ሀገር ለጠቢባን የሕያው ሥራዎቻቸው ምስክር ሐውልት ታቆማለች!
ዛሬ በአርበኞች ቀን በተለያዩ መስኮች የጀግንነት ሚና የተወጡ አርበኞቻችንን በማስታወስ እየዘከርናቸው ነው።
ሀገር በልማት ስራዎች፣ ድንበርን በመከላከል፣ በሰንደቅ ዓላማ እና በሕግ ብቻ አትገነባም። ሀገር የምትገነባው በሕዝብ የጋራ ትውስታ፣ በጋራ ስሜት እና በታላላቅ የጥበብ ውጤቶችም ጭምር ነው። ይህ እውነት ዛሬ በቆሙት የሀገር ባለውለታ ታላላቅ ጠቢባን ሐውልቶች በአዲስ አበባ ከተማችን እውን አድርገናል።
ከተማ አስተዳደራችን በኮሪደር ልማት እና በታላላቅ ፕሮጀክቶች ውስጥ፣ ጥበብን ማዕከል አድርጓል።
ዛሬ ሃውልት የቆመላቸው ለሃገራቸው ሰላም፣ ለኢትዮጵያዊነት ግንባታ፣ ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት፣ ለወንድማማችነትና እህትማማችነት፣ ለፍትሃዊነት፣ ለነፃነትና እኩልነት ላቀነቀኑት አንጋፋዎቹ የሀገር ባለውለታዎች ሎሬት ጸጋዬ ጸጋዬ ጋብረ መድኅን፣ የክብር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ፣ ማሕሙድ አሕመድ፣ ዓሊ ቢራ፣ ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር እና ሐጫሉ ሑንዴሣ ናቸው። ከእነዚህ በተጨማሪም ልናከብራቸው የሚገባን የሀገር ባለውለታዎች የሆኑ የጥበብ ሰዎች መኖራቸው ስለሚታወቅ ይህ ስራ የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ አይደለም።
ጥበብ ሀገርን ትስራለች፤ ሀገርም ጠቢብን ታስታውሳለች።
ፍጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዛሬ በአርበኞች ቀን በተለያዩ መስኮች የጀግንነት ሚና የተወጡ አርበኞቻችንን በማስታወስ እየዘከርናቸው ነው።
ሀገር በልማት ስራዎች፣ ድንበርን በመከላከል፣ በሰንደቅ ዓላማ እና በሕግ ብቻ አትገነባም። ሀገር የምትገነባው በሕዝብ የጋራ ትውስታ፣ በጋራ ስሜት እና በታላላቅ የጥበብ ውጤቶችም ጭምር ነው። ይህ እውነት ዛሬ በቆሙት የሀገር ባለውለታ ታላላቅ ጠቢባን ሐውልቶች በአዲስ አበባ ከተማችን እውን አድርገናል።
ከተማ አስተዳደራችን በኮሪደር ልማት እና በታላላቅ ፕሮጀክቶች ውስጥ፣ ጥበብን ማዕከል አድርጓል።
ዛሬ ሃውልት የቆመላቸው ለሃገራቸው ሰላም፣ ለኢትዮጵያዊነት ግንባታ፣ ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት፣ ለወንድማማችነትና እህትማማችነት፣ ለፍትሃዊነት፣ ለነፃነትና እኩልነት ላቀነቀኑት አንጋፋዎቹ የሀገር ባለውለታዎች ሎሬት ጸጋዬ ጸጋዬ ጋብረ መድኅን፣ የክብር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ፣ ማሕሙድ አሕመድ፣ ዓሊ ቢራ፣ ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር እና ሐጫሉ ሑንዴሣ ናቸው። ከእነዚህ በተጨማሪም ልናከብራቸው የሚገባን የሀገር ባለውለታዎች የሆኑ የጥበብ ሰዎች መኖራቸው ስለሚታወቅ ይህ ስራ የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ አይደለም።
ጥበብ ሀገርን ትስራለች፤ ሀገርም ጠቢብን ታስታውሳለች።
ፍጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍8👏3❤2
በመዲናዋ ለ5 ቀናት ሲካሄድ የቆየው የልማት ስራዎች የፎቶ አውደ-ርዕይ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተጠናቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ አዘጋጅነት "የእርጅና ገፅታን የገፈፈ ፤የውበት ፀዳል ያላበሰ" በሚል መሪ ቃል ባለፉት አምስት አመታት በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ለህዝብ ሲያስተዋውቅ የቆየው የፎቶ አውደ-ርዕይ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
ከመጋቢት 23 ቀን ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ክፍት ሆኖ የቆየው ይህ አውደ-ርዕይ የከተማዋን ሁለገብ ለውጥ የሚያሳዩ በርካታ ምስሎች ለአንባቢያንና ለተመልካች እንዲቀርቡ የተደረገበት ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር እንደገለፁት አውደ ርዕዬ ከለውጡ ወዲህ ባሉት አምስት ዓመታት መንግስት ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር መፈጸሙን፣የተመዘገቡ የልማት ውጤቶችንና የከተማዋን ጉዞ በተጨባጭ ለማሳየት ያለመ እንደነበር ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በመንግስትና በህዝብ መካከል ጠንካራ የኮሙኒኬሽን ሥርዓት በመዘርጋት በቂ መረጃ ያለውና በልማት ስራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርግ ማህበረሰብ ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝም አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር አክለዉ ገልፀዋል።
አውደ ርዕዩ በመዲናዋ የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ ሲሆን ጎብኚዎች በመዲናዋ የታዩትን የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ፣ የሰው ተኮር ስራዎችንና የከተማ ውበት ስራዎችን በፎቶ አውደ-ርዕይ ሲመለከቱ መሰንበታቸው ተገልፃል።
በማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸዉ አዲስ አበባ እውነትም በየጊዜው አዲስ ለውጥ እና ፈጣን እድገት የሚታይባት ከተማ እየሆነች መምጣቷን ተናግረዋል።
በተለይም ልማቱ የከተማዋን ገፅታ ከማሳመር ባለፈ ነዋሪውን ማዕከል ያደረገ ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጠ መሆኑን የፎቶ አውደ-ርዕዬ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ አዘጋጅነት "የእርጅና ገፅታን የገፈፈ ፤የውበት ፀዳል ያላበሰ" በሚል መሪ ቃል ባለፉት አምስት አመታት በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ለህዝብ ሲያስተዋውቅ የቆየው የፎቶ አውደ-ርዕይ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
ከመጋቢት 23 ቀን ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ክፍት ሆኖ የቆየው ይህ አውደ-ርዕይ የከተማዋን ሁለገብ ለውጥ የሚያሳዩ በርካታ ምስሎች ለአንባቢያንና ለተመልካች እንዲቀርቡ የተደረገበት ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር እንደገለፁት አውደ ርዕዬ ከለውጡ ወዲህ ባሉት አምስት ዓመታት መንግስት ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር መፈጸሙን፣የተመዘገቡ የልማት ውጤቶችንና የከተማዋን ጉዞ በተጨባጭ ለማሳየት ያለመ እንደነበር ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በመንግስትና በህዝብ መካከል ጠንካራ የኮሙኒኬሽን ሥርዓት በመዘርጋት በቂ መረጃ ያለውና በልማት ስራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርግ ማህበረሰብ ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝም አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር አክለዉ ገልፀዋል።
አውደ ርዕዩ በመዲናዋ የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ ሲሆን ጎብኚዎች በመዲናዋ የታዩትን የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ፣ የሰው ተኮር ስራዎችንና የከተማ ውበት ስራዎችን በፎቶ አውደ-ርዕይ ሲመለከቱ መሰንበታቸው ተገልፃል።
በማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸዉ አዲስ አበባ እውነትም በየጊዜው አዲስ ለውጥ እና ፈጣን እድገት የሚታይባት ከተማ እየሆነች መምጣቷን ተናግረዋል።
በተለይም ልማቱ የከተማዋን ገፅታ ከማሳመር ባለፈ ነዋሪውን ማዕከል ያደረገ ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጠ መሆኑን የፎቶ አውደ-ርዕዬ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል።
👍6
ዛሬ በ11ንዱም ክፍለከተሞች የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው እንደየፍላጐታቸው አደራጅተን ላሰለጠንናቸው 1,278 ኢንተርፕራይዞችና 3,889 አንቀሳቃሾች ሼዶች እና የመስሪያ ቦታዎችን እናስተላልፋለን።
የሚሰሩ እጆችን እናበረታታለን!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የሚሰሩ እጆችን እናበረታታለን!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍7❤2👎2