ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦላቸው በውጤቶቹ ላይ ግምገማ እና ውይይት ተደርጓል።
#PMOEthiopia
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
#PMOEthiopia
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤6🤣4
አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸው ተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው።
አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን÷ በአፍሪካ ሕብረትና በተባባሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ መልዕክተኛ በመሆንም ሰርተዋል።
ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011 ዓ.ም ደግሞ ኢጋድ በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ላይ ልዩ አማካሪ ሆነው ማገልገላቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸው ተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው።
አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን÷ በአፍሪካ ሕብረትና በተባባሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ መልዕክተኛ በመሆንም ሰርተዋል።
ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011 ዓ.ም ደግሞ ኢጋድ በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ላይ ልዩ አማካሪ ሆነው ማገልገላቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
😢4❤1
ኢራን የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አደረገች፤ የፕሬዝዳንት ትራምፕ የማስጠንቀቂያ ቀነ-ገደብም ሰዓታት ቀርተውታል
በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ዙሪያ የቀረበውን የተኩስ አቁም የሰላም ጥያቄ ኢራን ውድቅ ማድረጓ ተሰምቷል።
ይህ የቴህራን ውሳኔ የተሰማው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥቃቱ ከመቀጠሉ በፊት የሰጡት የ10 ቀናት ቀነ-ገደብ ሊጠናቀቅ ጥቂት ሰዓታት በቀሩበት ወቅት ነው።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን የቀረበላትን የሰላም አማራጭ ካልተቀበለች አሜሪካ ጥቃቷን በከፍተኛ ሁኔታ እንደምታጠናክር ገልፀዋል::
ፕሬዝዳንቱ ይህ ጥቃት ለኢራን "ከባዱ ቅዠት" ይሆንባታል ሲሉም ነው በድጋሚ ያስጠነቀቁት።
ምንም እንኳን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ድርድሩ በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን ቢገልጹም ኢራን ግን የአሜሪካው የሰላም ዕቅድ "አድሏዊና የእስራኤልን ጥቅም ብቻ የሚያስቀድም ነው" በሚል ሳትቀበለው ቀርታለች።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል የንግድና የሰብዓዊ እርዳታ ፍሰቱ እንዳይቋረጥ አዲስ የሥራ ቡድን በማቋቋም ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ይሁን እንጂ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀነ-ገደብ ዛሬ ማክሰኞ ከእኩለ ሌሊት በኃላ የሚያበቃ በመሆኑ፣ ቀጣዮቹ ሰዓታት ለቀጣናው ሰላም ወሳኝ ሆነው ይጠበቃል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ዙሪያ የቀረበውን የተኩስ አቁም የሰላም ጥያቄ ኢራን ውድቅ ማድረጓ ተሰምቷል።
ይህ የቴህራን ውሳኔ የተሰማው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥቃቱ ከመቀጠሉ በፊት የሰጡት የ10 ቀናት ቀነ-ገደብ ሊጠናቀቅ ጥቂት ሰዓታት በቀሩበት ወቅት ነው።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን የቀረበላትን የሰላም አማራጭ ካልተቀበለች አሜሪካ ጥቃቷን በከፍተኛ ሁኔታ እንደምታጠናክር ገልፀዋል::
ፕሬዝዳንቱ ይህ ጥቃት ለኢራን "ከባዱ ቅዠት" ይሆንባታል ሲሉም ነው በድጋሚ ያስጠነቀቁት።
ምንም እንኳን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ድርድሩ በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን ቢገልጹም ኢራን ግን የአሜሪካው የሰላም ዕቅድ "አድሏዊና የእስራኤልን ጥቅም ብቻ የሚያስቀድም ነው" በሚል ሳትቀበለው ቀርታለች።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል የንግድና የሰብዓዊ እርዳታ ፍሰቱ እንዳይቋረጥ አዲስ የሥራ ቡድን በማቋቋም ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ይሁን እንጂ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀነ-ገደብ ዛሬ ማክሰኞ ከእኩለ ሌሊት በኃላ የሚያበቃ በመሆኑ፣ ቀጣዮቹ ሰዓታት ለቀጣናው ሰላም ወሳኝ ሆነው ይጠበቃል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤4
ጥሰት የፈፀመ ድጋሚ አይሾምም‼️
በመንግሥት ተሿሚዎች ላይ ጠንካራ ቁጥጥር የሚያደርግ አዲስ ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ‼️
የገንዘብ ሚኒስቴር በመንግሥት ተሿሚዎች ላይ ጠንካራ ቁጥጥር የሚያደርግ አዲስ ረቂቅ መመሪያ ማዘጋጀቱ ተሰማ። በዚህ መመሪያ መሠረት፣ ማንኛውም የመንግሥት ተሿሚ ከመንግሥት የግዥ አፈጻጸምና ከንብረት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ጥሰት የፈጸመ መሆኑ ከተረጋገጠ፣ በየትኛውም የመንግሥት ተቋም ውስጥ ዳግም እንዳይመደብ ወይም እንዳይሾም የሚደነግግ መሆኑ ተገልጿል። ይህ እርምጃ በመንግሥት ሀብት ላይ የሚፈጸሙ ብክነቶችን ለመግታትና ተጠያቂነትን ለማስፈን ያለመ መሆኑን የሪፖርተር ዘገባ ያመለክታል።
በረቂቅ መመሪያው ላይ በዋናነት በጥፋተኝነት ከተጠቀሱት ነጥቦች መካከል፦ ዓመታዊ የመንግሥት የግዥ ዕቅድን በወቅቱና በጥራት በኤሌክትሮኒክ ዘዴ አለማቅረብ፣ የንብረት አስተዳደር ሪፖርቶችን በጊዜው አለመላክ፣ እንዲሁም አገልግሎት የጨረሱ ንብረቶችን በወቅቱ አለማስወገድ ይገኙበታል። በተጨማሪም፣ የግዥ መረጃዎችን ለሕዝብ ግልጽ አለማድረግ እንደ ትልቅ ጥሰት ተቆጥሮ ተሿሚዎችን ከቀጣይ የሥራ ድልድል የሚያግድ መሆኑ ተመላክቷል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
በመንግሥት ተሿሚዎች ላይ ጠንካራ ቁጥጥር የሚያደርግ አዲስ ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ‼️
የገንዘብ ሚኒስቴር በመንግሥት ተሿሚዎች ላይ ጠንካራ ቁጥጥር የሚያደርግ አዲስ ረቂቅ መመሪያ ማዘጋጀቱ ተሰማ። በዚህ መመሪያ መሠረት፣ ማንኛውም የመንግሥት ተሿሚ ከመንግሥት የግዥ አፈጻጸምና ከንብረት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ጥሰት የፈጸመ መሆኑ ከተረጋገጠ፣ በየትኛውም የመንግሥት ተቋም ውስጥ ዳግም እንዳይመደብ ወይም እንዳይሾም የሚደነግግ መሆኑ ተገልጿል። ይህ እርምጃ በመንግሥት ሀብት ላይ የሚፈጸሙ ብክነቶችን ለመግታትና ተጠያቂነትን ለማስፈን ያለመ መሆኑን የሪፖርተር ዘገባ ያመለክታል።
በረቂቅ መመሪያው ላይ በዋናነት በጥፋተኝነት ከተጠቀሱት ነጥቦች መካከል፦ ዓመታዊ የመንግሥት የግዥ ዕቅድን በወቅቱና በጥራት በኤሌክትሮኒክ ዘዴ አለማቅረብ፣ የንብረት አስተዳደር ሪፖርቶችን በጊዜው አለመላክ፣ እንዲሁም አገልግሎት የጨረሱ ንብረቶችን በወቅቱ አለማስወገድ ይገኙበታል። በተጨማሪም፣ የግዥ መረጃዎችን ለሕዝብ ግልጽ አለማድረግ እንደ ትልቅ ጥሰት ተቆጥሮ ተሿሚዎችን ከቀጣይ የሥራ ድልድል የሚያግድ መሆኑ ተመላክቷል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤2👍1🔥1
የሪል ስቴት ዘርፉ ከሕዝብ አመኔታ በማጣት እየተቀዛቀዘ ነው ተባለ
በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ኢንዱስትሪው የሕዝብ አመኔታ በማጣቱ ምክንያት እየተቀዛቀዘ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማኅበር አስታውቋል።
ማኅበሩ ይህን ያስታወቀው፤ ኢትዮጵያ ከሚያዝያ 15 እስከ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የመጀመሪያውን የአፍሪካ ሪል ስቴት ማኅበር የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ጉባዔና ‹‹አዲስ - አፍሪካ›› የተሰኘውን የሪል ስቴት ኤግዚቢሽን የምታስተናግድ መሆኑን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማኅበር የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ዓለማየሁ ከተማ እንደተናገሩት፤ የሪል ስቴት ኢንዱስትሪው የሕዝብ አመኔታን በማጣቱ እንዳያድግና ወደፊት እንዳይራመድ እየሆነ ይገኛል ብለዋል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ኢንዱስትሪው የሕዝብ አመኔታ በማጣቱ ምክንያት እየተቀዛቀዘ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማኅበር አስታውቋል።
ማኅበሩ ይህን ያስታወቀው፤ ኢትዮጵያ ከሚያዝያ 15 እስከ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የመጀመሪያውን የአፍሪካ ሪል ስቴት ማኅበር የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ጉባዔና ‹‹አዲስ - አፍሪካ›› የተሰኘውን የሪል ስቴት ኤግዚቢሽን የምታስተናግድ መሆኑን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማኅበር የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ዓለማየሁ ከተማ እንደተናገሩት፤ የሪል ስቴት ኢንዱስትሪው የሕዝብ አመኔታን በማጣቱ እንዳያድግና ወደፊት እንዳይራመድ እየሆነ ይገኛል ብለዋል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤2
አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
አምባሳደር ቆንጂት በአገልግሎት ዘመናቸው፣ በኦታዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭ እና ቪዬና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ኾነው ያገለገሉ ሲኾን፤ በአፍሪካ ኅብረትና በተባባሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ መልዕክተኛ በመሆን ሠርተዋል።
አምባሳደር ቆንጂት፣ በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክቶሬትንም ለበርካታ ዓመታት በዋና ዳይሬክተርነት መርተዋል። ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ቆንጂት፣ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴርን በወጣትነታቸው የተቀላቀሉት በ1950ዎቹ ነበር።
ጠቅላይ ሚሚንስትር ዐቢይ፣ አምባሳደር ቆንጂት ከእርሳቸው በኋላ በርካታ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል በማለት በአምባሳደሯ ሕልፈት የተሠማቸውን ሐዘን በገለጹበት መልዕክት ላይ ጠቅሠዋል።
@Addis_Magazine
አምባሳደር ቆንጂት በአገልግሎት ዘመናቸው፣ በኦታዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭ እና ቪዬና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ኾነው ያገለገሉ ሲኾን፤ በአፍሪካ ኅብረትና በተባባሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ መልዕክተኛ በመሆን ሠርተዋል።
አምባሳደር ቆንጂት፣ በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክቶሬትንም ለበርካታ ዓመታት በዋና ዳይሬክተርነት መርተዋል። ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ቆንጂት፣ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴርን በወጣትነታቸው የተቀላቀሉት በ1950ዎቹ ነበር።
ጠቅላይ ሚሚንስትር ዐቢይ፣ አምባሳደር ቆንጂት ከእርሳቸው በኋላ በርካታ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል በማለት በአምባሳደሯ ሕልፈት የተሠማቸውን ሐዘን በገለጹበት መልዕክት ላይ ጠቅሠዋል።
@Addis_Magazine
❤1
ሰበር መረጃ‼️
በኢራን ላይ ትልቁ የአሜሪካ ጥቃት ዛሬ ለሊት 9:47 ላይ እንደሚጀመር ዶናልድ ትራምፕ ተናገሩ።
ከሁሉም የተሻለ እቅድ አለኝ፣ ግን እቅዴ ምን እንደሆነ በግልጽ መናገር አልፈልግም" ያሉ ሲሆን የነገው ጥቃት ከዛሬው ይብሳል ብለዋል። ኢራን ከነገ ጀምሮ ድልድይ፣ የሀይል ማመንጫ... አይኖራቸውም። የድንጋይ ዘመን ሰዎች ይሆናሉ ብለዋል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
በኢራን ላይ ትልቁ የአሜሪካ ጥቃት ዛሬ ለሊት 9:47 ላይ እንደሚጀመር ዶናልድ ትራምፕ ተናገሩ።
ከሁሉም የተሻለ እቅድ አለኝ፣ ግን እቅዴ ምን እንደሆነ በግልጽ መናገር አልፈልግም" ያሉ ሲሆን የነገው ጥቃት ከዛሬው ይብሳል ብለዋል። ኢራን ከነገ ጀምሮ ድልድይ፣ የሀይል ማመንጫ... አይኖራቸውም። የድንጋይ ዘመን ሰዎች ይሆናሉ ብለዋል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
😁9❤4👏1😡1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ሕልፈት የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የኀዘን መልዕክት÷ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ በማረፋቸው የተሰማኝን ኀዘን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት ከልጅነት እስከ ዕውቀት ኢትዮጵያን በዲፕሎማትነት በማገልገል ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥለው ሁለተኛዋ ሴት የኢትዮጵያ አምባሳደር መሆናቸውን ገልጸዋል።
ለሕግ፣ ለአሠራር፣ ለፕሮቶኮል እና ለኢትዮጵያ ጥቅሞች በነበራቸው የጸና አቋም እናስታውሳቸዋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ ከእርሳቸው በኋላ አያሌ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ስላሴ እና የአፍሪካ ህብረትም በአምባሳደር ቆንጂት ስነ ጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል፡፡
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የኀዘን መልዕክት÷ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ በማረፋቸው የተሰማኝን ኀዘን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት ከልጅነት እስከ ዕውቀት ኢትዮጵያን በዲፕሎማትነት በማገልገል ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥለው ሁለተኛዋ ሴት የኢትዮጵያ አምባሳደር መሆናቸውን ገልጸዋል።
ለሕግ፣ ለአሠራር፣ ለፕሮቶኮል እና ለኢትዮጵያ ጥቅሞች በነበራቸው የጸና አቋም እናስታውሳቸዋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ ከእርሳቸው በኋላ አያሌ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ስላሴ እና የአፍሪካ ህብረትም በአምባሳደር ቆንጂት ስነ ጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል፡፡
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤6
በአየርላንድ ደሴቶች ላይ ለመኖር ፈቃደኛ የሆነ 90 ሺህ ዶላር ክፍያ እሰጣለው አለች
አዲስ ህይወት በውብ የባህር ዳርቻ ላይ ለመጀመር ለሚያልሙ ሰዎች አየርላንድ አስገራሚ እድል ይዛ ቀርባለች።
"Our Living Islands" የተሰኘውና በመላው ዓለም ከፍተኛ ትኩረት የሳበው ይህ አዲስ መርሃ ግብር፣ በሀገሪቱ ገለልተኛ ደሴቶች ላይ ሄደው ለሚኖሩ ዜጎች እስከ 90 ሺህ የአሜሪካ ዶላር (84 ሺህ ዩሮ) የሚደርስ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ማበረታቻ የቀረበው የህዝብ ቁጥራቸው በእጅጉ እየቀነሰ የመጡ 30 የሚጠጉ ራቅ ያሉ የደሴት ማህበረሰቦችን እንደገና ለማነቃቃትና ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ለመመለስ ታስቦ የተዘጋጀ የ10 ዓመት ስትራቴጂ አካል ነው።
ነገር ግን ይህ ማራኪ አሃዝ በነጻ የሚታደል ገንዘብ አይደለም።
መንግስት ይህንን ድጋፍ የሚሰጠው አዲስ ሰፋሪዎች በነዚህ ደሴቶች ላይ ለዓመታት ተጥለው የቆዩና የፈራረሱ ቤቶችን ገዝተው ሙሉ በሙሉ እንዲያድሱ ለማገዝ ነው።
በአሁኑ ወቅት በነዚህ ደሴቶች ላይ የሚኖሩት ሰዎች ቁጥር ከ3 ሺህ በታች ሲሆን፤ አንዳንዶቹ ደሴቶች ደግሞ በከፍተኛ የባህር ሞገድ ወቅት ከዋናው የሀገሪቱ ክፍል ሙሉ በሙሉ የሚቆረጡ ናቸው።
በመሆኑም እድሉን የሚጠቀሙ ሰዎች የከተማውን ግርግር በባህር ዳርቻው ድምጽ ለመቀየር የሚወስኑት ቁርጠኝነትና የጥገና ስራውን የመወጣት አቅም ሊኖራቸው ይገባል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
አዲስ ህይወት በውብ የባህር ዳርቻ ላይ ለመጀመር ለሚያልሙ ሰዎች አየርላንድ አስገራሚ እድል ይዛ ቀርባለች።
"Our Living Islands" የተሰኘውና በመላው ዓለም ከፍተኛ ትኩረት የሳበው ይህ አዲስ መርሃ ግብር፣ በሀገሪቱ ገለልተኛ ደሴቶች ላይ ሄደው ለሚኖሩ ዜጎች እስከ 90 ሺህ የአሜሪካ ዶላር (84 ሺህ ዩሮ) የሚደርስ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ማበረታቻ የቀረበው የህዝብ ቁጥራቸው በእጅጉ እየቀነሰ የመጡ 30 የሚጠጉ ራቅ ያሉ የደሴት ማህበረሰቦችን እንደገና ለማነቃቃትና ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ለመመለስ ታስቦ የተዘጋጀ የ10 ዓመት ስትራቴጂ አካል ነው።
ነገር ግን ይህ ማራኪ አሃዝ በነጻ የሚታደል ገንዘብ አይደለም።
መንግስት ይህንን ድጋፍ የሚሰጠው አዲስ ሰፋሪዎች በነዚህ ደሴቶች ላይ ለዓመታት ተጥለው የቆዩና የፈራረሱ ቤቶችን ገዝተው ሙሉ በሙሉ እንዲያድሱ ለማገዝ ነው።
በአሁኑ ወቅት በነዚህ ደሴቶች ላይ የሚኖሩት ሰዎች ቁጥር ከ3 ሺህ በታች ሲሆን፤ አንዳንዶቹ ደሴቶች ደግሞ በከፍተኛ የባህር ሞገድ ወቅት ከዋናው የሀገሪቱ ክፍል ሙሉ በሙሉ የሚቆረጡ ናቸው።
በመሆኑም እድሉን የሚጠቀሙ ሰዎች የከተማውን ግርግር በባህር ዳርቻው ድምጽ ለመቀየር የሚወስኑት ቁርጠኝነትና የጥገና ስራውን የመወጣት አቅም ሊኖራቸው ይገባል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤12
የእስራኤል ጦር ኢራናውያን ዛሬ ባቡር እንዳይጠቀሙ አስጠነቀቀ፡፡
ትራምፕ በበኩላው የኢራን ስልጣኔ ዛሬ ምሽት መጥፊያው ነው ብለዋል፡፡
የእስራኤል ጦር በይፋዊ የማኅበራዊ የትስስር ገጹ ላይ በፋርስ ቋንቋ ባሰፈረው መልዕክት በኢራን የሚኖሩ ሰዎች “ለደህንነታችሁ” በማለት ”በባቡር ከመጓዝ ተቆጠቡ” ብሏል።
ማስጠንቀቂያው በመላው አገሪቱ ለሚኖሩ ኢራናውያን መሆኑን የገለጸው ጦሩ በኢራን ሰዓት አቆጣጠር “እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት” ድረስ ማስጠንቀቂያው እንደሚቆይ ገልጿል።
አክሎም “በባቡር ውስጥ መሆን አና በባር ሃዲዶች አቅራቢያ መገኘት ሕይወታችሁን አደጋ ላይ ይጥለዋል” ብሏል።
የእስራኤል ጦር ማስጠንቀቂያ የተሰማው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመላው ኢራን የሚገኘው የሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር መዛታቸውን ተከትሎ ነው።
በተመሳሳይ ዜና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራን ስልጣኔ ዛሬ ምሽት መጥፊያው ነው ሲሉ ዝተዋል፡፡
ይህ እንዳይሆን ሀገሪቱ ስምምነት መድረስ እንዳለባት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በማኅበራዊ ገጻቸው ባሰራጩት የዛቻ መልዕክት ጠቁመዋል፡፡
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
ትራምፕ በበኩላው የኢራን ስልጣኔ ዛሬ ምሽት መጥፊያው ነው ብለዋል፡፡
የእስራኤል ጦር በይፋዊ የማኅበራዊ የትስስር ገጹ ላይ በፋርስ ቋንቋ ባሰፈረው መልዕክት በኢራን የሚኖሩ ሰዎች “ለደህንነታችሁ” በማለት ”በባቡር ከመጓዝ ተቆጠቡ” ብሏል።
ማስጠንቀቂያው በመላው አገሪቱ ለሚኖሩ ኢራናውያን መሆኑን የገለጸው ጦሩ በኢራን ሰዓት አቆጣጠር “እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት” ድረስ ማስጠንቀቂያው እንደሚቆይ ገልጿል።
አክሎም “በባቡር ውስጥ መሆን አና በባር ሃዲዶች አቅራቢያ መገኘት ሕይወታችሁን አደጋ ላይ ይጥለዋል” ብሏል።
የእስራኤል ጦር ማስጠንቀቂያ የተሰማው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመላው ኢራን የሚገኘው የሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር መዛታቸውን ተከትሎ ነው።
በተመሳሳይ ዜና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራን ስልጣኔ ዛሬ ምሽት መጥፊያው ነው ሲሉ ዝተዋል፡፡
ይህ እንዳይሆን ሀገሪቱ ስምምነት መድረስ እንዳለባት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በማኅበራዊ ገጻቸው ባሰራጩት የዛቻ መልዕክት ጠቁመዋል፡፡
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤5🕊2👍1😱1
ከ40,000 በላይ ፊሊፒናውያን በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት የተነሳ ስራ ማቆማቸዉ ተነገረ
በእስራኤል፣ በሊባኖስ እና በገልፍ ሀገራት ለስራ ሊያቀኑ የነበሩ ከ40,000 በላይ ፊሊፒናውያን ከፊሊፒንስ መውጣት አልቻሉም ሲል የፊሊፒንስ ዴይሊ ስታር ዘግቧል።ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚደረጉ የበረራዎች እጥረት ሰራተኞች ወደ ባህር ማዶ ለመጓዝ አዳጋች ሆነዋል። በ2026 በሁለተኛውና በሶስተኛው ሩብ አመት የሰራተኞች ምደባ እየቀነሰ እንደሚሄድ ዘገባው የፍልሰት ባለሙያን ጠቅሷል።
ወደ ቀጠናዉ መሄድ የነበረባቸው ሰራተኞች አሁን በማኒላ በሚገኙ የቅጥር ኤጀንሲዎች በተሰጡ የመጠለያ ማዕከላት ውስጥ ለጊዜው እየቆዩ ሲሆን አንዳንዶቹም ወደ ትውልድ ግዛታቸው ተልከዋል።የፊሊፒንስ መንግስት እስካሁን ከ4,000 የሚበልጡ የፊሊፒንስ ሰራተኞችን እና ጥገኞቻቸውን ከመካከለኛው ምስራቅ ወደ ሀገራቸው መልሷል።በመካከለኛው ምስራቅ ወደ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ፊሊፒናውያን በአብዛኛው በባህረ ሰላጤው ክልል ውስጥ ይሰራሉ።
በሌላ መረጃ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚካሄደው የአሜሪካ ወታደራዊ ዘመቻ ኃላፊነት ያለው እና በኢራን ላይ የሚደርሰውን ጥቃት እየመራ ያለው የዩናይትድ ስቴትስ ሴንትራል ኮማንድ ኃይሉ ከ13,000 በላይ የኢራን ኢላማዎችን ማጥቃት ችሏል።በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባሰራጨው ጽሁፍ ከ155 በላይ የኢራን መርከቦች ተጎድተዋል ወይም ወድመዋል በማለት የአሜሪካ ኒውክሌር ኃይል አውሮፕላኖች አጓጓዦች እና ሰርጓጅ መርከቦች በኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ እንዲሁም ከኤፍ-35 ስውር ተዋጊ አውሮፕላኖች እስከ ቢ-52 ቦምቦች የሚደርሱ አውሮፕላኖች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጿል። ( ዳጉ_ጆርናል )
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
በእስራኤል፣ በሊባኖስ እና በገልፍ ሀገራት ለስራ ሊያቀኑ የነበሩ ከ40,000 በላይ ፊሊፒናውያን ከፊሊፒንስ መውጣት አልቻሉም ሲል የፊሊፒንስ ዴይሊ ስታር ዘግቧል።ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚደረጉ የበረራዎች እጥረት ሰራተኞች ወደ ባህር ማዶ ለመጓዝ አዳጋች ሆነዋል። በ2026 በሁለተኛውና በሶስተኛው ሩብ አመት የሰራተኞች ምደባ እየቀነሰ እንደሚሄድ ዘገባው የፍልሰት ባለሙያን ጠቅሷል።
ወደ ቀጠናዉ መሄድ የነበረባቸው ሰራተኞች አሁን በማኒላ በሚገኙ የቅጥር ኤጀንሲዎች በተሰጡ የመጠለያ ማዕከላት ውስጥ ለጊዜው እየቆዩ ሲሆን አንዳንዶቹም ወደ ትውልድ ግዛታቸው ተልከዋል።የፊሊፒንስ መንግስት እስካሁን ከ4,000 የሚበልጡ የፊሊፒንስ ሰራተኞችን እና ጥገኞቻቸውን ከመካከለኛው ምስራቅ ወደ ሀገራቸው መልሷል።በመካከለኛው ምስራቅ ወደ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ፊሊፒናውያን በአብዛኛው በባህረ ሰላጤው ክልል ውስጥ ይሰራሉ።
በሌላ መረጃ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚካሄደው የአሜሪካ ወታደራዊ ዘመቻ ኃላፊነት ያለው እና በኢራን ላይ የሚደርሰውን ጥቃት እየመራ ያለው የዩናይትድ ስቴትስ ሴንትራል ኮማንድ ኃይሉ ከ13,000 በላይ የኢራን ኢላማዎችን ማጥቃት ችሏል።በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባሰራጨው ጽሁፍ ከ155 በላይ የኢራን መርከቦች ተጎድተዋል ወይም ወድመዋል በማለት የአሜሪካ ኒውክሌር ኃይል አውሮፕላኖች አጓጓዦች እና ሰርጓጅ መርከቦች በኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ እንዲሁም ከኤፍ-35 ስውር ተዋጊ አውሮፕላኖች እስከ ቢ-52 ቦምቦች የሚደርሱ አውሮፕላኖች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጿል። ( ዳጉ_ጆርናል )
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
😢3❤2
ትራምፕ የኢራን ስልጣኔ ዛሬ ምሽት መጥፊያው ነው ሲሉ አስፈራሩ
ይህ እንዳይሆን ሀገሪቱ ስምምነት መድረስ እንዳለባት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በማኅበራዊ ገጻቸው ባሰራጩት የዛቻ መልዕክት ጠቁመዋል፡፡ ስፑትኒክ
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
ይህ እንዳይሆን ሀገሪቱ ስምምነት መድረስ እንዳለባት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በማኅበራዊ ገጻቸው ባሰራጩት የዛቻ መልዕክት ጠቁመዋል፡፡ ስፑትኒክ
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
👏6❤3😡1