በዓለም አቀፍ ደረጃ ይፈለግ የነበረ አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ ይትባረክ ዳዊት (ክብሮም) ከነግብረ-አበሮቹ በቁጥጥር ስር ዋለ
ከ3 ሺህ በላይ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ በማዘዋወር፣ ከ100 በላይ ሰዎችን ለሞት የዳረገ እና ከ50 በላይ ሴቶች እንዲደፈሩ ያደረገው ይትባረክ ዳዊት (ክብሮም)ን ከ9 ግብረ-አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ አጠናቆ ለዓቃቢ ሕግ መላኩን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
ይህንን ውስብስብ እና ድንበር ተሻጋሪ የወንጀል ምርመራ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ከሚሠራ “The Regional Operational Centre in support of the Khartoum process (ROCK) ከተባለ ድርጅት ጋር ባደረገው የመረጃ ልውውጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ ይፈለግ የነበረው አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ ይትባረክ ዳዊት አለሙን በትግራይ ክልል ሽሬ ከተማ ላይ ፖሊስ በቅንጅት በቁጥጥር ሥር አውሏል።
ተጠርጣሪው በፓስፖርት ስሙ ይትባረክ ዳዊት አለሙ፣ ቤተሰቦቹ በልጅነቱ ያወጡለት ስም ጳውሎስ ዳዊት ወልዳይ፤ ወንጀል መሥራት ሲጀምር የሚታወቅባቸው ስሞች አድሀኖም፣ ሱዳን ሀገር የሚታወቅበት ስም አሕመድ፤ ሱማሊያ፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የሚጠቀምበት ስም ሙኒር ሲሆን ክብሮም ደግሞ በስዊድን እና በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት የሚጠቀምባቸው ሀሰተኛ ስሞች መሆናቸውን ፖሊስ በምርመራው አረጋግጧል።
ፖሊስ እነዚህን ስሞች ለምርመራው አጋዥ አድርጎ ያደገ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተጠናከረ ምርመራና ክትትል በማድረግ ከ70 በላይ በሀገር ውስጥና በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ዋና ዋና የሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎችን ከለየ በኋላ ዋናውን ተጠርጣሪ ጨምሮ በአጠቃላይ 10 ህገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን ተከታትሎ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራውን ሲያከናውን ቆይቷል።
ፖሊስ የተያዙትንም ሆነ ያልተያዙትን ተጠርጣሪዎች በወንጀሉ ያፈሩትን ሀብት በጥናት በመለየት ሌሎች ሀብቶቻቸውንና በባንክ የሚገኝ ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ በፍርድ ቤት እንዲታገድ ማድረጉን ገልጿል።
ሕገ-ወጥ አዘዋዋሪ ቡድኑ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ወጣቶችን ከኢትዮጵያ፣ ከሱዳን፣ ከኤርትራ፣ ከጅቡቲ፣ ከኬንያ እና ከሶማሊያ በመመልመል ወደ ሊቢያ በመውሰድ ሊቢያ ውስጥ ባዘጋጁት መጋዝን እንዲታገቱ በማድረግ የተለያየ መጠን ያለው ገንዘብ ከቤተሰቦቻቸው በማስላክ፤ ገንዘብ ያልከፈሉትን በቀን አንድ ጊዜ ብቻ በትንሹ ምግብ እንዲመገቡ በማድረግ፣ በጎማ፣ በዱላ እና በኤሌክትሪክ ገመድ በሰንሰለት እጅ እና እግራቸውን አስረው በመግረፍና በማስገረፍ፣ የውሃ ማሸጊያ ፕላስቲክ አቃጥለው ሰውነታቸው ላይ በማንጠባጠብ ከፍተኛ ስቃይ በማድረስ፣ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት በመፈፀም በርካታ ሰዎች ሕይወታቸው እንዲያልፍ፣ የአካል ጉዳት እንዲደርስባቸው፣ ሴቶች እንዲደፈሩ እና ከፍተኛ አካላዊና ስነ-ልቦናዊ ጉዳት እንዲደርስባቸው ማድረጋቸውን ፖሊስ በምርመራ ማረጋገጥ ችሏል።
ሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎቹ ሊቢያ ውስጥ ተጎጅዎችን አግተው የሚያሰቃዩባቸው አምስት ማከማቻ መጋዘን እንዳላቸው እና በዚህ አደገኛ ወንጀል ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ በህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎቹ ሲንቀሳቀስ እንደነበረ ፖሊስ በሰበሰበው ማስረጃ ማረጋገጥ የቻለ ሲሆን ከ100 በላይ ተጎጂዎችና ቤተሰቦቻቸውን በሀገር ወስጥና በውጭ ሀገር የምስክርነት ቃል የመቀበል ሥራ መሰራቱንም ጨምሮ ገልጿል።
ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሊቢያ፤ ሱዳን፤ ቤልጂየም፤ እንግሊዝ፤ ካናዳ፤ ኖርዌይ፤ ኔዘርላንድ፤ ሉግዘንበርግ እና ስዊዘርላንድ ከሚገኙ አሥራ ስድስት ተጎጅዎች ላይ ቃል መቀበሉንም ፖሊስ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሀገርና በህዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ያለውን ይህንን ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ለመከላከል ዘመኑ ያፈራቸውን የምርመራ ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም በተሟላ ፖሊሳዊ ስብዕናና ስነ-ምግባር እየተመራ በላቀ ቁርጠኝነት ተልዕኮውን እየተወጣ ይገኛል።
ተቋሙ ከሀገራት ጋር በፈጠረው የፖሊስ ለፖሊስ ግንኙነትም ዓለም አቀፍ የወንጀል ተፈላጊዎችን ጭምር በቁጥጥር ሥር አውሎ በተለያየ ጊዜ ምርመራ በማጣራት በሀገር ውስጥ በሕግ እንዲጠየቁና የተወሰኑት ደግሞ ከሀገራት ጋር ባለው የወንጀለኛ ልውውጥ ስምምነት መሰረት ተላልፈው እንዲሰጡ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ውስብስብ ድንበር ተሸጋሪ የወንጀል ጉዳይ በተሳካ ሁኔታ እንዲጣራ ከፖሊስ ጋር በትብብር ለሰሩት ለፍትህ ሚኒስቴር፣ ለብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ለROCK እና በጉዳዩ ላይ መረጃ ሲሰጡ ለነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ላቅ ያለ ምስጋና እያቀረበ ኅብረተሰቡ ማንኛውንም የወንጀል ድርጊት ሲመለከት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp)፤ በ991 ነፃ የስልክ መስመር እና ሰው አልባ ፖሊስ ጣቢያ (SPS) በመጠቀም ወይም በአቅራቢያው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ቀርቦ ጥቆማ በመስጠት የዘወትር ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
ከ3 ሺህ በላይ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ በማዘዋወር፣ ከ100 በላይ ሰዎችን ለሞት የዳረገ እና ከ50 በላይ ሴቶች እንዲደፈሩ ያደረገው ይትባረክ ዳዊት (ክብሮም)ን ከ9 ግብረ-አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ አጠናቆ ለዓቃቢ ሕግ መላኩን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
ይህንን ውስብስብ እና ድንበር ተሻጋሪ የወንጀል ምርመራ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ከሚሠራ “The Regional Operational Centre in support of the Khartoum process (ROCK) ከተባለ ድርጅት ጋር ባደረገው የመረጃ ልውውጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ ይፈለግ የነበረው አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ ይትባረክ ዳዊት አለሙን በትግራይ ክልል ሽሬ ከተማ ላይ ፖሊስ በቅንጅት በቁጥጥር ሥር አውሏል።
ተጠርጣሪው በፓስፖርት ስሙ ይትባረክ ዳዊት አለሙ፣ ቤተሰቦቹ በልጅነቱ ያወጡለት ስም ጳውሎስ ዳዊት ወልዳይ፤ ወንጀል መሥራት ሲጀምር የሚታወቅባቸው ስሞች አድሀኖም፣ ሱዳን ሀገር የሚታወቅበት ስም አሕመድ፤ ሱማሊያ፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የሚጠቀምበት ስም ሙኒር ሲሆን ክብሮም ደግሞ በስዊድን እና በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት የሚጠቀምባቸው ሀሰተኛ ስሞች መሆናቸውን ፖሊስ በምርመራው አረጋግጧል።
ፖሊስ እነዚህን ስሞች ለምርመራው አጋዥ አድርጎ ያደገ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተጠናከረ ምርመራና ክትትል በማድረግ ከ70 በላይ በሀገር ውስጥና በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ዋና ዋና የሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎችን ከለየ በኋላ ዋናውን ተጠርጣሪ ጨምሮ በአጠቃላይ 10 ህገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን ተከታትሎ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራውን ሲያከናውን ቆይቷል።
ፖሊስ የተያዙትንም ሆነ ያልተያዙትን ተጠርጣሪዎች በወንጀሉ ያፈሩትን ሀብት በጥናት በመለየት ሌሎች ሀብቶቻቸውንና በባንክ የሚገኝ ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ በፍርድ ቤት እንዲታገድ ማድረጉን ገልጿል።
ሕገ-ወጥ አዘዋዋሪ ቡድኑ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ወጣቶችን ከኢትዮጵያ፣ ከሱዳን፣ ከኤርትራ፣ ከጅቡቲ፣ ከኬንያ እና ከሶማሊያ በመመልመል ወደ ሊቢያ በመውሰድ ሊቢያ ውስጥ ባዘጋጁት መጋዝን እንዲታገቱ በማድረግ የተለያየ መጠን ያለው ገንዘብ ከቤተሰቦቻቸው በማስላክ፤ ገንዘብ ያልከፈሉትን በቀን አንድ ጊዜ ብቻ በትንሹ ምግብ እንዲመገቡ በማድረግ፣ በጎማ፣ በዱላ እና በኤሌክትሪክ ገመድ በሰንሰለት እጅ እና እግራቸውን አስረው በመግረፍና በማስገረፍ፣ የውሃ ማሸጊያ ፕላስቲክ አቃጥለው ሰውነታቸው ላይ በማንጠባጠብ ከፍተኛ ስቃይ በማድረስ፣ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት በመፈፀም በርካታ ሰዎች ሕይወታቸው እንዲያልፍ፣ የአካል ጉዳት እንዲደርስባቸው፣ ሴቶች እንዲደፈሩ እና ከፍተኛ አካላዊና ስነ-ልቦናዊ ጉዳት እንዲደርስባቸው ማድረጋቸውን ፖሊስ በምርመራ ማረጋገጥ ችሏል።
ሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎቹ ሊቢያ ውስጥ ተጎጅዎችን አግተው የሚያሰቃዩባቸው አምስት ማከማቻ መጋዘን እንዳላቸው እና በዚህ አደገኛ ወንጀል ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ በህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎቹ ሲንቀሳቀስ እንደነበረ ፖሊስ በሰበሰበው ማስረጃ ማረጋገጥ የቻለ ሲሆን ከ100 በላይ ተጎጂዎችና ቤተሰቦቻቸውን በሀገር ወስጥና በውጭ ሀገር የምስክርነት ቃል የመቀበል ሥራ መሰራቱንም ጨምሮ ገልጿል።
ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሊቢያ፤ ሱዳን፤ ቤልጂየም፤ እንግሊዝ፤ ካናዳ፤ ኖርዌይ፤ ኔዘርላንድ፤ ሉግዘንበርግ እና ስዊዘርላንድ ከሚገኙ አሥራ ስድስት ተጎጅዎች ላይ ቃል መቀበሉንም ፖሊስ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሀገርና በህዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ያለውን ይህንን ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ለመከላከል ዘመኑ ያፈራቸውን የምርመራ ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም በተሟላ ፖሊሳዊ ስብዕናና ስነ-ምግባር እየተመራ በላቀ ቁርጠኝነት ተልዕኮውን እየተወጣ ይገኛል።
ተቋሙ ከሀገራት ጋር በፈጠረው የፖሊስ ለፖሊስ ግንኙነትም ዓለም አቀፍ የወንጀል ተፈላጊዎችን ጭምር በቁጥጥር ሥር አውሎ በተለያየ ጊዜ ምርመራ በማጣራት በሀገር ውስጥ በሕግ እንዲጠየቁና የተወሰኑት ደግሞ ከሀገራት ጋር ባለው የወንጀለኛ ልውውጥ ስምምነት መሰረት ተላልፈው እንዲሰጡ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ውስብስብ ድንበር ተሸጋሪ የወንጀል ጉዳይ በተሳካ ሁኔታ እንዲጣራ ከፖሊስ ጋር በትብብር ለሰሩት ለፍትህ ሚኒስቴር፣ ለብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ለROCK እና በጉዳዩ ላይ መረጃ ሲሰጡ ለነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ላቅ ያለ ምስጋና እያቀረበ ኅብረተሰቡ ማንኛውንም የወንጀል ድርጊት ሲመለከት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp)፤ በ991 ነፃ የስልክ መስመር እና ሰው አልባ ፖሊስ ጣቢያ (SPS) በመጠቀም ወይም በአቅራቢያው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ቀርቦ ጥቆማ በመስጠት የዘወትር ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤10
ስጋ 650 ብር እንዲሸጥ ተወስኗል
ለትንሳዔ በዓል የሸቀጦች አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል፡- የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በከተማዋ የሸቀጦች አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰትና ገበያው እንዲረጋጋ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቋል።
የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ከተማ አስተዳደሩ በዓሉን ተከትሎ ሊከሰት የሚችለውን የፍላጎት መጨመር ታሳቢ በማድረግ ካለፈው ወር ጀምሮ ከተለያዩ ክልሎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ምርት የማሰባሰብ ሥራ ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸዋል።
ወቅታዊው ዓለም አቀፍ የነዳጅ ችግር በምርት ስርጭት ላይ ተፅዕኖ እንዳያሳድር የተቀናጀ ዝግጅት መደረጉን ኃላፊዋ አመላክተዋል፡፡
በዚህም ለኅብረተሰቡ አማራጭ የገበያ ቦታዎችን ለማቅረብ በተሰራው ሥራ በመንግሥት በተዘጋጁ 6 ዋና ዋና የግብርና ምርት መሸጫ ማዕከላት፣ በ246 የሰንበት ገበያዎችና በ2 ሺህ 56 የኅብረት ሥራ ማህበራት ሱቆች በቂ ምርት እንዲገባ መደረጉን ተናግረዋል።
በተለይም መሰረታዊ ሸቀጦችንና እንደ ዘይት ያሉ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለተጠቃሚው ለማድረስ ሰፊ የገበያ ትስስር መፈጠሩ የተገለጸ ሲሆን፤ የሥጋ ምርትን በተመለከተም ኅብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ በህብረት ሥራ ማህበራት በኩል አንድ ኪሎ ሥጋ በ650 ብር እንዲቀርብ መወሰኑ ተመላክቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በበዓሉ ወቅት የዋጋ ንረትና የንግድ ማጭበርበር እንዳይኖር ቢሮው በሁሉም የገበያ ማዕከላት፣ ባዛሮችና መደበኛ ሱቆች ላይ ቁጥጥር የሚያደርግ ግብረ ኃይል አሰማርቷል።
በዚህም መሰረት ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ፣ በምርት ላይ ባዕድ ነገር በሚቀላቅሉና በሚዛን በሚያጭበረብሩ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቋል።
ኅብረተሰቡ የምርት እጥረት ሳያጋጥመው በዓሉን እንዲያከብር የሚያስችሉ እነዚህ የገበያ ማረጋጋት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ቢሮው አስታውቋል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
ለትንሳዔ በዓል የሸቀጦች አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል፡- የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በከተማዋ የሸቀጦች አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰትና ገበያው እንዲረጋጋ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቋል።
የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ከተማ አስተዳደሩ በዓሉን ተከትሎ ሊከሰት የሚችለውን የፍላጎት መጨመር ታሳቢ በማድረግ ካለፈው ወር ጀምሮ ከተለያዩ ክልሎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ምርት የማሰባሰብ ሥራ ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸዋል።
ወቅታዊው ዓለም አቀፍ የነዳጅ ችግር በምርት ስርጭት ላይ ተፅዕኖ እንዳያሳድር የተቀናጀ ዝግጅት መደረጉን ኃላፊዋ አመላክተዋል፡፡
በዚህም ለኅብረተሰቡ አማራጭ የገበያ ቦታዎችን ለማቅረብ በተሰራው ሥራ በመንግሥት በተዘጋጁ 6 ዋና ዋና የግብርና ምርት መሸጫ ማዕከላት፣ በ246 የሰንበት ገበያዎችና በ2 ሺህ 56 የኅብረት ሥራ ማህበራት ሱቆች በቂ ምርት እንዲገባ መደረጉን ተናግረዋል።
በተለይም መሰረታዊ ሸቀጦችንና እንደ ዘይት ያሉ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለተጠቃሚው ለማድረስ ሰፊ የገበያ ትስስር መፈጠሩ የተገለጸ ሲሆን፤ የሥጋ ምርትን በተመለከተም ኅብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ በህብረት ሥራ ማህበራት በኩል አንድ ኪሎ ሥጋ በ650 ብር እንዲቀርብ መወሰኑ ተመላክቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በበዓሉ ወቅት የዋጋ ንረትና የንግድ ማጭበርበር እንዳይኖር ቢሮው በሁሉም የገበያ ማዕከላት፣ ባዛሮችና መደበኛ ሱቆች ላይ ቁጥጥር የሚያደርግ ግብረ ኃይል አሰማርቷል።
በዚህም መሰረት ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ፣ በምርት ላይ ባዕድ ነገር በሚቀላቅሉና በሚዛን በሚያጭበረብሩ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቋል።
ኅብረተሰቡ የምርት እጥረት ሳያጋጥመው በዓሉን እንዲያከብር የሚያስችሉ እነዚህ የገበያ ማረጋጋት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ቢሮው አስታውቋል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤5
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የጥላቻ ንግግሮችንና ሀሰተኛ መረጃዎችን ሲያጋራ የነበረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
በጅማ ዞን ጮራ ቦተሪ ወረዳ ኮራ ዲማ ቀበሌ ውስጥ የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን በመክፈት የጥላቻ እና ሃሰተኛ የሆኑ ማስረጃዎችን በማሰራጨት ህብረተሰቡ ውስጥ አለመግባባት እንዲፈጠር ያደረገው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱ ተገለፀ። እንደ ወረዳዉ አቃቢ ህግ ገለፃ ተከሳሽ ሸለማ አበራ የተባለ የ22 ዓመት ወጣት ፣ሮብ ገብያ የተባለ ስፍራ ማህበራዊ ሚዲያውን እንደ ሽፋን በመጠቀም የጥላቻ ንግግሮች ሲያሰራጭ መቆየቱን ገልጿል ።
ከታህሳስ 2018 ዓም ጀምሮ አባ ሴና የሚል ሀሰተኛ ገጽ በመክፈት ድርጊቱን ሲፈጽም ቆይቷል።በዚህም በሮብ ገብያ አካባቢ ዙርያው ማህበረሰብ መካከል ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ ድርጊቶች መከሰታቸው አጋርቷል።ለዘመናት ባህሉን፣ እምነቱን፣ እሴቱንና ልማዱን ጠብቆ ተከባብሮ የሚኖርን ማህበረሰብ እርስ በእርስ እንዲጠራጠር እና ግጭት ውስጥ እንዲገባ ማድረጉን ፖሊስ በበቂ ማስረጃ አረጋግጧል። ፖሊስ በተከሳሹ ላይ ክትትል በማድረግ በቁጥጥር ስር ካዋለው በኋላ አስፈላጊ ነው ያለውን ማስረጃ በማጠናከር የምርመራ መዝገቡን ለአቃቢ ህግ ልኳል።
አቃቢ ህግ የሀሰተኛ መረጃዎች እና የጥላቻ ንግግሮችን ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ፣የማህበረሰብን መብት በመጣስ የሀሰት ስም ማጥፋት ድርጊት ክስ መስርቷል። ክሱን ሲከታተል የቆየው የወረዳዉ ፍርድ ቤት መጋቢት 22 ቀን 2018 በዋለው ቸሎት ተከሳሹን ጥፋተኛ ሆኖ በማለት በሶስት አመት ከስድስት ወር እስራት እና በአንድ ሺህ ብር ገንዘብ እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
በጅማ ዞን ጮራ ቦተሪ ወረዳ ኮራ ዲማ ቀበሌ ውስጥ የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን በመክፈት የጥላቻ እና ሃሰተኛ የሆኑ ማስረጃዎችን በማሰራጨት ህብረተሰቡ ውስጥ አለመግባባት እንዲፈጠር ያደረገው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱ ተገለፀ። እንደ ወረዳዉ አቃቢ ህግ ገለፃ ተከሳሽ ሸለማ አበራ የተባለ የ22 ዓመት ወጣት ፣ሮብ ገብያ የተባለ ስፍራ ማህበራዊ ሚዲያውን እንደ ሽፋን በመጠቀም የጥላቻ ንግግሮች ሲያሰራጭ መቆየቱን ገልጿል ።
ከታህሳስ 2018 ዓም ጀምሮ አባ ሴና የሚል ሀሰተኛ ገጽ በመክፈት ድርጊቱን ሲፈጽም ቆይቷል።በዚህም በሮብ ገብያ አካባቢ ዙርያው ማህበረሰብ መካከል ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ ድርጊቶች መከሰታቸው አጋርቷል።ለዘመናት ባህሉን፣ እምነቱን፣ እሴቱንና ልማዱን ጠብቆ ተከባብሮ የሚኖርን ማህበረሰብ እርስ በእርስ እንዲጠራጠር እና ግጭት ውስጥ እንዲገባ ማድረጉን ፖሊስ በበቂ ማስረጃ አረጋግጧል። ፖሊስ በተከሳሹ ላይ ክትትል በማድረግ በቁጥጥር ስር ካዋለው በኋላ አስፈላጊ ነው ያለውን ማስረጃ በማጠናከር የምርመራ መዝገቡን ለአቃቢ ህግ ልኳል።
አቃቢ ህግ የሀሰተኛ መረጃዎች እና የጥላቻ ንግግሮችን ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ፣የማህበረሰብን መብት በመጣስ የሀሰት ስም ማጥፋት ድርጊት ክስ መስርቷል። ክሱን ሲከታተል የቆየው የወረዳዉ ፍርድ ቤት መጋቢት 22 ቀን 2018 በዋለው ቸሎት ተከሳሹን ጥፋተኛ ሆኖ በማለት በሶስት አመት ከስድስት ወር እስራት እና በአንድ ሺህ ብር ገንዘብ እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤6👏1
ትክክለኛ የባህል መዳኒት ይፈልጋሉ??
👆መርጌታ የባህል ህክምና 0915398834
1🌿ለሀብት ማምጫ
2🌿ለእቁብ (እቁብ እንዲወጣላችሁ የሚያረግ)
3ለመስተፋቅር
4🌿 &መጠብቅ (ከጠላት ከሚላክ ሟርት የሚጠብቅ)
5🌿ለጋኔን
6🌿ለማንኛውም ዓይነት በሽታ መፍትሔ
7🌿ለራእይ (በህልም የሚያሳይ)7
8🌿 ለፀር (ለጠላት)
9🌿ዓቃቤ_ርእስ (ጠላት እንዳይጎዳን የሚጠብቅ)
10🌿 ለዘኢያገድፍ (ለትምህርት የማያስጠፋ የማያስጥል)
11🌿ለመክስተ_ምስጢር (ትምህርት የሚያጎብዝ)
12🌿ለመፍትሔ_ሀብት(ሀብቱ በጠላት ድግምት ለተሰወረበት)
13🌿 መስተፋቅር
14🌿ለግርማ_ሞገስ (ሰው እንዲያከብረን እንዲወደን)
15🌿ለመድፍነ_ፀር (ጠላት እንዳይናገረን እና እንዲፈራ
16🌿ለሌባ(እንዳንሰረቅ እንዳንዘረፍ የሚጠብቅ)
17🌿የትዳር አጋር ላጣ ወይም ላጣች
የሚያስገኝ
18🌿ለምስያጥ ለገበያ (ገበያ እንዲቀናን እንድናገኝ)
19🌿መስተኃድር (ከብት ቢጠፋብን ሳይበሉ በሰላም እቤታቸው
የሚያመጣ)
20🌿መንድግ(በገበያ ገንዘብ ማግኛ)
21🌿ለዓይነ_ጥላ (የፍራቻ መንፈስ ማስለቀቂያ)
22🌿ለልሳነ_ሰብእ
23🌿ለበረከት
24🌿ለእግረ_መልስ (ጥሎ ለጠፋ ሰው መመለሻ ማምጫ)
25🌿ምስሀበ_ነዋይ(ገንዘብ ማግኛ)
26🌿ጸሎተ_ዕለታት
27🌿ለጽሑፍ ለስእል ለከበሮ ለበገና ለክራር በእጂ ለሚሰሩ
28🌿ንባብ ስናነብ ቀልጣፋ የሚያረግ
29🌿ለከበሮ
30🌿ለመፍዝዝ (ጠላት እኛን ለማጥቃት ሲሞክር አጠገባችን ሲደርስ
መጣላቱን አስረስቶ አፍዝዞ የሚያስቀር የማያስመታ)
31🌿ለሙግት
32🌿ለሰላቢ
33🌿ለስንፈት ወሲብ
34🌿ዘኢያወርድ ( ለወንዶች በፆታዊ ግንኙነት ወቅት የዘር ፍሬ ቶሎ
እንዳይወርድ የሚያረግ አግዶ የሚያቆይ)
35🌿ለመደንግፅ (የተጣላን ሰው እኛን ሲያይ እንዲደነግጥ እንዲፈራ
የሚያረግ)
36🌿ለጥይት (ጥይት የማያስመታ)
በ 0915398834 ይደውሉልን
👆መርጌታ የባህል ህክምና 0915398834
1🌿ለሀብት ማምጫ
2🌿ለእቁብ (እቁብ እንዲወጣላችሁ የሚያረግ)
3ለመስተፋቅር
4🌿 &መጠብቅ (ከጠላት ከሚላክ ሟርት የሚጠብቅ)
5🌿ለጋኔን
6🌿ለማንኛውም ዓይነት በሽታ መፍትሔ
7🌿ለራእይ (በህልም የሚያሳይ)7
8🌿 ለፀር (ለጠላት)
9🌿ዓቃቤ_ርእስ (ጠላት እንዳይጎዳን የሚጠብቅ)
10🌿 ለዘኢያገድፍ (ለትምህርት የማያስጠፋ የማያስጥል)
11🌿ለመክስተ_ምስጢር (ትምህርት የሚያጎብዝ)
12🌿ለመፍትሔ_ሀብት(ሀብቱ በጠላት ድግምት ለተሰወረበት)
13🌿 መስተፋቅር
14🌿ለግርማ_ሞገስ (ሰው እንዲያከብረን እንዲወደን)
15🌿ለመድፍነ_ፀር (ጠላት እንዳይናገረን እና እንዲፈራ
16🌿ለሌባ(እንዳንሰረቅ እንዳንዘረፍ የሚጠብቅ)
17🌿የትዳር አጋር ላጣ ወይም ላጣች
የሚያስገኝ
18🌿ለምስያጥ ለገበያ (ገበያ እንዲቀናን እንድናገኝ)
19🌿መስተኃድር (ከብት ቢጠፋብን ሳይበሉ በሰላም እቤታቸው
የሚያመጣ)
20🌿መንድግ(በገበያ ገንዘብ ማግኛ)
21🌿ለዓይነ_ጥላ (የፍራቻ መንፈስ ማስለቀቂያ)
22🌿ለልሳነ_ሰብእ
23🌿ለበረከት
24🌿ለእግረ_መልስ (ጥሎ ለጠፋ ሰው መመለሻ ማምጫ)
25🌿ምስሀበ_ነዋይ(ገንዘብ ማግኛ)
26🌿ጸሎተ_ዕለታት
27🌿ለጽሑፍ ለስእል ለከበሮ ለበገና ለክራር በእጂ ለሚሰሩ
28🌿ንባብ ስናነብ ቀልጣፋ የሚያረግ
29🌿ለከበሮ
30🌿ለመፍዝዝ (ጠላት እኛን ለማጥቃት ሲሞክር አጠገባችን ሲደርስ
መጣላቱን አስረስቶ አፍዝዞ የሚያስቀር የማያስመታ)
31🌿ለሙግት
32🌿ለሰላቢ
33🌿ለስንፈት ወሲብ
34🌿ዘኢያወርድ ( ለወንዶች በፆታዊ ግንኙነት ወቅት የዘር ፍሬ ቶሎ
እንዳይወርድ የሚያረግ አግዶ የሚያቆይ)
35🌿ለመደንግፅ (የተጣላን ሰው እኛን ሲያይ እንዲደነግጥ እንዲፈራ
የሚያረግ)
36🌿ለጥይት (ጥይት የማያስመታ)
በ 0915398834 ይደውሉልን
❤1
#ሾተላይ ( RH incompatibility )
ሾተላይ ( RH incompatibility )፡ - የእናት እና የፅንስ የደም አይነት አለመጣጣም ሲሆን RH negative በሆኑ ሴቶች ላይ የሚከሰት ችግር ነው ።
ስለሾተላይ ለማወቅና ጥንቃቄ ለማድረግ በመጀመሪያ ስለ ቀይ የደም አይነት እንዴት እንደሚከፈል ማወቅ ያስፈልጋል ። ቀይ የደም አይነት በተለያየ መንገድ ይከፈላል:-
1. ABO System፡- መሰረት በማድረግ Group A, B, AB, እና O ተብሎ ይከፈላል
2. Rh System:– ከላይ ABO ተብለው የተከፈሉት እያንዳንዳቸው በሁለት ማለትም Rh negative እና Rh positive ተብለው ይከፈላሉ, ይህም ማለት A (A+, A-), B (B+, B-), AB (AB+, AB-), እና O (O+ O-) ነው።
Rh negative እና Rh positive ምን ማለት ነው?
✓Rh በቀይ የደም አይነት ላይ የሚገኝ protein ነው ። ይህ Rh protein በላዩ ላይ ያለው ቀይ የደም አይነት Rh+ ሲባል, ይህ protein የሌለው ደግሞ Rh- የደም አይነት ይባላል ።
✓አንድ ሰው የደም አይነቱ የሚወሰነው በወላጆቹ የደም አይነት መሰረት ነው ።
1. ሁለቱም ወላጆች Rh+ ከሆኑ, እርሱም Rh+ የመሆን እድሉ የሰፋ ነው ።
2. ሁለቱም ወላጆች Rh- ከሆኑ እርሱም Rh- ይሆናል።
3. እናት Rh+ ከሆነችና አባት Rh- ከሆነ፣ ልጅ Rh+ወይም Rh- ሊሆን ይችላል ።
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ነገሮች ሁሉ ብዙ ጊዜ ምንም ችግር የላቸውም።
✓ሾተላይ የሚከሰተው ግን እናት ( Rh-) ከሆችና አባት ( Rh+) ሆኖ Rh+ የሆነ ፅንስ በምትፀንስበት ጊዜ ነው።
✓እናት Rh- ሁና፣ Rh+ ፅንስ በምትፀንስበት ጊዜ በተለያዩ አጋጣሚዎች ደም መፍሰስ ሲያጋጥም የፅንሱ ደም ወደ እናት የደም ስር ይገባል፣ በዚህም ጊዜ ከልጁ የቀይ ደም ላይ የሚገኙ ፕሮቲኖችን የእናት በሽታ ተከላካይ ህወሳት ያዩና እንደ ባእድ ነገር በመቁጠር መከላከያ ( antibody ) ያመርታሉ። እነዚህ የተመረቱ antibodies በእናት ደም ውስጥ ተመርተው ወደፅንስ ከሚሄደው የእናት ደም ጋር አብረው በመሄድ የፅንሱን ደም ማጥቃት ይጀምራሉ።
✓Antibody ለማምረት ጊዜ ስለሚፈጅና አብዛኛው ጊዜ የልጅ ደም ወደ እናት የሚሄደው በወሊድ ጊዜ በመሆኑ የመጀመሪያ ልጅ ላይ ችግር አይፈጥርም ።
✓በተከታታይ የሚረገዘው ፅንስ Rh- ከሆነም ምንም አይነት ችግር አይገጥማቸውም።
✓ነገር ግን Rh+ በተረገዘ ጊዜ፣ በእናት ደም ውስጥ ተመረተው የተቀመጡ antibodies የልጁን Rh+ የደም ዓይነት እንደ ባዕድ በመቁጠር እየሄዱ ያጠቁታል።
✓የሰውነታችን በሽታ ተከላካይ ህዋስ፣ በሽታ አምጭ ነገሮች ወደሰውነት ሲገባ የተለያዩ መንገዶች ተጠቅሞ እንደሚጠቃው ሁሉ ፅንሱንም Rh+ የሚል ምልክት በቀይ የደም ሴሉ ሲያይ እንደ ባዕድ ነገር ያየውና ጥቃት ያደርስበታል።
✓ይህ የተፈጠረው antibody የእንግዴ ልጁን በማለፍ የፅንሱን ቀይ የደም ህዋስ ያጠቃል።
በዚህም ምክንያት
-የፅንስ የደም ማነስ
-የፅንስ የልብ ድካም
-በሰውነት በተለያዩ ቦታወች ውሀ መቋጠር
-የፅንስ ውርጃ
-ከተወለደ በኋላ የህፃን ቆዳና አይን ቢጫ መሆን
-እንዲሁም ሞት ሊያስከትል ይችላል
የፅንሱ ደም ወደ እናት እንዲገባ በማድረግ ለሾተላይ የሚያጋልጡ ምክንያቶች
✓በእርግዝና ወቅት ደም መፍሰስ
✓በእርግዝና ወቅት ሆድን መምታት
✓የፅንስ አቀማመጥን ለማስተካከል መሞከር(ECV)
✓የፅንስ በማህፀን ውስጥ መሞት
✓በቅድመ ወሊድ የተለያዩ የምርመራ ሂደቶች (amniocentesis(ከሽርት ውሀ ናሙና መውሰድ)፣ chorion villus sampling ፣ የፅንስ የደም ናሙና)
✓ከማህፀን ውጭ እርግዝና
በእነዚህ ክስተቶች ወቅት የፅንስ ደም ወደ እናት ደም ውስጥ በመግባት በእናትየው ደም ውስጥ ፀረ-እንግዳ(Antibodies) እንዲፈጠር ያደርጋል።
ሾተላይን መከላከል እንዴት ይቻላል?
✓የሾተላይ የመጀመሪያ ደረጃ መከላከል የሚጀምረው RH Negative ሴቶችን ለRH Positive ደም ከመጋለጣቸው በፊት Anti-D መስጠት ነው፡፡
✓በመጀመርያው የእርግዝና ክትትል Indirect coombs test ኔጋቲቭ ሆኖ ከተገኘ:-
1. ከ28-32 ሳምንት ባለው ጊዜ፣
2. ከወሊድ በኋላ የልጁ ደም አይነት RH+ ከሆነ በ72 ሰዓት ውስጥ፣
3. በእርግዝና ወቅት ደም መፍሰስ (ውርጃ፣ ከማህፅን ውጭ እርግዝና እና ሌሎችም ሁኔታዎች እና
4. RH+ ደም ከወሰዱ (በድንገተኛ ጊዜ) Anti-D በመውሰድ ሾተላይን መከላከል ይቻላል።
ሕክምናው
1. የደም ዓይነቷ አር ኤች ኔጋቲቭ (Rh-) የሆነች እናት ክትትሏ ሆስፒታል ቢሆን ይመረጣል
2. በደሟ ውስጥ ያለውን የንጥረ-ነገር መጠን በመለካትና የጽንሱን የጉዳት መጠን በማየት ብዙ ሳይጎዳ እንዲወለድ ማድረግ።
3. ጽንሱ በማህጸን ውስጥ እያለ ደም በመለገስ እንዲያድግና እንዲወለድ ማድረግ ይቻላል ።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
ሾተላይ ( RH incompatibility )፡ - የእናት እና የፅንስ የደም አይነት አለመጣጣም ሲሆን RH negative በሆኑ ሴቶች ላይ የሚከሰት ችግር ነው ።
ስለሾተላይ ለማወቅና ጥንቃቄ ለማድረግ በመጀመሪያ ስለ ቀይ የደም አይነት እንዴት እንደሚከፈል ማወቅ ያስፈልጋል ። ቀይ የደም አይነት በተለያየ መንገድ ይከፈላል:-
1. ABO System፡- መሰረት በማድረግ Group A, B, AB, እና O ተብሎ ይከፈላል
2. Rh System:– ከላይ ABO ተብለው የተከፈሉት እያንዳንዳቸው በሁለት ማለትም Rh negative እና Rh positive ተብለው ይከፈላሉ, ይህም ማለት A (A+, A-), B (B+, B-), AB (AB+, AB-), እና O (O+ O-) ነው።
Rh negative እና Rh positive ምን ማለት ነው?
✓Rh በቀይ የደም አይነት ላይ የሚገኝ protein ነው ። ይህ Rh protein በላዩ ላይ ያለው ቀይ የደም አይነት Rh+ ሲባል, ይህ protein የሌለው ደግሞ Rh- የደም አይነት ይባላል ።
✓አንድ ሰው የደም አይነቱ የሚወሰነው በወላጆቹ የደም አይነት መሰረት ነው ።
1. ሁለቱም ወላጆች Rh+ ከሆኑ, እርሱም Rh+ የመሆን እድሉ የሰፋ ነው ።
2. ሁለቱም ወላጆች Rh- ከሆኑ እርሱም Rh- ይሆናል።
3. እናት Rh+ ከሆነችና አባት Rh- ከሆነ፣ ልጅ Rh+ወይም Rh- ሊሆን ይችላል ።
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ነገሮች ሁሉ ብዙ ጊዜ ምንም ችግር የላቸውም።
✓ሾተላይ የሚከሰተው ግን እናት ( Rh-) ከሆችና አባት ( Rh+) ሆኖ Rh+ የሆነ ፅንስ በምትፀንስበት ጊዜ ነው።
✓እናት Rh- ሁና፣ Rh+ ፅንስ በምትፀንስበት ጊዜ በተለያዩ አጋጣሚዎች ደም መፍሰስ ሲያጋጥም የፅንሱ ደም ወደ እናት የደም ስር ይገባል፣ በዚህም ጊዜ ከልጁ የቀይ ደም ላይ የሚገኙ ፕሮቲኖችን የእናት በሽታ ተከላካይ ህወሳት ያዩና እንደ ባእድ ነገር በመቁጠር መከላከያ ( antibody ) ያመርታሉ። እነዚህ የተመረቱ antibodies በእናት ደም ውስጥ ተመርተው ወደፅንስ ከሚሄደው የእናት ደም ጋር አብረው በመሄድ የፅንሱን ደም ማጥቃት ይጀምራሉ።
✓Antibody ለማምረት ጊዜ ስለሚፈጅና አብዛኛው ጊዜ የልጅ ደም ወደ እናት የሚሄደው በወሊድ ጊዜ በመሆኑ የመጀመሪያ ልጅ ላይ ችግር አይፈጥርም ።
✓በተከታታይ የሚረገዘው ፅንስ Rh- ከሆነም ምንም አይነት ችግር አይገጥማቸውም።
✓ነገር ግን Rh+ በተረገዘ ጊዜ፣ በእናት ደም ውስጥ ተመረተው የተቀመጡ antibodies የልጁን Rh+ የደም ዓይነት እንደ ባዕድ በመቁጠር እየሄዱ ያጠቁታል።
✓የሰውነታችን በሽታ ተከላካይ ህዋስ፣ በሽታ አምጭ ነገሮች ወደሰውነት ሲገባ የተለያዩ መንገዶች ተጠቅሞ እንደሚጠቃው ሁሉ ፅንሱንም Rh+ የሚል ምልክት በቀይ የደም ሴሉ ሲያይ እንደ ባዕድ ነገር ያየውና ጥቃት ያደርስበታል።
✓ይህ የተፈጠረው antibody የእንግዴ ልጁን በማለፍ የፅንሱን ቀይ የደም ህዋስ ያጠቃል።
በዚህም ምክንያት
-የፅንስ የደም ማነስ
-የፅንስ የልብ ድካም
-በሰውነት በተለያዩ ቦታወች ውሀ መቋጠር
-የፅንስ ውርጃ
-ከተወለደ በኋላ የህፃን ቆዳና አይን ቢጫ መሆን
-እንዲሁም ሞት ሊያስከትል ይችላል
የፅንሱ ደም ወደ እናት እንዲገባ በማድረግ ለሾተላይ የሚያጋልጡ ምክንያቶች
✓በእርግዝና ወቅት ደም መፍሰስ
✓በእርግዝና ወቅት ሆድን መምታት
✓የፅንስ አቀማመጥን ለማስተካከል መሞከር(ECV)
✓የፅንስ በማህፀን ውስጥ መሞት
✓በቅድመ ወሊድ የተለያዩ የምርመራ ሂደቶች (amniocentesis(ከሽርት ውሀ ናሙና መውሰድ)፣ chorion villus sampling ፣ የፅንስ የደም ናሙና)
✓ከማህፀን ውጭ እርግዝና
በእነዚህ ክስተቶች ወቅት የፅንስ ደም ወደ እናት ደም ውስጥ በመግባት በእናትየው ደም ውስጥ ፀረ-እንግዳ(Antibodies) እንዲፈጠር ያደርጋል።
ሾተላይን መከላከል እንዴት ይቻላል?
✓የሾተላይ የመጀመሪያ ደረጃ መከላከል የሚጀምረው RH Negative ሴቶችን ለRH Positive ደም ከመጋለጣቸው በፊት Anti-D መስጠት ነው፡፡
✓በመጀመርያው የእርግዝና ክትትል Indirect coombs test ኔጋቲቭ ሆኖ ከተገኘ:-
1. ከ28-32 ሳምንት ባለው ጊዜ፣
2. ከወሊድ በኋላ የልጁ ደም አይነት RH+ ከሆነ በ72 ሰዓት ውስጥ፣
3. በእርግዝና ወቅት ደም መፍሰስ (ውርጃ፣ ከማህፅን ውጭ እርግዝና እና ሌሎችም ሁኔታዎች እና
4. RH+ ደም ከወሰዱ (በድንገተኛ ጊዜ) Anti-D በመውሰድ ሾተላይን መከላከል ይቻላል።
ሕክምናው
1. የደም ዓይነቷ አር ኤች ኔጋቲቭ (Rh-) የሆነች እናት ክትትሏ ሆስፒታል ቢሆን ይመረጣል
2. በደሟ ውስጥ ያለውን የንጥረ-ነገር መጠን በመለካትና የጽንሱን የጉዳት መጠን በማየት ብዙ ሳይጎዳ እንዲወለድ ማድረግ።
3. ጽንሱ በማህጸን ውስጥ እያለ ደም በመለገስ እንዲያድግና እንዲወለድ ማድረግ ይቻላል ።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤7
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዶርም ገብቶ ሁከት የፈጠረው ዝንጀሮ
ዝንጀሮው በዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ማደሪያ ውስጥ ገብቶ ምግብ ሲሰርቅ እና ተማሪዎችን ሲያሽበር ታይቷል፡፡
እንዲህ ያለ ገጠመኝ ስንቶቻቹ አላችሁ?
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
ዝንጀሮው በዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ማደሪያ ውስጥ ገብቶ ምግብ ሲሰርቅ እና ተማሪዎችን ሲያሽበር ታይቷል፡፡
እንዲህ ያለ ገጠመኝ ስንቶቻቹ አላችሁ?
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
😁15
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦላቸው በውጤቶቹ ላይ ግምገማ እና ውይይት ተደርጓል።
#PMOEthiopia
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
#PMOEthiopia
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤6🤣4
አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸው ተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው።
አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን÷ በአፍሪካ ሕብረትና በተባባሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ መልዕክተኛ በመሆንም ሰርተዋል።
ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011 ዓ.ም ደግሞ ኢጋድ በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ላይ ልዩ አማካሪ ሆነው ማገልገላቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸው ተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው።
አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን÷ በአፍሪካ ሕብረትና በተባባሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ መልዕክተኛ በመሆንም ሰርተዋል።
ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011 ዓ.ም ደግሞ ኢጋድ በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ላይ ልዩ አማካሪ ሆነው ማገልገላቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
😢4❤1
ኢራን የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አደረገች፤ የፕሬዝዳንት ትራምፕ የማስጠንቀቂያ ቀነ-ገደብም ሰዓታት ቀርተውታል
በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ዙሪያ የቀረበውን የተኩስ አቁም የሰላም ጥያቄ ኢራን ውድቅ ማድረጓ ተሰምቷል።
ይህ የቴህራን ውሳኔ የተሰማው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥቃቱ ከመቀጠሉ በፊት የሰጡት የ10 ቀናት ቀነ-ገደብ ሊጠናቀቅ ጥቂት ሰዓታት በቀሩበት ወቅት ነው።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን የቀረበላትን የሰላም አማራጭ ካልተቀበለች አሜሪካ ጥቃቷን በከፍተኛ ሁኔታ እንደምታጠናክር ገልፀዋል::
ፕሬዝዳንቱ ይህ ጥቃት ለኢራን "ከባዱ ቅዠት" ይሆንባታል ሲሉም ነው በድጋሚ ያስጠነቀቁት።
ምንም እንኳን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ድርድሩ በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን ቢገልጹም ኢራን ግን የአሜሪካው የሰላም ዕቅድ "አድሏዊና የእስራኤልን ጥቅም ብቻ የሚያስቀድም ነው" በሚል ሳትቀበለው ቀርታለች።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል የንግድና የሰብዓዊ እርዳታ ፍሰቱ እንዳይቋረጥ አዲስ የሥራ ቡድን በማቋቋም ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ይሁን እንጂ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀነ-ገደብ ዛሬ ማክሰኞ ከእኩለ ሌሊት በኃላ የሚያበቃ በመሆኑ፣ ቀጣዮቹ ሰዓታት ለቀጣናው ሰላም ወሳኝ ሆነው ይጠበቃል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ዙሪያ የቀረበውን የተኩስ አቁም የሰላም ጥያቄ ኢራን ውድቅ ማድረጓ ተሰምቷል።
ይህ የቴህራን ውሳኔ የተሰማው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥቃቱ ከመቀጠሉ በፊት የሰጡት የ10 ቀናት ቀነ-ገደብ ሊጠናቀቅ ጥቂት ሰዓታት በቀሩበት ወቅት ነው።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን የቀረበላትን የሰላም አማራጭ ካልተቀበለች አሜሪካ ጥቃቷን በከፍተኛ ሁኔታ እንደምታጠናክር ገልፀዋል::
ፕሬዝዳንቱ ይህ ጥቃት ለኢራን "ከባዱ ቅዠት" ይሆንባታል ሲሉም ነው በድጋሚ ያስጠነቀቁት።
ምንም እንኳን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ድርድሩ በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን ቢገልጹም ኢራን ግን የአሜሪካው የሰላም ዕቅድ "አድሏዊና የእስራኤልን ጥቅም ብቻ የሚያስቀድም ነው" በሚል ሳትቀበለው ቀርታለች።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል የንግድና የሰብዓዊ እርዳታ ፍሰቱ እንዳይቋረጥ አዲስ የሥራ ቡድን በማቋቋም ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ይሁን እንጂ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀነ-ገደብ ዛሬ ማክሰኞ ከእኩለ ሌሊት በኃላ የሚያበቃ በመሆኑ፣ ቀጣዮቹ ሰዓታት ለቀጣናው ሰላም ወሳኝ ሆነው ይጠበቃል።
@Addis_Magazine
@Addis_Magazine
❤4