በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው "የሲቲ ማውንቴን ባይክ ኤሊሚኔተር ፕሮ ሊግ (City Mountain Bike Eliminator Pro League)” ውድድር በኢትዮጵያ - በአዲስ አበባ አስተናጋጅነት ተካሂዷል።
አዲስ አበባ በታሪኳ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተች ነው።
መነሻውንና መድረሻውን የመላው ጥቁር ህዝቦች ታሪክ በሆነው የአድዋ ድል መታሰቢያ ያደረገ "የሲቲ ማውንቴን ባይክ ኤሊሚኔተር ፕሮ ሊግ (City Mountain Bike Eliminator Pro League)” ውድድር ከ24 በላይ ሃገራት በመጡ ፕሮፌሽናል ተወዳዳሪዎች መካከል በከፍተኛ ፉክክር እና ወኔ የተካሄደ እጅግ ደማቅ ውድድር ነው።
ስፖርት ከዓለም ጋር የምንገናኝበት፣ የምንግባባበት እና ትብብርን የምናጠናክርበት አንዱና ትልቁ ዘርፍ ነው።
መንግሥታችን ለስፖርት ዘርፍ ያለው እይታ በመቀየሩ ስፖርት ወዳዱን ማህበረሰባችንን ከዓለም የስፖርት ውድድሮች ጋር ለማያያዝ በሰራነው ሥራ በሁለት ሳምንታት ብቻ 3 ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ማዘጋጀት ችለናል።
ይህ ውድድር የአፍሪካ ዲፕሎማሲ መዲና እና በጥቁር ህዝቦች የድል ታሪክ መታሰቢያ እንዲካሄድ ለመረጣችሁ እና ቀጣይ ዓመትም እዚሁ እንደሚካሄድ ላረጋገጣችሁልን የዓለም አቀፉ የብስክሌት ህብረት (UCI)፣ ለዝግጅቱ ስኬት ሌት ተቀን ለደከማችሁ የስፖርት አመራሮችና አካላት በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ ስም የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በተጨማሪም በከፍተኛ እንግዳ ተቀባይነት፣ ጨዋነት እና ስፓርት አድናቂነት ድጋፋችሁን ለገለፃችሁ የከተማችን ነዋሪዎችም የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ በታሪኳ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተች ነው።
መነሻውንና መድረሻውን የመላው ጥቁር ህዝቦች ታሪክ በሆነው የአድዋ ድል መታሰቢያ ያደረገ "የሲቲ ማውንቴን ባይክ ኤሊሚኔተር ፕሮ ሊግ (City Mountain Bike Eliminator Pro League)” ውድድር ከ24 በላይ ሃገራት በመጡ ፕሮፌሽናል ተወዳዳሪዎች መካከል በከፍተኛ ፉክክር እና ወኔ የተካሄደ እጅግ ደማቅ ውድድር ነው።
ስፖርት ከዓለም ጋር የምንገናኝበት፣ የምንግባባበት እና ትብብርን የምናጠናክርበት አንዱና ትልቁ ዘርፍ ነው።
መንግሥታችን ለስፖርት ዘርፍ ያለው እይታ በመቀየሩ ስፖርት ወዳዱን ማህበረሰባችንን ከዓለም የስፖርት ውድድሮች ጋር ለማያያዝ በሰራነው ሥራ በሁለት ሳምንታት ብቻ 3 ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ማዘጋጀት ችለናል።
ይህ ውድድር የአፍሪካ ዲፕሎማሲ መዲና እና በጥቁር ህዝቦች የድል ታሪክ መታሰቢያ እንዲካሄድ ለመረጣችሁ እና ቀጣይ ዓመትም እዚሁ እንደሚካሄድ ላረጋገጣችሁልን የዓለም አቀፉ የብስክሌት ህብረት (UCI)፣ ለዝግጅቱ ስኬት ሌት ተቀን ለደከማችሁ የስፖርት አመራሮችና አካላት በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ ስም የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በተጨማሪም በከፍተኛ እንግዳ ተቀባይነት፣ ጨዋነት እና ስፓርት አድናቂነት ድጋፋችሁን ለገለፃችሁ የከተማችን ነዋሪዎችም የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍10❤5👏5
ጥበብ ሀገር ትሠራለች፤ ሀገርም ጠቢብን ታከብራለች።
የሀገር ባለውለታ ለሆኑና በጥበብ ሞያቸው ለኢትዮጵያ ሀገራችን ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽዖ በከተማችን አዲስ አበባ የመታሰቢያ ሐውልት ቆሞላቸዋል።
ሚያዚያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
ፈጣሪ ኢትዮዽያና ህዝቦቿን ይባርክ!!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የሀገር ባለውለታ ለሆኑና በጥበብ ሞያቸው ለኢትዮጵያ ሀገራችን ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽዖ በከተማችን አዲስ አበባ የመታሰቢያ ሐውልት ቆሞላቸዋል።
ሚያዚያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
ፈጣሪ ኢትዮዽያና ህዝቦቿን ይባርክ!!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍6👏3❤2
ሀገር ለጠቢባን የሕያው ሥራዎቻቸው ምስክር ሐውልት ታቆማለች!
ዛሬ በአርበኞች ቀን በተለያዩ መስኮች የጀግንነት ሚና የተወጡ አርበኞቻችንን በማስታወስ እየዘከርናቸው ነው።
ሀገር በልማት ስራዎች፣ ድንበርን በመከላከል፣ በሰንደቅ ዓላማ እና በሕግ ብቻ አትገነባም። ሀገር የምትገነባው በሕዝብ የጋራ ትውስታ፣ በጋራ ስሜት እና በታላላቅ የጥበብ ውጤቶችም ጭምር ነው። ይህ እውነት ዛሬ በቆሙት የሀገር ባለውለታ ታላላቅ ጠቢባን ሐውልቶች በአዲስ አበባ ከተማችን እውን አድርገናል።
ከተማ አስተዳደራችን በኮሪደር ልማት እና በታላላቅ ፕሮጀክቶች ውስጥ፣ ጥበብን ማዕከል አድርጓል።
ዛሬ ሃውልት የቆመላቸው ለሃገራቸው ሰላም፣ ለኢትዮጵያዊነት ግንባታ፣ ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት፣ ለወንድማማችነትና እህትማማችነት፣ ለፍትሃዊነት፣ ለነፃነትና እኩልነት ላቀነቀኑት አንጋፋዎቹ የሀገር ባለውለታዎች ሎሬት ጸጋዬ ጸጋዬ ጋብረ መድኅን፣ የክብር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ፣ ማሕሙድ አሕመድ፣ ዓሊ ቢራ፣ ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር እና ሐጫሉ ሑንዴሣ ናቸው። ከእነዚህ በተጨማሪም ልናከብራቸው የሚገባን የሀገር ባለውለታዎች የሆኑ የጥበብ ሰዎች መኖራቸው ስለሚታወቅ ይህ ስራ የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ አይደለም።
ጥበብ ሀገርን ትስራለች፤ ሀገርም ጠቢብን ታስታውሳለች።
ፍጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዛሬ በአርበኞች ቀን በተለያዩ መስኮች የጀግንነት ሚና የተወጡ አርበኞቻችንን በማስታወስ እየዘከርናቸው ነው።
ሀገር በልማት ስራዎች፣ ድንበርን በመከላከል፣ በሰንደቅ ዓላማ እና በሕግ ብቻ አትገነባም። ሀገር የምትገነባው በሕዝብ የጋራ ትውስታ፣ በጋራ ስሜት እና በታላላቅ የጥበብ ውጤቶችም ጭምር ነው። ይህ እውነት ዛሬ በቆሙት የሀገር ባለውለታ ታላላቅ ጠቢባን ሐውልቶች በአዲስ አበባ ከተማችን እውን አድርገናል።
ከተማ አስተዳደራችን በኮሪደር ልማት እና በታላላቅ ፕሮጀክቶች ውስጥ፣ ጥበብን ማዕከል አድርጓል።
ዛሬ ሃውልት የቆመላቸው ለሃገራቸው ሰላም፣ ለኢትዮጵያዊነት ግንባታ፣ ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት፣ ለወንድማማችነትና እህትማማችነት፣ ለፍትሃዊነት፣ ለነፃነትና እኩልነት ላቀነቀኑት አንጋፋዎቹ የሀገር ባለውለታዎች ሎሬት ጸጋዬ ጸጋዬ ጋብረ መድኅን፣ የክብር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ፣ ማሕሙድ አሕመድ፣ ዓሊ ቢራ፣ ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር እና ሐጫሉ ሑንዴሣ ናቸው። ከእነዚህ በተጨማሪም ልናከብራቸው የሚገባን የሀገር ባለውለታዎች የሆኑ የጥበብ ሰዎች መኖራቸው ስለሚታወቅ ይህ ስራ የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ አይደለም።
ጥበብ ሀገርን ትስራለች፤ ሀገርም ጠቢብን ታስታውሳለች።
ፍጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍10👏4❤2