Addis Ababa Design And Construction Works Bureau
20.6K subscribers
12.2K photos
197 videos
90 files
759 links
Government Organization
Download Telegram
በከተማዋ የተለያዩ ክፍሎች እየተከናወኑ የሚገኙት የትምህርት መሰረተ ልማት ግንባታዎች በመጠናቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

የተለያዩ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ግንባታዎችን እያከናወነ የሚገኘው የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ተግባራዊ አድርጎ ውጤቶችን ባስመዘገበበት የስራ ዕድል ፈጠራ መርኃ-ግብሩ የትምህርት ቤት ማስፋፊያ ግንባታዎችና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪያል ሼድ ግንባታዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል፡፡

በማሕበራቱ እየተከናወኑ ከሚገኙትና የተለያየ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ ከደረሱት 22 ትምህርትቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የለሚኩራ ወረዳ 06 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት G+4 ህንፃ ተጠናቆ ለርክክብ ለማዘጋጀት የፅዳት ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል፡፡

የቢሮው የስራ ዕድል ተጠቃሚ በሆኑት በሊትሆፕስ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ ስራ ተቋራጭነት እንዲሁም በበላቸው ተሰጋ እና ጓደኞቻችው አማካሪነት በለሚኩራ ክፍለከተማ ወረዳ 06 በ 405 ካ.ሜ. ቦታ ላይ እየተገነባ የሚገኘው ይህ ትምህርት ቤት ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ የተያዘለት ሲሆን በሚቀጥሉት 2 ቀናት ሙሉ ስራውን ለማጠናቀቅ የሚያስችል የፅዳት ስራዎች ላይ ይገኛል፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰኔ 29/2015 ዓ/ም

ለከተማችን መሻሻል እንሰራለን!!!! Dedicated for the betterment of our City!!!!

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡

https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity

https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg
👍10
ቢሮው አምስተኛውን ዙር አረንጓዴ አሻራውን አኖረ፡፡

የአዲስ አበባ ደዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ 20 ሺህ ችግኞችን ለመትከል ግብ የያዘበትን የዘንድሮውን አረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር ማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት የቢሮውን ሰራተኞች እንዲሁም የተቋሙን ባለድርሻ አካለት በማሳተፍ አካሂዷል፡፡

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለከተማ ወረዳ 05 ልዩ ቦታው ኤፍ. ኤም. ራዲዮ ጣቢያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በተካሄደው የዘንድሮው ችግኝ ተከላ የመጀመሪያ ዙር መርኃ-ግብር 5 ሺህ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን ለመርኃ-ግብሩ አስተዋፅዖ ላበረከቱ አካላትም ዕውቅና ተሰጥቷል፡፡

የቢሮውን የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር በይፋ መጀመሩን ያበሰሩትና መርኃ-ግብሩን በንግግር ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር አያልነሽ ሐብተማርያም እንዳሉት ቢሮው ከዚህ ቀደም የነበሩትን የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብሮችን በስኬት ማከናወኑን አንስተው በዘንድሮው ዓመት ከወትሮው በቁጥር ላቅ ያለ ችግኝ በቀጣይነት እንደሚተከል በመጥቀስ ይህንንም ቢሮው በግንባታው ዘርፍ እያስመዘገበ በሚገኘው ውጤት ልክ በማሳካት ለታላቁ ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ ትልም የድርሻውን ያበረክታል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ለዚህ ለትውልድ ተሻጋሪ ለሆነ ታላቅ ተግባር ስኬት ከቢሮው ጎን በመቆም የላቀ አስተዋፅዖ ላበረከቱ ስራ ተቋራጮችና አማካሪ ድርጅቶች በቢሮው ስም ምስጋናቸውን አስተላልፈዋል፡፡......
👍51
.......ቢሮው ከዚህ ቀደም በእንጦጦ ፓርክ፣በለሚ ኢንዱስትሪያል ፓርክ፣አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ፋኩልቲ እና በየካ ሚሊኒየም ፓርኮች የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብሮቹን ማካሄዱ የሚታወስ ነው ፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰኔ 30/2015 ዓ/ም

ለከተማችን መሻሻል እንሰራለን!!!! Dedicated for the betterment of our City!!!!

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡

https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity

https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg
👍4
ቢሮው ለአረንጓዴ አሻራው ስኬት አስተዋፅዖ ላበረከቱ አካላት ዕውቅና ሰጥቷል፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ተግባራዊ ያደረገውን የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር እንዲሳካ አስተዋፅዖ ላበረከቱ የስራ ተቋራጮችና አማካሪ ድርጅቶች ቢሮው የዕውቅና ሰርተፍኬት አበርክቷል፡፡

በዕውቅና ስነ-ስርዓቱ ላይም የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር አያልነሽ ሐብተማርያም እንዳሉት ቢሮው በጠራችሁ ማንኛውም ጊዜ ያለ አንዳች ማቅማማት ማሕበራዊ ኃላፊነታችሁን በመወጣት ሀገራዊ ዕቅዶች እንዲሳኩ ሁሌም ፍቃዳችሁን በመስጠት የልማት አጋርነታችሁን በተግባር ስላረጋገጣችሁልን በቢሮው ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ ያሉ ሲሆን ለዕለቱ የተዘጋጀውን የምስክር ወረቀትም በቢሮው ስም አበርክተውላቸዋል፡፡

በስነ-ስርዓቱ ላይ ቢ.ጂ.ኤም. ኮንስትራክሽን፣ታቡ ኮንስትራክሽን፣ፍቃዱ ሙላቱ ሕንፃ ስራ ተቋራጭ፣አዞይ ኮንስትራክሽን እንዲሁም ኔማድ ኮንሰልቲንግ በቢሮው ዕውቅና ያገኙ አጋሮች ናቸው፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰኔ 30/2015 ዓ/ም

ለከተማችን መሻሻል እንሰራለን!!!! Dedicated for the betterment of our City!!!!

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡

https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity

https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg
👍7
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለም/ቤት ካቀረቡት ሪፖርት /በበጀት አመቱ የኘሮጀክቶች አፈፃፀምን በተመለከተ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ ተግባራት/

👉 የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች መመለስ ላይ ጉልህ ሚና ያላቸው አዳዲስና ከባለፈው በጀት አመት የተሻገሩ ኘሮጀክቶችን ከ6ዐ ቢሊየን ብር በላይ በጀት በመመደብ በጊዜ የለንም መንፈስ፣ ወጪ ቆጣቢና ቶሎ ለአገልግሎት ለማብቃት በሚያስችል ፍጥነትና ጥራት እየገነቡ ይገኛሉ፤
👉በዝርዝር ለመመልከት፡-
=> 538 የመንገድና ተያያዥ ኘሮጀክቶች፣
=> 264 የውሃና ፍሳሽ ኘሮጀክቶች፣
=> 39 የጤና ፕሮጀክቶች፣
=> 1ዐ7 የትምህርት ፕሮጀክቶች፣
=> 99 የሼዶች፣
=> 9 የአረንጓዴና የፓርክ ኘሮጀክቶች፣
=> 28 የእስፖርት ማዘወተሪያ እና የወጣቶች ስብዕና መገንቢያዎች፣
=> 258 ልዩ ልዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ኘሮጀክቶች፣
=> ከ1ዐ,ዐዐዐ በላይ መኖሪያ ቤቶች፣
=> በጥቅሉ በከተማው በጀት 11,3ዐ7 ኘሮጀክቶች እየተገነቡ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 5,256 ኘሮጀክቶችን ማጠናቀቅ የተቻለ ሲሆን፣ ይህ ቁጥር በህብረተሰብ ተሳትፎ የተሰሩትን አይጨምርም፡፡
--------
👉 የነባር ሜጋ ፕሮጀክቶች ግንባታ አፈፃፀምን በተመለከተ:-
=> አድዋ ሙዚየም ዜሮ ኪ.ሜ ፕሮጀክት ግንባታ ከነበረበት 74.78% ወደ (86%)፣ ማድረስጠተችሏል፤
=> የትራንስፖርት ቢሮ ተቋማት ህንፃ ግንባታን ከነበረበት 45.79% ወደ (61.5%) ማድረስ ተችሏል፤
=> የአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ግንባታ ከነበረበት 43% ወደ (71.2%) ማድረስ ተችሏል.........
👍3👏2