Addis Ababa Design And Construction Works Bureau
20.6K subscribers
12.2K photos
196 videos
90 files
759 links
Government Organization
Download Telegram
የልደታ ክፍለከተማ አስተዳደር B+G+11 ሕንፃ ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ አዲስ በታሰረው የ6 ወራት ውል መሰረት እየተሰራ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ እያስገነባው የሚገኘውና የግንባታ ስራው ከዓመት በላይ በመቆሙ ምክንያት ከፍተኛ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምንጭ ሆኖ የቆየው የልደታ ክፍለከተማ አስተዳደር ሕንፃ በተሰጠው ህጋዊ ውሳኔ መሰረት ለቀሪ ስራዎቹ አዲስ ውለታ ታስሮ ስራውን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ የምሽት ፈረቃ ጭምር ተግባራዊ ተደርጎ እየተሰራ ነው፡፡

ቀድሞ በህንፃው ላይ የነበሩና የበሰበሱ ስካፎልዲንጎችን በማፍረስና እንደገና በማዋቀር እንዳዲስ የተጀመረው የቀሪ ስራዎች ግንባታ በውሀ ተሞልቶ የነበረውን የብሎክ A ሁለተኛ ቤዝመንት ከውሀው ነፃ የማድረግ እንዲሁም ውል በተቋረጠ ጊዜ በቁፋሮ ሂደት ላይ በነበረው ብሎክ C ላይ ያቆረውን ውሀ ቀናትን የወሰደ የማውጣት ስራና ቦታውን በድጋሚ የመቆፈር ብሎም እንደአዲስ የሰሌክትድ ማቴሪያል ሙሌት ከተከናወነ በኋላ ወደዋናው ስራ ተገብቷል፡፡

ዋናው ስራ ከተጀመረ በኋላ የብሎኬትና የውጪ ልስን ስራዎች፣የኮለንና የስላብ ኮንክሪት ሙሌቶች በብሎክ A እና B የተከናወኑ ሲሆን በብሎክ C ደግሞ የግሬድ ቢም ፎርምዎርክና የብረት ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡

ከ 883 ሚሊዮን ብር በላይ ተይዞለት በባማኮን ኢንጂነሪንግ ስራ ተቋራጭነት እንዲሁም በኔማድ ኮንሰልቲንግ አማካሪነት በ3,364 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ እየተገነባ የሚገኘው ይህ ባለ 13 ወለል ሕንፃ ሲጠናቀቅ የክፍለከተማውን አስተዳደር ከፍተኛ የህንፃ ኪራይ ወጪ ከማስቀረቱም ባሻገር አስተዳደሩ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ ሕብረተሰቡ የተሻለና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ይጠበቃል፡፡…..
👍2👏21
የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰኔ 20/2015

ለከተማችን መሻሻል እንሰራለን!!!! Dedicated for the betterment of our City!!!!

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡

https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity

https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg
👍4
የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444ኛው ዓመተ ሂጂራ የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡

#የአዲስ_አበባ_ከተማ_አስተዳደር_ዲዛይንና_ግንባታ_ስራዎች_ቢሮ
👍6
በዛሬው ዕለት በ2389 ኢንተርፕራይዞች ለተደራጁ 12 ሺህ የከተማችን ነዋሪዎች የመስሪያ ቦታ አስረክበናል።
ከ2 ወራት በፊት ከከተማችን ሴቶችና ወጣቶች ጋር ባደረግናቸው ውይይቶች ከመስሪያ ቦታና የስራ ዕድል ፈጣራ ጋር የተያያዘ ኢ-ፍትሀዊነት መኖሩን በነገሩን መሰረት አጣርተን ችግሮች መኖራቸውን በማረጋገጥ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ባልተወጡና የአሰራር ጥሰት በፈፀሙ አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ ተገቢ የእርምት እርምጃ ወስደን በ2389 ኢንተርፕራይዞች ለተደራጁ 12 ሺህ የከተማችን ነዋሪዎች የመስሪያ ቦታ አስረክበናል።
እንዲሁም በሸራ ቤት ሲነግዱ የነበሩት የመስሪያ ቦታ የሚገባቸውን አካል ጉደተኞች እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች መሆናቸውን በማረጋገጥ የመስሪያ ቦታ በመስጠት ስራዎቻቸውን በህጋዊ መንገድ እንዲቀጥሉ አድርገናል።

ዛሬ የመስሪያ ቦታ የሰጠናቸው የአካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶችና ሴቶች የመስሪያ ቦታ ማግኘት በራሱ ግብ አይደለምና፣ ተግታችሁ በመስራት ለሌሎች የስራ እድል በመፍጠር ራሳችሁን እንድትለውጡ አደራ ማለት እወዳለሁ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ


ለከተማችን መሻሻል እንሰራለን!!!! Dedicated for the betterment of our City!!!!

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡

https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity

https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg
👍6😁21