Addis Ababa Design And Construction Works Bureau
20.6K subscribers
12.1K photos
193 videos
89 files
759 links
Government Organization
Download Telegram
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የግንባታ ስራው በተያዘለት የውለታ ጊዜ የተጠናቀቀውና ለአገልግሎት ዝግጁ የተደረገው የጎዴ አንደኛ ደረጃ SB+G+4 ትምህርት ቤት


የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ግንቦት 21/2015

ለከተማችን መሻሻል እንሰራለን!!!! Dedicated for the betterment of our City!!!!

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡

https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity

https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg
👍3
በአጠቃላይ 499 የታካሚ አልጋዎች የሚኖሩት የጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል ማስፋፊያ ፕሮጀክት 34.06 በመቶ ደርሷል፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በበጀት ዓመቱ እያስገነባቸው ከሚገኙና በተለያየ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ ከደረሱ 6 ፕሮጀክቶች ውስጥ አንዱ በመሆን አዲስ አበባን የህክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ወደተያዘው ጉዞ ያንደረድራል ተብሎ የሚጠበቀው የጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል 2B+G+6 ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለሕብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት እንዲችል በቢሮው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ይገኛል፡፡

2 ቤዝመንትን ጨምሮ 9 ወለሎች የሚኖሩትና ከጊዜ ወደጊዜ እየተበራከተ የመጣውን የድንገተኛ አደጋዎች ሕክምና በልዩነት እንዲሰጥ ዓላማ ተይዞለት እየተገነባ የሚገኘው ሆስፒታሉ 34.06 በመቶ ፊዚካል አፈፃፀም ላይ የደረሰ ሲሆን በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ላይ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል፡፡

ከ588 ሚ. ብር በላይ የውለታ መጠን የተያዘለት ፕሮጀክቱ ለድንገተኛ አደጋዎች የተጋለጡ የሕብረተሰብ ክፍሎችን አካላዊ ህክምና ከመስጠት ባለፈ ተጎጂዎች ከሚደርስባቸው ስነልቦናዊ ጉዳት የሚያገግሙበት ምቹ እና ሰላማዊ ከባቢ እንዲኖረው ታስቦ በ6,310 ሜ.ስ. ቦታ ላይ እየተገነባ ሲሆን የግንባታ ስራውን ብርሀን ጦቢያው ሕንፃ ስራ ተቋራጭ በስራ ተቋራጭነት እንዲሁም አዱኛ ከቡ አርክቴክቸራል ኢንጂነሪንግ በአማካሪነት እያከናወኑት ይገኛል፡፡

ተቋራጩ በቅርቡ ከተማ አስተዳደሩ በጎ ፍቃደኛ ባለሀብቶችን በማስተባበር በለሚኩራ ክ/ከተማ ባስገነባውና ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በሞያዊ ድጋፍ በተሳተፈበት የዓቅመ ደካሞች የጋራ መኖሪያ ፕሮጀክት ላይ በ3 ወራት ውስጥ ግንባታቸው ተጠናቆ ለተጠቃሚዎች ከተላለፉት 6 ባለ አምስት ወለል ሕንፃዎች ውስጥ አንዱን ሰርቶ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡......
👍103🔥1
የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ግንቦት 24/2015 ዓ/ም

ለከተማችን መሻሻል እንሰራለን!!!! Dedicated for the betterment of our City!!!!

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡

https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity

https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg
👍4
የዓለም ብርሀን ት/ቤት G+4 ማስፋፊያ ግንባታ በዚህ ሳምንት ይጠናቀቃል፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በቀጣዩ በጀት ዓመት ለትምህርት ማሕበረሰቡ ጥራ ያለው አገልግሎት እንዲሰጡ ዓላማ የተያዘላቸው የትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን በጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጁ ማሕበራት ሰጥቶ በመከታተል ፕሮጀክቶቹን እያከናወነ ይገኛል፡፡

ከነዚህ ፕሮጀክቶች ውስጥ አንዱ በመሆን 61 ሚሊዮን ብር ገደማ የውለታ መጠን ተይዞለት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ወረዳ 01 እየተገነባ የሚገኘው የዓለም ብርሀን የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት G+4 ማስፋፊያ ፕሮጀክት አንዱ ነው፡፡

በ ኤፍ ቲ ኤፍ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጭ ኃ/የተ/የግ/ማ እየተገነባ የሚገኘውና ሳሙኤል አብረሀም እና ጓደኞቻቸው ሕ/ሽ/ማ የሚያማክሩት ፕሮጀክቱ 98 በመቶ ፊዚካል አፈፃፀም ላይ የደረሰ ሲሆን አሁን ላይ እየተሰሩ የሚገኙት የደረጃ ስራ፣የመብራት ገጠማ፣የቀለም እንዲሁም የፅዳት ስራዎች በያዝነው ሳምንት ውስጥ ተጠናቀው ከውለታ ጊዜው ቀድሞ ለርክክብ ዝግጁ እንደሚደረግ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ግንቦት 28/2015

ለከተማችን መሻሻል እንሰራለን!!!! Dedicated for the betterment of our City!!!!

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡

https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity

https://www.youtube.com/channel/UCwuES6TQUZmVlUT8tazLHmg
👍42😁1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቢሮው በበጀት ዓመቱ እያከናወናቸው ከሚገኙ ፕሮጀክቶች ውስጥ አንዱ ስለሆነው የጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል 2B+G+6 ማስፋፊያ ፕሮጀክት አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ኤፍ ኤም 96.3 የሰጠው አጭር ሽፋን
👍52
'ዛሬ ነገን እንትከል'! ይህ ዛሬ ለምንጀምረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የሁለተኛው ምእራፍ ጅማሮ መሪ ሐሳብ ነው:: 25 ቢሊዮን ችግኞችን የተከልንበት የመጀመሪያ ምእራፍ ተሳክቷል። በሁለተኛው ዙር ደግሞ ኢትዮጵያ 25 ቢሊዮን ችግኞችን ትተክላለች። አረንጓዴ ዐሻራ ለትውልድ የሚተርፍ ቅርስ ነው። የአየር ንብረት ለውጥን እና የአካባቢ መራቆትን ለመቋቋም የወጠንነው ሀገር በቀል አካሄዳችን ነው። የሥራ ዕድል ለመፍጠር አንዱ መንገዳችን ነው። እንዲሁም ለምግብ የሚውሉ ዕጽዋትን በመትከል የምግብ ዋስትናችንን የምናረጋግጥበት አንዱ መንገድ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
👎8👍6