞች ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን ወስዷል፡፡
በደንበኞቹ በቀረቡት ጥቆማዎች መሰረት 14 የፅሁፍ፣ 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 2 ከቦታ የማንሳትና 7 ስንብት በድምሩ 103 እርምጃዎች ተወስዷል፡፡
ይህም የጥቆማ መቀበያ ስርዓቱ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ፣ ደንበኞች የሚሰጡት ጥቆማ ዋጋ ያለው መሆኑንና የሚታዩ ብልሹ አሰራርን ለመታገል አገልግሎቱ እያደረገ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው፡፡
የብልሹ አሰራር ጥቆማ ከቀረበባቸው ጉዳዮች መካከል የአዲስ ቆጣሪ ጥያቄ፣ የኃይል መቆራረጥና አስቸኳይ ጥገና፣ የቆጣሪ ንባብና የቢል ስብሰባ እንዲሁም ንብረት አያያዝና አጠቃቀም ይገኙበታል፡፡
ደንበኞች አሁንም የዲጂታል የብልሹ አሰራር ጥቆማ መቀበያ (www.eeuethics.et) በመጠቀም በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የሚታዩ የሙስናና ብልሹ አሰራር ችግሮችን እንዲጠቁሙ አገልግሎቱ ያበረታታል፡፡
አገልግሎቱም ማንኛውም የህግና የሥነምግባር ጥሰት ድርጊቶችን ለሚያጋልጡ ጠቋሚዎች እውቅና የሚሰጥ ሲሆን፤ ተገቢውን ጥበቃ በማድረግ በነፃነትና በተነሳሽነት የሙስና ወንጀሎችን እንዲያጋልጡ የማበረታታና ምቹ ሁኔታዎችን የሚፍጠር መሆኑን ይገልፃል፡፡
ደንበኞች በወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699/2003 መሰረት ህጋዊ ከለላ የማግኘት መብታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፤ በአገልግሎቱ አሰራርና መመሪያ መሰረት ጠቋሚዎች የሚያቀርቡት ህጋዊ ጥያቄ ያለተጽዕኖ እንዲስተናገዱ ተገቢውን ከለላና ጥበቃ ይሰጣል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት 9 ወራት የብልሹ አሰራርና ስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 1 ሺህ 139 የአገልግሎቱ ሠራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃ ወሰደ፡፡
እርምጃ ከተወሰደባቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች መካከል 16 ሲሰናበቱ፤ 721 የደሞዝ ቅጣት የተቀጡ እንዲሁም 402 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ናቸው፡፡
አገልግሎቱ በ1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ ከወሰዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል 103 ሠራተኞች ላይ በደንበኞች የቀረበን ጥቆማ በመመርመር የወሰደው ነው፡፡ ቀሪ 1 ሺህ 36ቱ ተቋሙ በራሱ ግኝት አጣርቶ የወሰዳቸው እርምጃዎች ናቸው፡፡
ባለፉት ዘጠኝ ወራት አገልግሎቱ በሙስና መጠቆሚያ ዘመናዊ መተግበሪያ (Corruption Reporting App) እና በሌሎች አማራጮች ከደንበኞቹ የደረሱትን 427 ጥቆማዎችን መርምሮ በ103 ኃላፊዎችና ሠራተኞች ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን ወስዷል፡፡
በደንበኞቹ በቀረቡት ጥቆማዎች መሰረት 14 የፅሁፍ፣ 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 2 ከቦታ የማንሳትና 7 ስንብት በድምሩ 103 እርምጃዎች ተወስዷል፡፡
ይህም የጥቆማ መቀበያ ስርዓቱ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ፣ ደንበኞች የሚሰጡት ጥቆማ ዋጋ ያለው መሆኑንና የሚታዩ ብልሹ አሰራርን ለመታገል አገልግሎቱ እያደረገ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው፡፡
የብልሹ አሰራር ጥቆማ ከቀረበባቸው ጉዳዮች መካከል የአዲስ ቆጣሪ ጥያቄ፣ የኃይል መቆራረጥና አስቸኳይ ጥገና፣ የቆጣሪ ንባብና የቢል ስብሰባ እንዲሁም ንብረት አያያዝና አጠቃቀም ይገኙበታል፡፡
ደንበኞች አሁንም የዲጂታል የብልሹ አሰራር ጥቆማ መቀበያ (www.eeuethics.et) በመጠቀም በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የሚታዩ የሙስናና ብልሹ አሰራር ችግሮችን እንዲጠቁሙ አገልግሎቱ ያበረታታል፡፡
አገልግሎቱም ማንኛውም የህግና የሥነምግባር ጥሰት ድርጊቶችን ለሚያጋልጡ ጠቋሚዎች እውቅና የሚሰጥ ሲሆን፤ ተገቢውን ጥበቃ በማድረግ በነፃነትና በተነሳሽነት የሙስና ወንጀሎችን እንዲያጋልጡ የማበረታታና ምቹ ሁኔታዎችን የሚፍጠር መሆኑን ይገልፃል፡፡
ደንበኞች በወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699/2003 መሰረት ህጋዊ ከለላ የማግኘት መብታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፤ በአገልግሎቱ አሰራርና መመሪያ መሰረት ጠቋሚዎች የሚያቀርቡት ህጋዊ ጥያቄ ያለተጽዕኖ እንዲስተናገዱ ተገቢውን ከለላና ጥበቃ ይሰጣል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤17👍9💯2🥰1
ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ልምምድ ላይ በገጠማት ድንገተኛ ህመም ሕይወቷ አለፈ
ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናቷ አትሌት የብርጓል መለሰ፤ ዛሬ ማለዳ ልምምዷን እየሠራች ባለችበት ወቅት ህመም ተሰምቷት ለህክምና በሄደችበት ሆስፒታል በሞት እንደተለየች ተሰምቷል፡፡
የ36 ዓመቷ የብርጓል የፓሪስ ግማሽ ማራቶንን ሁለት ጊዜ፣ ሊዝበን ግማሽ ማራቶንን አንድ ጊዜ እንዲሁም የሻንጋይ፣ ፕራግና ሂውስተን ማራቶንን በበላይነት አጠናቃለች፡፡
በ2015ቱ የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በግማሽ ማራቶን ለኢትዮጵያ የነሀስ ሜዳሊያ አስገኝታለች፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናቷ አትሌት የብርጓል መለሰ፤ ዛሬ ማለዳ ልምምዷን እየሠራች ባለችበት ወቅት ህመም ተሰምቷት ለህክምና በሄደችበት ሆስፒታል በሞት እንደተለየች ተሰምቷል፡፡
የ36 ዓመቷ የብርጓል የፓሪስ ግማሽ ማራቶንን ሁለት ጊዜ፣ ሊዝበን ግማሽ ማራቶንን አንድ ጊዜ እንዲሁም የሻንጋይ፣ ፕራግና ሂውስተን ማራቶንን በበላይነት አጠናቃለች፡፡
በ2015ቱ የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በግማሽ ማራቶን ለኢትዮጵያ የነሀስ ሜዳሊያ አስገኝታለች፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
💔41😢20❤8😱4👍2
አፍሪካ ካልተሳካላት አውሮፓ ተስፋ የላትም! - ማክሮን
የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አፍሪካን በሚመለከት ባደረጉት ንግግር፣ የአውሮፓና የአፍሪካ ዕጣ ፈንታ የማይነጣጠል መሆኑን በግልጽ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ አፍሪካን "ምን ማድረግ እንዳለባት" ለመንገር አለመምጣታቸውን ገልጸው፣ የአፍሪካ ስኬትም ሆነ ውድቀት የአውሮፓም ጭምር መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
"አፍሪካ ከወደቀች አውሮፓ ምንም ዕድል አይኖራትም፤ በመከራና በሁከት ትዋጣለች" በማለት፣ የአህጉሪቱ መረጋጋት ለአለም ሰላም ያለውን ወሳኝነት አመላክተዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ስለ አውሮፓ የቅኝ ግዛት ታሪክ እውነቱን ከመናገር ወደኋላ አላሉም።
"የአውሮፓ ቅኝ ግዛት ወንጀሎች የማይካዱ ናቸው" በማለት፣ በታሪክ የተፈጸሙ ስህተቶችንና አስከፊ እውነታዎችን በይፋ አምነዋል።
እርሳቸው የሚወክሉት ትውልድ ቅኝ ግዛት በሌለበት ወቅት የተወለደ መሆኑን የጠቀሱት ማክሮን፣ ንግግራቸው ለትምህርት ሳይሆን ለወደፊት አብሮነትና አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ንግግር አውሮፓ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የቀድሞ የጌታና የሎሌ ግንኙነት ወደ እኩልነት ለመቀየር ያላትን ፍላጎት የሚያሳይ ሆኖ ተወስዷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አፍሪካን በሚመለከት ባደረጉት ንግግር፣ የአውሮፓና የአፍሪካ ዕጣ ፈንታ የማይነጣጠል መሆኑን በግልጽ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ አፍሪካን "ምን ማድረግ እንዳለባት" ለመንገር አለመምጣታቸውን ገልጸው፣ የአፍሪካ ስኬትም ሆነ ውድቀት የአውሮፓም ጭምር መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
"አፍሪካ ከወደቀች አውሮፓ ምንም ዕድል አይኖራትም፤ በመከራና በሁከት ትዋጣለች" በማለት፣ የአህጉሪቱ መረጋጋት ለአለም ሰላም ያለውን ወሳኝነት አመላክተዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ስለ አውሮፓ የቅኝ ግዛት ታሪክ እውነቱን ከመናገር ወደኋላ አላሉም።
"የአውሮፓ ቅኝ ግዛት ወንጀሎች የማይካዱ ናቸው" በማለት፣ በታሪክ የተፈጸሙ ስህተቶችንና አስከፊ እውነታዎችን በይፋ አምነዋል።
እርሳቸው የሚወክሉት ትውልድ ቅኝ ግዛት በሌለበት ወቅት የተወለደ መሆኑን የጠቀሱት ማክሮን፣ ንግግራቸው ለትምህርት ሳይሆን ለወደፊት አብሮነትና አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ንግግር አውሮፓ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የቀድሞ የጌታና የሎሌ ግንኙነት ወደ እኩልነት ለመቀየር ያላትን ፍላጎት የሚያሳይ ሆኖ ተወስዷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪24❤17😡5👍2😁1
የ6 ዓመት ታዳጊን በማገት ገንዘብ ሲቀበሉ የተያዙ ሁለት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ
በሁለት ግለሰቦች ታግቶ የነበረውን የ6 ዓመት ታዳጊ ልጅ ከነ አጋቾቹ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን የዲላ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።ተከሳሾቹ ሲሆኑ ጌቱ ገረመው እና እንዳሻው በቀለ የተባሉ ናቸው።
የ6 ዓመት ታዳጊ የሆነውን ብሩክ ወ/ኪዳነ የተባለ ሲሆን ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ/ም ከዲላ ከተማ ሴሳ ክ/ከተማ ቡኖ ቀበሌ ካለው መኖርያ ቤት ወጥቶ ሳይመለስ በመቅረቱ ቤተሰቦቹ ፈለጋ ላይ እያሉ ተከሳሽ የሆነው ጌቱ ገረመው ስልክ በመደወል ልጃችሁ ለማግኘት 80 ሺህ ብር በባንክ ይግባልን ይላል።የታጋች ወላጆች የተጠየቁትን ገንዘብ ለፖሊስ በማሳወቅ ገቢ ይደረጋል። ከሰዓታት በኋላ ተከሳሽ ጌቱ ገረመው ባንክ በመሄድ 50 ሺህ ብር ወጪ አድርጎ ሲወጣ በቁጥጥር ስር መዋሉ ይታወሳል።
ፖሊስም 48 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ህፃኑ የተደበቀበትን ስፍራ በማወቅ ሁለተኛ ተከሳሽን በቁጥጥር ስር በማዋል የታገተውን የ6 ዓመት ታዳጊውን ለቤተሰብ ማስረከቡን ተገልጿል:: በዚህም ተከሳሾቹ ላይ የወንጀል ምርመራ አጠናክሮ የቀጠለው የዲላ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከዐ/ህግ ጋር ባደረገው የጋራ ጥምረት ክስ መስርቷል፡፡
ክሱን የተመለከተዉ የዲላ ከተማ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት 1ኛ ተከሳሽ በ12 ዓመት እና ሁለተኛ ተከሳሽን ደግሞ በ9 ዓመት ጽኑ እስራት እንድቀጡ ወሳኔ መተላለፉን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ኢንስፔክተር አሸናፊ ሀይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሁለት ግለሰቦች ታግቶ የነበረውን የ6 ዓመት ታዳጊ ልጅ ከነ አጋቾቹ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን የዲላ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።ተከሳሾቹ ሲሆኑ ጌቱ ገረመው እና እንዳሻው በቀለ የተባሉ ናቸው።
የ6 ዓመት ታዳጊ የሆነውን ብሩክ ወ/ኪዳነ የተባለ ሲሆን ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ/ም ከዲላ ከተማ ሴሳ ክ/ከተማ ቡኖ ቀበሌ ካለው መኖርያ ቤት ወጥቶ ሳይመለስ በመቅረቱ ቤተሰቦቹ ፈለጋ ላይ እያሉ ተከሳሽ የሆነው ጌቱ ገረመው ስልክ በመደወል ልጃችሁ ለማግኘት 80 ሺህ ብር በባንክ ይግባልን ይላል።የታጋች ወላጆች የተጠየቁትን ገንዘብ ለፖሊስ በማሳወቅ ገቢ ይደረጋል። ከሰዓታት በኋላ ተከሳሽ ጌቱ ገረመው ባንክ በመሄድ 50 ሺህ ብር ወጪ አድርጎ ሲወጣ በቁጥጥር ስር መዋሉ ይታወሳል።
ፖሊስም 48 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ህፃኑ የተደበቀበትን ስፍራ በማወቅ ሁለተኛ ተከሳሽን በቁጥጥር ስር በማዋል የታገተውን የ6 ዓመት ታዳጊውን ለቤተሰብ ማስረከቡን ተገልጿል:: በዚህም ተከሳሾቹ ላይ የወንጀል ምርመራ አጠናክሮ የቀጠለው የዲላ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከዐ/ህግ ጋር ባደረገው የጋራ ጥምረት ክስ መስርቷል፡፡
ክሱን የተመለከተዉ የዲላ ከተማ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት 1ኛ ተከሳሽ በ12 ዓመት እና ሁለተኛ ተከሳሽን ደግሞ በ9 ዓመት ጽኑ እስራት እንድቀጡ ወሳኔ መተላለፉን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ኢንስፔክተር አሸናፊ ሀይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤18👏5👍4
"በሳዑዲ በሞት ጥላ ሥር ላሉ ኢትዮጵያውያን ምሕረት እንዲደረግ እንጠይቃለን" - አቡነ ማትያስ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያሊክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ወገኖችን በማስመልከት ጥሪ አስተላለፉ።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በከፍተኛ ደረጃ ተነጋግሮ የሞት ፍርዱ እንዲነሳና ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥም አሳስበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያሊክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ወገኖችን በማስመልከት ጥሪ አስተላለፉ።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በከፍተኛ ደረጃ ተነጋግሮ የሞት ፍርዱ እንዲነሳና ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥም አሳስበዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤64👍9🤪9😢1😍1
UAE በኢራን ላይ በድብቅ ጥቃት ፈጸመች።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) በወሰደችው የአፀፋ እርምጃ በኢራን የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መፈጸሟ ተገልጿል።
በላቫን አይስላንድ የሚገኘው የነዳጅ ማጣሪያ በአቡዳቢ ጥቃት ከባድ ጉዳት አስተናግዷል ተብሏል።
አሜሪካ ዩኤኢ የአፀፋ እርምጃ መውሰዷን ማድነቋም ተመላክቷል።
ኢራን በጦርነቱ ከየትኛውም የገልፍ ሀገር በበለጠ ብዙ ጥቃት ያደረሰችው በአቡዳቢ ላይ መሆኑ ተገልጿል። #trtworld
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) በወሰደችው የአፀፋ እርምጃ በኢራን የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መፈጸሟ ተገልጿል።
በላቫን አይስላንድ የሚገኘው የነዳጅ ማጣሪያ በአቡዳቢ ጥቃት ከባድ ጉዳት አስተናግዷል ተብሏል።
አሜሪካ ዩኤኢ የአፀፋ እርምጃ መውሰዷን ማድነቋም ተመላክቷል።
ኢራን በጦርነቱ ከየትኛውም የገልፍ ሀገር በበለጠ ብዙ ጥቃት ያደረሰችው በአቡዳቢ ላይ መሆኑ ተገልጿል። #trtworld
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤19👍8🤪3😢2👏1😁1🎉1👌1
አንጋፋዉ ጋዜጠኛ ወደ ቴሌግራም መጣ፡፡ መረጃዎችን ጎልጉሎ በማዉጣት እራስ ምታት ሆኖል ፡፡
ተቀላቀሉት Join👇👇
"በዚህ ሊንክ ግቡ 👇👇
https://t.me/darashMedia
https://t.me/darashMedia
ተቀላቀሉት Join👇👇
"በዚህ ሊንክ ግቡ 👇👇
https://t.me/darashMedia
https://t.me/darashMedia
❤3👍3
ትራምፕ ወደ ቻይና እየበረሩ ነው‼️
ዶናልድ ትራምፕ ወደ ቻይና አቀኑ።
ፕሬዝዳንቱ ወደ ቻይና ያቀኑት በዋናነት በኢራን፣በንግድ እንዲሁም በታይዋን ጉዳይ ለመምከር ሲሆን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከ10 አመታት በኋላ ወደ ቻይና የተጓዙ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነዋል።
ትራምፕ ከቻይና ጋር ከተወያዩ በኋላ በኢራን ላይ አዲስ ውሳኔ እንደሚወስኑ CNN ዘግቧል።
ቻይና የኢራን ዋነኛ አጋር መሆኗ ይታወቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ዶናልድ ትራምፕ ወደ ቻይና አቀኑ።
ፕሬዝዳንቱ ወደ ቻይና ያቀኑት በዋናነት በኢራን፣በንግድ እንዲሁም በታይዋን ጉዳይ ለመምከር ሲሆን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከ10 አመታት በኋላ ወደ ቻይና የተጓዙ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነዋል።
ትራምፕ ከቻይና ጋር ከተወያዩ በኋላ በኢራን ላይ አዲስ ውሳኔ እንደሚወስኑ CNN ዘግቧል።
ቻይና የኢራን ዋነኛ አጋር መሆኗ ይታወቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12😁11👍2😱1🙉1😡1
በፖሊስ አባል ህይወቱ ለጠፋው ግለሰብ ቤተሰቦች የመኖሪያ ቤትና የመሥሪያ ቦታ ተሰጠ
በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 በፖሊስ አባል ህይወቱ ያለፈው የአቶ ተገኝ ባልቻ ቤተሰቦች፣ ከአዲስ አበባ አስተዳደር የመኖሪያ ቤትና የመሥሪያ ቦታ ርክክብ ተደረገ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 በፖሊስ አባል ህይወቱ ያለፈው የአቶ ተገኝ ባልቻ ቤተሰቦች፣ ከአዲስ አበባ አስተዳደር የመኖሪያ ቤትና የመሥሪያ ቦታ ርክክብ ተደረገ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🌚40🤣28❤14🙉9👍7🤪5🤔3👏2😢2🥰1👌1
የአሜሪካ የፀሐይ ብርሃን ኃይል አምራቾች በኢትዮጵያ ላይ የንግድ ምርመራ እንዲደረግ ጠየቁ
በአሜሪካ የሚገኙ የፀሐይ ብርሃን ኃይል አምራቾች፣ የቻይና ኩባንያዎች የአሜሪካን የታሪፍ ቀረጥ ለማምለጥ ምርቶቻቸውን በኢትዮጵያ በኩል እያሳለፉ ነው በሚል የንግድ ምርመራ እንዲደረግ ለፌዴራል ባለስልጣናት ጥያቄ ማቅረባቸው ታዉቋል።
ኩባንያዎቹ ለአሜሪካ የንግድ ሚኒስቴር ባስገቡት አቤቱታ፣ "ቶዮ" እና "ኦሪጅን ሶላር ማንፋክቸሪንግ" የተባሉ የጃፓን ኩባንያዎች በቻይና የተሰሩ ግብዓቶችን በመጠቀም በኢትዮጵያ ውስጥ የሶላር ሴሎችን እንደሚያመርቱ ገልጸዋል። እነዚህም ምርቶች በኢትዮጵያ ወይም በቬትናም ተገጣጥመው ወደ አሜሪካ እንደሚላኩ ተጠቁሟል።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2025 አጋማሽ ላይ የጀመረው የኢትዮጵያ የሶላር ምርቶች ወደ አሜሪካ የመላክ ሂደት፣ እስከ ዓመቱ መጨረሻ 300 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ይህም ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰባተኛዋ ከፍተኛ የሶላር ምርት ወደ አሜሪካ ላኪ ሀገር አድርጓታል።
አቤቱታውን ካቀረቡት መካከል "ፈርስት ሶላር" እና የደቡብ ኮሪያው "ኪውሴልስ" የሚገኙበት ሲሆን፣ ኩባንያዎቹ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በአሜሪካ ፋብሪካዎች ላይ ኢንቨስት ማድረጋቸውንና ይህ "ህገ-ወጥ የታሪፍ ማምለጫ መንገድ" እድገታችንን ያደናቅፋል ሲሉ ተከራክረዋል።
አሜሪካ ከዚህ ቀደም መሰል እርምጃዎችን በቻይና፣ ማሌዢያ፣ ታይላንድ፣ ካምቦዲያ እና ቬትናም ምርቶች ላይ መውሰዷ ይታወሳል። የንግድ ሚኒስቴሩ የቀረበለትን አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በኢያሱ ዘካሪያስ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በአሜሪካ የሚገኙ የፀሐይ ብርሃን ኃይል አምራቾች፣ የቻይና ኩባንያዎች የአሜሪካን የታሪፍ ቀረጥ ለማምለጥ ምርቶቻቸውን በኢትዮጵያ በኩል እያሳለፉ ነው በሚል የንግድ ምርመራ እንዲደረግ ለፌዴራል ባለስልጣናት ጥያቄ ማቅረባቸው ታዉቋል።
ኩባንያዎቹ ለአሜሪካ የንግድ ሚኒስቴር ባስገቡት አቤቱታ፣ "ቶዮ" እና "ኦሪጅን ሶላር ማንፋክቸሪንግ" የተባሉ የጃፓን ኩባንያዎች በቻይና የተሰሩ ግብዓቶችን በመጠቀም በኢትዮጵያ ውስጥ የሶላር ሴሎችን እንደሚያመርቱ ገልጸዋል። እነዚህም ምርቶች በኢትዮጵያ ወይም በቬትናም ተገጣጥመው ወደ አሜሪካ እንደሚላኩ ተጠቁሟል።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2025 አጋማሽ ላይ የጀመረው የኢትዮጵያ የሶላር ምርቶች ወደ አሜሪካ የመላክ ሂደት፣ እስከ ዓመቱ መጨረሻ 300 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ይህም ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰባተኛዋ ከፍተኛ የሶላር ምርት ወደ አሜሪካ ላኪ ሀገር አድርጓታል።
አቤቱታውን ካቀረቡት መካከል "ፈርስት ሶላር" እና የደቡብ ኮሪያው "ኪውሴልስ" የሚገኙበት ሲሆን፣ ኩባንያዎቹ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በአሜሪካ ፋብሪካዎች ላይ ኢንቨስት ማድረጋቸውንና ይህ "ህገ-ወጥ የታሪፍ ማምለጫ መንገድ" እድገታችንን ያደናቅፋል ሲሉ ተከራክረዋል።
አሜሪካ ከዚህ ቀደም መሰል እርምጃዎችን በቻይና፣ ማሌዢያ፣ ታይላንድ፣ ካምቦዲያ እና ቬትናም ምርቶች ላይ መውሰዷ ይታወሳል። የንግድ ሚኒስቴሩ የቀረበለትን አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በኢያሱ ዘካሪያስ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤21👍6