አዲስ MAGAZINE - መረጃ
31.5K subscribers
6.42K photos
221 videos
3 files
262 links
#አዲስ_Magazine_መረጃ

#መረጃዎች_በትኩሱ ና ሳይዉሉ እንዲሁም ሳያድሩ በቻናሉ በኩል ይደርሳሉ

#ለአስተያየት እና ለማስታወቂያ ስራዎች 👇👇
@Addis_Magazinebot

Addis Ababa , Ethiopia

የአዲስ ነገር መረጃ ቻናል አጋር ሚዲያ
Download Telegram
ሰበር ዜና፦ በኤምሬትስ እና ኩዌት ላይ ጥቃት ተሰነዘረ

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ቢኖርም፣ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና በኩዌት ላይ ጥቃት መፈጸሙ ተሰማ። ጥቃቱ የተሰነዘረው በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር በሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ አካባቢ ባለው የደህንነት ስጋት ምክንያት መሆኑ ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁኔታውን እየተከታተሉ ሲሆን፣ ክስተቱ በቀጣናው አዲስ የጂኦፖለቲካ ውጥረት እና በነዳጅ ገበያው ላይ ስጋት ደቅኗል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
1
"ተኩስ አቁሙ ይፈርሳል"ኢራን

ኢራን ይህን ያለችው እሰራኤል በሊባኖስ እያደረገች ያለችውን ጥቃት ካላቆመች የተኩስ አቁም ስምምነቱ ይፈርሳል ብላለች ።

ኢራን በሊባኖስ ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ዛሬ ፈጽማለች።

እሰራኤል በ10 ደቂቃ ውስጥ ከ100 በላይ ጥቃቶችን ፈጽማለች ።

ከዚህ በፊት ኢላማ ያልነበሩ ቦታዎችም በሊባኖስ ጥቃት ደርሶባችዋል ።

ከተኩስ አቁሙ በሗላ የአሜሪካው ምክትል ኘሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ "በቀላሉ ሊፈርስ የሚችል ስምምነት" ሲሉ መደመጣቸውም ሌላው የተኩስ አቁሙ መጽናት ስጋት ሆኗል።(አልጀዚራ)

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
1
ሰበር

በሆርሙዝ ሰርጥ ሲያልፉ የነበሩ ነዳጅ የጫኑ መርከቦች እንዲቆሙ ተደረገ ።

እስራኤል ሊባኖስ ላይ ጥቃት መሰንዘሯን ተከትሎ በሆርሙዝ ሰርጥ ያልፉ የነበሩ መርከቦችን ኢራን ማስቆሟን ዋልተር ብሉምበርግ ገልፍ ኒውስን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል ።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
4😱3
ትራምፕ በሆርሙዝ ሰርጥ የመርከቦች ጉዞን ከኢራን ጋር መቆጣጠር ይፈልጋሉ

ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን የፍኖተ ሆርሙዝ ለመርከቦች ክፍት መሆን የተኩስ አቁሙ ስምምነት ቁልፍ ቅድመ ሁኔታ እንደነበር ገለጠች።

እንደ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጻ፦ ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን ደሕንነት በማስጠበቅ አብረው ሊሠሩ ይችላሉ።

ይህን በተመለከተም ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሲናገሩ፤ በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፉ መርከቦች ደሕንነት በኢራን እና በአሜሪካ ጥበቃ እንደሚደረግላቸው ተናግረዋል።

ፕሬዚደንቱ ለኤቢሲ ኒውስ እንደተናገሩት ከሆነ፤ የመርከቦች ደሕንነትን ለማስጠበቅ በዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን መካከል የጋራ ፕሮጄክትን ለመተግበር እያሰቡበት መሆኑንም ገልጠዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ኢራን አሁንም በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ የመርከብ ጭነቶችን መቆጣጠርዋን እንደቀጠለች መሆኑ ተዘግቧል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በሰጡት መግለጫ መሠረት፣ የመርከቦች ትራፊክ ፍሰት እንደቀድሞው ሁሉ «በኢራን የጦር ኃይሎች ፈቃድ» ተገዢ ሆኖ ይቀጥላል ብለዋል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
8👏3
ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን መልሳ ዘጋች

እስራኤል በሊባኖስ ላይ የሰነዘረችውን ተከታታይ ጥቃት ተከትሎ የኢራን መንግስት ለአለም የነዳጅ ንግድ ቁልፍ መተላለፊያ የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ የንግድ መርከቦች እንዳያልፉበት ሙሉ በሙሉ መዝጋቱን አስታውቋል።

የኢራን ይፋዊ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ከሆነ ይህ እርምጃ የተወሰደው ቀጠናዊ ውጥረቱ በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ ሲሆን ይህም በቅርቡ ተደርሶ የነበረውን ደካማ የተኩስ አቁም ስምምነት ወደ መፍረስ ደረጃ አድርሶታል።

በአሁኑ ሰዓት በወሽመጡ ላይ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች እንቅስቃሴ ተቋርጦ የሚገኝ ሲሆን፥ ይህ ድንገተኛ ውሳኔ በአለም አቀፍ የኢነርጂ አቅርቦት እና በኢኮኖሚ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ አደጋ ሊደቅን እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች በስጋት እየገለጹ ይገኛሉ።

የእስራኤል ጥቃት በሊባኖስ ውስጥ እያደረሰ ያለው ጉዳት መቀጠሉ ኢራን እንዲህ ያለውን ጠንከር ያለ እርምጃ እንድትወስድ ያስገደዳት ሲሆን፥ ሁኔታው ወደ ሰፋ ያለ ቀጠናዊ ጦርነት የማምራት እድሉ ሰፊ ሆኗል።

"የቀጠናው ደህንነት እስካልተረጋገጠ ድረስ የሆርሙዝ ወሽመጥ ዝግ ሆኖ ይቆያል።" ይላል ከቴህራን የተሰጠ መግለጫ


@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
6👍3😁1😢1
ትክክለኛ የባህል መዳኒት ይፈልጋሉ??
👆መርጌታ
የባህል ህክምና 0915398834


1🌿ለሀብት ማምጫ
2🌿ለእቁብ (እቁብ እንዲወጣላችሁ የሚያረግ)
3ለመስተፋቅር
4🌿 &መጠብቅ (ከጠላት ከሚላክ ሟርት የሚጠብቅ)
5🌿ለጋኔን
6🌿ለማንኛውም ዓይነት በሽታ መፍትሔ
7🌿ለራእይ (በህልም የሚያሳይ)7
8🌿  ለፀር (ለጠላት)
9🌿ዓቃቤ_ርእስ (ጠላት እንዳይጎዳን የሚጠብቅ)
10🌿 ለዘኢያገድፍ (ለትምህርት የማያስጠፋ የማያስጥል)
11🌿ለመክስተ_ምስጢር (ትምህርት የሚያጎብዝ)
12🌿ለመፍትሔ_ሀብት(ሀብቱ በጠላት ድግምት ለተሰወረበት)
13🌿 መስተፋቅር
14🌿ለግርማ_ሞገስ (ሰው እንዲያከብረን እንዲወደን)
15🌿ለመድፍነ_ፀር (ጠላት እንዳይናገረን እና እንዲፈራ
16🌿ለሌባ(እንዳንሰረቅ እንዳንዘረፍ የሚጠብቅ)
17🌿የትዳር አጋር ላጣ ወይም ላጣች
የሚያስገኝ
18🌿ለምስያጥ ለገበያ (ገበያ እንዲቀናን እንድናገኝ)
19🌿መስተኃድር (ከብት ቢጠፋብን ሳይበሉ በሰላም እቤታቸው
የሚያመጣ)
20🌿መንድግ(በገበያ ገንዘብ ማግኛ)
21🌿ለዓይነ_ጥላ (የፍራቻ መንፈስ ማስለቀቂያ)
22🌿ለልሳነ_ሰብእ
23🌿ለበረከት
24🌿ለእግረ_መልስ (ጥሎ ለጠፋ ሰው መመለሻ ማምጫ)
25🌿ምስሀበ_ነዋይ(ገንዘብ ማግኛ)
26🌿ጸሎተ_ዕለታት
27🌿ለጽሑፍ ለስእል ለከበሮ ለበገና ለክራር በእጂ ለሚሰሩ
28🌿ንባብ ስናነብ ቀልጣፋ የሚያረግ
29🌿ለከበሮ
30🌿ለመፍዝዝ (ጠላት እኛን ለማጥቃት ሲሞክር አጠገባችን ሲደርስ
መጣላቱን አስረስቶ አፍዝዞ የሚያስቀር የማያስመታ)
31🌿ለሙግት
32🌿ለሰላቢ
33🌿ለስንፈት ወሲብ
34🌿ዘኢያወርድ ( ለወንዶች በፆታዊ ግንኙነት ወቅት የዘር ፍሬ ቶሎ
እንዳይወርድ የሚያረግ አግዶ የሚያቆይ)
35🌿ለመደንግፅ (የተጣላን ሰው እኛን ሲያይ እንዲደነግጥ እንዲፈራ
የሚያረግ)
36🌿ለጥይት (ጥይት የማያስመታ)

በ 0915398834  ይደውሉልን
1🙈1
በሊባኖስ በትላንትናው እለት ብቻ ቢያንስ 254 ሰዎች በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ

የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዋፍ ሳላም "የእስራኤልን የግድያ ማሽን ለማስቆም ሁሉንም የሊባኖስ ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ሀብቶች" እያሰባሰቡ ባሉበት በዚህ ወቅት ረቡዕ ዕለት ብቻ ቢያንስ 254 ሰዎች ሲገደሉ ከ1,165 በላይ በእስራኤል የጥቃት ማዕበል ቆለስዋል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ሊባኖስ በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ውስጥ አልተካተተችም ያሉ ሲሆን የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ እንዲሁ “ይህንን ቃል አልገባንም” ብለዋል ።

በዚህ ጥቃት እስራኤል አለም አቀፍ ህግን፣ አለም አቀፍ የሰብአዊ ህግጋትን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተርን መርሆችን ጥሳለች ሲል የሶሪያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ የዜጎችን ጥበቃ እና የሊባኖስን ሉዓላዊነት ለማክበር አግባብነት ያለው የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎች በአስቸኳይ ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ጠይቋል ሲል በኤክስ ላይ በተጋራው መግለጫ ተመላክቷል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
6
የ10 ዓመት ታዳጊ የሆነችውን የስጋ ዘመዱን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

በምስራቅ ቦረና ዞን ጐሮ  ዶላ ወረዳ ውስጥ የወንጀለ ድርጊቱ ተፈጽሟል፡፡ተከሳሽ  የቅርብ ዝምድና ያላትን የአስር አመት ልጅ አታሎ በመውሰድ የግብረ ስጋ ድፍረት ፈጽሟል፡፡

የምስራቅ ቦረና ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ ኮማንደር በቃሉ በለጠ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ተከሣሽ ደንቦባ ነፃነት የተባለው ሲሆን የቅርብ የስጋ ዝምድና ያላትን  የአስር አመት ታዳጊ አታሎ በመውሠድ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል  እንደፈፀመባት ተናግረዋል። ታዳጊዋ ከልጆች ጋር ስትጫወት አታሎ በመውሰድ የአገድዶ መድፈር ወንጀል ከፈፀመባት በኃላ እራሱን ሸሽጎ የተሠወረ ሲሆን ታዳጊዋ ሽንት መሽናት ሲያቅታት ቤተሠቦች ተጠራጥረው ሲጠይቋት የመደፈር ጥቃት እንደተፈፀመባት በመናገገሯ ቤተሰቦች ጉዳዩን ለፖሊስ በማሳወቅ የድርጊቱ ፈፃሚ ከተሸሸገበት ስፍራ  በቁጥጥር ስር ዉሏል፡፡

ፖሊስም ጥቃት የደረሠባት ታዳጊ በነገሌ ሆስፒታል በማስመርመር የምርመራ መዝገቡን ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር በማያያዝ ለአቃቢ ህግ ይልካል።ክሱን የተመለከተው የምስራቅ ቦረና ዞን መጋቢት28 ቀን 2018 ዓም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ደንቦባ ነፃነት ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ  በ14 ዓመት እስራት እንዲቀጣ የተወሠነበት መሆኑን ኮማደር በቃሉ በለጠ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
2😢2
ትራምፐ እና ኤርዶዋን ምን መከሩ?

የቱርክ ፕሬዝዳንት ረጂብ ጠይብ ኤርዶዋን እና የአሜሪካው አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ በቀጠናዊ ጉዳዮችና በኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት ዙሪያ በስልክ ተወያዩ፡፡

ውይይቱ በዋናነት ትኩረቱን ያደረገው በኢራን እና አሜሪካ መካከል በተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ነው።

ፕሬዝዳንት ኤርዶዋን ከ40 ቀናት ውጥረት በኋላ የተገኘው የሁለት ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት ወደ ዘላቂ ሰላም ለመሸጋገር ወሳኝ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል።

ቱርክ ከወዳጅ አገራት ጋር በመሆን ለቀጣይ የሰላም ስምምነቶች የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ያረጋገጡት ኤርዶዋን ይህንን ሂደት ሊያደናቅፉ ከሚችሉ ማናቸውም ድርጊቶች መቆጠብ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ፕሬዝዳንት ኤርዶዋን ቱርክ ለሰላም ጥረቱ የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ካረጋገጡ በኋላ ፤ እንደ ፓኪስታን ካሉ ወዳጅ እና ወንድም አገራት ጋር በመሆን ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን ለማጠናከር ቃል ገብተዋል።

ትራምፕ በበኩላቸው የኢራን መንግስት ለድርድር ተግባራዊ ሊሆን የሚችል ባለ 10 ነጥብ የውሳኔ ሃሳብ አቅርቧል ቢሉም አሁንም ድረስ የተኩስ አቁሙ ጉዳይ ከስጋት አልወጣም ሲሉ ተንታኞች ይሞግታሉ፡፡

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
7
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለትንሳኤ በዓል አስተማማኝ የኃይል አቀርባለው አለ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመጪው የትንሳኤ በዓል ወቅት ሊከሰት የሚችለውን የኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ለመቀነስ ሰፊ የቅድመ-ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል።

ተቋሙ በበዓላት ሰሞን የሚኖረውን ከፍተኛ የኃይል ፍላጎትና በመሰረተ-ልማቱ ላይ የሚፈጠረውን ጫና ታሳቢ ያደረገ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገልጿል።

የተቋሙ የኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ አንዋር አብራር እንደገለጹት፣ ከበዓሉ አስቀድሞ የመካከለኛና ዝቅተኛ ማሰራጫ መስመሮችን የመፈተሽ፣ የረገቡ ገመዶችን የመወጠር እና የእንጨት ምሰሶዎችን በኮንክሪት የመተካት ስራዎች ተከናውነዋል።

በተጨማሪም የኃይል ጫና ያለባቸውን ትራንስፎርመሮች አቅም የማሳደግና አዳዲስ አጋዥ ትራንስፎርመሮችን የመትከል ስራ መከናወኑን አስረድተዋል።

በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ ለሚከሰቱ ድንገተኛ የኃይል መቆራረጦች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት በሁሉም የአገልግሎት አደረጃጀቶች ውስጥ የአስቸኳይ ጥገና ግብረ-ኃይል ተዋቅሮ ወደ ስራ መግባቱ ተገልጿል።

ይህም ደንበኞች አስተማማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል እንደሆነ ተቋሙ አመልክቷል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
😁63👏1🕊1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ፣ ዛሬ ጠዋት ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች እና ጽሕፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሕጻናት ማዕድ አጋርተዋል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
5
"ሦስት የጤና ባለሙያዎች በጥይት ተገድለዋል" - ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ በአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ሦስት ጤና ባለሙያዎች ተገድለዋል አሉ።

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ በአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ/ም ሦስት የጤና ባለሙያዎች በጥይት ተገድለዋል ሲሉ አሳውቀዋል።

አንድ ነርስና ሁለት ጤና ባለሙያዎች "አቢዮት ፋና" የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ፣ ሦስተኛው ደግሞ በግል የጤና ተቋም ውስጥ ይሰሩ እንደነበር ገልጸው፣ " ግድያው የተፈጸመው በኢትዮጵያ መንግስት እና በአማራ ክልል ኃይሎች መካከል ግጭት እየተስፋፋ ባለበት ወቅት ነው " ብለዋል።

"የጤና ባለሙያዎች በማንኛውም ጊዜ ሊጠበቁ እና ለሚያስፈልጋቸው ሰው ሁሉ ህይወትን የሚያድኑ ስራዎቻቸውን ሊያከናውኑ ይገባል" ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የዓለም ጤና ድርጅት ግድያው በገለልተኛ አካል ምርመራ እንዲያደረግ ይጠይቃል የሚል መረጃ አጋርተዋል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
7
#ፋይዳ ተራዝሟል‼️
የፋይዳ መታወቂያን ከባንክ ሂሳብ ጋር ለማጣመር ተቅምጦ የነበረው የጊዜ ገደብ ተራዝሟል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ለማጣመር ተቀምጦ የነበረው የመጋቢት 30/2018 ዓ.ም የጊዜ ገደብ ለአንድ ጊዜ እንዲራዘም መወሰኑ  ተገልጿል።

እስካሁን የተመዘገበው ሰው ቁጥር አመርቂ ባለመሆኑ እና በአንዳንድ ባንኮች ላይ የታዩ የሲስተም ችግሮችን ለመፍታት ሲባል ለአንድ ጊዜ እንዲራዘም ተወስኗል።

የተራዘመበት ትክክለኛ ቀን እስካሁን ያልተወሰነ ሲሆን በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ ብሔራዊ ባንክ  አሳውቋል።

እንዲራዘም የተወሰነው ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ተወያይተውበት ነው።

ህብረተሰቡ በሊንክ ወይም ደግሞ በአካል በመቅረብ ምዝገባውን እንዲያከናውን እና ባንኮች የቴክኒክ ችግሮችን እንዲያስተካክሉ መመሪያ ተሰጥቷል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
6
በአሶሳ ወታደራዊ ካምፕ ለሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የሚያሳይ አዲስ ሪፖርት ወጣ

በዬል ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ጤና ትምህርት ቤት የሰብአዊ ምርምር ላብራቶሪ (HRL) ያወጣው አዲስ ሪፖርት፤ ኢትዮጵያ ለሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) ወታደራዊ ድጋፍ እያደረገች መሆኑን የሚያሳዩ “ከፍተኛ እምነት የሚጣልባቸው” ማስረጃዎች ማግኘቱን ገልጿል።

ይህም ቀጣናዊ ደህንነትን አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል የሚል ስጋት ይፈጥራል ሲል ገልጿል።

በ የካቲት2018 ዓ.ም “ኢትዮጵያ ለሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ታጣቂዎች የሥልጠና ካምፕ ገንብታለች” ሲል ሮይተርስ የምርመራ ዘገባ ማውጣቱ ይታወሳል።

ዘገባውን ተከትሎም፤ የዩናይትድ ስቴትስ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ሴናተር ሪሽ ድርጊቱ የሚያስከትለው “መዘዝ” እንደሚኖር አስጠንቅው ነበር።

የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት እስካሁን ለቀረበው ክስ ይፋዊ ምላሽ ባይሰጡም፤ መንግሥት በአዲስ አበባ የሚገኙ ሦስት የሮይተርስ ጋዜጠኞችን የሥራ ፈቃድ ለማደስ ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን የዜና ወኪሉ አስታውቋል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
9
#ኢትዮጵያዊው ዕጩ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ኮሚቴ አባል ሆነው ተመረጡ

አዲስ አበባ — ኢትዮጵያዊው ዕጩ ዓብዲ ጅብሪል ዓሊ (ዶ/ር)፤ በኒውዮርክ በተካሄደው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በተሰጠ ድምፅ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ መብቶች ኮሚቴ አባልነት ተመረጡ።

ዓብዲ ጅብሪል ለሁለት የአፍሪካ መቀመጫዎች ከተወዳደሩ ስድስት ዕጩዎች መካከል 49 ድምፅ በማግኘት ማሸነፍ ችለዋል። ኮሚቴው በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ መብቶች ስምምነት አፈጻጸምን የሚከታተሉ 18 ገለልተኛ ባለሙያዎችን የያዘ ነው።

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለዓብዲ ጅብሪል የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን፤ በአራት ዓመት የሥራ ዘመናቸው ስኬትን ተመኝቶላቸዋል።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በበኩሉ ባወጣው መግለጫ፤ በአሁኑ ወቅት በኮሚሽኑ የሲቪል፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ኮሚሽነር ሆነው እያገለገሉ ያሉት ዓብዲ ጅብሪል የተመረጡት ትናንት መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑን አስታውቋል። ኮሚሽኑ አክሎም፤ የባለሙያው መመረጥ ያላቸውን የሰብአዊ መብት ዕውቀትና ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማት ጋር ያላትን ቀጣይነት ያለው ግንኙነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጿል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
4🔥1
ወደ ካናዳ‼️
ዜጎችን አሰልጥኖ ወደ ካናዳ መላክ የሚያስችል ስምምነት ተደረገ‼️
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎችን አብቅቶ ወደ ካናዳ ለመላክ ከፊውቸር ፊል ኢንተርናሽናል ጋር ስምምነት አደረገ።

የስራና ክህሎት ሚንስትር ሙፈሪያት ካሚል በወቅቱ እንደገለፁት
ስምምነቱ ብቁ የሆኑ ዜጎችን አሰልጥኖ ወደ ካናዳ ለመላክ የተደረገ ነው።

የካናዳ መንግስት እውቅና ባለው መልኩ ዜጎችን ለይቶ ወደ ውጪ በመላክ ሁለቱም ሃገራት የጋራ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ በኩል ዜጎች በቅተው የስራ እድል የሚያገኙበት እንዲሁም በካናዳ በኩል ደግሞ በቂ የሰለጠነ የሰው ሃይል እንዲኖር የሚያደርግ ነው ብለዋል።

እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ ወደ ካናዳ እንልካለን የሚሉ ህገወጦች አሉ። ይህ ተገቢ አይደለም። በተለያየ ጊዜም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዜጎች ከነዚህ ህገወጦች እንዲጠነቀቁ አሳስቧል።

የዛሬው ስምምነት ግን ዜጎች ሰልጥነው ወደ ካናዳ የሚሄዱበት ነው ብለዋል።

የፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ አብይ ራይሞንድ በበኩላቸው፤ የተደረገው ስምምነት የዜጎችን ችሎታ እና አቅምን ለማውጣት የሚያስችል ነው ብለዋል።

ስልጠናው ለተማሩ ዜጎች ቅድሚያ የሚሰጥ ቢሆንም አቅም አለኝ የሚሉ ዜጎች ተመዝግበው ስልጠናውን ማግኘት ይችላሉ ነው ያሉት።

አክለውም ምዝገባ የሚጀምርበትን ቀን በዋና ዋና መገናኛ ብዙሃም የምናሳውቅ ይሆናል ብለዋል።

ስምምነቱ ኢትዮጵያን ብቻ የሚጠቅም ሳይሆን ለካናዳም የሰለጠነ በቂ የሰው ሃይል እንድታገኝ የሚያደርጋት መሆኑን ገልፀዋል።

@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
👍111