#Update
The student portal is now reopened. If you have anything to check or edit, please do so before it closes.
🔗 Link 🔗
|| @ASTU_Network
The student portal is now reopened. If you have anything to check or edit, please do so before it closes.
🔗 Link 🔗
https://estudent.astu.edu.et
|| @ASTU_Network
😁11🙏3
#Ad
> LinkedIn rental በመከራየት በየሳምንቱ 20$ (3000ብር) ተከፋይ ይሁኑ! 💰
> ከተከፈተ አንድ አመት የሆነውና ከ 100 በለይ connection ያለው Linkedin
> አካውንት ያላቹ ማከራየት ትችላላችሁ።
ማወቅ ያለባችሁ የናንተን LinkedIn አካውንት email እና password መስጠት አለባችሁ ለማከራየት ፣ ነገርግን ያለ እናንተ ፈቃድ email ወይም password መቀየር ስለማንችል አካውንታችሁ አደጋ ላይ አይወድቅም።
>በአሁኑ ጊዜ፣ ለማስታወቂያ ብዙ ተከታዮች
ያሏቸው በርካታ የLinkedIn አካውንት እንፈልጋለን።
● *ዓላማ:* > የማስተዋወቂያ እና ህጋዊ የንግድ አላማዎችን ብቻ ማገልገል
> የመለያውን ደህንነት ያረጋግጡ
> እናንተ አካውንት ውስጥ ላሉ friendoch/ ጓደኞች መልእክት አይላክም
● *መስፈርቶች:* > ከ 100 በላይ ግንኙነቶች (connection ) እና ከተኸፈተ ቢያንስ 1 አመት የሆነው አካውንት
> የLinkedIn መለያዎን ለመከራየት ፍላጎት ካሎት እባክዎን በቴሌግራም
@linkedin_rentalll ያውሩን
> LinkedIn rental በመከራየት በየሳምንቱ 20$ (3000ብር) ተከፋይ ይሁኑ! 💰
> ከተከፈተ አንድ አመት የሆነውና ከ 100 በለይ connection ያለው Linkedin
> አካውንት ያላቹ ማከራየት ትችላላችሁ።
ማወቅ ያለባችሁ የናንተን LinkedIn አካውንት email እና password መስጠት አለባችሁ ለማከራየት ፣ ነገርግን ያለ እናንተ ፈቃድ email ወይም password መቀየር ስለማንችል አካውንታችሁ አደጋ ላይ አይወድቅም።
>በአሁኑ ጊዜ፣ ለማስታወቂያ ብዙ ተከታዮች
ያሏቸው በርካታ የLinkedIn አካውንት እንፈልጋለን።
● *ዓላማ:* > የማስተዋወቂያ እና ህጋዊ የንግድ አላማዎችን ብቻ ማገልገል
> የመለያውን ደህንነት ያረጋግጡ
> እናንተ አካውንት ውስጥ ላሉ friendoch/ ጓደኞች መልእክት አይላክም
● *መስፈርቶች:* > ከ 100 በላይ ግንኙነቶች (connection ) እና ከተኸፈተ ቢያንስ 1 አመት የሆነው አካውንት
> የLinkedIn መለያዎን ለመከራየት ፍላጎት ካሎት እባክዎን በቴሌግራም
@linkedin_rentalll ያውሩን
🤔4😡4❤2
#EthiopianDefenceUniversity
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በቢሾፍቱ እያስመረቀ ነው።
ዩኒቨርሲቲው በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ እና በማኅበረሰብ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ተማሪዎችን በማስመረቅ ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ እንደሚገባ በትምህርት ሚኒስቴር መገለፁ ይታወቃል፡፡
©️ tikvahuniversity
|| @ASTU_Network
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በቢሾፍቱ እያስመረቀ ነው።
ዩኒቨርሲቲው በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ እና በማኅበረሰብ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ተማሪዎችን በማስመረቅ ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ እንደሚገባ በትምህርት ሚኒስቴር መገለፁ ይታወቃል፡፡
©️ tikvahuniversity
|| @ASTU_Network
😁7🔥5🗿1
በአዲስ አበባ በፒኤስጂ እና ቼልሲ መካከል የተደረገውን የዓለም የክለቦች ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ በዲኤስቲቪ ሲመለከቱ የነበሩ ደጋፊዎች በነበሩበት ሆቴል በተፈጠረ ግጭት የሰው ህይወት አለፈ።
ትላንት ምሽት በአሜርካ ኒው ጀርሲ በሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም በፒኤስጂ እና ቼልሲ መካከል የተደረገውን የዓለም የክለቦች ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ "ለቡ" አካባቢ በሚገኝ ሆቴል ውስጥ በዲኤስቲቪ እየተመለከቱ በነበሩ ተመልካቾች መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ለጋ ወጣት ህይወት አልፏል።
በቀብር ስነስርዓቱ ላይ የተገኙ የሟቹ ወዳጆች ፣ ጓደኞች "አሟሟቱ እጅግ የሚያሳዝን ነው" ያሉ ሲሆን "ግለሰቡም ተይዟል" ብለዋል።
"እስከ ምሽት 3:00 ሰአት ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር ካመሸ በኋላ ከጓደኞቼ ጋር ትንሽ ልዝናና ብሎ ሆቴሉ እንደገባ ነው ክስተቱ የተፈጠረው" ሲሉ ተናግረዋል።
በአሟሟቱ ቤተሰቦቹ እጅግ ከፍተኛ ሀዘን ውስጥ እንደሚገኙ ለመመልከት ችለናል።
"ወጣቱ ከኳስ ስሜታዊነት መቆጠብ ወይም የእግር ኳስ ጨዎታዎችን ተሰባስቦ ከማየት መቆጠብ አለበት ካልሆነ ግን የቤተሰብን ሀዘን ማብዛት ነው" ሲሉ ለቀስተኞች ተናግረዋል።
"ወጣቶች እባካችሁ ለቤተሰቦቻችሁ ሀዘን አታብዙ፣ ሁሉን በማስተዋል አድርጉ፣ ማታ ማታ አታምሹ፣ በአጭሩ እየተቀጫችሁ ሃዘናችንን አታብዙት" የሚሉ እና ሌሎች ልብ የሚነኩ ሃሳቦች ተሰንዝረዋል።
በስልክ ቃላቸውን የሰጡ አንድ እናት ሟቹን ወጣት እንደሚያውቁት ገና በ22 ዓመቱ በተፈጠረው ፀብ እንደተቀጠፈ ገልጸዋል።
"በውጭ ኳስ ምክንያት የለጋ ወጣት ህይወት መጥፋቱ እጅግ ያሳዝናል። ሁሉም ወጣቱ ከስሜታዊነት መራቅ አለበት፣ የሚመለከታቸው አካላትም እንዲህ ያለው ነገር እንዳይፈጠር የራሳቸውን ድርሻ መወጣት አለባቸው" ሲሉ እናታዊ መልዕክታቸውን በሀዘን ስሜት አስተላልፈዋል።
|| @ASTU_Network
ትላንት ምሽት በአሜርካ ኒው ጀርሲ በሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም በፒኤስጂ እና ቼልሲ መካከል የተደረገውን የዓለም የክለቦች ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ "ለቡ" አካባቢ በሚገኝ ሆቴል ውስጥ በዲኤስቲቪ እየተመለከቱ በነበሩ ተመልካቾች መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ለጋ ወጣት ህይወት አልፏል።
በቀብር ስነስርዓቱ ላይ የተገኙ የሟቹ ወዳጆች ፣ ጓደኞች "አሟሟቱ እጅግ የሚያሳዝን ነው" ያሉ ሲሆን "ግለሰቡም ተይዟል" ብለዋል።
"እስከ ምሽት 3:00 ሰአት ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር ካመሸ በኋላ ከጓደኞቼ ጋር ትንሽ ልዝናና ብሎ ሆቴሉ እንደገባ ነው ክስተቱ የተፈጠረው" ሲሉ ተናግረዋል።
በአሟሟቱ ቤተሰቦቹ እጅግ ከፍተኛ ሀዘን ውስጥ እንደሚገኙ ለመመልከት ችለናል።
"ወጣቱ ከኳስ ስሜታዊነት መቆጠብ ወይም የእግር ኳስ ጨዎታዎችን ተሰባስቦ ከማየት መቆጠብ አለበት ካልሆነ ግን የቤተሰብን ሀዘን ማብዛት ነው" ሲሉ ለቀስተኞች ተናግረዋል።
"ወጣቶች እባካችሁ ለቤተሰቦቻችሁ ሀዘን አታብዙ፣ ሁሉን በማስተዋል አድርጉ፣ ማታ ማታ አታምሹ፣ በአጭሩ እየተቀጫችሁ ሃዘናችንን አታብዙት" የሚሉ እና ሌሎች ልብ የሚነኩ ሃሳቦች ተሰንዝረዋል።
በስልክ ቃላቸውን የሰጡ አንድ እናት ሟቹን ወጣት እንደሚያውቁት ገና በ22 ዓመቱ በተፈጠረው ፀብ እንደተቀጠፈ ገልጸዋል።
"በውጭ ኳስ ምክንያት የለጋ ወጣት ህይወት መጥፋቱ እጅግ ያሳዝናል። ሁሉም ወጣቱ ከስሜታዊነት መራቅ አለበት፣ የሚመለከታቸው አካላትም እንዲህ ያለው ነገር እንዳይፈጠር የራሳቸውን ድርሻ መወጣት አለባቸው" ሲሉ እናታዊ መልዕክታቸውን በሀዘን ስሜት አስተላልፈዋል።
|| @ASTU_Network
😭8❤3💔1
ASTU Network ®️
በአዲስ አበባ በፒኤስጂ እና ቼልሲ መካከል የተደረገውን የዓለም የክለቦች ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ በዲኤስቲቪ ሲመለከቱ የነበሩ ደጋፊዎች በነበሩበት ሆቴል በተፈጠረ ግጭት የሰው ህይወት አለፈ። ትላንት ምሽት በአሜርካ ኒው ጀርሲ በሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም በፒኤስጂ እና ቼልሲ መካከል የተደረገውን የዓለም የክለቦች ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ "ለቡ" አካባቢ በሚገኝ ሆቴል ውስጥ በዲኤስቲቪ እየተመለከቱ በነበሩ ተመልካቾች…
ለዚህ እኮ ነው ይሄ ነገር ልክ ይኑረው የሚባለው 😣... ወይ የሀገራችን ኳስ አይደለ 🤷♂️😕 ... የራሳችን ቢሆን እንኳ አንድ ነገር ይባላል 😐 ... ኧረ እንደውም እሱም አያስፈልግም! 🙅♂️
ጭራሽ ከእኛ ጋር በምንም በማይገናኝ በውጪ ኳስ ይሄን ያክል ነፍስ እስከሚጠፋ ድረስ በዚህ ልክ ያለ ስሜታዊነት ምን ማለት ነው? ጥቅሙስ ምንድንነው??🤔
ልጁ ቀኑን ሙሉ ከቤተሰቡ ጋር ውሎ ኳስ ለማየት ሄዶ አስከሬኑ ከኳስ ቦታ ሲመለስ ቤተሰቡ (በተለይ እናቱ) የሚሰማቸውን ስሜት አስቡት... 😭💔
ኧረ ጎበዝ ወዴት እየሄድን ነው? ኧረ ነገ ኮ ብዙ ነገር ነው የሚጠብቀን ... ኧረ ይሄ ነገርኮ የራሳችንን ኑሮ አስጥሎን ሁሉ ነገራችንን ቁማር (bet) እና ጊዜ ማባከን ላይ አስደረገን ... ኧረ ለራሳችን ማሰብ ቢያቅተን እና እንደው ህልም ምናምን የምንለው ፣ የምንኖርለት እና የምንጠነቀቅለት ነገር ባይኖረን እንኳን ቢያንስ ዋጋ ለከፈሉልን ቤተሰቦቻችን እናስብ ... ኧረ እንሰብሰብ ... ቅዱስ መጽሐፉም እኮ "ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ" ይላል... 😭🤲
በእውነት እጅግ በጣም ያሳዝናል! 😭💔
Bro ነፍስህ በሰላም ትረፍ! 🕊
.
ጭራሽ ከእኛ ጋር በምንም በማይገናኝ በውጪ ኳስ ይሄን ያክል ነፍስ እስከሚጠፋ ድረስ በዚህ ልክ ያለ ስሜታዊነት ምን ማለት ነው? ጥቅሙስ ምንድንነው??🤔
ልጁ ቀኑን ሙሉ ከቤተሰቡ ጋር ውሎ ኳስ ለማየት ሄዶ አስከሬኑ ከኳስ ቦታ ሲመለስ ቤተሰቡ (በተለይ እናቱ) የሚሰማቸውን ስሜት አስቡት... 😭💔
ኧረ ጎበዝ ወዴት እየሄድን ነው? ኧረ ነገ ኮ ብዙ ነገር ነው የሚጠብቀን ... ኧረ ይሄ ነገርኮ የራሳችንን ኑሮ አስጥሎን ሁሉ ነገራችንን ቁማር (bet) እና ጊዜ ማባከን ላይ አስደረገን ... ኧረ ለራሳችን ማሰብ ቢያቅተን እና እንደው ህልም ምናምን የምንለው ፣ የምንኖርለት እና የምንጠነቀቅለት ነገር ባይኖረን እንኳን ቢያንስ ዋጋ ለከፈሉልን ቤተሰቦቻችን እናስብ ... ኧረ እንሰብሰብ ... ቅዱስ መጽሐፉም እኮ "ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ" ይላል... 😭🤲
በእውነት እጅግ በጣም ያሳዝናል! 😭💔
Bro ነፍስህ በሰላም ትረፍ! 🕊
.
😭7🤷♂3❤1🤷♀1👍1
Many students have been asking this... 👇
Which school is better according to the education provided at ASTU? Choose one and share your reasoning in the comments section:
Which school is better according to the education provided at ASTU? Choose one and share your reasoning in the comments section:
Anonymous Poll
29%
#SoMCME [School of Mechanical, Chemical and Material Engineering]
20%
#SoCEA [School of Civil Engineering and Architecture]
10%
I am not sure [IDK]
40%
Just to see the vote!
🤔5❤3😁1
በ2018 ዓ.ም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የጥራት ቁጥጥር እንደሚጀመር ታውቋል።
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ በመጪው አመት 2018 ዓ.ም በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ የጥራት ቁጥጥር እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡
የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ በአሁን ወቅት በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ እየተካወነ ያለው ዳግም ምዝገባና ምዘና ስራ ሲጠናቀቅ ይኸው እንቅስቃሴ በመንግስት ኮሌጆች፣ የማሰልጠኛ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች ላይም በቀጣዩ አመት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አሁን እየተከናወነ ያለውን የመጀመሪያው ዙር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ምዝገባና ግምገማ እንደጨረስን፣ በሁለተኛውና በሶስተኛው ዙር የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን እንመዘግባለን፣ እንገመግማለን፡፡ በፌደራልና በክልሎች የተከፈቱ ኮሌጆችና የማሰልጠኛ ተቋማት አሉ፡፡ መጀመሪያ የምናየው እነሱን ነው፡፡ ቀጥለን ደግሞ ሁሉንም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን እናያለን፡፡
እስካሁን የግል ተቋማት ላይ ያተኮርነው፣ እዚህ ዘርፍ ላይ የነበረው ችግር ሰፊ ስለሆነ ነው፡፡ ያለንን የሰው ሀይልና ሀብት ወደዚህ ዘርፍ በማዞር ቅድሚያ ሰጥተናል፡፡ ሁሉንም አንድ ላይ ማየት አንችልም፡፡ አሁን የግሎቹን ተቋማት ካጠናቀቅን በኋላ፣ ወደ መንግስት ትምህርት ተቋማት ግምገማ እንገባለን፡፡
የመንግስት የትምህርት ተቋማት በመሰረተልማት በኩል ችግር የለባቸውም፡፡ የራሳቸው ህንፃና ግቢ አላቸው፡፡ ስለዚህ እነሱ ጋ ትኩረት የምናደርገው ጥራት ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ፕሮግራሞቹ/ትምህርቱ በበቂ መምህራንና አኳሀን መሰጠቱን እናያለን፡፡ አካዳሚያዊ የድርጊት መርሀግብራቸው ትክክል መሆኑን እንፈትሻለን፡፡
የተገቢነትና አስፈላጊነት ጥያቄ የሚነሳባቸው፣ ዝም ብለው ያለ በቂ ጥናት የሚከፈቱ ፕሮግራሞች አሉ፡፡ የትምህርት ግብአት እና የላቦራቶሪ ቁሳቁሶች፣ እንዲሁም የዳታ ማዕከላቸው ይታያል፡፡ ለተማሪዎችና ለአስተማሪዎች የሚቀርቡት አገልግሎቶች ደረጃቸውን የጠበቁ ናቸው ወይ የሚለውን እናያለን፡፡
ቀደም ብለው የተቋቋሙት ነባሮቹ ዩኒቨርሲቲዎች የዚህ አይነት ችግር ላይኖርባቸው ይችላል፡፡ አዳዲሶቹ ዩኒቨርሲቲዎች ግን በነዚህ መስፈርቶች በኩል ክፍተት ይኖሩባቸዋል፡፡
በአጠቃላይ ግን ጥራትን እናምጣ ካልን፣ ሁሉንም የመንግስት ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎችን መፈተሽ አለብን፡፡ በዳግመ ምዝገባችን፣ በተቋማቱ የሚሰጡትን ሁሉንም ፕሮግራሞቻቸውን እናያለን፡፡ ፋይሎቻቸውን እንዲያስገቡ አድርገን እያንዳንዱን ፕሮግራም እንመዝናለን፡፡ አያስፈልጉም የምንላቸውን ፕሮግራሞች እንዲዘጉ፣ ያስኬዳሉ የምንላቸውን ደግሞ እንዲያስቀጥሉ እናደርጋለን፡፡
የመንግስት ተቋማትን ከግሎቹ በበለጠ ጠንከር ያለ ምዘና እናደርጋለን፡፡ ጠበቅ አድርገን ለማየት እንሞክራለን፡፡ የግሎቹን እንደጨረስን፣ በየክልሉ ያሉትንና በፌደራል ደረጃም ያሉትን ኮሌጆችና የማሰልጠኛ ተቋማትን እናያለን፡፡ ከዛም ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንሔዳለን፡፡ ይህ ስራ በ 2018 ዓ.ም የሚጀመር ይመስለኛል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ በመጪው አመት 2018 ዓ.ም በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ የጥራት ቁጥጥር እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡
የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ በአሁን ወቅት በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ እየተካወነ ያለው ዳግም ምዝገባና ምዘና ስራ ሲጠናቀቅ ይኸው እንቅስቃሴ በመንግስት ኮሌጆች፣ የማሰልጠኛ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች ላይም በቀጣዩ አመት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አሁን እየተከናወነ ያለውን የመጀመሪያው ዙር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ምዝገባና ግምገማ እንደጨረስን፣ በሁለተኛውና በሶስተኛው ዙር የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን እንመዘግባለን፣ እንገመግማለን፡፡ በፌደራልና በክልሎች የተከፈቱ ኮሌጆችና የማሰልጠኛ ተቋማት አሉ፡፡ መጀመሪያ የምናየው እነሱን ነው፡፡ ቀጥለን ደግሞ ሁሉንም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን እናያለን፡፡
እስካሁን የግል ተቋማት ላይ ያተኮርነው፣ እዚህ ዘርፍ ላይ የነበረው ችግር ሰፊ ስለሆነ ነው፡፡ ያለንን የሰው ሀይልና ሀብት ወደዚህ ዘርፍ በማዞር ቅድሚያ ሰጥተናል፡፡ ሁሉንም አንድ ላይ ማየት አንችልም፡፡ አሁን የግሎቹን ተቋማት ካጠናቀቅን በኋላ፣ ወደ መንግስት ትምህርት ተቋማት ግምገማ እንገባለን፡፡
የመንግስት የትምህርት ተቋማት በመሰረተልማት በኩል ችግር የለባቸውም፡፡ የራሳቸው ህንፃና ግቢ አላቸው፡፡ ስለዚህ እነሱ ጋ ትኩረት የምናደርገው ጥራት ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ፕሮግራሞቹ/ትምህርቱ በበቂ መምህራንና አኳሀን መሰጠቱን እናያለን፡፡ አካዳሚያዊ የድርጊት መርሀግብራቸው ትክክል መሆኑን እንፈትሻለን፡፡
የተገቢነትና አስፈላጊነት ጥያቄ የሚነሳባቸው፣ ዝም ብለው ያለ በቂ ጥናት የሚከፈቱ ፕሮግራሞች አሉ፡፡ የትምህርት ግብአት እና የላቦራቶሪ ቁሳቁሶች፣ እንዲሁም የዳታ ማዕከላቸው ይታያል፡፡ ለተማሪዎችና ለአስተማሪዎች የሚቀርቡት አገልግሎቶች ደረጃቸውን የጠበቁ ናቸው ወይ የሚለውን እናያለን፡፡
ቀደም ብለው የተቋቋሙት ነባሮቹ ዩኒቨርሲቲዎች የዚህ አይነት ችግር ላይኖርባቸው ይችላል፡፡ አዳዲሶቹ ዩኒቨርሲቲዎች ግን በነዚህ መስፈርቶች በኩል ክፍተት ይኖሩባቸዋል፡፡
በአጠቃላይ ግን ጥራትን እናምጣ ካልን፣ ሁሉንም የመንግስት ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎችን መፈተሽ አለብን፡፡ በዳግመ ምዝገባችን፣ በተቋማቱ የሚሰጡትን ሁሉንም ፕሮግራሞቻቸውን እናያለን፡፡ ፋይሎቻቸውን እንዲያስገቡ አድርገን እያንዳንዱን ፕሮግራም እንመዝናለን፡፡ አያስፈልጉም የምንላቸውን ፕሮግራሞች እንዲዘጉ፣ ያስኬዳሉ የምንላቸውን ደግሞ እንዲያስቀጥሉ እናደርጋለን፡፡
የመንግስት ተቋማትን ከግሎቹ በበለጠ ጠንከር ያለ ምዘና እናደርጋለን፡፡ ጠበቅ አድርገን ለማየት እንሞክራለን፡፡ የግሎቹን እንደጨረስን፣ በየክልሉ ያሉትንና በፌደራል ደረጃም ያሉትን ኮሌጆችና የማሰልጠኛ ተቋማትን እናያለን፡፡ ከዛም ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንሔዳለን፡፡ ይህ ስራ በ 2018 ዓ.ም የሚጀመር ይመስለኛል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤6👏3
#ዜና
መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚገባበት እለት መሆኑ ተነገረ
መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የቀጣዩ አመት የዩኒቨርስቲ ት/ት ይጀመራል ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የፈተና ውጤት ጳጉሜ ላይ ይፋ ይሆናል በማለት እስከዚያም ድረስ የሚቆየው ፈተና ያልወሰዱና በመጪው ነሐሴ ወር ለፈተና የሚቀመጡ ቀሪ ተፈታኝ ተማሪዎች በመኖራቸው መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።
በተለያየ ምክንያት ዘግይተው ትምህርት የጀመሩ በመኖራቸው ነው ፈተና እኩል ያልወሰዱ ተፈታኞች ያሉት በማለትም በመሆኑም ጳጉሜ ወር ላይ የ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤት ከታወቀ በኋላ መስከረም 8 ቀን ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚጀምርበት እለት እንደሚሆን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የትምህርት ካላንደርን በአግባቡ አክብሮ በመስራት የፈተና ጊዜያትንም ላለመሻማት ይሰራል ሲሉ ያከሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ከመስከረም ጀምሮ ጥብቅ አሰራር እንደሚኖር ገልጸዋል።
እንደ ሀገር እኩል ውጤት ተናግሮ በእኩል ትምህርት ለማስጀመር ሲባል ቀሪ ያልተፈተኑ ተፈታኝ ተማሪዎችን ጠብቆ ማስጨረስ እንደሚገባ የተናገሩት የትምህርት ሚኒስትሩ በራሳቸው ፈቃድና ምክንያት አስቀድመው ፈተና ላይ ካልተቀመጡት በቀር ሌሎቹ የመመዘኛ መስፈርቱ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።
|| @ASTU_Network
መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚገባበት እለት መሆኑ ተነገረ
መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የቀጣዩ አመት የዩኒቨርስቲ ት/ት ይጀመራል ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የፈተና ውጤት ጳጉሜ ላይ ይፋ ይሆናል በማለት እስከዚያም ድረስ የሚቆየው ፈተና ያልወሰዱና በመጪው ነሐሴ ወር ለፈተና የሚቀመጡ ቀሪ ተፈታኝ ተማሪዎች በመኖራቸው መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።
በተለያየ ምክንያት ዘግይተው ትምህርት የጀመሩ በመኖራቸው ነው ፈተና እኩል ያልወሰዱ ተፈታኞች ያሉት በማለትም በመሆኑም ጳጉሜ ወር ላይ የ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤት ከታወቀ በኋላ መስከረም 8 ቀን ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚጀምርበት እለት እንደሚሆን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የትምህርት ካላንደርን በአግባቡ አክብሮ በመስራት የፈተና ጊዜያትንም ላለመሻማት ይሰራል ሲሉ ያከሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ከመስከረም ጀምሮ ጥብቅ አሰራር እንደሚኖር ገልጸዋል።
እንደ ሀገር እኩል ውጤት ተናግሮ በእኩል ትምህርት ለማስጀመር ሲባል ቀሪ ያልተፈተኑ ተፈታኝ ተማሪዎችን ጠብቆ ማስጨረስ እንደሚገባ የተናገሩት የትምህርት ሚኒስትሩ በራሳቸው ፈቃድና ምክንያት አስቀድመው ፈተና ላይ ካልተቀመጡት በቀር ሌሎቹ የመመዘኛ መስፈርቱ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።
|| @ASTU_Network
😢27❤9👎4💔2🤷♀1
Forwarded from 𝐀𝐒𝐓𝐔 𝐄𝐧𝐭𝐞𝐫𝐭𝐚𝐢𝐧𝐦𝐞𝐧𝐭 ™️
#Ethiopia 🇪🇹 — the land of diverse societies and cultures! 🤗😁
.
.
🤣12❤2👎1💔1😭1
#Tech_News
የቻይና ሳይንቲስቶች የንቦችን እንቅስቃሴ መቆጣጠር የሚያስችል ቴክኖሎጂን ተግባራዊ አደረጉ
****
የቤጂንግ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲስቶች 74 ሚሊግራም የሚመዝን የነፍሳት እንቅስቃሴ መቆጣጠሪያ ቴክኖሎጂን ንብ ላይ በመጠቀም በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን ፈጠራቸውን አስተዋውቀዋል።
|| @ASTU_Network
የቻይና ሳይንቲስቶች የንቦችን እንቅስቃሴ መቆጣጠር የሚያስችል ቴክኖሎጂን ተግባራዊ አደረጉ
****
የቤጂንግ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲስቶች 74 ሚሊግራም የሚመዝን የነፍሳት እንቅስቃሴ መቆጣጠሪያ ቴክኖሎጂን ንብ ላይ በመጠቀም በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን ፈጠራቸውን አስተዋውቀዋል።
|| @ASTU_Network
❤3😱2
#ዜና
በየአመቱ የዩኒቨርሲቲዎችን ደረጃ በማውጣት የሚታወቀው ፣ ፈር-ቀዳጅ እና አንጋፋ የሆነው ‛UNIRANK’ የ 2025 አመት የዩኒቨርስቲዎችን ደረጃ ይፋ አድርጓል።
አሁን ያለውን ሁኔታ መሰረት በማድረግም የኢትዮጵያን ዩኒቨርስቲዎች ደረጃ አውጥቷል። በዚህም መሰረት ከኢትዮጵያ ከ50 በላይ ዩኒቨርስቲዎችን ያወዳደረ ሲሆን ፣ በውድድሩ የመደበኛ ፣ የመንግስት ሰራተኞች እና የፖሊስ ዩኒቨርስቲዎችንም አሳትፏል።
በ 2025 ከኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች አንደኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሲሆን ጅማ ዩኒቨርስቲ እና ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁለተኛ እና ሶስተኛ በመሆን ሲከተሉት ፣ ዩኒቨርስቲያችን አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ደግሞ በስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ከአንደኛ እስከ ሃምሳኛ ደረጃ የተቀመጡትን ዩኒቨርስቲዎች ከላይ ከተያያዙት ፎቶዎች ላይ ይመልከቱ!
📰 ዘገባው የASTU Network ነው!
|| @ASTU_Network
በየአመቱ የዩኒቨርሲቲዎችን ደረጃ በማውጣት የሚታወቀው ፣ ፈር-ቀዳጅ እና አንጋፋ የሆነው ‛UNIRANK’ የ 2025 አመት የዩኒቨርስቲዎችን ደረጃ ይፋ አድርጓል።
አሁን ያለውን ሁኔታ መሰረት በማድረግም የኢትዮጵያን ዩኒቨርስቲዎች ደረጃ አውጥቷል። በዚህም መሰረት ከኢትዮጵያ ከ50 በላይ ዩኒቨርስቲዎችን ያወዳደረ ሲሆን ፣ በውድድሩ የመደበኛ ፣ የመንግስት ሰራተኞች እና የፖሊስ ዩኒቨርስቲዎችንም አሳትፏል።
በ 2025 ከኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች አንደኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሲሆን ጅማ ዩኒቨርስቲ እና ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁለተኛ እና ሶስተኛ በመሆን ሲከተሉት ፣ ዩኒቨርስቲያችን አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ደግሞ በስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ከአንደኛ እስከ ሃምሳኛ ደረጃ የተቀመጡትን ዩኒቨርስቲዎች ከላይ ከተያያዙት ፎቶዎች ላይ ይመልከቱ!
📰 ዘገባው የASTU Network ነው!
|| @ASTU_Network
😭14❤6💔2🙊1
ASTU Network ®️
Photo
#UNIRANK የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲን በተመለከተ ምን አለ❓
በ 2025 ያለውን የኢትዮጵያ የዩኒቨርስቲዎች ደረጃ ይፋ ያደረገው ‛UNIRANK’ ስለ ዩኒቨርስቲያችን አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የተወሰኑ መረጃዎችን አውጥቷል።
ዩኒቨርስቲው በ1993 እንደተመሰረተ እና በተለያዩ መስኮች በዲግሪ ፣ በማስተርስ እና በዶክትሬት ዲግሪ ተማሪዎቹን እያበቃ ያለ ተቋም እንደሆነ ገልጿል። በተጨማሪም ትምህርታዊ እና ትምህርታዊ-ያልሆኑ አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑንም አክሏል።
ደረጃውን በተመለከተ ባወጣው መረጃም ዩኒቨርስቲው በ 2025 በኢትዮጵያ 8ኛ ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ 7689ኛ ደረጃ መያዙን አስታውቋል።
ድህረገጹ ስለ አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ያወጣቸውን መረጃዎች ከላይ ከተያያዙት ፎቶዎች ላይ ይመልከቱ!
📰 ዘገባው የASTU Network ነው!
|| @ASTU_Network
በ 2025 ያለውን የኢትዮጵያ የዩኒቨርስቲዎች ደረጃ ይፋ ያደረገው ‛UNIRANK’ ስለ ዩኒቨርስቲያችን አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የተወሰኑ መረጃዎችን አውጥቷል።
ዩኒቨርስቲው በ1993 እንደተመሰረተ እና በተለያዩ መስኮች በዲግሪ ፣ በማስተርስ እና በዶክትሬት ዲግሪ ተማሪዎቹን እያበቃ ያለ ተቋም እንደሆነ ገልጿል። በተጨማሪም ትምህርታዊ እና ትምህርታዊ-ያልሆኑ አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑንም አክሏል።
ደረጃውን በተመለከተ ባወጣው መረጃም ዩኒቨርስቲው በ 2025 በኢትዮጵያ 8ኛ ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ 7689ኛ ደረጃ መያዙን አስታውቋል።
ድህረገጹ ስለ አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ያወጣቸውን መረጃዎች ከላይ ከተያያዙት ፎቶዎች ላይ ይመልከቱ!
📰 ዘገባው የASTU Network ነው!
|| @ASTU_Network
🙉13🙊4😭3❤1👍1💔1