Addis Ababa Design And Construction Works Bureau
20.6K subscribers
12.2K photos
198 videos
90 files
759 links
Government Organization
Download Telegram
የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ መግባት ይኖርባቸዋል ተባለ

የሲሚንቶ አቅርቦትና ፍላጎት እንዲጣጣም ሁሉም የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ መግባት እንደሚገባቸው ተገለጸ::

የሲሚንቶ አምራቾች ማህበርና የሲሚንቶ አምራቾች ባለቤቶች ማህበር በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫቸውም÷በተለያዩ የፀጥታ ችግሮችና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ሳቢያ ምርት ያቆሙና በሙሉ አቅማቸው የማያመርቱ ፋብሪካዎች መኖራቸውን ገልጸዋል::

ከዚህ ጋር ተያይዞ የአዳዲስ ፋብሪካዎች ግንባታም መፋጠን እንዳለበት ተጠቁሟል፡፡

ምርት አቁሞ የነበረው መሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካም በቅርቡ ወደ ስራ እንደሚገባ በመግለጫው ተነስቷል::

ፋብሪካው በቅርቡ ስራ እንዲጀምር ለማድረግም አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች እንደሚላኩ ተመላክቷል፡፡

የመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ምርት ማቆሙ ከ 20 እስከ 30 በመቶ የሚሆነው የሲሚንቶ ምርት አቅርቦት እንዲቀንስ አድርጎት እንደነበረም ነው የተገለጸው ።

ቸርቻሪዎችም የሚሸጡበትን የሲሚንቶ ዋጋ የመለጠፍ ግዴታ እንዳለባቸውም ነው የተገለጸው::

(FBC)
👍1
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማው እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።


ለከተማው ሕብረተሰብ ዘርፈብዙ ፋይዳ ያላቸውና በከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተገነቡ የሚገኙ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ግንባታ ሂደት በዛሬው ዕለት በክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተጎብኝቷል።


በምልከታው በአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ባለቤትነት እንዲሁም በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን(ኢኮስኮ) እየተገነቡ የሚገኙት የኮልፌ መንዲዳ ሆስፒታል፣የላፍቶ ሆስፒታል፣የላፍቶ አትክልትና ፍራፍሬ መሸጫ ማዕከል ምዕራፍ 2 ግንባታ ፣ የልማት ተነሺ አርሶ አደሮች ማቋቋምያ ማዕከል ፕሮጀክቶች ተካተዋል።


በምልከታው በተለይ በሆስፒታሎቹ የግንባታ ሂደት ላይ የተስተዋለውን መዘግየት በአስቸኳይ በሚፈታበት አግባብ ዙሪያ የአሰሪ መስሪያ ቤቱ፣ የስራ ተቋራጩ እንዲሁም የአማካሪ ድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮችን ያሳተፈና ተስፋ ሰጪ ውይይት ተደርጓል።


የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ታሕሳስ 23/2015 ዓ/ም


በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡
https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity
በስልጠና የዳበረ እውቀት ለስራ ውጤታማነት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል፡፡

በኮንስትራክሽኑ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሙያዎች እውቀትና ክህሎታቸውን በተለያዩ ስልጠናዎች ሲያዳብሩና ሲያሻሽሉ በዘርፉ አመርቂ ውጤት ማምጣት ይቻላል፡፡

ይህን የተረዳው የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስትቲዩት ጋር በመተባበር ለተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ባለሙያዎች ስልጠናዎችን በመስጠት የፈፃሚዎችን የመፈፀም አቅም እንዲሻሻል እያረገ ይገኛል፡፡

ቢሮው የያዝነውን ሳምንት ጨምሮ ለተከታታይ 12 ቀናት ከቢሮውና ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ የኮንትራት አስተዳደር ፣ የፕሮጀክት ኦዲት ፣ የምህንድስና ግዥ ፣ የላብራቶሪ እንዲሁም የዲዛይንና ዋጋ ተከላ ባለሙያዎች በ FIDIK, tender and bid procedure, construction manual, , PPA contract administration, claim and dispute resolution, ዙሪያ የሚያተኩር ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡

በስልጠናው ከ110 በላይ ሰዎች የተሳተፉ ሲሆን ከኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት እና ከስራ ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ የተውጣጡ ሰራኞችም ተሳታፊ ሁነዋል፡፡

ስልጠናው የስራ ተነሳሽነትን የሚፈጥር፣ አነቃቂ እንዲሁም ጉድለቶችን በመለየት የማሻሻያ እርምጃዎችን መውሰድ የሚያስችል እንደሆነ ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ታህሳስ 25/2015 ዓ.ም

በቢሮው የሚወጡ አዳዲስ ጨረታዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን የቢሮውን ይፋዊ ገፆች ይከተሉ፡፡
https://www.facebook.com/AddisConstruction/

https://t.me/AddisCityCon

https://twitter.com/AddisCity
👍2